ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት
Ir al canal en Telegram
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርሥትያን ስንክሣር ውስጥ የተጻፉ የቅዱሳን አባቶቻችንና የቅዱሳት እናቶቻችን ገድላቸውና አስገራሚ ታሪካቸው ዓመቱን ሙሉ ምንም ሳይቋረጥ በየቀኑ ይነገርበታል! ለአሥትያየትዎ @abitago
Mostrar más1 214
Suscriptores
Sin datos24 horas
+47 días
+330 días
Carga de datos en curso...
Canales Similares
Nube de Etiquetas
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Menciones Entrantes y Salientes
---
---
---
---
---
---
Atraer Suscriptores
julio '26
julio '26
+8
en 0 canales
junio '26
+25
en 0 canales
Get PRO
mayo '26
+27
en 0 canales
Get PRO
abril '26
+11
en 0 canales
Get PRO
marzo '26
+15
en 0 canales
Get PRO
febrero '26
+23
en 0 canales
Get PRO
enero '26
+38
en 0 canales
Get PRO
diciembre '25
+39
en 0 canales
Get PRO
noviembre '25
+36
en 0 canales
Get PRO
octubre '25
+21
en 0 canales
Get PRO
septiembre '25
+20
en 0 canales
Get PRO
agosto '25
+10
en 0 canales
Get PRO
julio '25
+32
en 0 canales
Get PRO
junio '25
+21
en 0 canales
Get PRO
mayo '25
+21
en 0 canales
Get PRO
abril '25
+26
en 0 canales
Get PRO
marzo '25
+54
en 0 canales
Get PRO
febrero '25
+34
en 0 canales
Get PRO
enero '25
+67
en 0 canales
Get PRO
diciembre '24
+90
en 0 canales
Get PRO
noviembre '24
+82
en 1 canales
Get PRO
octubre '24
+46
en 0 canales
Get PRO
septiembre '24
+61
en 0 canales
Get PRO
agosto '24
+67
en 0 canales
Get PRO
julio '24
+57
en 0 canales
Get PRO
junio '24
+65
en 0 canales
Get PRO
mayo '24
+66
en 0 canales
Get PRO
abril '24
+85
en 1 canales
Get PRO
marzo '24
+68
en 0 canales
Get PRO
febrero '24
+118
en 0 canales
Get PRO
enero '24
+99
en 0 canales
Get PRO
diciembre '23
+98
en 0 canales
Get PRO
noviembre '23
+25
en 0 canales
Get PRO
octubre '23
+13
en 1 canales
Get PRO
septiembre '23
+7
en 0 canales
Get PRO
agosto '23
+17
en 0 canales
Get PRO
julio '23
+16
en 0 canales
Get PRO
junio '23
+9
en 0 canales
Get PRO
mayo '23
+3
en 0 canales
Get PRO
abril '23
+4
en 0 canales
Get PRO
marzo '23
+3
en 0 canales
Get PRO
febrero '23
+5
en 0 canales
Get PRO
enero '23
+14
en 0 canales
Get PRO
diciembre '22
+10
en 0 canales
Get PRO
noviembre '22
+10
en 0 canales
Get PRO
octubre '22
+8
en 0 canales
Get PRO
septiembre '22
+11
en 0 canales
Get PRO
agosto '22
+4
en 0 canales
Get PRO
julio '22
+11
en 0 canales
Get PRO
junio '22
+11
en 0 canales
Get PRO
mayo '22
+5
en 0 canales
Get PRO
abril '22
+4
en 0 canales
Get PRO
marzo '22
+6
en 0 canales
Get PRO
febrero '22
+10
en 0 canales
Get PRO
enero '22
+7
en 0 canales
Get PRO
diciembre '21
+7
en 0 canales
Get PRO
noviembre '21
+8
en 0 canales
Get PRO
octubre '21
+3
en 0 canales
Get PRO
septiembre '21
+11
en 0 canales
Get PRO
agosto '21
+9
en 0 canales
Get PRO
julio '21
+13
en 0 canales
Get PRO
junio '21
+6
en 0 canales
Get PRO
mayo '21
+8
en 0 canales
Get PRO
abril '21
+26
en 0 canales
Get PRO
marzo '21
+500
en 0 canales
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 11 julio | 0 | |||
| 10 julio | 0 | |||
| 09 julio | +2 | |||
| 08 julio | 0 | |||
| 07 julio | +2 | |||
| 06 julio | 0 | |||
| 05 julio | 0 | |||
| 04 julio | 0 | |||
| 03 julio | +1 | |||
| 02 julio | +3 | |||
| 01 julio | 0 |
Publicaciones del Canal
| 2 | Sin texto... | 28 |
| 3 | መቄዶንያን፣ ጠርጤስን፣ ጢሮአዳን፣ ድልማጥያን፣ እልዋሪቆን፣ ኒቆጵልዮን፣ ብረንዲስን ጎብኝቷል፡፡ በዚህ የመጨረሻ የስብከት ጉዞው ለአራት ዓመታት ያህል ቆይቷል፡፡ ሐዋርያው በተለያዩ ጊዜያት ዐሥራ ዐራት መልዕክታትን ጽፏል፡፡
በመጨረሻ በ64 ዓ.ም ኔሮን ቅጥ ባጣ በጥጋቡ ‹‹የሮማ ከተማ ስትቃጠል ምን እንደምትመስል ማየት እፈልጋለሁ›› ብሎ በእሳት አቃጠላት፡፡ የሮም ሕዝብ በከተማው መቃጠል በማዘኑና በማመጹ ጥጋበኛው ኔሮን ነገሩን ሁሉ በክርስቲያኖች ላይ አሳበበ፡፡ በዚህም የተነሣ ክርስቲያን የተባለ ሁሉ እጣ ፈንታው መሰደድ፣ መሠየፍ፣ መታረድ ሆነ፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም በኒቆጵልዮን ከተማ ሲያስተምር በ65 ዓ.ም ተይዞ ወደ ወኅኒ ገባ፡፡ ለሁለት ዓመት ከስድስት ወር በጨለማ ቤት ታሥሮ ከቆየ በኋላ በ74 ዓመቱ በሮም ከተማ በኦስትያ መንገድ አንገቱን ተሰይፎ በ67 ዓ.ም ሐምሌ 5 ቀን ሰማዕትነቱን በድል ፈጽሞ የክብር አክሊሉን ተቀዳጀ፡፡
የብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን! | 26 |
| 4 | በ32 ዓመቱ ከኢየሩሳሌም 223 ኪ.ሜ ርቀት በስተሰሜን በኩል በምትገኘው በደማስቆ ከተማ ብዙ ክርስቲያኖች መኖራቸውን ሲሰማ ወደ ሊቀ ካህናቱ ቀርቦ ክርስቲያኖችን ለማጥፋት የሚያስችለውን የፈቃድ ደብዳቤ አጻፈና ጭፍሮችን አስከትሎ ወደ ደማስቆ አመራ፡፡ ጳውሎስ ወደ ከተማዋ ለመድረስ ጥቂት ሲቀረው ነበር ከሰማይ የወረደው ብርሃን አካባቢውን ያለበሰውና «ሳውል ሳውል ለምን ታሳድደኛለህ?» የሚለውን ድምፅ የሰማው፡፡ ጳውሎስም «ጌታ ሆይ ማን ነህ?» ብሎ ሲጠይቅ ጌታችን «አንተ የምታሳድደኝ እኔ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነኝ፣ የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል» ሲል ተናገረው፡፡ ያን ጊዜም በወደቀበት ሆኖ እየተንቀጠቀጠ «ጌታ ሆይ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ?» ሲል ጠየቀ፡፡ ከዚህ በኋላ ተነሥቶ ወደ ደማስቆ እንዲገባ ተነገረው። ሐዋ 9፡1-15፡፡ ዐይኖቹ ማየት ስላልቻሉ እየተመራ ወደ ደማስቆ ገባ፡፡ ለሦስት ቀናት ያህልም እህል ሳይቀምስ ቆየ፡፡ በዚያች ዕለት እግዚአብሔር አምላክ በደማስቆ ለሚገኘውና ሐናንያ ለተባለው አባት በራእይ ተገለጦለት ቅዱስ ጳውሎስም ያለበትን አድራሻ ነገረውና ሄዶ እንዲያጠምቀው አዘዘው፡፡ ሐናንያም አስቀድሞ የቅዱስ ጳውሎስን ማንነት ያውቃል፡፡ አብዛኞቹ በደማስቆ የሚገኙት የቅዱስ ጳውሎስን ማንነት ያውቁታል፡፡ አብዛኞቹ በደማስቆ የሚገኙት ክርስቲያኖች ከኢየሩሳሌም በስደት የመጡ ናቸው፡፡ ያን ስደት ያስነሣው ደግሞ በቅዱስ እስጢፋኖስ ላይ የደረሰው መከራ ነው፡፡ በዚህ የቅዱስ እስጢፋኖስ ሰማዕትነት ደግሞ ዋናው ተዋናይ ሐዋርያው ጳውሎስ ነበር፡፡ ይህን የሚያውቀው ሐናንያ ጳውሎስን ሄደህ አጥምቀው ሲባል ከእግዚአብሔር ጋር መከራከር ጀምሮ ነበር፡፡ እግዚአብሔር አያውቀው ይመስል ስለ ቅዱስ ጳውሎስ ማስረዳት ጀመረ፡፡ በመጨረሻ ግን «ይህ በአሕዛብም በነገሥታትም በእሥራኤልም ልጆች ፊት ስሜን ይሸከም ዘንድ ለእኔ የተመረጠ ዕቃ ነውና ሂድ፤ ስለ ስሜ ስንት መከራ ሊቀበል እንዲያስፈልገው እኔ አመለክተዋለሁና» በማለት እግዚአብሔር ሐናንያን ላከው፡፡ እርሱም ሄዶ አጠመቀው፡፡ ሐዋ 9፡5-16፡፡ ሐናንያ ካጠመቀውና ካስተማረው በኋላ ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ዓረብ ሀገር መሄዱን ራሱ ተናግሮአል፡፡ ገላ 1፡17፡፡
ጳውሎስም ወዲያው ወደ ዐረቢያ ምድር ሄዶ ለ3 ዓመታት ካስተማረ በኋላ ወደ ደማስቆ ተመልሶ በአይሁድ መካከል በፊት ያሳድደው የነበረውን ኢየሱስ ክርስቶስን መስበክ ጀመረ፡፡ ከዚያ በፊት በፈሪሳዊነቱና ለአይሁድ ሕግ በነበረው ቅንዓት የሚታወቀው ጳውሎስ ዛሬ ወንጌል ሲሰበክ በማየታቸው አይሁድ በክፋት ተነሱበት፡፡ በዚህም የተነሣ የደማስቆ ክርስቲያኖች በቅርጫት አድርገው ወደ ኢየሩሳሌም ላኩት፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ኢየሩሳሌም ሲደርስ የገጠመው ሁለት ችግር ነበር፡፡ በቅድሚያ አይሁድ ጳውሎስን እንደሚያውቁትና እንደለመዱት ሆኖ ስላላገኙት ሊገድሉት ተነሡ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ክርስቲያኖች የቅዱስ ጳውሎስን መመለስ ሊያምኑ አልቻሉም ነበር፡፡ በመጨረሻ ግን በርናባስ ወደ ሐዋርያት ዘንድ ወስዶ የጳውሎስን መመለስ በመንገር እንዲያምኑት አደረጋቸው፡፡
ከዚህም በኋላ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በኢየሩሳሌም በድፍረት በማስተማሩ አይሁድ ስለተቃወሙት ከተማዋን ትቶ በቂሳርያ በኩል ወደ ትውልድ ሀገሩ ጠርሴስ ተመለሰ፡፡ በዚያም ለዘጠኝ ዓመታት ሲቆይ ወንጌልን እያስተማረ እስከ አንጾኪያ ድረስ ሰበከ፡፡ ከኢየሩሳሌም ውጭ የአሕዛብ ከተማ በነበረችው በአንጾኪያ የክርስትና ሃይማኖት ተስፋፋ፡፡ ከኢየሩሳሌም የተሰደዱት ክርስቲያኖች የአንጾኪያን ሕዝብ ተግተው በማስተማራቸው ዝናው እስከ ኢየሩሳሌም ደረሰ፡፡ በዚህም ምክንያት በኢየሩሳሌም የነበሩት ሐዋርያት በርናባስን ወደ አንጾኪያ ላኩት፡፡ በርናባስ የግሪክ ቋንቋ ችሎታ ያለውንና ከማንኛውም ሰው ጋር መግባባት የሚችለውን ደግሞም እግዚአብሔር ለአሕዛብ ሐዋርያ እንዲሆን የመረጠውን ቅዱስ ጳውሎስን ይዞ በአንጾኪያ ሥራቸውን ጀመሩ፡፡ በገላትያ መልዕክቱ ምዕራፍ ሁለት ላይ ራሱ እንደገለጠው ከዐሥራ አራት ዓመት በኋላ ከአንጾኪያ ክርስቲያኖች የሰበሰበውን ርዳታ ይዞ ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ፡፡ በዚህም በአይሁድና በአሕዛብ መካከል የነበረውን መለያየት ክርስትና አንድ እንዳደረገው አስመሰክሯል። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በመጀመሪያው ጉዞው ከኢየሩሳሌም ወደ አንጾኪያ ከተመለሰ በኋላ በልዑል እግዚአብሔር ጥሪ በአሕዛብ ሀገር ወንጌልን ለመስበክ ከበርናባስ ጋር ወጡ፡፡ በዚህ ጉዞአቸው በጠቅላላ ወደ 2000 ኪ.ሜ የሚደርስ መንገድ በእግር ተጉዟል፡፡ ይህም ጉዞ የተከናወነው በ46 ዓ.ም አካባቢ ነው፡፡ በጉዞውም የተሸፈኑት ሀገሮች ሲሊንውቂያ፣ ቆጵሮስ፣ ስልማን፣ ጳፋ፣ ጰርጌን፣ ገላትያ፣ ጵስድያ፣ ኢቆንዮን፣ ሊቃኦንያ፣ ልስጥራ፣ ደርቤን፣ ጵንፍልያ፣ አታልያ እና አንጾኪያ ናቸው፡፡
ሁለተኛው ጉዞ የተከናወነው በ50 ዓ.ም ገደማ ሲሆን በመጀመሪያው ጉዞ ቅዱስ ማርቆስ አብሮ ተጉዞ ነበር፡፡ ነገር ግን ጵንፍልያ ከተማ ሲደርስ እናቱ ስለናፈቀችው መመለስ በመፈለጉ በርናባስ ወደ ኢየሩሳሌም ይዞት መጣ፡፡ ስለዚህም በሁለተኛው ጉዞ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሲላስን ይዞ ወደ ኪልቂያ ሶርያ ሲጓዝ በርናባስ ደግሞ ማርቆስን አስከትሎ ወደ ቆጵሮስ ሄደ፡፡ በዚህ ጉዞው ቅዱስ ጳውሎስ እስከ ግሪክ ደርሷል፡፡ የተጓዘባቸውና ያስተማረባቸው ከተሞችም፡- ደርብያ፣ ልስጥራ፣ ፍርግያ፣ ገላትያ፣ ሚስያ፣ ጢሮአዳ፣ ሳሞትራቄ፣ ናፑሊ፣ ፊልጵስዩስ፣ ተሰሎንቄ፣ በርያ፣ አቴና፣ ቆሮንቶስ፣ አንክራኦስ፣ አፌሶን፣ ቂሳርያ፣ ኢየሩሳሌምና አንጾኪያ ናቸው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ የመንፈስ ልጁ ጢሞቴዎስን ያገኘው በዚሁ ጉዞው በልስጥራ ከተማ ነው፡፡
ሦስተኛው ጉዞ የተከናወነው በ54 ዓ.ም ሲሆን የተሸፈኑት ሀገሮች የሚከተሉት ነበሩ፡- ገላትያ፣ ፍርግያ፣ ኤፌሶን፣ መቄዶንያ፣ ፊልጵስዩስ፣ ቆሮንቶስ፣ ጢሮአዳ፣ አሶን፣ ሚልጢኒን፣ አንጠቀከስዩ፣ ትሮጊሊዩም፣ መስጡ፣ ቆስ፣ ሩድ፣ ጳጥራ፣ ጢሮስ፣ ጵቶልማይስ፣ ቂሳርያና ኢየሩሳሌም ናቸው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ከልዩ ልዩ ሀገሮች ክርስቲያኖች የሰበሰበውን ዕርዳታ ለኢየሩሳሌም ቤተ ክርስቲያን በመያዝ ሦስተኛውን ጉዞ አጠናቆ ኢየሩሳሌም ገባ፡፡ ነገር ግን ኢየሩሳሌም የገባበት ጊዜ የፋሲካ በዓል ስለነበር ከልዩ ልዩ ሀገሮች የተሰበሰቡ አይሁድ በከተማዋ ነበሩ፡፡ እነዚህ በዝርወት የሚኖሩ አይሁድ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስን በየሀገራቸው በትምህርቱ የተነሣ ሲቃወሙት የነበሩ ናቸው፡፡ እኒህ አይሁድ ቅዱስ ጳውሎስን በኢየሩሳሌም ሲያዩት ታላቅ ተቃውሞ አነሡበት፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ተቃውሞአቸውን ለመግታት እንደ አይሁድ ሕግ በቤተ መቅደስ የመንጻት ሥርዓት መፈጸም ጀመረ፡፡ ነገር ግን ከኤፌሶን የተከተለውን ጥሮፊሞስን ወደ መቅደስ ያስገባው ስለመሰላቸው ተቃውሞአቸው በረታ፡፡ ከተማውንም አወኩት፡፡ ይህም ቅዱስ ጳውሎስን በ58 ዓ.ም ለሮም እሥር ዳረገው፡፡
ከብዙ መከራና ሥቃይ በኋላ ታስሮ ሮም ገባ፡፡ በዚያም በቁም እሥር ለሁለት ዓመታት ያህል ወንጌልን ሰበከ፡፡ የሁለቱን ዓመት የቁም እሥር እንደጨረሰ ወደ ኔሮን ፍርድ ቤት ቀረበ፡፡ ይህም በ60ዎቹ ዓ.ም ነው፡፡ በፍርድ ቤቱ በተደረገው ምርመራ የሮሜን ሕግ የሚቃወም ምንም ወንጀል ስላልተገኘበት በነፃ ተለቀቀ፡፡ ከዚህ በኋላ ነው ሐዋርያው አራተኛውንና የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ያልመዘገበውን ጉዞውን ያደረገው፡፡ ይህ ጉዞው በመታሠሩ አዝነው ተክዘው የነበሩ ክርስቲያኖችን ለማጽናናትና የጀመራቸውን ሥራዎች ፍጻሜ ለማየት የተደረገ ጉዞ ነበር፡፡ በዚህም ጉዞው ኢየሩሳሌምን፣ ኤፌሶንን፣ ሎዶቅያን፣ | 18 |
| 5 | ሐዋርያው ልዑል እግዚአብሔር ባደለው ጸጋ ጥላው እንኳን ድውያንን ይፈውስ ነበር፡፡ የሐዋ 5፡15፡፡ በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 15 ላይ እንደተጠቀሰው በ50 ዓ.ም አካባቢ በኢየሩሳሌም በተደረገው የሐዋርያት ሲኖዶስ ከአንጾኪያ ክርስቲያኖች ለቀረበው ጥያቄ የመጀመሪያውን መልስ የሰጠው እርሱ ነበር፡፡ ስለ ቅዱስ ጴጥሮስ መልክና ቁመና ጥንታዊያን መዛግብት እንደሚከተለው ያቀርቡታል። «ፊቱ ሰፋ ያለ ሲሆን ሪዛምና መካከለኛ ቁመት የነበረው ራሰ በራ ነው።
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ እንደ አባት ይታይ ስለነበረ ታዴዎስን ወደ ሀገረ ስብከቱ ለማድረስ አብሮት ተጕዞ ነበር፡፡ ወደ ከተማዋ ሲጠጉም አንድ የሚያርሱ ሽማግሌ አገኙ፡፡ ሐዋርያቱ ወደ ሽማግሌው ጠጋ ብለው የእግዚአብሔር ሰላምታ ሰጧቸው፡፡ የሚበላ ነገር ያላቸው እንደሆነም ጠየቋቸው፡፡ ሽማግሌው ገበሬም ደግ ነበሩና ‹‹ከቤት እስካመጣላችሁ ድረስ በሬዎቼን ጠብቁልኝ›› ብለው ወደ መንደር ገቡ፡፡ ሐዋርያቱም ‹‹የተጠመዱትን በሬዎች ተቀምጦ መመልከት ሐፍረት ነው›› አሉና ታዴዎስ ማረስ ጀመረ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም የስንዴውን ዘር አነሣ፡፡ ‹‹ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! በረከትህ በዚህ እርሻ ላይ ትውረድ›› ብሎ ጸለየ፡፡ ታዴዎስም ‹‹የምድር በረከት በዚች እርሻ ይታይ ዘንድ አምላኬ ሆይ ፈቃድህ ይሁን›› አለ፡፡ 30 ትልም አረሱና የስንዴውን ቡቃያ ዕለቱን ወዲያው አበቀሉት፡፡ ወዲያውም ዕለቱን ዐይንን የሚማርክ የስንዴ እሸት ሆኖ ታየ፡፡ አረጋዊው ገበሬ ሲመለስ የእርሻውን መለምለም ተመልክቶ አደነቀና ‹‹ጌቶቼ እናንተ እነማን ናችሁ? በእውነት እናንተ ከሰማይ የወረዳችሁ አማልክት ናችሁ›› ብሎ በእግራቸው ሥር ወደቀ፡፡ ሐዋርያቱ ግን ‹‹እኛ የአምላክ ባሪያዎች እንጂ አማልክት አይደለንም›› ብለው የመጡበትን ምክንያት ነግረውት ወንጌልን አስተማሩት፡፡ ገበሬውም እየተደነቁ እሸቱን ታቅፈው ለቤተሰባቸው ሊያሳዩ ወደ ቤታቸው ሮጡ፡፡ የከተማዋ ሰዎችም ነገሩ ገርሟቸው ከበቧቸው፡፡ ሽማግሌው ገበሬም ያዩትንና የሰሙትን ሁሉ ተረኩላቸው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ በማናቸውም ነገር ፈጣንና ቀልጣፋ ነበር፡፡ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ መሠረት ቅዱስ ጴጥሮስ በፍልስጤም፣ በሶርያ፣ በጳንጦን፣ በገላትያ፣ በቀጰዶቅያ፣ በቢታንያ እና በሮሜ ወንጌልን ሰብኳል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ በሮሜ አንድ ዓመት ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር ካስተማረ በኋላ የሮሜ ክርስቲያኖች እየበዙ ከመምጣታቸውም በላይ የክርስትናው ጉዞ እስከ ሮማ ባለሥልጣናት ደረሰ፡፡ በትምህርቱና በተአምራቱ ካመኑት መካከል የሮማ ንጉሥ ባለሟልና የቅርብ ወዳጅ የሆነው አልታብዮስ ሚስቱ ክርስቲያን በመሆኗ በታላቅ ሀዘን ተለያዩ፡፡ በርካታ ሴቶችም አብረዋት ወደ ክርስትናው ዓለም ገቡ፡፡ የኔሮን የቅርብ ባለሥልጣናት የሆኑት የአልቢኖስና የአግሪጳ ሚስቶች ወደ ክርስትናው ገቡ፡፡ በዚህን ጊዜ ኔሮን ንጉሠ ሮማ በቅንዓት ተነሣባቸው፡፡ ኔሮን በሮም የነገሠው በ54 ዓ.ም ነው፡፡ በመንግሥቱ መጀመሪያ ደግ ሰው ነበረ፡፡ ነገር ግን በነገሠ በዓመቱ የጨካኝነት ዐመሉ ብቅ ማለት ጀመረና የአባቱን ልጅ አስገደለ፡፡ በ59 ዓ.ም ደግሞ እናቱን በመርዝ ገደለ፡፡ በ63 ዓ.ም እያስተማረ ያሳደገውን መምህሩን፣ በ62 ዓ.ም የልጅነት ሚስቱን አግታሺያን አስገደለ፡፡ ከእርሷም በኋላ ያገባትን ሚስቱን ፓፒያንም እንዲሁ ገደላት፡፡ ኔሮን በ64 ዓ.ም እርሱ ከከተማው ወጣ ብሎ በሚገኘው ቤተ መንግሥቱ ተቀምጦ የሮማን ከተማ እሳት ለቀቀባትና የሮም ሕዝብ በደረሰው አደጋ እጅግ መቆጣቱን ሲመለከት በክርስቲያኖች አመካኘ፡፡ በዚህም የተነሣ በሮማ ከተማ ሁለት ዓይነት ወሬ መናፈስ ጀመረ፡፡ ‹‹የሮማ አማልክት በክርስቲያኖች ሃይማኖት ስለተቆጡ በከተማዋ እሳት አዘነቡባት›› የሚለው የመጀመሪያው ሲሆን ‹‹ክርስቲያኖች ሆን ብለው ከተማዋን አቃጥለዋታል›› የሚለው ደግሞ ሁለተኛው ወሬ ነበር፡፡
የከተማው መጋየት ያበሳጨው የሮማ ሕዝብ፣ ክርስቲያን የሆነውን ሁሉ እያወጣ መግደሉን ተያያዘው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ሰዓት በእሥር ቤት ነበርና ተሰይፎ ዐረፈ፡፡ ይህን የሰሙት የአግቢኖስና የአግሪጳ ሚስቶች እነዚህም የሮም ባለሟሎች ነበሩና እነርሱም «ባይሆን አንተ ትረፍልን» ብለው ቅዱስ ጴጥሮስን በከተማዋ ግንብ በገመድ አሥረው በቅርጫት በማውረድ ቅጽረ ሮማን ለቅቆ እንዲወጣ አደረጉት፡፡ ሐዋርያው እንዳይታወቅ ራሱን ሰውሮ በኦፒየም ጎዳና ጉዞውን ቀጠለ፡፡ ሮማን ለቆ እያዘገመ በሸመገለ ጉልበቱ ሲጓዝ አንድ ቀይ ጐልማሳ መስቀል ተሸክሞ ወደ እርሱ ሲመጣ አየ፡፡ እየቀረበ ሲመጣ ግን ጌታችን መሆኑን ተረዳ፡፡ ወዲያው በፊቱ ተደፋና «ጌታዬ ወዴት እየተጓዝክ ነው?» ብሎ ጠየቀው፡፡ ጌታችንም ‹‹ልሰቀል ወደ ሮም ከተማ እሄዳለሁ›› አለው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ‹‹ዳግመኛ ትሰቀላለህን?›› አለው፡፡ አስቀድሞ በምን ዓይነት ሞት ይሞት ዘንድ እንዳለው ሲነግረው ‹‹አንተ ጎልማሳ ሳለህ ወገብህን በገዛ ራስህ ታጥቀህ ወደ ምትወደው ትሄድ ነበር፤ ነገር ግን በሸመገልህ ጊዜ እጆችህን ትዘረጋለህ፣ ሌላውም ያስታጥቅሃል፣ ወደማትወደውም ይወስድሃል›› ያለውን አስታውሶ እጅግ አዝኖ ወደ ሮም ከተማ ተመልሰ፡፡ የኔሮን ወታደሮችም እየፈለጉት ነበርና «እነሆኝ ስቀሉኝ» አላቸው፡፡ ያን ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስን ይዘው አሠሩት፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላም ሮማውያን የመስቀያውን እንጨት ሲያቀርቡ ተመልክቶ ‹‹እኔ እንደጌታዬ ልሰቀል አይገባኝም እንደ ጌታዬ ሳይሆን ቁልቁል ዘቅዝቃችሁ ሰቀሉኝ›› ብሎ ለመናቸው፡፡ እነርሱም ፈቃዱን ፈጽመውለት ሐምሌ 5 ቀን 67 ዓ.ም ዘቅዝቀው ሰቅለውታል፡፡
+ + +
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ፡- የዕብራይስጥ ስሙ ሳውል ነው ትርጉሙም ስጦታ ማለት ነው፡፡ በሮማዊ ስሙ ደግሞ ጳውሎስ ተብሏል፡፡ ሐዋ 13፡9፡፡ በሮማውያን ጳውሎስ ማለት ‹‹ንዋየ ኅሩይ-ምርጥ ዕቃ›› ማለት ነው፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ዘሩ ከዕብራዊያን ከብንያም ነገድ ሲሆን የተወለደውም በጠርሴስ ከተማ ነው፡፡ ጠርሴስ በንግድ የታወቀች የኪልቂያ ዋና ከተማ ናት፡፡ በከተማዋ እስከ አምስት መቶ ሺህ የሚገመቱ ከየሀገሩ የተሰባሰቡ ሕዝቦች ነበሩባት፡፡ ሮማውያን በሥራቸው ለሚተዳደሩት ሕዝቦች ሮማዊ ዜግነትን ይሰጡ ስለነበር የቅዱስ ጳውሎስ አባት በዜግነት ሮማዊ ነበር፡፡ ይህም ለቅዱስ ጳውሎስ ተላልፎለታል፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ በ15 ዓመት ዕድሜው ወደ ትውልድ ሀገሩ በመመለስ በኢየሩሳሌም ከነበረው የታወቀው የገማልያል ትምህርት ቤት ገባ፡፡ በዚያም የአይሁድን ሕግና ሥርዓት እየተማረ እስከ 30 ዓመቱ ቆየ፡፡ ገማልያል ፈሪሳዊ ስለነበር ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ይህን ተቀብሎታል፡፡ በ30 ዓመቱ የአይሁድ ሸንጎ አባል ሆነ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያስተምርበት ዘመን ቅዱስ ጳውሎስ በኢየሩሳሌም ስለነበረ ሁኔታዎቹን ሁሉ ያውቃል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ በአይሁድ ሸንጎ አባልነት ለሁለት ዓመታት በሠራበት ወቅት ለኦሪታዊ እምነቱ ቀናተኛ ፈሪሳዊ በመሆኑ ክርስቲያኖችን በማናቸውም አጋጣሚ ይቃወም ነበር፡፡ ለዚህም ነው ሊቀ ዲያቆናት እስጢፋኖስ ወንጌልን በማስተማሩ ምክንያት ተከሶ በአይሁድ ሸንጎ በቀረበ ጊዜ የተከራከረው፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ በድንጋይ ተወግሮ በሰማዕትነት ሲያርፍም የወጋሪዎችን ልብስ ይጠብቅ የነበረው እርሱ ነው፡፡ ቅዱስ አውግስጢኖስ ‹‹በእስጢፋኖስ ጸሎት ቤተ ክርስቲያን የጠፋውን ጳውሎስን አገኘች›› በማለት ተናግሯል፡፡ | 16 |
| 6 | አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን
ሐምሌ 5-እጅግ የከበሩ ሐዋርያት ብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ ሰባ ሁለቱ አርድእት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓላቸው ነው፡፡
+ መልአኩ ቅዱስ ሳቁኤል የበዓሉ መታሰቢያ መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሳል፡፡
+ የሀገረ ጋዛው ሰማዕት ቅዱስ ይስሃቅና የደብረ ዓሣ ጻድቃንም መታሰቢያቸው መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሳቸዋል፡፡
ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ፡- በአራማይክ ኬፋ፣ በግሪክ ጴጥሮስ ማለት ‹‹ዓለት›› ማለት ነው፡፡ አንድም ጴጥሮስ ማለት የሃይማኖት መሠረት ማለት ነው፡፡ ማቴ 16፡18፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ የመጀመሪያ ስሙ ስምዖን ሲሆን ጌታችን ኬፋ ብሎ ሰይሞታል፡፡ በገሊላ ባሕር ዳር በምትገኘው በቤተሳይዳ ተወለደ፡፡ ትውልዱ ከነገደ ሮቤል ሲሆን አባቱ ዮና ይባላል፡፡ የተወለደው በገሊላ አውራጃ በቤተ ሳይዳ ነው፡፡ ከአምስት ዓመቱ ጀምሮ ያደገው በቅፍርናሆም ነው፡፡ ጴርቴዋ የምትባል ሚስት የነበረችው ሲሆን የሚተዳደረው ዓሣ በማጥመድ ነበር፡፡ ከወንድሙ ከእንድርያስ ጋር ዓሣ ከሚያጠምድበት ተጠርቶ ሐዋርያ ሆኗል፡፡
ለደቀመዛሙርነት ሲመረጥ ዕድሜው 53 ዓመት እንደነበረ ይነገራል፡፡ ወደ ጌታችን ያመጣውም ወንድሙ እንድርያስ ነው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ፣ በርናባስ እና ወንጌላዊው ማርቆስ ቤተ ዘመድ ናቸው፡፡ የማርቆስ አባት አርስጦቡሎስ እና በርናባስ በእናት የሚገናኙ ወንድማማች ናቸው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ያገባው የበርናባስንና የአርስጦቡሎስን እኅት ስለነበር በጋብቻ ይዛመዳሉ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ለሐዋርያነት ሲጠራ መተዳደሪያው የነበረውን መረቡንና ታንኳውን እንዲሁም አባቱን እርግፍ አድርጐ ትቶ ጌታውን የተከተለ ሐዋርያ ነው፡፡ የመጀመሪያ ስሙ ስምዖን ሲሆን ይህንንም እናቱ በነገዿ ስም ያወጣችለት ነው፡፡
በቂሳርያ ከተማ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «ማን ትሉኛላችሁ?» ብሎ በጠየቀ ጊዜ «አንተ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ» ብሎ ለአይሁድ ሊቃውንት የተሰወረውን ምሥጢረ ተዋሕዶ ገልጦ በመመስከሩ ጌታችን «አንተ ጴጥሮስ ነህ» ብሎታል ይህም በላቲን ቋንቋ ዓለት ማለት ነው፡፡ በአርማይክ ደግሞ ኬፋ ይባላል፡፡ በመቀጠልም ቅዱስ ጴጥሮስ ይህን ሲመልስ ከጌታችን ዘንድ የተሰጠው መልስ ‹‹በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ስጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ፣ እኔም እልሃለሁ አንተ ጴጥሮስ ነህ፣ በዚህችም ዓለት ላይ ቤተክርስቲያኔን እሠራለሁ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም፡፡ የመንግስተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ፣ በምድር የምታስረው ሁሉ በሰማያት የታሰረ ይሆናል፤ በምድር የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል›› የሚል ነው፡፡ ይኸውም በወቅቱ የነበሩ ሐዋርያትና በኋላም በእርሱ እግር የሚተኩትን ካህናት አባቶችን ወክሎ የተቀበለው እጅግ አስደናቂና ቃልኪዳን ነው፡፡
ቅዱስ ጴጥሮስ ከአዕማድ ወይንም የምሥጢር ሐዋርያት ከሚባሉት ከእነ ዮሐንስ እና ያዕቆብ ጋር በመጀመሪያ የሚቆጠር ነው፡፡ ከሐዋርያት ሁሉ ቀደም ቀደም የማለት ባሕርይ ነበረው፡፡ ጌታችን በጥብርያዶስ ባሕር ላይ ሌሊት በእግሩ ሲመጣ ቢመለከት ‹‹ወደ አንተ እመጣ ዘንድ እዘዘኝ›› በማለት ካስፈቀደ በኋላ ወደ ጌታ ለመምጣት መንገድ ጀምሮ በመሐል ጥርጣሬ ገባውና መስጠም ስለጀመረ ጌታችን «ያመንክ እንጂ ያላመንክ አትሁን» ብሎ ገሥጾ ከመስጠም አድኖታል፡፡ ማቴ 14፡22-33፡፡ በቅፍርናሆም ጉባኤ ጌታችን ምሥጢረ ቍርባንን ሲያስተምር አይሁድ ስላልገባቸው ወደ ኋላ አፈገፈጉ፡፡ ከደቀ መዛሙርቱም «ብዙዎቹ ወደ ኋላ ተመለሱ» በዚህን ጊዜ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «እናንተ ደግሞ ልትሄዱ ትወዳላችሁ?» ብሎ ሐዋርያትን ጠየቃቸው፡፡ በዚህ ሰዓት «ጌታ ሆይ ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ የዘለዓለም የሕይወት ቃል አለህ፣ እኛስ አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ እንደሆንክ እናምናለን» በማለት ሐዋርያትን ወክሎ የመለሰ እርሱ ነው፡፡ ዮሐ 6፡66-68፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታችንን በጣም ይወድ ነበር፡፡ ፍቅሩ ግን ቅንዓት የተቀላቀለበት በመሆኑ ጌታችን ለደቀ መዛሙርቱ የሞቱን ነገር ቀድሞ ሲነግራቸው አይሁንብህ በማለት ተከራክሯል። ማቴ 16፡23፡፡ በኋላም «ሁሉም በአንተ ቢሰናከሉ እኔ ከቶ አልሰናከልም» ብሎ በራሱ ቅንዓት ተማምኖ ተናግሮ ነበር፡፡ ጌታችን «ዶሮ ሳይጮህ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ» እያለው እንኳን «ከአንተ ጋር መሞት እንኳን የሚያስፈልገኝ ቢሆን ከቶ አልክድህም» በማለት ተከራክሯል፡፡ ማቴ 26፡34፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ አስቀድሞ የተናገረውን ቃል ለመጠበቅ ሞክሮ ነበር፡፡ ጌታችን ዛሬ «የሰው ልጅ ተላልፎ ይሰጣል» ብሎ አስተምሮአቸው ነበርና መከላከያ ይሆነኛል ብሎ ሠይፍ ደብቆ ይዞ ነበር፡፡ የሮም ጭፍሮችም ጌታችንን ለመያዝ ሲጠጉ የሊቀ ካህናቱን ባርያ (ማልኰስን) በሰይፍ ጆሮውን ቆረጠው፡፡ ዮሐ 18፡10፡፡ ጌታችን ግን ሞቱ በፍቃዱ ለድኅነተ ዓለም ነውና «ሰይፍህን ወደ ሰገባው መልስ›› ሲል ገሠጸው፡፡
ቅዱስ ጴጥሮስ የሚታወቅበት ሌላው ትልቁ ነገር ንስሓው ነው፡፡ ጌታችን በአይሁድ እጅ ከተያዘ በኋላ ጌታው አስቀድሞ ‹‹ትክደኛለህ›› ብሎ የነገረው መድረሱንና አምላኩን በመካድ መበደሉን እንዳወቀ ከግቢው ወጥቶ ተንሰቅስቆ አለቀሰ፡፡ በፍጹም ንስሓም ተመለሰ፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በዕድሜው ታላቅነት በሐዋርያት ዘንድ እንደ አባት ይታይ ስለነበር ጌታችን ከተሰቀለ በኋላ ሐዋርያቱን ሊመግብ ወደሚያውቀው ሙያ ዓሳ ወደ ማስገሩ ተሠማራ፡፡ ጌታችንም አስቀድሞ የመረጠው እርሱ ነውና ቢክደው እንኳን በንስሐ በመመለሱ ንስሐውን መቀበሉን ዛሬም እንደሚወደው ይገልጽለት ዘንድ ዓሣ በሚያጠምድበት በጥብርያዶስ ባሕር ተገለጠለት፡፡ ሦስት ጊዜ ክዶት ነበርና ቀኖና ሰጠው፡፡ አሁን ቅዱስ ጴጥሮስ በራስ መተማመኑ እንዳላዋጣው ዐውቆአልና «ትወደኛለህን?» ተብሎ ሲጠየቅ «አንተ ታውቃለህ» ነበረ መልሱ፡፡ የራሱ ዕውቀት የት እንዳደረሰው ያውቃልና ጌታችንም በቀልን የሚተው ነውና ዛሬም እንደሚወደው በንስሓ ተመልሷልና ዛሬም ለእርሱ የሰጠውን ክብር እንደማያጐድልበት ሲነግረው (ግልገሎቼን አሰማራ፣ ጠቦቶቼን ጠብቅ፣ በጐቼን አሰማራ» በማለት ምእመናንን ልጆቹን በአደራ አስረከበው፡፡ ዮሐ 21፡15-17፡፡ ከዚያም በሞቱ እንዴት አድርጐ እግዚአብሔርን እንደሚያከብረው ነግሮት ወደ ሰማያት ዐረገ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ በይሁዳ ምትክ ሌላ ሐዋርያ እንዲመረጥ ሐሳብ ያቀረበ እርሱ ነበር። የሐዋ 1፡16-23፡፡ በበዓለ ሃምሳም ለደቀመዛሙርቱ መንፈስ ቅዱስ በወረደላቸው ጊዜ ለተሰበሰቡት አይሁድ አፈ ጉባዔ ሆኖ ወንጌልን የሰበከ በአንዲት ዕለት ሦስት ሺህ ምእመናንንም አሳምኖ የመጀመሪያዋን አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን በኢየሩሳሌም የመሠረተ እርሱ ነው፡፡ የሐዋ 2፡14-37፡፡ አስቀድሞ ፈሪ የነበረውና በሊቀ ካህናት ቀያፋ ግቢ ጌታውን የካደው ቅዱስ ጴጥሮስ የመንፈስ ቅዱስን ኃይል ካገኘ በኋላ ግን በአይሁድ ሸንጐ ድውይ ፈወስክ ተብሎ በተከሰሰ ጊዜ በድፍረት ስለ መድኃኔዓለም ክርስቶስ መሰከረ፡፡ የሐዋ 4፡1-22፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ቆርነሌዎስን በማጥመቅ ወንጌልን ለአሕዛብ አስቀድሞ የሰበከው ሐዋርያ ነው። የሐዋ 10፡1-11፡፡ | 23 |
| 7 | Sin texto... | 97 |
| 8 | አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ሐምሌ 4-ስለክርስቶስ ትንቢታቸውን እንደፈሳሽ ውኃ ያጎረፉ የ12ቱ ደቂቀ ነቢያት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓላቸው ነው፡፡
+ ነቢዩ ቅዱስ ሶፎንያስ ዕረፍቱ ነው፡፡
+ ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ቅዱሳን የሆኑ ሰማዕታት የአቡቂርና የዮሐንስ የሥጋቸው ፍልሰት ሆነ፡፡ እነዚህም ቅዱሳን በሰማዕትነት ካረፉ በኋላ ሥጋቸውን ምእመናን በእስክንድርያ ሰሜናዊ ከተማ ውስጥ ባለች በቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሥውር አኖሩ፡፡ እስከ ሊቀጳጳሳት አቡነ ቄርሎስ ዘመንም በዚያ ኖሩ፡፡ የታዘዘ መልአክ ለአቡነ ቄርሎስ ተገለጠለትና የቅዱሳኑን ሥጋቸውን አፍልሶ በባሕር ዳርቻ ወዳለች ሌላይቱ የቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን እንዲወስድ ነገረው፡፡ ምእመናንም የሰማዕታቱን ሥጋቸውን አፍልሰው ታላቅ በዓልን አከበሩ፡፡ ከሥጋቸውም ብዙ ድንቅ ድንቅ የሆኑ የሆኑ ተአምራት ተገለጡ፡፡ አረማውያንም ተሰብስበው የተደረጉትን ታላላቅ ተአምራት አይተው በጌታችን አመኑ፡፡ አስቀድመው ያመልኩበት የነበረው የጣዖት ቤታቸውም በተአምራት አሸዋ ተከመረበትና ታላቅ ኮረብታ ሆነ፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ፣ ቅዱስ አቡቂር፣ ቅድስት አትናስያና ሦስቱ ደናግል ልጆቿ፡- የቅድስት አትናስያ ልጆች ስማቸው ቴዎድራ፣ ቴዎፍና፣ ቴዎዶክስያ ይባላል፡፡ የስማቸውም ትርጓሜ በቅደም ተከተል ‹‹የእግዚአብሔር ስጦታ››፣ ‹‹የእግዚአብሔር ሃይማኖት›› እና ‹‹የእግዚአብሔር ምስጋና›› የሚል ነው፡፡ ቅዱስ አቡቂር ከታናሽነቱ ጀምሮ በገድል ተጠምዶ የሚኖር መነኮስ ነው፡፡ የከበረ ዮሐንስ ግን በንጉሥ ሠራዊት ውስጥ የሚያገለግል ነው፡፡ የእነርሱም ሀገራቸው እስክንድርያ ሲሆን የሚኖሩት ግን አንጾኪያ ነው፡፡ በዚያም እነዚህ ሦስት ቅዱሳት ደናግል ቴዎድራ፣ ቴዎፍና፣ ቴዎዶክስያ ከሃዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ፊት ቆመው የጌታችንን ክብር መሰከሩ፡፡ ንጉሡም ከወዴት እንደሆኑ በጠየቃቸው ጊዜ ከእስክንድርያ እንደሆኑ ሲነገሩት ወደዚያ ወስደው ያሠቃዩአቸው ዘንድ አዘዘ፡፡
እነዚህም ሦስት ቅዱሳት ደናግል እስክንድርያ በደረሱ ጊዜ ዳግመኛ በመኮንኑ ፊት ቆመው የጌታችንን አምላክነት በመመስከር በጣዖት ማምለክን ረገሙ፡፡ በዚህም የተናደደው መኮንን ጽኑ ሥቃይን አሠቃያቸው፡፡ በመጨረሻም ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ፡፡ እናታቸው የከበረች ቅድስት አትናስያም ደናግል ልጆቿን በጌታችን ስም ምስክር ሆነው በሰማዕትነት ከሞቱ ለሰማያዊው ሙሽራ ለክርስቶስ ሙሽሮቹ እንደሚሆኑ በመንገር ታጽናናቸው ነበር፡፡ ቅዱስ አቡቂርም በከበረች ሐዋርያዊት በቅድስት ቴክላ ላይ የደረሰውን መከራና ያገኘችውን ክብር ይገልጥላቸውና ያጽናናቸው ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ወታደሮቹ ሦስቱን ቅዱሳት ደናግል ቴዎድራን፣ ቴዎፍናንና ቴዎዶክስያን በየተራ እያቀረቡ አንገታቸውን ሰየፏቸውና የሰማዕትነታቸው ፍጻሜ ሆነ፡፡ ቀጥለውም ጭፍሮቹ እናቸው ቅድስት አትናስያን፣ ቅዱስ አቡቂርንና ቅዱስ ዮሐንስን ሁሉንም በየተራ ሰየፏቸውና ሁሉም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጁ፡፡ ምእመናንም ሥጋቸውን ወስደው የመከራው ዘመን እስኪፈጸም ድረስ በክብር አስቀመጡት፡፡ በኋላም ያማረች ቤተ ክርስቲያን ሠርተው ቅዱስ ሥጋቸውን በዚያ አኖሩ፡፡ ከቅዱሳኑም ሥጋ ብዙ ድንቅ የሆኑ ተአምራት ተፈጽመው ታዩ፡፡ የሰማዕታቱ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
ነቢዩ ቅዱስ ሶፎንያስ፡- ይኸውም ቅዱስ ነቢይ የአማርያ ልጅ፣ የሴዴቅያስ ልጅ፣ የጎዶልያ ልጅ፣ የኩሲ ልጅ ነው፡፡ እርሱም በይሁዳ ንጉሥ በኢዮስያስ ዘመን ትንቢትን ሲናገር የነበረ ነው፡፡ እግዚአብሔር ይህችን ዓለም ፈጽሞ እንደሚያጠፋት ሰዎችና ከብቶች የባሕር አሣዎችና የሰማይ ወፎችም ጭምር እንደሚጠፉ ትንቢት ተናገረ፡፡ ስለሞአብም መጥፋት ተናገረ፡፡ ዳግመኛም ስለ ፋርስና ስለ ነነዌ መጥፋት ሲናገር ‹‹እግዚአብሔር ‹የፋርስን ሰዎች አጠፋቸዋለሁ፣ ነነዌንም ፍርስራሽና ውኃ እንደሌለባት ምድረ በዳ አድርጋታለሁ› ብሏል›› አለ፡፡ ቅዱሱ ነቢይ እንደተናገረውም ይህች ከተማ በመቄዶናዊው እስክንድር እጅ ጠፍታለች፡፡
ቅዱስ ሶፎንያስ ዳግመኛም ስለጌታችን መምጣት ትንቢትን ሲናገር ‹‹ያን ጊዜም ሁሉ የእግዚአብሔርን ስም ይጠራ ዘንድ በአንድ ሕግም ይገዙልኝ ዘንድ የአሕዛብን ሁሉ አንደበት ወደ ሕግ እመልሳለሁ›› አለ፡፡ደግሞም ቅዱሱ ነቢይ ስለ ሀገራችን ትንቢትን ሲናገር ‹‹ከኢትዮጵያ ወንዞች ማዶ መሥዋዕቴን ያመጡልኛል›› አለ።
የትንቢቱንም ወራት ፈጽሞ እግዚአብሔርን አገልግሎ በዚኽች ዕለት ዐረፈ።ረድኤት በረከቱ ትደርብን በጸሎቱ ይማረን!
ከገድላት አንደበት | 93 |
| 9 | Sin texto... | 112 |
| 10 | ‹‹በእግዚአብሔር ልጅ ሕማምን በተቀበለ ሞቶ በተነሣ ዳግመኛም ለፍርድ በሚመጣ በኢየሱስ ክርስቶስ ታምናለህን/›› አሉት፡፡ እርሱም ‹‹አዎን አምናለሁ››አለ፡፡ እነርሱም ‹‹መልእክተኛን ልከህ ልጃችንን ክልስቲያኖስን ወደ መንበሩ መልሰው›› አሉት፡፡ እርሱም መልእክተኞችን ወደ አንጾኪያው ሊቀ ጳጳሳት ልኮ አባ ክልስቲያኖስን ወደ መንበሩ በክብር መለሰው፡፡ ሕዝቡም በታላቅ ክብር ተቀበለው፡፡በዚያም ወራት ንጉሡ ከጦርነት በሰላም ተመለሰ፡፡ ቤተ ክርስቲያንም በሰላም ኖረች፡፡ከዚህም በኋላ በዘመኑ የንስጥሮስ ክህደት በተገለጠ ጊዜ የከበሩ ቅዱሳን
አባቶች የአንድነት ስብሰባ ሲያደርጉ አባ ክልስቲያኖስ ግን ከደዌውና ከእርጅናው የነተሣ ወደ ጉባኤው መሄድ ባይችልም ንስጥሮስን ከሚያወግዝ ደብዳቤ ጋራ ሁለት ሊቃውንት ቀሳውስትን ላከ፡፡ እርሱም የእረፍቱ ጊዜ በቀረበ ጊዜ አባ ዮናክንዲኖስና አባ አትናስዮስ ተገለጡለትና ‹‹ጌታችን ወደ ሕይወት ጠርቶሃልና አንተ ወደ እኛ ስለምትመጣ ሕዝቡን በሃይማኖት እንዲጸኑ አስጠንቅቃቸው ››አሉት፡፡ የእስክንድርያው ቅዱስ ቄርሎስ ዓምደ ሃይማኖትና የሀገረ ፃን ኤጲስቆጶስ አባ ሉቅያስም እንዲሁ ተገለጡለት፡፡ ወዲያውም ሕዝቡን ሁሉ ጠርቶ‹‹ተኩላዎች ወደዚህች ከተማ ይገቡ ዘንድ አላቸውና ተጠንቀቁ፣እስከመጨረሻው በሃይማኖት ጽኑ›› ብሎ ከመከራቸው በኋላ በሰላም ዐረፈ፡፡
ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን! | 97 |
| 11 | አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ሐምሌ 3 ‹‹ዓምደ ሃይማኖት›› የተባለ የእስክንድርያው ቅዱስና ሊቅ አቡነ ቄርሎስ ዕረፍቱ ነው፡፡
+ ዳግመኛም በዚኽች ዕለት የሮሜው አባ ክልስቲያኖስ ዐረፈ፡፡
አቡነ ቄርሎስ ዓምደ ሃይማኖት፡- በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ብሉይንና ሐዲስን አጠናቆ የተማረው ገና በ12 ዓመቱ ነው፡፡ ይኸውም ፓትርያርኩ አቡነ ቴዎፍሎስ ሃይማኖትን እንዲማር ለአባ ሰራብዮን ከሰጠውና ገዳም ከገባ በኋላ ነው፡፡ከዚህም በኋላ አቡነ ቴዎፍሎስ ቅዱስ ወንጌልን ለምእመናን ይሰብክ ዘንድ ወደ ከተማ ላከው፡፡በስብከቱም ብዙዎችን ከአምልኮተ ጣዖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር መልሷል፡፡ከወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ጀምሮ በእስክንድርያ የተሾሙት ፓትርያርኮች 23 የነበሩ ሲሆን ቅዱስ ቄርሎስን መንፈስ ቅዱስ በማርቆስ መንበር 24ኛው ፓትርያርክ አድርጎ ሾሞታል፡፡ በ431 ዓ.ም የቅርብ ጓደኛው የነበረውን ንስጥሮስ ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችንን "ሁለት አካል ሁለት ባሕርይ
ነው" የሚል የሰይጣንን ትምህርት ይዞ በመነሳት ቤተ ክርስቲያንን ማወክ ጀመረ፡፡ ለስም አጠራሯ ክብር ምስጋና ይግባትና ወላዲተ አምላክ ቅድስት ድንግል ማርያምንም "የአምላክ እናት አትባልም" ብሎ ማስተማር ጀመረ፡፡አምደ ሃይማኖት የተባለው ሊቁ ቅዱስ ቄርሎስም ንስጥሮስን ከክህደት ትምህርቱ እንዲመለስ ቢያስተምረውና ቢመክረው አልመለስ ቢል በኤፌሶኑ ጉባዔ ከ200 ሊቃውንት ጋር ሆኖ አውግዞታል፡፡ ቅዱስ ቄርሎስ በጉባኤው ፊት ንስጥሮስን ከቅዱሳት መጻሕፍት እያጣቀሰ የተለያዩ ተአምራትን እያደረገ ጌታችን አንድ ባሕርይ መሆኑንና እመቤታችንም ወላዲተ አምላክ መሆኗን ቢያስረዳውም አንድ ጊዜ ሰይጣን በልቡ አድሮበታልና ሊመለስ አልቻለም፡፡ ቅዱስ ቄርሎስ እንደ
ጓደኝነቱም ሆነ እንደ ሃይማኖት አባትነቱ ንስጥሮስን ቢያስተምረውና ቢለምነው እምቢ አሻፈረኝ ቢለው ካወገዘው በኋላ እረግሞታል፡፡ የቄርሎስም እርግማኑ ደርሶበት ንስጥሮስ ጆሮው ደንቁሮ፣ አንበደቱ ተዘግቶ፣ ሆዱ ተልቶ ምላሱ ተጎጉሎ በልቡ ወድቆ ሸቶ ደምና መግል እየተፋ እጅግ ክፉ አሟሟት ነው የሞተው፡፡ ቅዱስ ቄርሎስም ይህንን በማየቱ ፈጣሪውን ሲያመስግን ጌታችንም በክብር ተገልጦለት ሃይማኖትን በማጽናቱ አመስግኖታል፡፡የንስጥሮስ የክህደት ትምህርት መገኛ ምንጯ ጥንተ ጠላት ዲያብሎስ ነው፡፡መነሻውም እንዲህ ነው፡- መጀመሪያ ሰይጣን ለጳውሎስ ሳምሳጢን ነው ያስተማረው፡፡ ጳውሎስ ሳምሳጢን በገዳም ቅጠል እየበላ የሚኖር ተሐራሚ መናኝ ነበር፡፡ በጾም በጸሎት ሲኖር ሰይጣን ራሱን ሰውሮ መጥቶ ተገለጠለትና
‹‹ጸሎትህ በእግዚአብሔር ዘንድ ተሰምቶልሃል፤ ነገር ግን አምላክ ያለሩካቤ በድንግልና የተወለደ አይምሰልህ በሩካቤ ተወለደ እንጂ፤ ይህም ልጅ ደግ ሰው ሆነ፣ በ30 ዘመኑ በዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ተጠመቀ፣ መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል በራ ላይ ተቀመጠ፣ ያን ጊዜም ይህ ሰው በጸጋ የሥላሴ ልጅ ሆነ›› ብሎ አስተማረው፡፡ ጳውሎስ ሳምሰጢንም ሰይጣን የነገረውን ነገር በልቡ አምኖ ለደቀ
መዝሙሩ ለተያስሮስ አስተማረው፡፡ ተያስሮስም ለድያድርስ አስተማረው፡፡ድያድርስም ለንስጥሮስ አስተማረው፡፡ ንስጥሮስም ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችንን አምላካችንን ‹‹መንፈስ ቅዱስ ያደረበት ዕሩቅ ብእሲ ነው›› ብሎ ለልዮንና ለመርቅያን አስተማራቸው፡፡ ንስጥሮስ ይህን አዲስ የክህደት ትምህርት እንዳመጣ በሰሙ ጊዜ 200 ኤጲስ ቆጶሳት በቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ መሪነት በኤፌሶን ተሰብስበው ሲያስተማሩት እምቢ ቢላቸው አውግዘው ለዩት፡፡ ንስጥሮስም ሰውነቱ መግሎ ክፉ አሟሟት ሞተ፡፡ በኋላም መርቅያን ሲነግሥና ልዩንም የሮም ሊቀ ጳጳስ ሲሆን ሁለቱም አባታቸው ንስጥሮስ
ያስተማራቸውን ሃይማኖት ማስፋፋት ቻሉ፡፡ እነ ልዮንም ንስጥሮስ በተወገዘበት ጉባዔ ላይ የነበሩትና አሁን ለሥጋቸው የፈሩ አባቶችን ይዘው ከንስጥሮስ ክህደትና ከቅዱስ ቄርሎስ ትምህርት አወጣጥተው የራሳቸውን የረከሰ
ሃይማኖታዊ ድንጋጌ አወጡ፡፡ ‹‹ክርስቶስ ሁለት አካል ነው፣ አንዱ የማርያም ልጅ አንዱ የእግዚአብሔር ልጅ በመቀራረብ አንድ ሆኑ ያለውን አውጥተው ከቅዱስ ቄርሎስም ቃልና ከንስጥሮስ ክህደት ቀላቅለው መለኮት የመለኮትን ሥራ
ይሠራል፣ ትስብእትም የትስብእትን ሥራ ይሠራል፤ በሁለት መንገድ አንዱ ተአምራትን ያደርጋል ሁለተኛው መከራን ይቀበላል ስለዚህም ትስብእት ከመለኮት ያንሳል›› ብለው ጻፉ፡፡ ይህንንም የክህደት ጽሕፈታቸውን ለቅዱስ ዲዮስቆሮስ ላኩለት፡፡ እርሱም ሄዶ ከክህደታቸው እንዲመለሱ አስተማራቸው፡፡‹‹በአንዱ ክርስቶስ ላይ ለምን የሁለትነት ነገር ትናገራላች? ወደ ሠርግ ቤት ተጠርቶ የሄደው ውኃውንም የወይን ጠጅ ያደረገው እርሱ አንዱ ክርስቶስ ነው…›› እያለ በብዙ ምሳሌ ካስተማራቸው በኋላ ልዮንንና መርቅያን የጻፉትን የክህደት ጽሕፈት በፊታቸው ቀደደው፡፡ እነርሱ ግን አንድ ጊዜ ክደዋልና የቅዱስ ዲዮስቆሮስን ፂሙን ነጭተው ጥርሱን አውልቀው ብዙ አሠቃዩት፡፡ እርሱም የነጩትን ፂሙንና ያወለቁትን ጥርሱን ሰብስቦ ‹‹እነሆ የሃይማኖቴን ፍሬ ተቀበሉ››ብሎ ለእስክንድርያ ክርስቲያኖች ላከላቸው፡፡ ከሃዲያኑም ወደ ጋግራ ደሴት አጋዙትና በዚያው ዐረፈ፡፡ቅዱስ ቄርሎስ በማርቆስ መንበር ለ31 ዓመት ከ8 ወር ሲያገለግል የኖረ ሲሆን ሲያርፍም የተቀበረው በመንበረ ማርቆስ ነው፡፡በስሙ የተጠራውን አንድ ቅዳሴና ሌሎች እጅግ ጠቂሚ በርካታ ድርሳናትን ደርሷል፡፡ገድል፣ ድርሳንና ዜና ተጽፎለታል፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
ሮሜው አባ ክልስቲያኖስ፡- ይኽም ቅዱስ የሮሜ አገር ሊቀጳጳሳት ተደርጎ የተሾመው ገድለኛውና ጻድቁ ንጉሥ አኖሬዎስ በሮሜ አገር ነግሦ በነበረበት ዘመን ነው፡፡ ይኽም ጻድቅ ንጉሥ ካረፈ በኋላ ከሃዲው ሉልያኖስ ነገሠ፡፡ እርሱም
አባ ክልስቲያኖስን ከመንበሩ አሳዶ መናፍቁን ንስጡርስን ሊቀ ጵጵስና ሾመው፡፡አባ ክልስቲያኖስንም ሊገድለው ይፈልግ ነበር፡፡ የከተማ ሰዎች ግን ከሃዲውን ንስጡርስን አልተቀበሉትም ነበር፡፡አባ ክልስቲያኖስም በሮሜ አገር ከሚገኙት ገዳማት በአንዱ ገብቶ እግዚአብሔርን እያገለገለ ኖረ፡፡ እግዚአብሔርም በእጆቹ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን ያደርግ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ከሃዲው ንጉሥ ወደ ጦርነት በሄደ ጊዜ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ለአባ ክልስቲያኖስ ተገለጠለትና ወደ አንጾከያ ከተማ ወደ ሊቀ ጳጳሳት ድምትርያኖስ ይሄድ ዘንድ አዘዘው፡፡ ይኸውም ንጉሡ አባ
ክልስቲያኖስ ያለበትን ዐውቆ ከጦርነቱ ሲመለስ ሊገድለው አስቦ ነበርና ነው፡፡ጻድቁም አንጾኪያ ከተማ ሄዶ አባ ድምትርያኖስን አገኘውና ከሃዲው ንጉሥ ያደረገውን ሁሉ ነገረው፡፡ እርሱም በአንጾኪያ ካሉት በአንዱ ገዳም አኖረው፡፡
ከዚህም በኋላ ከአባ ክልስቲያኖስ በፊት የሮሜ አገር ሊቀ ጳጳሳት የነበረው አባ ዮናክንዲኖስና ሊቀ ጳጳሳት ቅዱስ አግናጥዮስ ለዚያ ከሃዲ ንጉሥ ሌሊት በራእይ ተገለጡለትና ‹‹ሊቀ ጳጳሳቱን አባ ክልስቲያኖስን አገሩን ለምን አስተውከው/ እነሆ እግዚአብሔር ነፍስህን ከአንተ ይወስዳል፣ በጠላቶችህም እጅ ፈጽመህ ትሞታለህ›› አሉት፡፡ ንጉሡም ‹‹አባቶቼ ሆይ! ምን ላድርግ/›› አላቸው፡፡ እነርሱም | 83 |
| 12 | Sin texto... | 108 |
| 13 | አራት ኪሎ ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሙዚየም ውስጥ የሚገኘው የሐዋርያው የቅዱስ ታዴዎስ የቀኝ እጅ!
ረድኤት በረከቱ ይደርብንና በዛሬዋ ዕለት በዓመታዊ የዕረፍት በዓሉ ታስቦ የሚውለው ሐዋርያው ቅዱስ ታዴዎስ ያደረው ታላቅ ተአምር ይህ ነው፡- የከበሩ ሐዋርያት ቅዱስ ታዴዎስና ቅዱስ ጴጥሮስ የቅዱስ ታዴዎስ የስብከት ዕጣው ወደሆነችው ወደ ሀገረ ሶርያ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሄዱ አረማውያን የሆኑ የከተማው መኳንንት ‹‹እነኚህ አይሁድ ከሰቀሉት ከናዝሬቱ ኢየሱስ 12 ወገኖች ውስጥ ከሆኑ ወዮልን፣ እንገድላቸውም ዘንድ ተዘጋጁ›› ተባባሉ፡፡ የተቀሩት ደግሞ ‹‹አምላካቸው ኢየሱስ የሚሹትን ነገር ሁሉ እንደሚያደርግላቸው ሰምተናል ነገር ግን ዝሙትን አጥብቀው ስለሚጠሉ አመንዝራ ሴትን በከተማው መግቢያ በር ላይ ራቁቷን እናስቀምጣትና እርሷን ባዩ ጊዜ ወደኃላቸው ይመለሳሉ፤ ወደ ከተማዋም አይገቡም›› ብለው መከሩ፡፡
እንደመከሩትም አድርገው አመንዝራ ሴት ራቁቷን አድርገው በከተማው መግቢያ በር ላይ አቆሟት፡፡ ሐዋርያው ታዴዎስም አመንዝራዋን ሴት ራቁቷን ባያት ጊዜ ‹‹ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ወደ ከተማው ገብተን በከበረ ስምህ እስክንሰብክ ድረስ በራሷ ጸጉር አየር ላይ ይሰቅላት ዘንድ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን ልክልን›› ብሎ ጸለየ፡፡ ያን ጊዜ ያች ዘማዊት ሴትም ወደ አየር ወጥታ በነፋስ አውታር ተንጠለጠለች፡፡ እርሷም የሀገሩ ሰዎች ሁሉ ወጥተው እስኪያዩዋትና እስኪደነቁ ድረስ ትጮህ ጀመር፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም በዚያች አገር ሰዎች ላይ አድረው ልቡናቸውን ያሳወሩትን አጋንንት ፈጃቸው፡፡ ቅዱስ ታዴዎስም ወንጌልን ሰበከላቸው፣ ያችንም የተሰቀለች ዘማዊ ሴት በጸሎቱ ከተሰቀለችበት አውርዶ አሳምኖ ካጠመቃት በኋላ ቤቷን የጉባዔ ቤት አደረገች፡፡ አገልጋይ ኤጲስ ቆጶሳትን፣ ካህናትንና ዲያቆናትን ሾመላቸው፡፡ ያችም ሴት ዲያቆናዊት ሆና ለቤተ ክርስቲያን የምትላላክ ሆነች፡፡
ግመልን በመርፌ ቀዳዳ አሾልኮ በማሳለፍና ሌሎችም እጅግ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን በማድረግ አሕዘብን ያሳመነው ሐዋርያው ቅዱስ ታዴዎስ በብዙ አገሮች ወንጌልን ሰብኳል፡፡ ወደ ፐርሺያም ሄዶ ሲሰብክ አረማውያን ብዙ አሠቃቂ መከራዎችን አድርሰውበት ሐምሌ 2 ቀን በሰማዕትነት ዐርፏል፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን፡፡ | 103 |
| 14 | Sin texto... | 66 |
| 15 | Sin texto... | 61 |
| 16 | ነበር፡፡ እሳቸውም ታስረው ሳለ ወደ አቡነ ተክለ
ሃይማኖት ዘንድ የሚላካቸው ሲያስቡ ቁራ መጥቶ ‹‹እኔ እላክሃለሁ›› ቢላቸው ‹‹ክፋትህ እንደ መልክህ ነው›› ብለው እምቢ አሉት፡፡ ርግብ መጥታ ‹‹እኔ እላክሃለሁ›› ብትላቸው ‹‹መጥተህ አድነኝ›› ብለው በክንፏ ላይ ጽፈው ልከዋት እርሷም መልእክቱን ለተክለ ሃይማኖት አድሳ ነበር፡፡ ስለዚህም ነው አቡነ ታዴዎስን ሕዝቡን ከኃጢአት ግዞት አኖሬዎስን ከእስራት እንዲያስፈቱ የላኳቸው፡፡ አቡነ ታዴዎስም በፋስ ሠረገላ ተጭነው መዩጥ ከተባለውና አኖርዮስን ካሰራቸው ንጉሥ ፊት ቢደርሱ ንጉሡ በግንጋጤ መልአክ የመጣበት መስሎት ሲፈራ ከሰው ወገን መሆናቸውን ነግረው ክርስትናን አስተማሩት፡፡ ጋኔን ከእሳት ጥሎት ሲሠቃይ የሚኖርና ሊሞት የደረሰ ልጁን ቢፈውሱለት በትምህርታቸውና በተአምራታቸው አምኖ ሕዝቡ ክርስትናን እንዲቀበል በአዋጅ አስነገረ፡፡
አፍጃል የሚባለው ባለጸጋ ወደ አቡነ ታዴዎስ ቀርቦ ሲማር ‹‹ባለጸጋ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ይልቅ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢሾልክ ይቀላል›› (ማቴ 19፡24፣ ማር 10፡25፣ ሉቃ 18፡25) የሚለውን የወንጌል ቃል ሲሰማ ለአእምሮው ረቆበት ‹‹እስቲ አድርገህ አሳየኝ?›› አላቸው፡፡ አቡነ ታዴዎስም እናቲቱን ግመል ከነጇ ቀጥሎም 28 ግመሎችን በየተራ በመርፌ ቀዳዳ እያሾለኩ አሳይተውታል፡፡ ሕዝቡ ሁሉ በእጅጉ ሲገረምና ‹‹በአምላከ ታዴዎስ ስም አምናለሁ›› ሲል የባለጸጋው ልጅ ሙሳ ግን ‹‹በምትሃት አሳይቶን ነው እንጂ የእውነት አይደለም›› በማለት አባቱንም እንዳያምን ይናገር ጀመር፡፡ ይህንንም ሲናገር በመጀመሪያ ያለፈችው እናቲቱ ግመል እረግጣ ገደለችው፡፡ አቡነ ታዴዎስም ንጉሡን፣ አባቱን አፍጃልንና ሕዝቡን የሞተ እንደሚነሣ ሲያስምሯቸው ‹‹የሞተ ይነሣልን? እስኪ ይህ የሞተው ልጅ ይነሳና ሁሉም አይቶ ይመን›› አሏቸው፡፡ እሳቸውም ‹‹ዛሬ ተቀብሮ ይዋልና ነገ በሦስተኛው ይነሣል›› ብለዋቸው ተቀብሮ ዋለ፡፡ በማግሥቱም አፍጃልን ጠርተው ‹‹‹አልዓዛርን ከሞት ባስነሣው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ልጄ ሆይ ና ውጣ› ብለህ ከልጅህ መቃብር ላይ አኑረው› ብለው ዘንጋቸውን ሰጡት፡፡ ሄዶም እንዳሉት ቢያደርግ ልጁ አፈፍ ብሎ ተነሥቷል፡፡ ይህንን ያዩ የሀገሩ ሰዎች ሁሉም አምነው ተጠምቀዋል፡፡ እሳቸውም 12 አብያተ ክርስቲያናትን አሳንጸው ሞቶ የተነሳውን ሙሳን ሙሴ ብለው ሰይመው አስተምረው ሊቀ ካህናት አድርገው ሾመውት አቡነ አኖሬዮስን ይዘው ወደ ጽላልሽ ዞረሬ ተመልሰዋል፡፡
አቡነ ተክለ ሃይማኖት ካረፉ በኋላ አባ ያዕቆብ የተባሉ ጳጳስ ከግብፅ መጡ፡፡ የአቡነ ታዴዎስን ዜና ሲሰሙ ተደስተው ከአቡነ ፊሊጶስ ጋር ሆነው አስጠርተዋቸው ‹‹የአባታችሁን ዜና ገድል ንገሩኝ›› አላቸው፡፡ አቡነ ታዴዎስም ‹‹ጨዋታ በአስተርጓሚ አይሰምርም›› ብለው ወደ ጌታችን ቢጸልዩ የጳጳሱ ቋንቋ ለታዴዎስ፣ የታዴዎስም ቋንቋ ለጳጳሱ ተገልጦላቸው የመሸ የነጋ ሳይመስላቸው 40 ጾምን ሲጨዋወቱ ቆይተዋል፡፡ ከዚህ በኋላ ጳጳሱ ከንጉሡ ተማክረው ‹‹ሊቀ ካህናት ዘጽላልሽ›› ብለው ሾመዋቸዋል፡፡
በነግህና በሰርክ ቤተ ክርስቲያንን እያገለገሉ፣ ቀን ወንጌልን እየሰበኩ፣ ሌሊት ከባሕር ገብተው ሲጸልዩ እያደሩ በታላቅ ተጋድሎ እየኖሩ ሳለ ከ10 ዓመት በኋላ ሰይጣን በንጉሡ በዓምደ ጽዮን ፍቅረ ዝሙት አሳድሮበት በክፉዎችም ምክር አታሎት የአባቱን ቅምጥ አገባ፡፡ አቡነ ታዴዎስም ይህን ሲሰሙ እንደ ነቢዩ ኤልያስና እንደ መጥምቁ ዮሐንስ በቀጥታ ሄደው ንጉሡን ገሥጸው አወገዙት፡፡ ገሥጸውና አውግዘው አቡነ ማትያስን አስከትለው ሲመለሱ ቅምጧ የንጉሡ ሚስት በፈረስ ተከትላ ደርሳ የኋሊት አሳስራ ዛሬ ‹‹ማርያም ገዳም›› ከሚባለው ቦታ ፊት ለፊት ካለው ትልቅ ገደል ውስጥ ሁለቱንም ጣለቻቸውና ጥር 29 ቀን በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡
በሰማዕትነት ዐርፈው ደማቸው ከፈሰሰበት ከገደሉ ስር በፈለቀው ጸበላቸው ‹‹ታዴዎስ ወማትያስ›› እያለ ሦስት ጊዜ ብቅ ጥልቅ እያለ የተጠመቀ ሰው እንደ 40 ቀን ሕፃን እንደሚሆን ጌታችን ቃልኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡ ይህ ሰማዕትነት በተቀበሉበት አካባቢ የተሠራው ቤተ ክርስቲያናቸው በጠላት ወረራ ጊዜ ፈርሶ ቦታው ጠፍ ሆኖ የኖረ ቢሆንም የአካባቢው ሕዝብ ቦታውን ከልሎ በክብር ሲጠብቀው ስለኖረ ፈቃደ እግዚአብሔር ሆኖ የአቡነ ታዴዎስ ታቦታቸው በ2005 ዓ.ም ከኢቲሣ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ወጥቶ ጻድቁ ሰማዕትነት በተቀበሉበት አካባቢ በተሠራው መቃኞ ቤተ ክርስቲያናቸው በታላቅ ክብር ገብቷል፡፡ ቤተ ክርስቲያኑም ከኢቲሣ በእግር የአንድ ሰዓት ተኩል ርቀት ላይ ይገኛል፡፡
(ምንጨ፡- የሐምሌ ወር ስንክሳር፣ ገድለ አቡነ ታዴዎስ፣ ቤተ ክርስቲያንህን ዕወቅ) | 54 |
| 17 | በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት):
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን
ሐምሌ 2-ግመልን በመርፌ ቀዳዳ አሾልኮ በማሳለፍና ሌሎችም እጅግ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን በማድረግ አሕዘብን ያሳመነው ሐዋርያው ቅዱስ ታዴዎስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ታዴዎስ ማለት ‹‹የአምላክ ካህን›› ማለት ነው፡፡ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ ሲሆን ግመል በመርፌ ቀዳዳ በማሾለክ አሕዛብን ያሳመነ ሐዋርያ ነው፡፡ በበዓለ 50 ቀን አጽናኝ መንፈስ ቅዱስን ከተቀበለ በኋላ ወደተለያዩ አገሮች ተዘዋውሮ ወንጌልን የሰበከ ቢሆንም ሀገረ ስብከቱ ግን ሶርያ ነበር፡፡ ጌታችንም መልኩ በሚያምር ጎማሳ አምሳል ተገልጦለት እንዳይፈራና ሁልጊዜም ከእርሱ ጋር እንደሚሆን በመንገር አጽናንቶታል፡፡
ቅዱስ ጴጥሮስ ወደ ሀገረ ስብከቱ ሊያደርሰው ወስዶት ከከተማው ዳርቻ ላይ እንዳሉ በማሳ ላይ የሚያርስ አንድ ሽማግሌ አገኙ፡፡ ጠጋ ብለውም የሚበሉት እህል እንዲሰጣቸው ጠየቁት፡፡ ሽማግሌውም ‹‹አህል ከዚህ አልያዝኩም ግን ከቤት ላምጣላችሁ ከዚህ ከበሬዎቹ ዘንድ ተቀምጣችሁ ጠብቁኝ›› ብሎ ወደ ቤቱ ሄደ፡፡ ሽማግሌውም ከሄደ በኋላ እነርሱም ደግነቱን ተመልከተው ተደሰቱ፡፡ ‹‹እስኪመለስም ድረስ እርሻውን እያረስንለት እንጠብቀው›› ተባለው ታዴዎስ ሲያርስ ጴጥሮስ መዝራት ጀመረ፡፡ ሠላሳ ትልም መሬት አርሰው እንደጨረሱ የዘሩት እህል ዕለቱን ወዲያው በቀለ፡፡ መብቀል ብቻም አይደለም እህሉ ዕለቱን አድጎ አሽቶ አፈራ፡፡ ሽማግሌውም ሲመለስ ቅዱሳን ሐዋርያት ያደረጉትን በተመለከተ ጊዜ ደንግጦ ከእግራቸው ሥር ወድቆ ሰገደላቸውና ‹‹ከሰማይ የወረዳችሁ አማላክት ናችሁን?›› አላቸው፡፡ እነርሱም ‹‹እኛ የአምላክ ባሮቹ ነን እንጂ አማልክት አይደልንም›› በማለት ከነገሩት በኋላ ወንጌልን ሰበኩለት፡፡ እርሱም ‹‹በምትሄዱበት ሁሉ ልከተላችሁ‹‹ ሲላቸው እነርሱ ግን ‹‹ይህን ልታደርግ አይገባም ነገር ግን ቤትህን አዘጋጅልን›› አሉት፡፡ ሽማግሌውም ከማሳው እሸት ቆርጦ ወስዶ በሬዎቹን እየነዳ ወደ ቤቱ ወሰዳቸው፡፡ በእርሻ ወቅት እሸት ተሸክሞ ሲሄድ ያዩት የሀገሩ ሰዎችም ይገረሙበት ነበር፡፡ ወሬውም የከተማው መኳንንት ዘንድ ደረሰ፡፡ ሽማግሌውንም በጠየቁት ጊዜ ከመጀመሪያው ጀምሮ የሆነውን ነገራቸው፡፡
የከተማውም መኳንንት ‹‹እነኚህ አይሁድ ከሰቀሉት ከናዝሬቱ ኢየሱስ 12 ወገኖች ውስጥ ከሆኑ ወዮልን፣ እንገድላቸውም ዘንድ ተዘጋጁ›› ተባባሉ፡፡ የተቀሩት ደግሞ ‹‹አምላካቸው ኢየሱስ የሚሹትን ነገር ሁሉ እንደሚያደርግላቸው ሰምተናል ነገር ግን ዝሙትን አጥብቀው ስለሚጠሉ አመንዝራ ሴትን በከተማው መግቢያ በር ላይ ራቁቷን እናስቀምጣትና እርሷን ባዩ ጊዜ ወደኃላቸው ይመለሳሉ፤ ወደ ከተማዋም አይገቡም›› ብለው መከሩ፡፡ እንደመከሩትም አድርገው አመንዝራ ሴት ራቁቷን አድርገው በከተማው መግቢያ በር ላይ አቆሟት፡፡
ሐዋርያው ታዴዎስም አመንዝራዋን ሴት ራቁቷን ባያት ጊዜ ‹‹ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ወደ ከተማው ገብተን በከበረ ስምህ እስክንሰብክ ድረስ በራሷ ጸጉር አየር ላይ ይሰቅላት ዘንድ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን ልክልን›› ብሎ ጸለየ፡፡ ያን ጊዜ ያች ዘማዊት ሴትም ወደ አየር ወጥታ በነፋስ አውታር ተንጠለጠለች፡፡ እርሷም የሀገሩ ሰዎች ሁሉ ወጥተው እስኪያዩዋትና እስኪደነቁ ድረስ ትጮህ ጀመር፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም በዚያች አገር ሰዎች ላይ አድረው ልቡናቸውን ያሳወሩትን አጋንንት ፈጃቸው፡፡ ቅዱስ ታዴዎስም ወንጌልን ሰበከላቸው፣ ያችንም የተሰቀለች ዘማዊ ሴት በጸሎቱ ከተሰቀለችበት አውርዶ አሳምኖ ካጠመቃት በኋላ ቤቷን የጉባዔ ቤት አደረገች፡፡ አገልጋይ ኤጲስ ቆጶሳትን፣ ካህናትንና ዲያቆናትን ሾመላቸው፡፡ ያችም ሴት ዲያቆናዊት ሆና ለቤተ ክርስቲያን የምትላላክ ሆነች፡፡
ሐዋርያውም ሙታንን እያስነሣ ድውያንን እየፈወሰ ብዙ ተአምራት እያደረገ አስተምሮ ወደ ቀናች ሃይማኖት መለሳቸው፡፡ ይህንንም ያየ ሰይጣን በቅናት ተነሥቶ በአንዱ ወጣት ባለጸጋ ልብ ውስጥ አደረና መጥቶ ስለ ምጽዋት ያስተምር የነበረውን ታዴዎስን አነቀው፡፡ ነገር ግን ቅዱስ ጴጥሮስ ስለድፍረቱ ገሠጸውና ለቀቀው፡፡ ታዴዎስም ወዲያው ‹‹ጌታችን እንደ አንተ ላለው ሀብታም ‹ባለጸጋ መንግስተ ሰማያት ከሚገባ ይልቅ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢያልፍ ይቀላል› ብሎ አስተምሯል›› አለው፡፡ ባለጸጋው ወጣትም ባጠገባቸው ወደሚያልፉ ግመል ነጋዴዎች እያመለከተ ‹‹እስኪ የተናገርከውን አድርገህ አሳየን›› እያለ ተከራከረው፡፡ ታዴዎስም ባለግመሉን ጠርቶ አስቆመውና መርፌ ከሚሸጥ ሰው ዘንድ ሀዶ መርፌ ፈለገ፡፡ መርፌ የሚሸጠው ሰው ግን ታዴዎስን ሊረዳው ፈልጎ ቀዳዳው ሰፊ የሆነ መርፌ አመጣለት፡፡ ታዴዎስም ‹‹እግዚአብሔር ዋጋህን ይክፈልህ ነገር ግን በዚህች ከተማ የጌታችን ክብር ይገለጥ ዘንድ ቀዳዳው ጠባብ የሆነ እንደማንኛውም ያለ መርፌ ስጠኝ፣ ለሚያምን ሁሉ ይቻላልና›› አለው፡፡ ቀዳዳው ጠባብ የሆነውን መርፌ አመጣለትና ታዴዎስ ወደ ጌታችን ከጸለየ በኋላ ባለ ግመሉን ጠርቶ ‹‹በጌታችን ስም አንተ ከግመልህ ጋር በመርፌ ቀዳዳው ውስጥ ግባና እለፍ›› አለው፡፡ ነጋዴውም ከነግመሉ በመርፌ ቀዳዳው ውስጥ ገብቶ አለፈ፡፡ ታዴዎስም ‹‹የፈጣሪያችንን የክርስቶስን ኃይል ይረዱ ዘንድ ድጋሚ እለፍ›› አለውና ጋዴው አሁንም ከነግመሉ በመርፌ ቀዳዳው ውስጥ አለፈ፡፡ ለ3ኛ ጊዜም እንዲሁ አደረገ፡፡ ሕዝቡም ይህን አይተው ‹‹ከቅዱሳን ሐዋርያት አምላክ በቀር ሌላ አምላክ የለም›› እያሉ ጮኹ፡፡ ያ ባለጸጋ ወጣትም መጥቶ በሐዋርያው እግር ሥር ወድቆ ‹‹ኃጢአቴን ሁሉ ይቅር በለኝ ገንዘቤንም ሁሉ ወስደህ ለድኖችና ለጦም አዳሪዎች ስጥልኝ›› አለው፡፡ ሁሉንም ሃይማትን በሚገባ አስተምሮ አጠመቃቸው፡፡ ሐዋርያው ቤተ ክርስያቲን ሠርቶ ቅዳሴ ቀድሶ ለሕዝቡ ሁሉ ሥጋ ወደሙን አቀበላቸው፡፡
ከዚህም በኀላ ቅዱስ ታዴዎስ ከዚያ ከተማ ወጥቶ ወደሌላ አገር በመሄድ በብዙ አገሮች ወንጌልን ሰበከ፡፡ ወደ ፐርሺያም ሄዶ ሲሰብክ አረማውያን ብዙ አሠቃቂ መከራዎችን አድርሰውበት ሐምሌ 2 ቀን በሰማዕትነት ዐርፏል፡፡ በረከቱ ይደርብን፡፡ በአማላጅነቱ ይማረን፡፡
ስማቸውም ሆነ ያደረጉት ተአምር ከሐዋርያው ቅዱስ ታዴዎስ ጋር ተመሳሳይ ታሪክ ያላቸው አትዮጵያዊ ታላቅ ጻድቅ አሉን፡፡
አቡነ ታዴዎስ ዘጽላልሽ፡- አባታቸው ካህኑ ሮማንዮስ የደብረ ሊባኖሱ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት አጎት ሲሆኑ እናታቸው ማርታ ይባላሉ፡፡ የትልድ ቦታቸው ጽላልሽ ዞረሬ ነው፡፡ ሲወለዱ ዓምደ ብርሃን ተተክሎ የታየ ሲሆን እርሳቸውም በብርሃን ልብስ ተጠቅልለው ታይተዋል፡፡ ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ ለሊቀ ካህናቱ ለሕይወት ብነ በጽዮን ተሰጥተው ሃይማኖትን በሚገባ ተምረዋል፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዳሞት ተሻግረው ሞተሎሚን አስተምረው ካሳመኑት በኋላ አቡነ ታዴዮስን ወደ እርሳቸው እንዲመጡ ልከውባቸው ሄደው አቡነ ተክለ ሃይማኖትን እያገለገሉ ዘጠኝ ዓመት ተቀመጡ፡፡ ከዘጠኝ ዓመት በኋላ ግን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ አባ በጸሎተ ሚካኤል ሲሄዱ አቡነ ታዴዎስም ወደ ጽላልሽ ተመልሰዋል፡፡ ሁለቱም ከ32 ዓመት በኋላ ተመልሰው በጽላልሽ ተገናኘተው አቡነ ተክለ ሃይማኖት ለአቡነ ታዴዎስ ማዕረገ ምንኩስናን ሰጥተዋቸዋል፡፡ አቡነ ታዴዎስም በሥጋ ዕድሜ ታላቅ ቢሆኑም እንደታናሽ ብላቴና አቡነ ተክለ ሃይማኖትን እያገለገሉ በደብረ ሊባኖስ ተቀምጠዋል፡፡ ከዚህ በኋላ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አቡነ ታዴዎስን ወደ ጽጋጋ እንዲሄዱ ነገሯቸው ምክንያቱም አቡነ አኖሬዎስ በዚያ ሲያስተምሩ ከሃዲያን ደብድበው አስረዋቸው | 75 |
| 18 | Sin texto... | 145 |
| 19 | በዚኽ በመጥምቀ መለኮት በቅዱስ ዮሐንስ ፍልፍል ዋጋ ቤተ መቅደስ የሚገኙትን እጅግ ውብ የኾኑ ቅዱሳት ሥዕላትን የሣሏቸው አንድ ዐይነ ሥዉር ሊቅ ናቸው። ሥዕላቱንም ሲሥሉ ዲያብሎስ እየተገለጠ እንዳይሥሉ ይፈትናቸው ነበር። እርሳቸውም በስመ ሥላሴ ገዝተው አቁመውት ሥዕሎቻቸውን ሥለው ጨርሰዋል። ሥለው ሲጨርሱም ያንን ገዝተው ያቆሙትን ዲያብሎስ በሥዕል ሥዕለው አስቀምጠውታል፣ ይኽም ሥዕል እስከዛሬ ድረስ አለ።
እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ለቅዱስ ዮሐንስ
ዓመታዊ የልደት በዓል አደረሳችሁ! የቅዱስ ዮሐንስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን! ከቃልኪዳኑ ይክፈለን፡፡ | 111 |
| 20 | Sin texto... | 87 |
