es
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Ir al canal en Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

El canal ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 13 342 suscriptores, ocupando la posición 1 756 en la categoría Transporte y el puesto 2 537 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 13 342 suscriptores.

Según los últimos datos del 18 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 91, y en las últimas 24 horas de 11, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 41.16%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 15.44% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 491 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 060 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 11.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 18 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Transporte.

13 348
Suscriptores
+1124 horas
+477 días
+9130 días
Archivo de publicaciones
ለ20ኛው የዓለም የሥራ ድርጅት አህጉራዊ ጉባኤ መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅና ስነ-ስርዓት ተካሄድ አዲስ አበባ፣ ግንቦት 27፣ 2017 (ኢ መ አ) ፡- ለ20ኛው የዓለም የሥራ ድርጅት አህጉራዊ ጉባኤ መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅና ስነ-ስርዓት በትላንትናው ምሽት በኢንተር-ሌግዤሪ ሆቴል ተካሂዷል፡፡ ሀገራችን በቅርቡ ያካሄደችው 20ኛው የአለም ሥራ ድርጅት አህጉራዊ ጉባኤ በስኬት እንዲጠናቀቅ በእውቀት፣ በጉልበትና በገንዘብ ድጋፍ ላበረከቱ አካላት የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ ሽልማቱ ለአጋሮች፣ ለስፖንሰሮች፣ ለብሔራዊ አዘጋጅ ኮሚቴ አባላት፣ ለሚዲያ ሙያተኞችና ተቋማት እንዲሁም ለጽሑፍ አቅራቢዎች የተበረከተ ሲሆን በሽልማት ስነ-ስርዓቱ ላይ የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ፤ ጉባኤው ኢትዮጵያ እያከናወነች ያለችውን ግዙፍ የልማት ሥራዎችን አፍሪካዊያንና የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እንዲመለከት እድል የሰጠ መሆኑን አሳውቀው፣ ለኮንፈረንሱ ስኬት በገንዘባቸው፣ በእውቀታቸውና በጉልበታቸው ድጋፍ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል፡፡ የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታና የብሔራዊ አዘጋጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ የትምጌታ አሥራት ከዝግጅቱ ጀማሮ አንስቶ እስከ ፍጻሜው ድረስ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሁሉ ምስጋና አቅርበው፣ መድረኩ ከተባበርንና ከተጋገዝን የማይቻል እንደሌለ ያየንበት ክስተት ነበር ብለዋል፡፡ አያይዘውም ያለንን አቅም ለሀገራዊ ልማትና ብልጽግና በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን መርህ መሰረት ተደምረን አስተዋጽኦ ማበርከታችንን እንቀጥላለን ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን፤ ጉባኤው ለመሰረት ልማት ዘርፉ አስፈላጊ የምርምር ውጤቶች ቀርበው ውይይት የተደረገባቸው መሆኑም አስታውሰው፣ የተገኙ ተሞክሮዎችና ልምምድ ልውውጦች ለሀገራችን መንገድ ልማት እጅግ ጠቃሚ መሆናቸው ገልጸዋል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

በድሬዳዋ - መልካ ጀብዱ መንገድ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ እየተከናወነ ነው ድሬዳዋ፣ ግንቦት 22፣ 2017 (ኢ መ አ):- በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር 7 ነጥብ 2 ኪሎሜትር በሚረዝመው የድሬዳዋ - መልካ ጀብዱ መንገድ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ እየተከናወነ ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ ከዚህ ቀደም በሀገር በቀል የሥራ ተቋራጭ ሲከናወን ቆይቶ ከወሰን ማስከበር ጋር በተያያዘ ችግር ግንባታው ተቋርጦ እንደነበር ይታወቃል። አሁን ላይ ችግሩ በመፈታቱ የግንባታውን ቀሪ 2 ነጥብ 1 ኪሎሜትር ሥራ ማጠናቀቅ እንዲቻል በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የድሬዳዋ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ፕሮጀክቱን ተረክቦ እየሠራ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ከአስፋልት ንጣፍ ሥራው በተጨማሪ የአፈር፣ የሰብቤዝ፣ ቤዝኮርስ እና የውኃ መፋሰሻ ቱቦ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። የመንገድ ግንባታውን አበረታች አፈጻጸም በማስቀጠል በሚቀጥሉት ጥቂት ወራት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተቀምጦ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል። በኮንክሪት አስፋልት ደረጃ እየተገነባ የሚገኘው የመንገድ ፕሮጀክቱ በሁለት አቅጣጫ መኪናዎችን ከማስተላለፉም ባለፈ የእግረኛ እና የብስክሌተኞች እንዲሁም የአረንጓዴ ሥፍራን ጨምሮ 50 ሜትር የጎን ስፋት ይኖረዋል። ለመንገድ ፕሮጀክቱ የተመደበው 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በፌደራል መንግስት ይሸፈናል። ቤዛ ኢንጅነሪንግ ሊሚትድ ኬኒያ የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን ያከናውናል። የመንገዱ መገንባት የኅብረተሰቡን የመሠረተ-ልማት ጥያቄ ከመፍታቱም ባለፈ የድሬዳዋ ከተማን የማኅበራዊ እና የምጣኔ ሀብታዊ ዕድገት የሚያፋጥን ነው። በተጨማሪም መንገዱ ከድሬዳዋ ኢንዱስትሪ መንደር፣ ከኢትዮ - ጅቡቲ ምድር ባቡር ጣቢያ እንዲሁም ከድሬዳዋ ነጻ ንግድ ቀጠና ጋር የተገናኘ በመኾኑ የምጣኔ ሀብት ትስስሩን ያጠናክራል። መንገዱ በራስ-ኅይል እንደመገንባቱ መጠን በቀጣይ ለሚኖሩ ሥራዎች በርካታ ልምድ እና ተሞክሮ የተገኘበት መኾኑም ተመልክቷል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የጉደር-አምቦ ከተማ የመንገድ ፕሮጀክት በማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ ይገኛል። በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ  የሚገኘው  የጉደር -አምቦ የአስፋልት  ኮንክሪት መንገድ እየተሰራ ሲሆን በአሁኑ ወቅት  የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻጸም  88.66 በመቶ ደርሷል። ከጉደር ከተማ በመነሳት አምቦ ድረስ የሚዘልቀውን ይኸው የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታ 19.132  ኪሎ ሜትር ይሸፍናል። በእስካሁኑ የመንገድ ግንባታ ስራ  የአስፋልት ንጣፍ፣ አፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣  የድሬኔጅ ስራዎች፣ ሰብ ቤዝ ንጣፍ ፣ ቤዝ ኮርስ ንጣፍ ፣ እንዲሁም የስትራክቸር ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። ለግንባታ  ማስፈጸሚያ የሚውለውን ገንዘብ  1,038,722,506.06 (አንድ ቢሊዮን፣ሰላሳ ስምንት ሚሊዮን፣ሰባት መቶ ሃያ ሁለት ሺህ፣አምስት መቶ ስድስት ብር፣ከስድስት ሳንቲም) ብር የሚሸፍነው  የኢትዮጵያ መንግስት ነው ። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱን እያከናወነ የሚገኘው  አገር በቀሉ ኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን የስራ ተቋራጭ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ፕሮሚነንት ኢንጅነሪንግ ሶሉሽን እያከናወነው ይገኛል። መንገዱ ካለው ዘርፈ-ብዙ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ፋይዳ አንፃር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ነው እየተገነባ የሚገኘው ። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በጉደር ከተማ ያለውን ትልቅ የገበያ  ትስስር በመፍጠር አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ያደርጋል። መስመሩ ሀገር አቋራጭ የመንገድ መስመር በመሆኑ የጉዞ ጊዜን  በማሳጠር ወደሚፈለግበት መዳረሻ ለመድረስ ያስችላል።  ግንባታው ሲጠናቀቅ ቶኬ ኩታዬ ቀበሌዎችን እና በአምቦ ወረዳ ጉደር እና አምቦ ከተማን በአስፋልት ኮንክሪት የሚያገናኝ ይሆናል። ከዚህ ቀደም በተሽከርካሪ ለመጓዝ ይወስድ የነበረውን  የአርባ አምስት ደቂቃ  ግንባታው ሲጠናቀቅ ወደ ሃያ ደቂቃ በማሳጠር የጉዞ ጊዜን ያቀላጥፋል።  የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ  የጎን ስፋት ትከሻን ጨምሮ   በከተማ 23.8 ሜትር፣ ሲሆን በገጠር 19.5 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ  ነው። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

20ኛው የዓለም የሥራ ድርጅት አህጉራዊ ጉባዔ ተጠናቀቀ አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2017 (ኢ መ አ):- ከግንቦት 11 - 15 በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው 20ኛው የዓለም የሥራ ድርጅት አህጉራዊ ጉባዔ በስኬት ተጠናቅቋል። የዘንድሮው ጉባዔ በከተማ እና መሠረተ ልማት ሚንስቴር፣ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እና የዓለም አቀፉ የሥራ ድርጅት የጋራ ትብብር መካሄዱ ይታወቃል። በጉባዔው ማጠቃለያ ላይ በወጣው መግለጫ፣ ኢትዮጵያ የተሳካ ጉባዔ ማካሄዷ ተገልጿል። በሩዋንዳ ኪጋሊ በተካሄደው 19ኛው ጉባዔ ላይ የተነሱ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ምቹ የሥራ ምህዳር ላይ ያተኮሩ ጉዳዩች ላይ መድረኩ በስፋት ተወያይቷል። ከጥናት እና ውይይት በዘለለ በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ጤናማ የሥራ ከባቢ በመፍጠር እንዲሁም ማኅበራዊ ፍትህን በማረጋገጥ ረገድ የአፍሪካ ሀገራት በጋራ መሥራት እንደሚገባቸው የአቋም መግለጫው አሳስቧል። ከዚህም ባለፈ ብልሹ አሠራር እና ሙስናን እንዲሁም ኢ-ፍትሀዊነትን በመዋጋት ረገድ ሀገራቱ በጋራ መቆም እንደሚኖርባቸው ተጠቅሷል። በጉባዔው ላይ በርካታ ጠቃሚ ልምዶች መገኘታቸውን የገለጹት የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚንስትር ጫልቱ ሳኒ፤ ለተግባራዊነቱ ሁላችንም ኃላፊነት አለብን ብለዋል። ጉባዔው በስኬት እንዲጠናቀቅ ያልተቆጠበ ድጋፋቸውን ያደረጉትን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ የአፍሪካ ሕብረት፣ የዓለም ባንክ እና ሌሎች አጋር ድርጅቶችን ሚንስትሯ አመስግነዋል፡፡ ከ2ሺህ በላይ ተሳታፊዎች በዘንድሮው ጉባዔ የተካፈሉ ሲኾን፣ ከመድረኩ ጎን ለጎን በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ በርካታ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል ። በመጨረሻም ዛምቢያ ከሁለት ዓመት በኋላ የሚካሄደውን 21ኛውን የዓለም የሥራ ድርጅት አህጉራዊ ጉባዔ እንድታዘጋጅ በመድረኩ ተመርጣለች። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

Call for paper
Call for paper

ILO Regional Conference For Labor-Based Practitioners (Day 4) Live Stream https://www.youtube.com/live/zo6imcUBAW4?si=vlo66Ma6f8lxiV13

የጉባኤው ተሳታፊዎች በከተማዋ የተከናወኑ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ አዲስ አበባ፣ ግንቦት 19 ፣ 2017 (ኢ መ አ):- ሦስተኛ ቀኑን በያዘው የ20ኛው የዓለም አቀፉ የሥራ ድርጅት አህጉራዊ ጉባኤ ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወኑ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል። ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የተውጣጡት ጎብኚዎቹ የቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን፣ የእንጦጦ ፓርክ እንዲሁም የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴ ተዘዋውረው የጎበኙ ሲኾን፣ በከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ገለጻ ተደርጎላቸዋል። ጎብኝዎቹ በተደረገላቸው አቀባበል ያመሰገኑ ሲኾን፣ በምልከታቸውም ደስተኛ መኾናቸውን ተናግረዋል። በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በምርት ሂደት፣ በገበያ ትስስር እንዲሁም ከተማዋን ውብ እና ጽዱ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራትን አድንቀዋል ። በተለይም በአርንጎዴ ልማት በኩል የተሠሩ ሥራዎች በርካታ ልምድ የሚወሰድባቸው መኾኑን አንስተዋል። የሥራ ቦታን ለሠራተኛው ደኅንነት ምቹ እና ተስማሚ በማድረግ በኩል የተከናወኑ ሥራዎችም አመርቂ መኾናቸውን ጎብኘዎቹ ተናግረዋል። አህጉራዊ ጉባኤው በነገው ዕለትም በሚካሄዱ የተለያዩ ሁነቶች ቀጥሎ ይውላል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

በአዲስ አበባ እየተካሄደ የሚገኘው 20ኛው የዓለም የሥራ ድርጅት በሥራ ላይ የተመሰረተ የባለሙያዎች ሌበር ቤዝድ ፕራክቲሽነርስ አህጉራዊ ጉባኤ እውነታዎች:- 👉 ጉባኤው በሁለት ዓመት አንዴ የሚካሄድ ሲኾን፣ በአዲስ አበባ እየተካሄደ የሚገኘውን የዘንድሮው ጉባኤ በዓለም አቀፉ የሥራ ድርጅት (ILO)፣ የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በጥምረት የተዘጋጀ ነው። 👉 የመጀመሪያው አህጉራዊ ጉባኤ የተካሄደው እ.ኤ.አ በ1990 በታንዛኒያ ነበር። 👉 ኢትዮጵያ 20ኛውን አህጉራዊ ጉባኤ እንድታዘጋጅ በከፍተኛ ድምጽ የተመረጠችው እ.ኤ.አ በ2023 በሩዋንዳ ኪጋሊ በተካሄደው ጉባኤ ወቅት ነበር። 👉 ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም እ.ኤ.አ በ2017 የተካሄደውን 17ኛውን አህጉራዊ ጉባኤ በድምቀት አስተናግዳለች። 👉 የዚህ ዓመት ጉባኤ "የማይበገር ማኅበረሰብ እና ጤናማ አካባቢ፦ የሰው ኃይልን በብዛት የሚጠቀሙ የኢንቨስትመንት ፕሮግራም አካሄዶች" በሚል መሪ ሐሳብ እየተካሄደ ይገኛል። 👉 በጉባኤው ላይ ሚንስትሮች፣ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ ተወካዮች፣ ዓለም አቀፍ የልማት አጋሮች፣ የሥራ ተቋራጮች እና አማካሪ መሀንዲሶች፣ እንዲሁም የዘርፉ ምሁራንን ጨምሮ በአጠቃላይ ከ1ሺህ 500 መቶ በላይ ተሳታፊዎች ይታደማሉ። 👉 የዘርፉ ተመራማሪዎች፣ ፖሊሲ አውጭዎች እና ባለሙያዎች በሳል የጥናትና ምርምር ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ። 👉 ከዋናው ጉባኤ በተጓዳኝ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ የጎን ለጎን ሁነቶች ይከናወናሉ። 👉 ጉባኤው ኢትዮጵያ በመሰረተ ልማት ዝርጋታ፣ በአካባቢ ጥበቃ እንዲሁም በአካታች እና ዘላቂ ልማት ረገድ እያስመዘገበች ያለችውን ውጤት ለአፍሪካ እና ለዓለም ለማስተዋወቅ እድል የምታገኝበት ይሆናል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads ቀጥታ ለመከታተል https://www.youtube.com/live/U5nGTg-XaE4?si=f_9UIRFE1LHlH6PA