ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት
الذهاب إلى القناة على Telegram
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርሥትያን ስንክሣር ውስጥ የተጻፉ የቅዱሳን አባቶቻችንና የቅዱሳት እናቶቻችን ገድላቸውና አስገራሚ ታሪካቸው ዓመቱን ሙሉ ምንም ሳይቋረጥ በየቀኑ ይነገርበታል! ለአሥትያየትዎ @abitago
إظهار المزيد1 215
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+47 أيام
+130 أيام
جاري تحميل البيانات...
القنوات المماثلة
سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
يوليو '26
يوليو '26
+8
في 0 قنوات
يونيو '26
+25
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '26
+27
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+11
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '26
+15
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '26
+23
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '26
+38
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '25
+39
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+36
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '25
+21
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '25
+20
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '25
+10
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '25
+32
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '25
+21
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '25
+21
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '25
+26
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '25
+54
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '25
+34
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '25
+67
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '24
+90
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '24
+82
في 1 قنوات
Get PRO
أكتوبر '24
+46
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '24
+61
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '24
+67
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '24
+57
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '24
+65
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '24
+66
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '24
+85
في 1 قنوات
Get PRO
مارس '24
+68
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '24
+118
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '24
+99
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '23
+98
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '23
+25
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '23
+13
في 1 قنوات
Get PRO
سبتمبر '23
+7
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '23
+17
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '23
+16
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '23
+9
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '23
+3
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '23
+4
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '23
+3
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '23
+5
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '23
+14
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '22
+10
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '22
+10
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '22
+8
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '22
+11
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '22
+4
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '22
+11
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '22
+11
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '22
+5
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '22
+4
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '22
+6
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '22
+10
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '22
+7
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '21
+7
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '21
+8
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '21
+3
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '21
+11
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '21
+9
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '21
+13
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '21
+6
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '21
+8
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '21
+26
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '21
+500
في 0 قنوات
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 09 يوليو | +2 | |||
| 08 يوليو | 0 | |||
| 07 يوليو | +2 | |||
| 06 يوليو | 0 | |||
| 05 يوليو | 0 | |||
| 04 يوليو | 0 | |||
| 03 يوليو | +1 | |||
| 02 يوليو | +3 | |||
| 01 يوليو | 0 |
منشورات القناة
| 2 | አራት ኪሎ ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሙዚየም ውስጥ የሚገኘው የሐዋርያው የቅዱስ ታዴዎስ የቀኝ እጅ!
ረድኤት በረከቱ ይደርብንና በዛሬዋ ዕለት በዓመታዊ የዕረፍት በዓሉ ታስቦ የሚውለው ሐዋርያው ቅዱስ ታዴዎስ ያደረው ታላቅ ተአምር ይህ ነው፡- የከበሩ ሐዋርያት ቅዱስ ታዴዎስና ቅዱስ ጴጥሮስ የቅዱስ ታዴዎስ የስብከት ዕጣው ወደሆነችው ወደ ሀገረ ሶርያ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሄዱ አረማውያን የሆኑ የከተማው መኳንንት ‹‹እነኚህ አይሁድ ከሰቀሉት ከናዝሬቱ ኢየሱስ 12 ወገኖች ውስጥ ከሆኑ ወዮልን፣ እንገድላቸውም ዘንድ ተዘጋጁ›› ተባባሉ፡፡ የተቀሩት ደግሞ ‹‹አምላካቸው ኢየሱስ የሚሹትን ነገር ሁሉ እንደሚያደርግላቸው ሰምተናል ነገር ግን ዝሙትን አጥብቀው ስለሚጠሉ አመንዝራ ሴትን በከተማው መግቢያ በር ላይ ራቁቷን እናስቀምጣትና እርሷን ባዩ ጊዜ ወደኃላቸው ይመለሳሉ፤ ወደ ከተማዋም አይገቡም›› ብለው መከሩ፡፡
እንደመከሩትም አድርገው አመንዝራ ሴት ራቁቷን አድርገው በከተማው መግቢያ በር ላይ አቆሟት፡፡ ሐዋርያው ታዴዎስም አመንዝራዋን ሴት ራቁቷን ባያት ጊዜ ‹‹ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ወደ ከተማው ገብተን በከበረ ስምህ እስክንሰብክ ድረስ በራሷ ጸጉር አየር ላይ ይሰቅላት ዘንድ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን ልክልን›› ብሎ ጸለየ፡፡ ያን ጊዜ ያች ዘማዊት ሴትም ወደ አየር ወጥታ በነፋስ አውታር ተንጠለጠለች፡፡ እርሷም የሀገሩ ሰዎች ሁሉ ወጥተው እስኪያዩዋትና እስኪደነቁ ድረስ ትጮህ ጀመር፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም በዚያች አገር ሰዎች ላይ አድረው ልቡናቸውን ያሳወሩትን አጋንንት ፈጃቸው፡፡ ቅዱስ ታዴዎስም ወንጌልን ሰበከላቸው፣ ያችንም የተሰቀለች ዘማዊ ሴት በጸሎቱ ከተሰቀለችበት አውርዶ አሳምኖ ካጠመቃት በኋላ ቤቷን የጉባዔ ቤት አደረገች፡፡ አገልጋይ ኤጲስ ቆጶሳትን፣ ካህናትንና ዲያቆናትን ሾመላቸው፡፡ ያችም ሴት ዲያቆናዊት ሆና ለቤተ ክርስቲያን የምትላላክ ሆነች፡፡
ግመልን በመርፌ ቀዳዳ አሾልኮ በማሳለፍና ሌሎችም እጅግ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን በማድረግ አሕዘብን ያሳመነው ሐዋርያው ቅዱስ ታዴዎስ በብዙ አገሮች ወንጌልን ሰብኳል፡፡ ወደ ፐርሺያም ሄዶ ሲሰብክ አረማውያን ብዙ አሠቃቂ መከራዎችን አድርሰውበት ሐምሌ 2 ቀን በሰማዕትነት ዐርፏል፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን፡፡ | 68 |
| 3 | لا يوجد نص... | 45 |
| 4 | لا يوجد نص... | 40 |
| 5 | ነበር፡፡ እሳቸውም ታስረው ሳለ ወደ አቡነ ተክለ
ሃይማኖት ዘንድ የሚላካቸው ሲያስቡ ቁራ መጥቶ ‹‹እኔ እላክሃለሁ›› ቢላቸው ‹‹ክፋትህ እንደ መልክህ ነው›› ብለው እምቢ አሉት፡፡ ርግብ መጥታ ‹‹እኔ እላክሃለሁ›› ብትላቸው ‹‹መጥተህ አድነኝ›› ብለው በክንፏ ላይ ጽፈው ልከዋት እርሷም መልእክቱን ለተክለ ሃይማኖት አድሳ ነበር፡፡ ስለዚህም ነው አቡነ ታዴዎስን ሕዝቡን ከኃጢአት ግዞት አኖሬዎስን ከእስራት እንዲያስፈቱ የላኳቸው፡፡ አቡነ ታዴዎስም በፋስ ሠረገላ ተጭነው መዩጥ ከተባለውና አኖርዮስን ካሰራቸው ንጉሥ ፊት ቢደርሱ ንጉሡ በግንጋጤ መልአክ የመጣበት መስሎት ሲፈራ ከሰው ወገን መሆናቸውን ነግረው ክርስትናን አስተማሩት፡፡ ጋኔን ከእሳት ጥሎት ሲሠቃይ የሚኖርና ሊሞት የደረሰ ልጁን ቢፈውሱለት በትምህርታቸውና በተአምራታቸው አምኖ ሕዝቡ ክርስትናን እንዲቀበል በአዋጅ አስነገረ፡፡
አፍጃል የሚባለው ባለጸጋ ወደ አቡነ ታዴዎስ ቀርቦ ሲማር ‹‹ባለጸጋ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ይልቅ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢሾልክ ይቀላል›› (ማቴ 19፡24፣ ማር 10፡25፣ ሉቃ 18፡25) የሚለውን የወንጌል ቃል ሲሰማ ለአእምሮው ረቆበት ‹‹እስቲ አድርገህ አሳየኝ?›› አላቸው፡፡ አቡነ ታዴዎስም እናቲቱን ግመል ከነጇ ቀጥሎም 28 ግመሎችን በየተራ በመርፌ ቀዳዳ እያሾለኩ አሳይተውታል፡፡ ሕዝቡ ሁሉ በእጅጉ ሲገረምና ‹‹በአምላከ ታዴዎስ ስም አምናለሁ›› ሲል የባለጸጋው ልጅ ሙሳ ግን ‹‹በምትሃት አሳይቶን ነው እንጂ የእውነት አይደለም›› በማለት አባቱንም እንዳያምን ይናገር ጀመር፡፡ ይህንንም ሲናገር በመጀመሪያ ያለፈችው እናቲቱ ግመል እረግጣ ገደለችው፡፡ አቡነ ታዴዎስም ንጉሡን፣ አባቱን አፍጃልንና ሕዝቡን የሞተ እንደሚነሣ ሲያስምሯቸው ‹‹የሞተ ይነሣልን? እስኪ ይህ የሞተው ልጅ ይነሳና ሁሉም አይቶ ይመን›› አሏቸው፡፡ እሳቸውም ‹‹ዛሬ ተቀብሮ ይዋልና ነገ በሦስተኛው ይነሣል›› ብለዋቸው ተቀብሮ ዋለ፡፡ በማግሥቱም አፍጃልን ጠርተው ‹‹‹አልዓዛርን ከሞት ባስነሣው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ልጄ ሆይ ና ውጣ› ብለህ ከልጅህ መቃብር ላይ አኑረው› ብለው ዘንጋቸውን ሰጡት፡፡ ሄዶም እንዳሉት ቢያደርግ ልጁ አፈፍ ብሎ ተነሥቷል፡፡ ይህንን ያዩ የሀገሩ ሰዎች ሁሉም አምነው ተጠምቀዋል፡፡ እሳቸውም 12 አብያተ ክርስቲያናትን አሳንጸው ሞቶ የተነሳውን ሙሳን ሙሴ ብለው ሰይመው አስተምረው ሊቀ ካህናት አድርገው ሾመውት አቡነ አኖሬዮስን ይዘው ወደ ጽላልሽ ዞረሬ ተመልሰዋል፡፡
አቡነ ተክለ ሃይማኖት ካረፉ በኋላ አባ ያዕቆብ የተባሉ ጳጳስ ከግብፅ መጡ፡፡ የአቡነ ታዴዎስን ዜና ሲሰሙ ተደስተው ከአቡነ ፊሊጶስ ጋር ሆነው አስጠርተዋቸው ‹‹የአባታችሁን ዜና ገድል ንገሩኝ›› አላቸው፡፡ አቡነ ታዴዎስም ‹‹ጨዋታ በአስተርጓሚ አይሰምርም›› ብለው ወደ ጌታችን ቢጸልዩ የጳጳሱ ቋንቋ ለታዴዎስ፣ የታዴዎስም ቋንቋ ለጳጳሱ ተገልጦላቸው የመሸ የነጋ ሳይመስላቸው 40 ጾምን ሲጨዋወቱ ቆይተዋል፡፡ ከዚህ በኋላ ጳጳሱ ከንጉሡ ተማክረው ‹‹ሊቀ ካህናት ዘጽላልሽ›› ብለው ሾመዋቸዋል፡፡
በነግህና በሰርክ ቤተ ክርስቲያንን እያገለገሉ፣ ቀን ወንጌልን እየሰበኩ፣ ሌሊት ከባሕር ገብተው ሲጸልዩ እያደሩ በታላቅ ተጋድሎ እየኖሩ ሳለ ከ10 ዓመት በኋላ ሰይጣን በንጉሡ በዓምደ ጽዮን ፍቅረ ዝሙት አሳድሮበት በክፉዎችም ምክር አታሎት የአባቱን ቅምጥ አገባ፡፡ አቡነ ታዴዎስም ይህን ሲሰሙ እንደ ነቢዩ ኤልያስና እንደ መጥምቁ ዮሐንስ በቀጥታ ሄደው ንጉሡን ገሥጸው አወገዙት፡፡ ገሥጸውና አውግዘው አቡነ ማትያስን አስከትለው ሲመለሱ ቅምጧ የንጉሡ ሚስት በፈረስ ተከትላ ደርሳ የኋሊት አሳስራ ዛሬ ‹‹ማርያም ገዳም›› ከሚባለው ቦታ ፊት ለፊት ካለው ትልቅ ገደል ውስጥ ሁለቱንም ጣለቻቸውና ጥር 29 ቀን በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡
በሰማዕትነት ዐርፈው ደማቸው ከፈሰሰበት ከገደሉ ስር በፈለቀው ጸበላቸው ‹‹ታዴዎስ ወማትያስ›› እያለ ሦስት ጊዜ ብቅ ጥልቅ እያለ የተጠመቀ ሰው እንደ 40 ቀን ሕፃን እንደሚሆን ጌታችን ቃልኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡ ይህ ሰማዕትነት በተቀበሉበት አካባቢ የተሠራው ቤተ ክርስቲያናቸው በጠላት ወረራ ጊዜ ፈርሶ ቦታው ጠፍ ሆኖ የኖረ ቢሆንም የአካባቢው ሕዝብ ቦታውን ከልሎ በክብር ሲጠብቀው ስለኖረ ፈቃደ እግዚአብሔር ሆኖ የአቡነ ታዴዎስ ታቦታቸው በ2005 ዓ.ም ከኢቲሣ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ወጥቶ ጻድቁ ሰማዕትነት በተቀበሉበት አካባቢ በተሠራው መቃኞ ቤተ ክርስቲያናቸው በታላቅ ክብር ገብቷል፡፡ ቤተ ክርስቲያኑም ከኢቲሣ በእግር የአንድ ሰዓት ተኩል ርቀት ላይ ይገኛል፡፡
(ምንጨ፡- የሐምሌ ወር ስንክሳር፣ ገድለ አቡነ ታዴዎስ፣ ቤተ ክርስቲያንህን ዕወቅ) | 34 |
| 6 | በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት):
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን
ሐምሌ 2-ግመልን በመርፌ ቀዳዳ አሾልኮ በማሳለፍና ሌሎችም እጅግ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን በማድረግ አሕዘብን ያሳመነው ሐዋርያው ቅዱስ ታዴዎስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ታዴዎስ ማለት ‹‹የአምላክ ካህን›› ማለት ነው፡፡ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ ሲሆን ግመል በመርፌ ቀዳዳ በማሾለክ አሕዛብን ያሳመነ ሐዋርያ ነው፡፡ በበዓለ 50 ቀን አጽናኝ መንፈስ ቅዱስን ከተቀበለ በኋላ ወደተለያዩ አገሮች ተዘዋውሮ ወንጌልን የሰበከ ቢሆንም ሀገረ ስብከቱ ግን ሶርያ ነበር፡፡ ጌታችንም መልኩ በሚያምር ጎማሳ አምሳል ተገልጦለት እንዳይፈራና ሁልጊዜም ከእርሱ ጋር እንደሚሆን በመንገር አጽናንቶታል፡፡
ቅዱስ ጴጥሮስ ወደ ሀገረ ስብከቱ ሊያደርሰው ወስዶት ከከተማው ዳርቻ ላይ እንዳሉ በማሳ ላይ የሚያርስ አንድ ሽማግሌ አገኙ፡፡ ጠጋ ብለውም የሚበሉት እህል እንዲሰጣቸው ጠየቁት፡፡ ሽማግሌውም ‹‹አህል ከዚህ አልያዝኩም ግን ከቤት ላምጣላችሁ ከዚህ ከበሬዎቹ ዘንድ ተቀምጣችሁ ጠብቁኝ›› ብሎ ወደ ቤቱ ሄደ፡፡ ሽማግሌውም ከሄደ በኋላ እነርሱም ደግነቱን ተመልከተው ተደሰቱ፡፡ ‹‹እስኪመለስም ድረስ እርሻውን እያረስንለት እንጠብቀው›› ተባለው ታዴዎስ ሲያርስ ጴጥሮስ መዝራት ጀመረ፡፡ ሠላሳ ትልም መሬት አርሰው እንደጨረሱ የዘሩት እህል ዕለቱን ወዲያው በቀለ፡፡ መብቀል ብቻም አይደለም እህሉ ዕለቱን አድጎ አሽቶ አፈራ፡፡ ሽማግሌውም ሲመለስ ቅዱሳን ሐዋርያት ያደረጉትን በተመለከተ ጊዜ ደንግጦ ከእግራቸው ሥር ወድቆ ሰገደላቸውና ‹‹ከሰማይ የወረዳችሁ አማላክት ናችሁን?›› አላቸው፡፡ እነርሱም ‹‹እኛ የአምላክ ባሮቹ ነን እንጂ አማልክት አይደልንም›› በማለት ከነገሩት በኋላ ወንጌልን ሰበኩለት፡፡ እርሱም ‹‹በምትሄዱበት ሁሉ ልከተላችሁ‹‹ ሲላቸው እነርሱ ግን ‹‹ይህን ልታደርግ አይገባም ነገር ግን ቤትህን አዘጋጅልን›› አሉት፡፡ ሽማግሌውም ከማሳው እሸት ቆርጦ ወስዶ በሬዎቹን እየነዳ ወደ ቤቱ ወሰዳቸው፡፡ በእርሻ ወቅት እሸት ተሸክሞ ሲሄድ ያዩት የሀገሩ ሰዎችም ይገረሙበት ነበር፡፡ ወሬውም የከተማው መኳንንት ዘንድ ደረሰ፡፡ ሽማግሌውንም በጠየቁት ጊዜ ከመጀመሪያው ጀምሮ የሆነውን ነገራቸው፡፡
የከተማውም መኳንንት ‹‹እነኚህ አይሁድ ከሰቀሉት ከናዝሬቱ ኢየሱስ 12 ወገኖች ውስጥ ከሆኑ ወዮልን፣ እንገድላቸውም ዘንድ ተዘጋጁ›› ተባባሉ፡፡ የተቀሩት ደግሞ ‹‹አምላካቸው ኢየሱስ የሚሹትን ነገር ሁሉ እንደሚያደርግላቸው ሰምተናል ነገር ግን ዝሙትን አጥብቀው ስለሚጠሉ አመንዝራ ሴትን በከተማው መግቢያ በር ላይ ራቁቷን እናስቀምጣትና እርሷን ባዩ ጊዜ ወደኃላቸው ይመለሳሉ፤ ወደ ከተማዋም አይገቡም›› ብለው መከሩ፡፡ እንደመከሩትም አድርገው አመንዝራ ሴት ራቁቷን አድርገው በከተማው መግቢያ በር ላይ አቆሟት፡፡
ሐዋርያው ታዴዎስም አመንዝራዋን ሴት ራቁቷን ባያት ጊዜ ‹‹ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ወደ ከተማው ገብተን በከበረ ስምህ እስክንሰብክ ድረስ በራሷ ጸጉር አየር ላይ ይሰቅላት ዘንድ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን ልክልን›› ብሎ ጸለየ፡፡ ያን ጊዜ ያች ዘማዊት ሴትም ወደ አየር ወጥታ በነፋስ አውታር ተንጠለጠለች፡፡ እርሷም የሀገሩ ሰዎች ሁሉ ወጥተው እስኪያዩዋትና እስኪደነቁ ድረስ ትጮህ ጀመር፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም በዚያች አገር ሰዎች ላይ አድረው ልቡናቸውን ያሳወሩትን አጋንንት ፈጃቸው፡፡ ቅዱስ ታዴዎስም ወንጌልን ሰበከላቸው፣ ያችንም የተሰቀለች ዘማዊ ሴት በጸሎቱ ከተሰቀለችበት አውርዶ አሳምኖ ካጠመቃት በኋላ ቤቷን የጉባዔ ቤት አደረገች፡፡ አገልጋይ ኤጲስ ቆጶሳትን፣ ካህናትንና ዲያቆናትን ሾመላቸው፡፡ ያችም ሴት ዲያቆናዊት ሆና ለቤተ ክርስቲያን የምትላላክ ሆነች፡፡
ሐዋርያውም ሙታንን እያስነሣ ድውያንን እየፈወሰ ብዙ ተአምራት እያደረገ አስተምሮ ወደ ቀናች ሃይማኖት መለሳቸው፡፡ ይህንንም ያየ ሰይጣን በቅናት ተነሥቶ በአንዱ ወጣት ባለጸጋ ልብ ውስጥ አደረና መጥቶ ስለ ምጽዋት ያስተምር የነበረውን ታዴዎስን አነቀው፡፡ ነገር ግን ቅዱስ ጴጥሮስ ስለድፍረቱ ገሠጸውና ለቀቀው፡፡ ታዴዎስም ወዲያው ‹‹ጌታችን እንደ አንተ ላለው ሀብታም ‹ባለጸጋ መንግስተ ሰማያት ከሚገባ ይልቅ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢያልፍ ይቀላል› ብሎ አስተምሯል›› አለው፡፡ ባለጸጋው ወጣትም ባጠገባቸው ወደሚያልፉ ግመል ነጋዴዎች እያመለከተ ‹‹እስኪ የተናገርከውን አድርገህ አሳየን›› እያለ ተከራከረው፡፡ ታዴዎስም ባለግመሉን ጠርቶ አስቆመውና መርፌ ከሚሸጥ ሰው ዘንድ ሀዶ መርፌ ፈለገ፡፡ መርፌ የሚሸጠው ሰው ግን ታዴዎስን ሊረዳው ፈልጎ ቀዳዳው ሰፊ የሆነ መርፌ አመጣለት፡፡ ታዴዎስም ‹‹እግዚአብሔር ዋጋህን ይክፈልህ ነገር ግን በዚህች ከተማ የጌታችን ክብር ይገለጥ ዘንድ ቀዳዳው ጠባብ የሆነ እንደማንኛውም ያለ መርፌ ስጠኝ፣ ለሚያምን ሁሉ ይቻላልና›› አለው፡፡ ቀዳዳው ጠባብ የሆነውን መርፌ አመጣለትና ታዴዎስ ወደ ጌታችን ከጸለየ በኋላ ባለ ግመሉን ጠርቶ ‹‹በጌታችን ስም አንተ ከግመልህ ጋር በመርፌ ቀዳዳው ውስጥ ግባና እለፍ›› አለው፡፡ ነጋዴውም ከነግመሉ በመርፌ ቀዳዳው ውስጥ ገብቶ አለፈ፡፡ ታዴዎስም ‹‹የፈጣሪያችንን የክርስቶስን ኃይል ይረዱ ዘንድ ድጋሚ እለፍ›› አለውና ጋዴው አሁንም ከነግመሉ በመርፌ ቀዳዳው ውስጥ አለፈ፡፡ ለ3ኛ ጊዜም እንዲሁ አደረገ፡፡ ሕዝቡም ይህን አይተው ‹‹ከቅዱሳን ሐዋርያት አምላክ በቀር ሌላ አምላክ የለም›› እያሉ ጮኹ፡፡ ያ ባለጸጋ ወጣትም መጥቶ በሐዋርያው እግር ሥር ወድቆ ‹‹ኃጢአቴን ሁሉ ይቅር በለኝ ገንዘቤንም ሁሉ ወስደህ ለድኖችና ለጦም አዳሪዎች ስጥልኝ›› አለው፡፡ ሁሉንም ሃይማትን በሚገባ አስተምሮ አጠመቃቸው፡፡ ሐዋርያው ቤተ ክርስያቲን ሠርቶ ቅዳሴ ቀድሶ ለሕዝቡ ሁሉ ሥጋ ወደሙን አቀበላቸው፡፡
ከዚህም በኀላ ቅዱስ ታዴዎስ ከዚያ ከተማ ወጥቶ ወደሌላ አገር በመሄድ በብዙ አገሮች ወንጌልን ሰበከ፡፡ ወደ ፐርሺያም ሄዶ ሲሰብክ አረማውያን ብዙ አሠቃቂ መከራዎችን አድርሰውበት ሐምሌ 2 ቀን በሰማዕትነት ዐርፏል፡፡ በረከቱ ይደርብን፡፡ በአማላጅነቱ ይማረን፡፡
ስማቸውም ሆነ ያደረጉት ተአምር ከሐዋርያው ቅዱስ ታዴዎስ ጋር ተመሳሳይ ታሪክ ያላቸው አትዮጵያዊ ታላቅ ጻድቅ አሉን፡፡
አቡነ ታዴዎስ ዘጽላልሽ፡- አባታቸው ካህኑ ሮማንዮስ የደብረ ሊባኖሱ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት አጎት ሲሆኑ እናታቸው ማርታ ይባላሉ፡፡ የትልድ ቦታቸው ጽላልሽ ዞረሬ ነው፡፡ ሲወለዱ ዓምደ ብርሃን ተተክሎ የታየ ሲሆን እርሳቸውም በብርሃን ልብስ ተጠቅልለው ታይተዋል፡፡ ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ ለሊቀ ካህናቱ ለሕይወት ብነ በጽዮን ተሰጥተው ሃይማኖትን በሚገባ ተምረዋል፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዳሞት ተሻግረው ሞተሎሚን አስተምረው ካሳመኑት በኋላ አቡነ ታዴዮስን ወደ እርሳቸው እንዲመጡ ልከውባቸው ሄደው አቡነ ተክለ ሃይማኖትን እያገለገሉ ዘጠኝ ዓመት ተቀመጡ፡፡ ከዘጠኝ ዓመት በኋላ ግን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ አባ በጸሎተ ሚካኤል ሲሄዱ አቡነ ታዴዎስም ወደ ጽላልሽ ተመልሰዋል፡፡ ሁለቱም ከ32 ዓመት በኋላ ተመልሰው በጽላልሽ ተገናኘተው አቡነ ተክለ ሃይማኖት ለአቡነ ታዴዎስ ማዕረገ ምንኩስናን ሰጥተዋቸዋል፡፡ አቡነ ታዴዎስም በሥጋ ዕድሜ ታላቅ ቢሆኑም እንደታናሽ ብላቴና አቡነ ተክለ ሃይማኖትን እያገለገሉ በደብረ ሊባኖስ ተቀምጠዋል፡፡ ከዚህ በኋላ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አቡነ ታዴዎስን ወደ ጽጋጋ እንዲሄዱ ነገሯቸው ምክንያቱም አቡነ አኖሬዎስ በዚያ ሲያስተምሩ ከሃዲያን ደብድበው አስረዋቸው | 48 |
| 7 | لا يوجد نص... | 113 |
| 8 | በዚኽ በመጥምቀ መለኮት በቅዱስ ዮሐንስ ፍልፍል ዋጋ ቤተ መቅደስ የሚገኙትን እጅግ ውብ የኾኑ ቅዱሳት ሥዕላትን የሣሏቸው አንድ ዐይነ ሥዉር ሊቅ ናቸው። ሥዕላቱንም ሲሥሉ ዲያብሎስ እየተገለጠ እንዳይሥሉ ይፈትናቸው ነበር። እርሳቸውም በስመ ሥላሴ ገዝተው አቁመውት ሥዕሎቻቸውን ሥለው ጨርሰዋል። ሥለው ሲጨርሱም ያንን ገዝተው ያቆሙትን ዲያብሎስ በሥዕል ሥዕለው አስቀምጠውታል፣ ይኽም ሥዕል እስከዛሬ ድረስ አለ።
እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ለቅዱስ ዮሐንስ
ዓመታዊ የልደት በዓል አደረሳችሁ! የቅዱስ ዮሐንስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን! ከቃልኪዳኑ ይክፈለን፡፡ | 100 |
| 9 | لا يوجد نص... | 73 |
| 10 | ቅዱስ ቶማስም ለሞተች በኋላ የት እንደነበረች ያችን በሕዝቡ ሁሉ ፊት ጠየቃት፡፡ እርሷም በሲኦል እንደነበረችና በዚያም ያሉትን ልዩ ልዩ የሆኑ እጅግ ጽኑ ሥቃዮችን ሁሉ በዝርዝር ለሕዝቡ አስረዳች፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስም ከዚያ የነበሩትን ‹‹ይህች ሴት ሞታ እንደነበር አይታችኋል፣ አሁንም አይታ የምትመሰክረውን ሰማችሁን? በሲኦል ያለው ሥቃይ ብቻ አይደለም ነገር ግን ከዚህ የሚከፋ አለ፡፡ እናንተም የኃጢአትን ሥራና ክፉ ሀሳብን ትታችሁ ወደ እግዚአብሔር ተመለሱ፡፡ ትሕትናን፣ የዋህነትን፣ ፍቅርንና ንጽሕናን ጠብቁ ከእግዚአብሔር ዘንድ ጸጋን ትቀበላላችሁ›› አላቸው፡፡ ሕዝቡም ሁሉ በክብር ባለቤት በጌታችን አመኑ፡፡ ለድኆቸም ምጽዋትን ሊሰጡ ብዙ ገንዘብ ሰብስበው አመጡ፡፡ ለድኆች ምጽዋት መስጠት ለሐዋርያው ልማዱ ነበርና፡፡ ወሬውም በሀገሩ ሁሉ ተሰማና ሕመምተኞችን ሁሉ ሰብስበው አምጥተው በፊቱ ጣሏቸው፡፡ ቅዱስ ቶማስም ሁሉንም ፈወሳቸው፡፡ የሐዋርያው የቅዱስ ቶማስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን! | 63 |
| 11 | አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ሐምሌ 1-ድንግልና መስተጋድልት የሆነች ቅድስት ቅፍሮንያ በሰማዕትነት ዐረፈች፡፡
+ ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ቀሳውስት የሆኑ መስተጋድላን ቅዱስ ብዮክና ቅዱስ ብንያሚን ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ በመሸታ ቤት አርደው በገደሏት አንዲት ሴት ላይ ታላቅ ተአምር አደረገ፡፡
+ ጻድቁ መነኮስ ገብረ መድኅን ዕረፍቱ መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሰዋል፡፡
ሰማዕቷ ቅድስት ቅፍሮንያ፡- ስሟ ኦርያና የተባለች 50 ደናግል መነኮሳይያትን እመ ምኔት ሆና የምትመራ ደገኛ እኅት አለቻት፡፡ ቅድስት ኦርያናም እኅቷን ቅድስት ቅፍሮንያን ፈሪሃ እግዚአብሔርንና ቅዱሳት መጻሕፍትን እያስተማረች አሳደገቻት፡፡ ቅድስት ቅፍሮንያ እስከ ሁለት ቀን ድረስ የምትጾም ተጋዳሊት እስከሆነች ድረስ ትሩፋት መሥራትንና በጎ ተግባራትን አበዛች፡፡
በወቅቱም ከ470,000 በላይ የሚሆኑ ክርስቲያኖችን በሰማዕትነት የሰየፈው ከሃዲው ዲዮቅልጥያኖስ በዓለም ላይ የጣዖት አምልኮን ባወጀ ጊዜ በገዳም ያሉ ደናግልም ወሬውን ሲሰሙ ወጥተው በመሄድ ተሠወሩ፡፡ እመ ምኔቷ ቅድስት ኦርያና እኅቷ ቅድስት ቅፍሮንያ ግን ብቻቸውን ቀሩ፡፡ በማግሥቱም ጭፍሮቹ መጥተው እመ ምኔቷን ያዟት ነገር ግን ቅድስት ቅፍሮንያ ‹‹እርሷ አርጅታለችና በእርሷን ትታችሁ እኔን ውሰዱኝ›› አለቻቸውና ይዘው ወደ መኮንኑ ወሰዷት፡፡ እመ ምኔቷም ተከተለቻቸው፡፡ መኮንኑም ለአማልክት እንድትሠዋ ብዙ በማባበል ቃልኪዳን ገባላት፡፡ ቅድስት ቅፍሮንያ ግን ቃልኪዳኑንም ሆነ አምልኮቱን አቃለለችበት፡፡ ትእዛዙንም እንዳልተቀበለችው ባየ ጊዜ ጽኑ ድብደባ አደረሰባት፡፡ ዳግመኛም ልብሷን ገፈው ሥጋዋን ግልጥ ባደረጋት ጊዜ እመ ምኔቷ ቅድስት ኦርያና ጮኻ መኮንኑን ‹‹አንተ ከሃዲ ይህችን ታናሽ ብላቴና እንሠቃየሃትና እንዳጎሳቆልካት እግዚአብሔር ያጎሳቁልህ›› ብላ ረገመቸው፡፡ በዚህም ጊዜ መኮንኑ እጅግ ተቆጥቶ ቅድስት ቅፍሮንያን አሥሮ በመንኮራኩር ውስጥ አሠቃያት፡፡ ሰውነቷንም በብረት መጋዝ ሠነጠቃት፡፡ እርሷም ወደ እግዚአብሔር በጮኸች ጊዜ ወዲያው ከሕመሟ ሁሉ ድና ምንም ጉዳት እንዳላገኛት ሆነች፡፡
ዳግመኛም መኮንኑ የቅድስት ቅፍሮንያን ምላሷንና ሕዋሳቶቿን ሁሉ ቆራረጣቸው፡፡ ጥርሶቿንም ሰበራቸው፡፡ አሁንም ጌታችን ፍጹም ጤነኛ አድርጎ ያለሕማም አስነሣት፡፡ መኮንኑም እርሷን ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ ራሷን በሰይፍ አስቆረጣትና የሰማዕትነቷ ፍጻሜ ሆኖ የድል አክሊልን ተቀዳጀች፡፡ አንድ ባለጸጋ ምእመንም መጥቶ የቅድስት ቅፍሮንያን ሥጋ ወስዶ ባማሩ የሐር ልብሶች ገንዞ በወርቅ ሣጥን አኖራት፡፡ ከሥጋዋም ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራት ተገለጡ፡፡ ረድኤት በረከቷ ይደርብን በጸሎቷ ይማረን!
+ + +
ወንድማማቾቹ መስተጋድላን ቅዱስ ብዮክና ቅዱስ ብንያሚን፡- እነዚህም ቅዱሳን በግብጽ ደቡባዊ አውራጃ በምትገኝ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቀሳውስት ናቸው፡፡ እነርሱም በእግዚአብሔር ጸጋና በቅድስና ፍጹማን ናቸው፡፡ እግዚአብሔርም በእጆቻቸው ብዙ አስገራሚ ተአምራትን አደረገ፡፡ እያጠመቁ ብዙ ድውያንን ፈወሰ፡፡ አባታቸውም ለሞት በተቃረበ ጊዜ በዚያን ሰዓት ቀሲስ ብንያሚን ቁርባንን ያሳርግ ዘንድ የቅዳሴ ልብስ ለብሶ በቤተ መቅደስ ነበረ፡፡ መልእክተኞችም መጥተው የቤተ ክርስቲያን ሹም የሆነው አባቱ ለሞት እንደተቃረበና ሊሰናበተው እንደፈለገው ነገሩት፡፡ አባ ብንያሚንም ‹‹የቁርባኑን ሥርዓት ሳልፈጽም ልብሰ ተክህኖውን አላወልቅም፣ አባቴ ከመሞቱ በፊት እንዳየው እግዚአብሔር ከፈቀደ በሕይወት ይቆየኛል፡፡ ካልሆነም የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን›› አለ፡፡ አባቱም 2ኛና 3ኛ ጊዜ መልእክት ላከበት ነገር ግን አባ ብንያሚንም አልመጣም፡፡ የቁርባኑንም ሥርዓት ፈጽሞ ቢመጣ አባቱን ሞቶ አገኘው፡፡ ከአባቱም በቀር የቤተ ክርስቲያንን ንዋያተ ቅዱሳት በምሥጢር ያኖረበትን ቦታ ማንም አያውቅም ነበርና አባ ብንያሚን ስለ ከበሩ ዕቃዎች እጅግ አዘነ፡፡
የአባ ብንያሚን ወንድሙ ብዮክ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሄዶ የከበሩ አረጋውያን አባቶችን ስለከበሩ የቤተ ክርስቲያን ዕቃዎች እንዲጠይቅ ነገረው፡፡ አባ ብንያሚንም በሄደ ጊዜ የገዳመ አስቄጥሱን የከበረ አባ ዳንኤልን አገኘውና የመጣበትን ጉዳይ ነገረው፡፡ አባ ዳንኤልም ዕቃዎቹ ያሉበትን የምሥጢር ቦታ የሚያውቅ ሌላ ጻድቅ እንዳለ ነግሮት ወደእርሱ ላከው፡፡ ያም ጻድቅ ዕቃዎቹ ያሉበትን ለአባ ብንያሚን ነገረው፡፡ በሄደም ጊዜ ጻድቁ እንዳስረዳው አገኛቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ሁለቱ ወንድማማቾቹ በጋራ ሆነው ከበፊቱ ይበልጥ በገድል ተጠምደው ኖሩ፡፡ ለሕሙማን ነፍሳቸው ሳትወጣ ያቀብሏቸው ዘንድ ከቅዱስ ቁርባን ከፍለው በሣጥን የማኖር ሥርዓት ነበራቸው፡፡ ሰይጣንም ከይሲን አነሣሣውና ሣጥኑን ሰብሮ ከዚያ ቅዱስ ቁርባን በላ፡፡ ቅዱሳን የሆኑ ብዮክና ብንያሚንም ይህንን ባወቁ ጊዜ እጅግ አዘኑ፡፡ ከይሲውንም ገደሉት፡፡ ከዚህም በኋላ የተቀደሰውን ቁርባን ስለበላ ከይሲውን ይበሉት ዘንድ ተማከሩ፡፡ ፈቃዱም እንደሆነ ያስረዳቸው ዘንድ እግዚአብሔርን በጸሎት ጠየቁት፡፡ እግዚአብሔርንም መልአኩን ላካላቸውና እንዲበሉት ነገራቸው፡፡ ቅዱሳኑም በሉት፡፡ ከበሉትም በኋላ ዐረፉ፡፡
እግዚአብሔርንም ሥራቸውንና ገድላቸውን ለአንዲት ድንግል ሴት ገለጠላት፡፡ እርሷም የቅዱሳኑን ገድል ለሕዝቡ ተናገረች፡፡ እነዘርሱም ያማረች ቤተ ክርስቲያን ሠርተው ሥጋቸውን በውስጧ አኖሩ፡፡ ከቅዱሳኑም ሥጋ ብዙ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራት ተገለጡ፡፡ የሰማዕታቱ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!
+ + +
ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ በመሸታ ቤት አርደው በገደሏት አንዲት ሴት ላይ ያደረገው ታላቅ ተአምር፡- አንድ ጎልማሳ በሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ እጅ የተባረከ እንጀራን ከሕዝቡ ጋር ተቀብሎ ሊበላ ሲል እጆቹ ፈጽመው ደረቁ፡፡ እርሱንም ያዩት ሰዎች በዚህ ጎልማሳ ላይ የሆነውን ነገር ለሐዋርያው ነገሩት፡፡ ቅዱስ ቶማስም ልጁን ጠራውና ‹‹ልጄ ሆይ! የእግዚአብሔር ቸርነት በግልጽ ዘልፎሃልና ያደረከውን ነገር ንገረኝ?›› አለው፡፡ ጎልማሳውም ከሐዋርያው እግር ሥር ወድቆ ሰገደና ‹‹መልካም ሥራ የሠራሁ መስሎኝ ክፉ ሥራን ሠርቻለሁ፡፡ ይኸውም አስቀድሜ ወደ አንዲት የጠጅ አበዛ ሴት ልጅ እገባ ነበር፡፡ አንተም በንጽሕና እንድንኖር አስተማርኸን፤ ያችም ሴት አብሬያት እተኛ ዘንድ ነዘነዘችኝ፡፡ ስለዚህም ሰይፍ አንሥቼ አረድኳት›› አለው፡፡ ሐዋርያውም ‹‹እንዴት እንዲህ ያለ ቁጣና የአውሬ ሥራን ትሠራለህ?›› ብሎ ከገሠጸው በኋላ ውኃ አስቀርቦ በላዩ ጸለየበትና ጎልማሳውን ‹‹በዚህ ታጠብ ትድናለህ›› አለው፡፡ ጎልማሳውም በውኃው በታጠበ ጊዜ የደረቁ እጆቹ ዳኑ፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱስ ቶማስ ‹‹የዚያቸ ሴት በድን ወዳለበት ቦታ ምራኝ›› አለው፡፡ ጎልማሳውም መርቶ ከቦታው አደረሰው፡፡ ሐዋርያውም በድኗን ባየ ጊዜ እጅግ አዘነ፡፡ ወደ ውጭ አውጥተው በአልጋ ላይ እንዲያኖሯት ካዘዘ በኋላ እጁን በላይዋ ጭኖ ጸለየ፡፡ ጸሎቱንም በፈጸመ ጊዜ ጎልማሳውን ‹‹ሂድ እጇን ይዘህ ‹እኔ ቀድሞ በእጄ ገደልኩሽ፣ አሁን ግን በሃይማኖት በእኔ እጅ ክርስቶስ ያስነሣሽ› በላት›› አለው፡፡ ጎልማሳውም ቅዱስ ቶማስ እንዳዘዘው ባደረገ ጊዜ ፈጥና ከሞት ተነሣች፡፡ ከአልጋዋም ፈጥና ወርዳ ከቅዱስ ቶማስ እግር ሥር ወድቃ ሰገደችለት፡፡ | 77 |
| 12 | لا يوجد نص... | 140 |
| 13 | لا يوجد نص... | 134 |
| 14 | ከጊዜም በኋላ ዮሐንስ ወደ ሕዝቡ ወጥቶ የጌታን መንገድ ማዘጋጀትና የንስሓን ጥምቀት ማጥመቅ ጀመረ፡፡ መንገዱንም ካዘጋጀ በኋላ ‹‹እኔ በውሃ አጠምቃችኋለሁ እርሱ ግን በእሳት ያጠምቃችኋል፣ እነሆ እኔ የእግሩን ጫማ ጠፈር እንኳ ልፈታ የማይገባኝ…›› እያለ ጌታችንን ለሕዝቡ በሚገባ ካስተዋወቀ በኋላ ጌታችን በፍጹም ትሕትና ወደ እርሱ መጥቶ በእጁ ተጠመቀ፡፡
ንጉሡ ርጉም ሄሮድስ የወንድሙን የፊሊጶስን ሚስት ሄሮድያዳን በማግባቱ መምህር ወመገሥጽ የሆነው መጥምቁ ዮሐንስ ሄዶ ንጉሡን ‹‹የወንድምህን ሚስት ልታገባ አይገባህም›› ብሎ ገሠጸው፡፡ ስለሌላውም ክፉ ሥራው ሁሉ ይዘልፈው ስለነበር ንጉሡ ቅዱስ ዮሐንስን አሠረው፡፡ በንጉሡም የልደት በዓል ቀን ትልቅ ድግስ አዘጋጅቶ የገሊላን መኳንንት፣ ሹማምንቱን፣ መሣፍንቱን ሁሉ ጠራቸው፡፡ የሄሮድያዳም ልጅ ወደ አዳራሹ ገብታ ዘፈነች፡፡ የሄሮድያዳ ልጅ ንጉሥ ሄሮድስን በዘፈኗ በጣም አድርጋ ስላስደሰተችው እርሱም በተራው ሊያስደስታት ፈለገ፡፡ እስከ መንግሥቱ እኩሌታ ድረስም ቢሆን የለመነችውን ይሰጣት ዘንድ በሕዝቦቹና በመኳንንቱ ሁሉ ፊት እንዳይከዳት በጽኑ ቃልኪዳን ማለላት፡፡ ‹‹የፈለግሽውን ጠይቂኝ፣ የመንግሥቴንም እኩሌታ ቢሆን እሰጥሻለሁ ምን ላድርግልሽ?›› እያለ በመሐላ በጠየቃት ጊዜ በእናቷ ምክር የዮሐንስን አንገት ቆርጦ ይሰጣት ዘንድ ለመነችው፡፡ ንጉሥ ሄሮድስም ይህን ልመና ከአፏ በሰማ ጊዜ ‹‹የፈለግሽውን እሰጥሻለሁ›› ብሎ በከበሩ መኳንንትና ሹማምንት ፊት ስለማለ ለሰው ይምሰል አዘነ፣ ተከዘ፡፡ ኃዘኑም ስለ ዮሐንስ መሞት አይደለም፣ ዮሐንስን ሕዝቡ ይወደው ስለነበር እነርሱን ስለ መፍራቱና መሐላ ምሎ ከዳ እንዳይባል ነው እንጂ፡፡ ስለ ዮሐንስ አዝኖ ቢሆን ኖሮ ቀድሞውንም በግፍ እንዲታሰር ባላደረገው ነበር፡፡ አስቀድሞ መሐላ መግባት እንዲህ ክፉ ነው፡፡ ንጉሡም ‹‹የለመንሽውን ሁሉ እሰጥሻለሁ›› ብሎ ስለማለ ሄሮድስ የዮሐንስ አንገት እንዲቆረጥ አደረገ፡፡
ዮሐንስም በእሥር ቤት ውስጥ ሆኖ እንደሚገድሉት ዐውቆ ለሰያፊዎቹ አንገቱን በመስኮት አውጥቶ ጠበቃቸው፡፡ እነርሱም ራሱን ቆርጠው በወጭት አድርገው ለዚያች ዘፋኝ ለሄሮድያዳ ልጅ ሰጧት፡፡ እርሷም ወስዳ ለእናቷ ሰጠቻት፡፡ ነገር ግን የዮሐንስ ራስ ክንፍ አውጥታ ከሄሮድያዳ እጅ ላይ ተነሥታ ወደ አየር ስለበረረች ታላቅ ድንጋጤ ሆነ፡፡ ደግሞም የዮሐንስ ራስ ክንፍ አውጥታ እየበረረች እንደቀድሞ ‹‹ሄሮድስ ሆይ የወንድምህን ሚስት ልታገባ አይገባህም›› እያለች በመጮህ ዘለፋቻቸው፡፡ በሌሊትም እየመጣች ትዘልፋቸው ነበር፡፡ ሄሮድያዳንም መሬት ተከፍታ ውጣታለች፡፡ ዘፋኟ ልጇም እናቴን ብላ እጇን ስትይዛት የራሷ እጇ ተቆርጦ ክፉ አሟሟት ሞተች፡፡
የሄሮድስም የፊተኛይቱ ሚስቱ አባቷ ንጉሡ አርጣ ሴት ልጁ ላይ በደረሰው ነገር ተናዶ ምድረ ገሊላን ወሮ ስላወደማትና በእሳትም ስላቃጠላት ንጉሥ ጢባርዮስ ይህን ሲሰማ እጅግ ተቆጥቶ ሄሮድስን ከሹመቱ ሽሮ እንድልኩ ወደምትባል አገር በግዞት ላከው፡፡ በዚያም ማቆ እጅግ ክፉ አሟሟት ሞተ፡፡ የዮሐንስም ራስ እስከ 15 ዓመት ድረስ እየበረረች ስታስተምር ኖራ ሚያዝያ 15 ቀን በዓረቢያ ምድር ዐርፋ በዚያው ተቀበረች፡፡ ከብዙ ዘመን በኋላ መጥምቁ ለሁለት ክርስቲያኖች ተገልጦላቸው የከበረች ራሱ ያለችበትን ነግሯቸው ከተቀበረችበት እንዲያወጡ ነገራቸው፡፡ ይኸውም ከተቀበረችበት ቦታ የተገኘችው በየካቲት 30 ቀን ነው፡፡
በቅዱስ ወንጌል ላይ ‹‹በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል›› (ሉቃ 1፡13) ተብሎ ለተነገረለት ለመጥምቁ ዮሐንስ ጌታችን የሰጠው ቃልኪዳን እጅግ ልዩ ነው፡፡ አስደናቂ ቃልኪዳኑም እንዲህ የሚል ነው፡- ‹‹ሰው ሁሉ ወደ ሥጋዊ ተግባርም ሆነ ወደ መንፈሳዊ ተግባርም ቢሆን ሲሄድ ‹ይህ የመጥምቀ መለኮት ዮሐንስ ቤተክርስቲያን ነው› ብሎ ቅጽሩን፣ ገራገሩን ቢሳለም የተሳለመው ሰው ቢኖር እኔ መንበረ መንግሥቴን አሳልመዋለሁ፡፡ የገድልህንም መጽሐፍ የተሳለመ ቢኖር እኔ መንበረ መንግሥቴን አሳልመዋለሁ፡፡ የገድልህ የተአምርህ መጽሐፍ የተነበበትን ውኃ እኔ እንደተጠመቅሁበት እንደ ማየ ዮርዳኖስ አደርገዋለሁ፡፡ የገድልህ መጽሐፍ በተነበበት ውኃ የተጠመቀበት ሰው ቢኖር የሰማንያ ዓመት ኃጢአቱን አስተሠርይለታለሁ፤ ወንዱን የአርባ ቀን፣ ሴቷን የሰማንያ ቀን ሕፃን አደርጋቸዋለሁ፤ እኔ በተጠመቅሁበት ማየ ዮርዳኖስ እንደተጠመቀ ሆኖለት ከኃጢአቱ ይነጻል፡፡ ሰውም ሆነ እንስሳ ቢታመም በጽኑ እምነት ይደረግልኛል ብሎ አምኖ ያለ ጥርጥር ውኃ አቅርቦ የገድልህን መጽሐፍ በላዩ ላይ አንብቦ የተነበበበትን ውኃ ቢታጠብበት ወይም ቢጠጣ ያለ ጥፋት ፈጥኖ ከደዌው ይፈወሳል፡፡ የገድልህ መጽሐፍ የተነበበበትን ማየ ጸሎት በቤቱ ውስጥ ቢረጭ ከዚያ ቤት በረከቴን እመላበታለሁ፤ ተድላን፣ ደስታን፣ ጥጋብን በዚያ ቤት አሳድራለሁ፤ እስከ ዘለዓለም ድረስ በቤቱ ውስጥ የእህል መታጣትና ርሃብ፣ የውኃ ጥማት፣ ተላላፊ በሽታ አይገባበትም፤ ፈጽሜም አላመጣበትም፡፡ ሥጋዬን ደሜን መቀበል ያልተቻለው ሰው ቢኖር ለመታሰቢያህ ዝክር ከተደረገው ፍርፋሪ ይቅመስ፣ ሥጋዬን ደሜን እንደተቀበለ እኔ አደርግለታለሁ፡፡ ፍርፋሪውን ባያገኝ እንጀራውና ዳቦው የተበላበትን ገበታ፣ ጠላው የተጠጣበትን ጽዋ በምላሱ ይላስ፣ እኔ ኢየሱስ ቃሌ የማያብለው ሥጋዬን ደሜን እንደተቀበለ አደርግለታለሁ፤ ስለ እምነቱ ሥጋዬን ደሜን ለመቀበል የሚያበቃውና እውነተኛውን ምግባር የጽድቅ ሥራ እንዲሠራ አደርገዋለሁ፡፡››
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን! የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ረድኤት በረከቱ ይደርብንን! በጸሎቱ ይማረን፡፡
(ምንጭ፡- ገድለ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ-ደብረ መንክራት ሚጣቅ ቅዱስ አማኑኤል አንድነት ገዳም ያሳተመው፣ የመስከረምና የየካቲት ወር ስንክሳር) | 112 |
| 15 | ንጉሥ ሄሮድስ በሞተ ጊዜ እነሆ የእግዚአብሔር መልአክ በግብፅ አገር ለዮሴፍ በሕልም ተገልጦ በመታየት ‹‹እነሆ የዚህን ሕፃን ነፍስ የሚሹ ሙተዋልና ተነሥተህ ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ምድረ እስራኤል ተመለስ›› ካለው በኋላ ዮሴፍ ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን ይዞ ወደ ምድረ እስራኤል ገባ፡፡ ጌታችን ‹‹ልጄ ናዝራዊ ይባላል›› ተብሎ በነቢይ የተነገረው ቃል ይደርስ ይፈጸም ዘንድ መጥቶ ናዝሬት በምትባል አገር ተቀመጠ፡፡ ለሞት ይፈልገው የነበረው የተረገመ ከሃዲ ሄሮድስ ከሞተ በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ከድንግል ማርያም ጋር ከምድረ ግብፅ ተመልሶ በናዝሬት ተቀምጦ ሳለ እነሆ የዕድሜ ባለፀጋ የሆነችው የዮሐንስ እናት ክብርት ኤልሳቤጥ ልጇን ዮሐንስን ይዛው ወደ ደብረሲና በረሃ ከገቡ ከአምስት ዓመት በኋላ ዐረፈች፡፡ ዮሐንስም በእናቱ አስክሬን አጠገብ ተቀምጦ በእጅጉ እያዘነ መሪር ልቅሶንም እያለቀሰ ሳለ የተሸሸገውን ሁሉ የሚያውቅ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በናዝሬት ተቀምጦ ሳለ የኤልሳቤጥን መሞት፣ እናቱም ስለሞተችበት ዮሐንስ ብቻውን ከበረሃ ውስጥ ተቀምጦ እያለቀሰ መሆኑን ዐወቀ፡፡
ጌታችን በናዝሬት ተቀምጦ ሳለ የኤልሳቤጥን መሞትና የወዳጁ ዮሐንስ ኃዘንና ማልቀስ ባወቀ ጊዜ እርሱም በናዝሬት ሆኖ ያለቅስ ጀመር፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ልጇ ወዳጇ ሲያለቅስ ባየችው ጊዜ ‹‹ልጄ ወዳጄ ሆይ! ምን ሆንክ? ስለምንስ ታለቅሳለህ?›› ብላ ጠየቀችው፡፡ ጌታችንም ለቅድስት እናቱ እንዲህ በማለት መለሰላት፡- ‹‹እነሆ ወገንሽ የሆነችው ኤልሳቤጥ ዐረፈች፤ ዮሐንስንም ብቻውን ከበረሃ ውስጥ ተወችው፡፡ ዮሐንስም ሕፃን ስለሆነ የሚያደርገውን አጥቶ በእናቱ አስክሬን አጠገብ ከፊት ለፊቷ ተቀምጦ በመረረ ኃዘን ያለቅሳል፡፡ እናቴ ሆይ እኔም ዘመድሽ የሆነ የዮሐንስን ልቆሶ ስላወቅሁኝና የእርሱም ኃዘን ስለተሰማኝ የማለቅሰው ስለዚህ ነው›› አላት፡፡ በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የፀናች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም የኤልሳቤጥን መሞት በሰማች ጊዜ በጣም ምርር ብላ አለቀሰች፡፡ ያንጊዜም ብርሕት ደመና መጥታ ከፊታቸው ቆመች፤ ፈጥናም ተሸከመቻቸውና ኤልሳቤጥ ከሞተችበት ዮሐንስም ካለበት ቦታ ከደብረሲና በረሃ ውስጥ ወስዳ አደረሰቻቸው፡፡ ዮሐንስም ባያቸው ጊዜ ደነገጠ፡፡ ከዚያ በፊት ሰው አይቶ ስለማያውቅ የእናቱን አስክሬን ብቻውን ትቶ ወደ ጫካ ሸሸ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የዮሐንስን ፍርሃት አራቀለትና እንዲህ አለው፡- ‹‹እኛን ከማየትህ የተነሣ አትፍራ፣ አትደንግጥም፤ አይዞህ እነሆ የእናትህ ዘመዶች ማርያምና ሰሎሜ በእናትህ አስክሬን ላይ መልካም ነገር ሊያደርጉ መጥተዋልና ና ወደ እኛ ቅረብ›› አለው፡፡ ዮሐንስም ይህን ቃል ከጌታችን አንደበት በሰማ ጊዜ ወደኋላው ተመለሰ፡፡ ከመሬትም ላይ ወድቆ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ሰገደለት፡፡
ጌታችንም እመቤታችን ማርያምንና ሰሎሜን ‹‹በጠማው ጊዜ ለእርሷ ይጠጣ ዘንድ ለዮሐንስ በፈለቀችለት ውኃ የኤልሳቤጥን ሥጋ አጥባችሁ ገንዙ›› አላቸው፡፡ እንዳዘዛቸውም የኤልሳቤጥን አስክሬን አጥበው ገነዙ፡፡ ጌታችንም ቅዱስ ሚካኤልንና ቅዱስ ገብርኤልን ይመጡ ዘንድ አዘዛቸው፡፡ እነርሱም ፈጥነው እንደ ዐይን ጥቅሻ ከሰማይ ወርደው መጡና ከጌታችን ፊት ቆሙ፡፡ ጌታችንም ‹‹የኤልሳቤጥን ሥጋ የሚቀበርበትን መሬት ቆፍሩ›› አላቸው፡፡ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤልም መቃብሩን ይቆፍሩ ዘንድ ጀመሩ፡፡ ጌታችን ዘካርያስንና ስምዖንን በአካለ ነፍስ ከሰማይ መጥተው በኤልሳቤጥ አስክሬን ላይ ጸሎተ ፍትሃቱን ያደርሱ ዘንድ አዘዛቸው፡፡ እነርሱም የኤልሳቤጥ አስክሬን ካለበት ቦታ ላይ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል፣ እመቤታችን ማርያምና ሰሎሜ ከጌታችን ፊት ቆመው ሳለ ስምዖንና ዘካርያስ በአስክሬኑ አጠገብ ቆመው ጸሎተ ፍትሃቱን ያደርሱ ጀመር፡፡ ጸሎተ ፍትሃቱንም በጨረሱ ጊዜ መላእክት በቆፈሩት መቃብር ውስጥ ቀበሩዋትና የስምዖንና የዘካርያስ ነፍስ ወደነበረችበት ቦታዋ ተመለሰች፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የኤልሳቤጥን መቃብር በትእምርተ መስቀል አምሳል ደፈነው፡፡ ኤልሳቤጥም ያረፈችበት ዕለት የካቲት ዓሥራ ስድስት ቀን ነው፡፡
ከዚህ በኋላ ዮሐንስን ብቻውን ከበረሃ ውስጥ ትተውት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ጋር ወደ ናዝሬት ለመመለስ ከደመናዋ ላይ ተሣፍሮ ተነሣ፡፡ ያንጊዜም ክብርት እመቤታችን ልጇን እንዲህ አለችው፡- ‹‹ጌታዬና አምላኬ ፈጣሪዬ ሆይ! ስለምን ዮሐንስን ብቻውን ከበረሃ ውስጥ ትተወዋለህ? እንዴትስ ትተነው እንሄዳለን? ወደዚህ ቦታ ይዛው የሸሸችው እናቱ ጥላው ሞታ በመቃብር ውስጥ ተቀብራለች ከእኛ ጋር ይዘነው እንሂድ እንጂ›› አለችው፡፡ ዳግመኛም እመቤታችን እንዲህ አለችው፡- ‹‹ነፍስ ያለወቀ ሕፃን ስላሆነ አራዊት ይበሉታልና ይዘነው መሄድ አለብን›› አለችው፡፡ ጌታችንም ለቅድስት እናቱ እንዲህ በማለት መለሰላት፡- ‹‹በመምህርነት ወጥቶ ለእስራኤል ታይቶ እስከሚያስተምር ድረስ የሰማያዊው አባቴ ፈቃድ በበረሃ ውስጥ ብቻውን እንዲኖር ነው፡፡ አንቺ ብቻውን እንዴት ከበረሃ ይኖራል ትያለሽ፤ አራዊቶች እንዳይጣሉት ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ከእርሱ አይለይም፡፡ በፈለገው ነገር ሁሉ እንዲራዱትና እንዲታዘዙለት መላእክተ ብርሃንን አዝለታለሁ፡፡ ብርሃናዊው መልአክ ገብርኤልም ሰማያዊ ኅብስትን ለምግቡ ያመጣለታል፤ በጠማውም ጊዜ እንደ ወተት የነጣችውን እንደ ወለላ ማርም የጣፈጠችውን ውኃ ከኤዶም ገነት ያመጣለታል፡፡ ይህችንም እርሱ ካለበት ድንጋይ ሥር የምትፈልቀውን ውኃ እንደ እናቱ ጡት ለአፉ የጣፈጠች አደርግለታለሁ፡፡ አንቺ ብቻውን እንዴት በበረሃ ውስጥ ይኖራል ትያለሽ እስከ ዛሬ ድረስም የጠበቅሁት እኔ ነኝ፣ ሌላ ማን ጠበቀው ብለሽ ነው? እኔ አይደለሁምን? ወዳጄ ዮሐንስን ሰማያዊው አባቴ ከዚህ ዓለም ፍጥረት ሁሉ በጣም አብልጦ ይወደዋል፡፡ አባቱ ዘካርያስም በሥጋው ቢሞት በነፍሱ ሕያው ስለሆነ ዮሐንስን ለማጽናናት በአካለ ነፍስ ከእርሱ እንዳይለየው አደርጋለሁ፡፡ እናቱ አልሳቤጥም በሥጋዋ ብትሞት በነፍሷ ሕያዊት ስለሆነች ታጽናናው ዘንድ በነፍሷ በፍጹም ከእርሱ እንዳትለየው አደርጋለሁ፡፡ ዮሐንስን የተሸከመች ማኅፀን ንዕድ፣ ክብርት ስለሆነች በሥጋዋ ውስጥ መጥፎ ሽታ ክፉ መዓዛ አይገኝባት፣ በመቃብሯም ውስጥ ትሎች አይገኙበት፡፡ ድንግል እናቴ ሆይ! አንቺ እኔን ፀንሰሽ ሳለሽ ወደ ኤልሳቤጥ በሄድሽ ጊዜ በእጇ ይዛ ጨብጣ፣ በአፏ በሳመችሽ ጊዜ እንዲህ ብላ ትንቢት ተናግራለች፡፡ ‹አንቺ ከሴቶች ሁሉ ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ፤ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው፤ የጌታዬ እናቱ ወደ እኔ ትመጪ ዘንድ እኔ ምንድነኝ? ከእግዚአብሔር አግኝተው የነገሩሽን ቃል ይደረጋል ብለሽ የተቀበልሽ አንቺ ብፅዕት ነሽ፣ ክብርት ነሽ› ብላ ስላመሰገነችሽ እንኳን ሥጋዋ ሊፈርስ ይቅርና መግነዟም አይለወጥም፤ መቃብሯም አይጠፋም፤ ነፍሷንም ከሥጋዋ ጋር እንድትኖር አደርጋታለሁ፡፡› ይህን የመሰለ ነገር ስለ ወዳጁ ዮሐንስ ለድንግል እናቱ ነግሯት ከጨረሰ በኋላ ዮሐንስን ከበረሃ ውስጥ ትተውት በደመና ላይ ተጭነው ወደ ናዝሬት ተመለሱ፡፡›› | 84 |
| 16 | አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ሰኔ 30-"በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል!" (ሉቃ 1:14)
እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ለቅዱስ ዮሐንስ ዓመታዊ የልደት በዓል አደረሰን!
+ ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ስለጽድቅ ሕይወቱ ሲል ራሱን የሰዋው የየዋሑ ገድለኛ አባት የአቡነ ጌራ ዕረፍት ነው፡፡ ይኸውም ገድለኛውና የዋሕ የሆነ አባ ጌራ፡- በሕንደኬ ካሉ ደሴቶች በአንዲቱ ውስጥ በታላቅ ተጋድሎ የሚኖር ጻዲቅ ነው፡፡ በጽኑ ተጋድሎው ይታወቃልና እግዚአብሔርም የሚለምነውን ሁሉ ይሰማው ነበር፡፡ በጸሎቱ በዚያች አገር ንዳድ፣ አባር ቸነፈር፣ ድርቅ፣ በጠላት መማረክ፣ የደም መፍሰስና የመርከቦች መስጠም ተወገደ፣ የፈለገውንም ሁሉ በጸሎቱ ያገኝ ነበር፡፡
ሰይጣንም ስለዚህ ስለተሰጠው ጸጋ ቀናበትና መልኩን ሰውቆ በፈተና ሊጥለው አሰበ፡፡ በዕንቁ የተሸለመ የነገሥታትን ልብስ በለበሰች መልከ መልካም ሴት አምሳል ተገልጦ ታየው፡፡ እርሷም ብቻዋን ሆና ትንጎራደድ ነበር፡፡ አባ ጌራም ባገኛት ጊዜ ሥራዋን ጠየቃት፡፡ እርሷም እንዲህ አለችው፡- ‹‹የንጉሥ ሰርስባን ልጅ ነኝ፣ እኅቴ ከአባቷ ባሮች ጋር ባመነዘረች ጊዜ ሁለታችንንም ሊገድለን ፈለገ፡፡ ስለዚህ ፈርቼ በሌሊት ወጥቼ ወደዚህ በረሓ መጣሁ፣ ቅዱሱን ሰው አንተን በማግኘቴም ዕድለኛ ነኝ›› አለችው፡፡ አባ ጌራም ‹‹ወደ እኔ የሚመጡ ሰዎች እንዳያዩሽ ወደዚያች የዓለት ዋሻ ሄደሽ ተቀመጪ›› አላት፡፡
እርሷም በሌሊት ከአራዊት የተነሣ እንደፈራ ሰው እየጮኸች መጥታ ‹‹የዱር አራዊት እንዳይበሉኝ ክፈትልኝ›› አለችው፡፡ አባ ጌራም አራዊት በልተዋት እግዚአብሔር በነፍሷ እንዳይጠይቀው ፈርቶ ከፈተላትና ገባች፡፡ ከዚህም በኋላ በጎኑ ተኝታ ደረቱን በማቀፍ ልቡን ወደ ፍቅሯ እስካዘነበለችው ድረስ ነገሯን አለሰለሰችለት፡፡ ያንጊዜም በእርሱ ያደረበት የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ተለየው፣ ከእርሷም ጋር ተኝቶ ኃጢአት እንደሚሠራ ሆነ፡፡ ከስሕተት ስካርም በነቃ ጊዜ በጠላት ሰይጣን ተንኮል ተሸንፎ እንደ በደለ ዐወቀ፡፡ ከዚህም በኋላ ከሰይጣን ተንኮል የተነሣ ያገኘውን ፈተና ሁሉ በሥጋውም ኃጢአት እንደሠራ በጽሑፍ ጽፎ አስቀመጠ፡፡
ከዚህም በኋላ ከደሴቲቱ ተራራ ትልቅ ድንጋይ አንሥቶ እስከሚሞት ድረስ ጭንቅላቱንና ደረቱን በኃይል እየደበደበ ብዙ ጊዜ ሲኖር ከቆየ በኋላ በዚህም ነፍሱ ከሥጋው ተለይታ ወደ ዘላለም ሕይወት በጌታችን ቸርነት ገባች፡፡ ሰዎችም እንደልማዳቸው ከእርሱ ቡራኬን ለመቀበል ሲመጡ አላገኙትም፡፡ በፈለጉትም ጊዜ ተኝቶ አገኙትና ያንቀላፋ መስሏቸው ሊቀሰቅሱት ሲሉ ዐርፎ አገኙት፡፡ ከተሳለሙት በኋላ ገንዘው ቀበሩት፡፡ አሟሟቱም በጠላት ሰይጣን ተንኮል ምክንያት ስለመሆኑ የጻፈውን መልእክት አግኝተው አነበቡት፡፡ ገድሉንም ለሁሉ ተናገሩ፡፡ የዚኽ ገድለኛ ጻድቅ ረድኤት በረከቱ ይደርብንን! በጸሎቱ ይማረን
+ + + + +
መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ፡- ዮሐንስ ማለት ‹‹ፍሥሐ ወሐሴት፣ ርኅራኄ›› ማለት ነው፡፡
የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መንገድ ጠራጊ የሆነው ቅዱስ ዮሐንስ የብሉይ ኪዳን የመጨረሻው የሐዲስ ኪዳን ደግሞ የመጀመሪያው ነቢይ ነው፡፡ ስለ ወላጆቹ ስለ ካህኑ ዘካርያስና ስለ ቅድስት ኤልሳቤጥ በቅዱስ ወንጌል ላይ እንዲህ ተብሎ ተመስክሮላቸዋል፡፡ ‹‹በይሁዳ ንጉሥ በሄሮድስ ዘመን ከአብያ ክፍል የሆነ ዘካርያስ የሚባል አንድ ካህን ነበረ፤ ሚስቱም ከአሮን ልጆች ነበረች፥ ስሟም ኤልሳቤጥ ነበረ። ሁለቱም በጌታ ትእዛዝና ሕግጋት ሁሉ ያለ ነቀፋ እየሄዱ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ።›› ሉቃ 1፡5-6፡፡
እግዚአብሔር ወደ በራክዩ ልጅ ወደ ዘካርያስ ልጅ እንደሚወልድ ይነግረው ዘንድ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤልን ላከው፡፡ መልአኩም በመጀመሪያ በመሠዊያው በስተቀኝ በኩል ተገልጦ ለዘካርያስ ታየው፡፡ ለሰይጣን ቀኝ የለውምና መልአክ ግን ብርሃናዊ የማናዊ ነውና መልአክ እንደሆነ ለማጠየቅ በቀኝ በኩል ተገልጦ ታየው፡፡ አንድም ሰው ሁሉ ወደ የማናዊ ግብር የሚመለስበት ዘመን ደረሰ ሲል በቀኝ በኩል ታየው፡፡ አንድም ሰውን ሁሉ መክሮ አስተምሮ ወደ ቀኝ ወደ መንፈስ ቅዱስ ሥራ የሚመልስ ልጅ ትወልዳለህ ሲለው በቀኝ በኩል ተገልጦ ታየው፡፡ ነገር ግን ዘካርያስ የእርሱም ሆነ የሚስቱ ዕድሜአቸው ስለገፋ የሚስቱን የመፀነሷን ነገር አላምን ቢል መልአኩ ድዳ አድርጎታል፡፡ ዮሐንስም ሲወለድ ‹‹ስሙን ማን እንበለው?›› ሲሉት በጽሑፍ አድርጎ ‹‹ዮሐንስ በሉት›› አላቸው፤ ያንጊዜም አንደበቱ ተፈታለት፡፡
መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ‹‹ዘካርያስ ሆይ፥ ጸሎትህ ተሰምቶልሃልና አትፍራ ሚስትህ ኤልሳቤጥም ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፥ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ። ደስታና ተድላም ይሆንልሃል›› (ሉቃ 1፡13) ባለው ሰዓት አላመነም ነበር፡፡ አሁን ግን የልጁን ስም ‹‹ዮሐንስ›› ብሎ ሲለው ተዘግቶ የነበረው አንደበቱ ተፈቶለታል፡፡ መጥምቁ ዮሐንስ ጌታችንን በዕድሜ በ6 ወር ይበልጠዋል፡፡ ርጉም የሆነ ሄሮድስ መሢሕ ሕፃን ክርስቶስ መወለዱን ሲሰማ መንግሥቴን ይቀማኛል ብሎ በመፍራት በቤቴልሔም ያሉ ሁለት ዓመትና ከዚያ በታች ያሉ 144,000 (መቶ ዐርባ አራት ሺህ) የቤቴልሔም ሕፃናትን በሰይፍ ሲያስገድል ድንግል ማርያም ከልጇ ጋር ወደ ግብፅ ስትሰደድ፣ ቅድስት ኤልሳቤጥ ደግሞ ወደ ሲና በረሃ ሄዳ ልጇን ዮሐንስን ከዚያ ደብቃዋለች፡፡ ከመሄዷ በፊት ግን ከባሏ ከዘካርያስ ጋር ሲሰነባበቱ የሚሆነውንም ሁሉ እርሱ ቀድሞ ያውቅ ነበርና ‹‹ሕፃኑን ልጄን ሲያጡ እኔን ይገድሉኛል፣ አንቺ ግን ወደ በረሃው ይዘሽው ሂጂና በዚያ ሸሽጊው›› ብሎ መክሯታል፡፡ እርሷም ከሄደች በኋላ የርጉም ሄሮድስ ጭፍሮች ዮሐንስን ባጡት ጊዜ ወደ ዘካርያስ መጥተው ‹‹ልጅህን ወዴት አድርሰኸው ነው? ወዴትስ ደበቅኸው? አሁን ከደበቅህበት አምጥተህ ፈጥነህ አስረክበን›› በማለት የፍጥኝ አስረው ካሠቃዩት በኋላ ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ከሚሠዋበት በቤተ መቅደስና በዕቃ ቤት መካከል አንገቱን ቆርጠው ገደሉት፡፡ የዘካርያስም ደም እስከ ሰባት ዓመት ድረስ እየፈላ ደሙ ሲካሰሳቸው ኖረ፡፡
‹‹ቅድስት ኤልሳቤጥም ልጇን ዮሐንስን ይዛ ወደ በረሃ ከገቡ አምስት ዓመት በሆናቸው ጊዜ ዮሐንስ ዕድሜው ሰባት ዓመት ከመንፈቅ ከሆነው በኋላ እናቱ ኤልሳቤጥ ሞተችበትና ብቻውን ከበረሃ ውስጥ ተወችው፡፡ ዮሐንስም በሰፊዋ በረሃ ውስጥ በአራዊቶች መካክል ብቻውን ቀረ፡፡ ለዮሐንስ ግን በእርሱ ላይ ምንም መጥፎ ነገር ሳያደርጉ የቶራና የአንበሳ የነብርም ልጆች እንደ ወንድምና እንደ እኅት ሆኑት፡፡ አራዊቶችም ሁሉ ወዳጅ ሆኑት፡፡ ምግቡም የበረሃ ቅጠል ነው፤ መጠጡም ከተቀመጠባት ድንጋይ ሥር የፈለቀችለት ውኃ ነበረች፡፡ ዮሐንስ ሰውነትን አለምልመው፣ ሥጋን አለስልሰው፣ ገጽንና ፊትን የሚያሳምሩትን ምግቦች አልተመገበም፡፡ የበረሃ ቅጠሎችንም አልተመገበም፡፡ አንቦጣ ከተባለችው ከአንዲት የበረሃ ቅጠልና ከጣዝማ ማር በስተቀር ከሚበሉት ምግቦች ሁሉ ዮሐንስ ኅርምተኛ ሆኖ የተለየ ነበር›› ይላል ቅዱስ ገድሉ፡፡ ነገር ግን ‹‹አንቦጣ›› ተብላ የምትጠራ አንዲት የበረሃ ቅጠልንና የጣዝማ ማርን እየተመገበ ማደጉን ለመግለጽ ብዙ ጊዜ በተለምዶ ‹‹የዮሐንስ ምግቡ የበረሃ አንበጣ ነበር›› ተብሎ የተሳሳተ ነገር ሲነገር ይሰማል፡፡ | 90 |
| 17 | لا يوجد نص... | 87 |
| 18 | ዳግመኛም በዚህች ዕለት ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ሰማያዊ መና ሲመግባቸውና የጌታችንንም ቅዱስ ሥና ደም በሰንበት እያመጣለቸው ያቆርባቸው የነበሩት ሰማዕቱ አቡነ ዓምደ ሚካኤል ፍልሠተ ዐፅማቸው ነው፡፡ ጻድቁ ኅዳር ሦስት በሰማዕትነት ካረፉ በኋላ መጀመሪያ በንጉሥ እስክንድር ዘመነ መንግሥት ወደ አባቶቹ መቃብር ዳግመኛም በንጉሥ ልብነ ድንግል ዘመን በዐረፉ በ40 ዓመታቸው ፈለሰ፡፡ ዐፄ ልብነ ድንግል በነገሠ ጊዜ ዐፅማቸውን አፍልሶ ወደ አትሮንስ ማርያም ወሰደውና በቅዱሳን ነገሥታት መቃብር በክብር
አኖረው፡፡
አቡነ ዓምደ ሚካኤል፡- ትውልዳቸው ወሎ ቦረና ነው፡፡ ወላጆቻቸው ገላውዲዮስና ኤልሳቤጥ ሁለቱም በሃይማኖትና በዓለም ገንዘብ የበለጸጉ ናቸው፡፡ ይህንንም ጻድቅ ልጃቸውን የአርባዕቱ እንስሳ በዓል ዕለት ወለዱትና ስሙን ዓምደ ሚካኤል ብለው ጠሩት፡፡ ለዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ፣ ለዐፄ በእደ ማርያምና ለዐፄ እስክንድር የሠራዊት አለቃ የነበረ ጻድቅ ነው፡፡ በአንድ ዓመቱ ወላጆቹ ወደ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ይዘውት እንደሄዱ ከወላጆቹ ተለይቶ ጠፍቶ ሳይገኝ ቀረ፡፡ መልአክም ከቤተ መቅደስ አግብቶ እየመገበው 3 ቀን አቆይቶታል፡፡ በ3ኛው ቀን ቄሱ ሊያጥን ሲገባ በከርሰ ሐመሩ ውስጥ ሕፃኑን አገኘውና ወስዶ ለወላጆቹ ሰጣቸው፡፡
ባደገም ጊዜ በመመጽወትና አብያተ ክርስቲያናትን በማደስ የሚተጋ ሆነ፡፡ ለድኆችም በቅንነት በመፍረድ በታላቅ ተጋድሎ የሚኖር ሆነ፡፡ ለነገሥታም ገዥ ከሆነ በኋላ በጸሎቱና በበረከቱ በሀገራችን ላይ ሁሉ ሰላም ሆነ፡፡ ጠላቶችም ሁሉ ለነገሥታቱ ተገዝተው ይገብሩ ነበር፡፡ በበጎ ምግባሩ የቀኑ ዐመፀኞችም በክፋ ተነሡበት፡፡ ጻድቁ በመንፈስ አድጎ መንኩሶ በታላቅ ተጋድሎ ሲኖር ነገር ሠሪዎች በሐሰት ወንጅለው ከሰሱት፡፡ ንጉሡም እጅግ ስለሚወደው የራራለት ቢሆንም በነገራቸው ባስጨነቁት ጊዜ ወደ ሩቅ አገር አስሮ አጋዘው፡፡ አባታችንም በግፍ ታስረው ሳሉ በእስር ቤቱ ውስጥ ብርሃን ወረደላቸው፣ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤልም ሰማያዊ መና እያመጣ ይመግባቸው ነበር፡፡ የጌታችንንም ሥና ደም በሰንበት እያመጣለቸው ያቆርባቸው ነበር፡፡ ነገረ ሠሪዎቹ ይገድሏቸው ዘንድ ንጉሡን ለመኑት፡፡ በዓመፃቸውም ብዛት ወደ ፍርድ ሸንጎ አምጥተው ገደሏቸው፡፡
አንድ ጻድቅ መነኩሴ የቅዱስ ዓምደ ሚካኤልን ሥጋ ሦስት ቅዱሳን መላእክት ሲያጥኑ አገኛቸውና ያየውን ለሕዝቡ ተናገረ፡፡ በሌላም ጊዜ የብርሃን ፋና ከሰማይ ሲወርድላቸው ብዙ ቀን የተመለከቱ ብዙ ቅዱሳን ምስክርነታቸውን ሰጡ፡፡ ንጉሡም ይህንን ሁሉ ሲሰማ በአሳቾቹ ልበ ደንዳናነትና ክፋት እጅግ ተጸጽቶ በሞት ቀጣቸው፡፡ ቅዱስ ዓምደ ሚካኤልንም በአባቶች መቃብር በክብር አስቀበራቸው፡፡ ስማቸውንም በበጎ እንጂ በክፋ ማንም እንዳያነሳቸው በአዋጅ አስነገረ፡፡ መታሰቢያም አቆመላቸው፡፡
ከዚህም በኋላ ዐፄ ልብነ ድንግል በነገሠ ጊዜ የአባቱን የበእደ ማርያምን ቃል ኪዳን ሰምቶ ዐፅማቸውን አፍልሶ ወደ አትሮንስ ማርያም ወሰደውና በቅዱሳን ነገሥታት መቃብር በክብር አኖረው፡፡ ሊቀ ብርሃናት መርቆሬዎስ አረጋም ጻድቁ ሲያርፉ በደብረ ሊባኖስ ገዳም የተቀበሩ ቢሆንም ከብዙ ዘመን በኋላ ዐፅማቸውን አፍልሰው በተድባበ ማርያም እንደቀበሯቸው ጽፈዋል፡፡ የሰማዕቱ የአቡነ ዓምደ ሚካኤል ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡ | 84 |
| 19 | አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ሰኔ 29-ንግሥናን ንቀው በመተው ሀብታቸውንም ሁሉ ሸጠው ለድኆች በመመጽወት መንነው ገዳም ገብተው ብዙ የተጋደሉት ኢትዮጵያዊው ንጉሥ አቡነ ቴዎድሮስ ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ ዳግመኛም በዚህች ዕለት ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ሰማያዊ መና ሲመግባቸውና የጌታችንንም ቅዱስ ሥና ደም በሰንበት እያመጣለቸው ያቆርባቸው የነበሩት ሰማዕቱ አቡነ ዓምደ ሚካኤል ፍልሠተ ዐፅማቸው ነው፡፡
+ በድንግልና ሆኖ ሲያገለግል የነበረውና በንግሥናም አገርን ሲመራ የመራውና የእመቤታችን ሥዕል በሰው አንበት ያናገረችው የሮሜው ጻድቅ ንጉሥ ቅዱስ ማርቆስ ዕረፍቱ ነው፡፡
+ አባ አብሲዳ፣ አባ ኮቶሎስ፣ አባ አርድማ፣ አባ ሙሴ፣ አባ እሴይ፣ አባ ኒኮላስ እና አባ ብሶይ የተባሉ ከቆና ገዳም የተገኙ ሰባት መስተጋድላን ቅዱሳን አባቶች በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡
+ ቅዱሳን አባ ብሶይና አባ ሖር ከእናታቸው ከቅድስት ይድራ ጋር በሰማዕት ዐረፉ፡፡ ከአንጾኪያ ሠራዊት ውስጥ የሆነ ሖርሳም አብሯቸው ሰማዕት ሆነ፡፡
+ + + + +
አቡነ ቴዎድሮስ፡- የኢትዮጵያው ንጉሡ የዐፄ ዳዊት ልጅ ናቸው፡፡ ከልጅነታቸው ጀምሮ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት በሚገባ ጠንቅቀው የተማሩ ናቸው፡፡ ለድኆች በመመጽወትና በበጎ ምግባር ኖረዋል፡፡ በመጨረሻም ንግሥናን ንቀው በመተው ያላቸውንም ሀብት ሁሉ ሸጠው ለድሆች በመመጽወት መንነው ገዳም የገቡ ታላቅ አባት ናቸው፡፡
ወደ ኢየሩሳሌምም ለመሄድ አስበው አባ ማርቆስን ሲያማክሯቸው በመንፈስ ቅዱስ ያውቁ ነበርና ክፍልህ አይደለም አሏቸው፡፡ ጻድቁ ባረፉ ጊዜ በክረምት አስክሬናቸውን ተሸክመው ወንዝ ሊያቋርጡ ሲሉ ወንዙ በተአምራት ለሁለት ተከፍሎላቸው በሰላም ተሻግረዋል፡፡ በተቀበሩበት ቦታም ፈዋሽ ጸበል ፈልቋል፡፡ ጻድቁ አቡነ ቴዎድሮስ በስማቸው የተሰየመው ታቦትና ቅዱስ ገድላቸው በደብረ ዳሞ ይገኛል፡፡ በስማቸው የተሰየመው ታቦትና ቅዱስ ገድላቸው በደብረ ዳሞ ይገኛል፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡
+ + + + +
ሰባቱ ሰማዕታት መስተጋድላን አባቶች፡- እነዚህም ቅዱሳን አባቶች አባ አብሲዳ፣ አባ ኮቶሎስ፣ አባ አርድማ፣ አባ ሙሴ፣ አባ እሴይ፣ አባ ኒኮላስ እና አባ ብሶይ ከቆና ገዳም የተገኙ ሰማዕታት ናቸው፡፡ በመጀመሪያ የታዘዘ መልአክ ተገለጠላቸውና በጌታችን ስም ሰማዕት እንዲሆኑ አዘዛቸው፡፡ ያን ጊዜም ወደ ከሃዲው መኮንን ዘንድ ሄደው በፊቱ የጌታችንን አምላክነት መሰከሩ፡፡ መኮንኑም ሀገራቸውን ከጠየቃቸው በኋላ ጽኑ በሆኑ ልዩ ልዩ ማሠቃያዎች አሠቃያቸው፡፡ በአንገታቸውም ላይ ከባድ ድንጊዮችን አንጠልጥሎ አሠራቸው፡፡ ጌታችንም በእሥር ቤት ሳሉ ተገልጦላቸው አጽናንቶ ቃልኪዳን ገባላቸው፡፡
ከዚህም በኋላ መኮንኑ ወደ እስክንድርያ ላካቸው፡፡ በዚያም ከሃድያኑ ብዙ አሠቃዩአቸው፡፡ ዝፍጥና የብረት ድኝ በተሞሉ የብረት ምጣዶች ውስጥ ከጨመሯቸው በኋላ ነበልባሉ አስከ 20 ክንድ ከፍ ከፍ እስኪል ድረስ ከታች እሳት አነደዱባቸው፡፡ ዳግመኛም ከምጣዶቹ ውስጥ አውጥተው ከምድጃ እሳት ውስጥ ከተቷቸው፡፡ ነገር ግን ጌታችን አሁንም ተገልጦ ያለ ምንም ጉዳት አዳናቸው፡፡ ሰማዕታቱም ዳግመኛ ወደ መኮንኑ ቀርበው በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ታመኑ፡፡ ይህንንም ድንቅ ሥራ ያዩ 130 ሰዎች በጌታችን አምነው እነርሱም መስክረው ሰማዕት ሆኑ፡፡
ከዚህም በኋላ መኮንኑ ቅዱሳኑን አስጨናቂ የሆኑ ሥቃዮችን አሠቃያቸው፡፡ አጵሎን የሚሉትን ጣዖትም አምጥቶ በፊታቸው በወንበር ላይ አስቀምጦ እንዲሰግዱለት አዘዛቸው፡፡ ቅዱሳኑ ግን በእግሮቻቸው ቢረግጡት ጣዖቱ ወድቆ ተሰበረ፡፡ መኮንኑም ይህንን ሲያይ ተቆጥቶ የቅዱሳኑንም እግሮቻቸውን በሰይፍ አስቆረጣቸው፡፡ የከበረ ቀሲስ አብሲዳንን ግን ራሱን በሰይፍ አስቆረጠውና የሰማዕትነት ፍጻሜው ሆነ፡፡ ቅዱስ ኮቶሎስንም በእሳት አቃጠለው፡፡ የቀሩትን አምስቱንም ከብዙ ሥቃይ በኋላ ራስ ራሶቻቸውን አሰይፍ አስቆረጣቸውና ሁሉም ሰማዕትነታቸውን በድል ፈጽመው የድል አክሊልን በመንግሥተ ሰማያት ተቀዳጁ፡፡ የእነዚኽ የከበሩ ሰማዕታት ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡
+ + + + +
ቅዱሳን ሰማዕታት አባ ብሶይ፣ አባ ሖር፣ ቅዱስ ሖርሳ እና እናታቸው ቅድስት ይድራ፡- እነዚህም ቅዱሳን በእስክንድርያው ከሃዲ መኮንን ፊት የጌታችንን አምላክነት በመሰከሩ ጊዜ መኮንኑ አባ ብሶይን ይዞ ቀኝ እጁን አሥሮ በከተማዎች መካከል በበሬዎች አስጎተተው፡፡ የተሳሉ ብረቶችንም በእሳት አግሎ ሰውነቱን በመውጋት አቃጠለው፡፡ ግራ እጁንም ቆረጠው፡፡ ዳግመኛም እርሳስ አግሎ በአፉ ውስጥ ጨመረ፡፡ መርዛማ እባቦችና ጊንጦች ወደተሞሉበት ቦታም ወስዶ ጣለው፣ ነገር ግን እነርሱ አባ ብሶይን አልነኩትም፡፡
ከዚህም በኋላ በብረት በትሮች በኃይል በደበደቡት ጊዜ አባ ብሶይ ወደጌታችን ጪኸ፡፡ ጌታችንም አጸናውና እንደቀድሞው ጤነኛ አድርጎ አስነሣው፡፡ እናቱም ወደ እርሱ መጥታ ባረጋጋችው ጊዜ መኮንኑ ያዛትና እርሷንም አሠቃያት፡፡ በእሳት በጋሉ ብረቶች ጎኖቿን ወግቶና አቃጠላት፡፡ እርሷም በዚህ መከራ ውስጥ ሆና ትዘምር ነበር፡፡ ሰማዕትነቷንም ፈጽማ ነፍሷን አሳልፋ ለእግዚአብሔር ሰጠች፡፡
ቅዱስ አባ ሖርንም ከቅባትና ከተቀመመ ነዳጅ ጋር ቀላቅለው በብረት ምጣድ ውስጥ አበሰሉት፡፡ እርሱንም ጌታችን በጽንቶታልና ያለ ሕማም ሆኖ ፈጣሪውን ሲያመሰግን መኮንኑ ሰምቶ በመደንገጥ እጅግ አድርጎ አደነቀ፡፡ ንጉሡ ግን ተቆጥቶና ተናዶ አባ ሖር በብረት ምጣዱ ላይ ሆኖ በእሳት እንደተጣደ በጦር ወጋው፡፡ ሰማዕትነቱንም በዚሁ ፈጸመ፡፡ ወንድሙን አባ ብሶይንም ብዙ ካሠቃዩት በኋላ ራሱን በሰይፍ ሰይፈውት ሰማዕትነቱን በድል ፈጸመ፡፡ ሁለቱም የድል አክሊልን ተቀዳጁ፡፡ ከእነርሱም ጋር ከአንጾኪያ ንጉሥ ሠራዊት ውስጥ የሆነ አባ ሖርሳም በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡ የሰማዕታቱ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡
+ + + + +
የሮሜው ጻድቁ ንጉሥ ቅዱስ ማርቆስ፡- ይኽም ቅዱስ በድንግል አምስት ዓመት ነገሠ፡፡ ሕዝቡንም እግዚአብሔርን በመፍራትና በቅን ፍርድ ጠበቀ፡፡ ሕዝቡም እርሱን ከመውደዳቸው የተነሣ ሚስት እንዲያገባ መኳንንቱ አስገደዱት፡፡ እርሱ ግን በሌሊት ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ከእመቤታችን ሥዕል ፊት ሰግዶ ጸለየ፡፡ ‹‹እመቤቴ ሆይ! ለአንቺና ለማይሻር ንጉሥ ልጅሽ እገዛ ዘንድ ወደምሄድበት ምሪኝ›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹ወደ ቶርማቅ ተራራ ሂድ፣ እግዚአብሔርም ከአንተ ጋር ይኑር›› አለችው፡፡ እርሱም በሌሊት ወጥቶ በመሄድ ወደ ባሕር ወደብ ደረሰ፡፡ በመርከብም ተሻግሮ ወደ ቆርማቅ ተራራ በደረሰ ጊዜ ቦታውን ደረቅ ሆኖ አገኘው፡፡ በዚያም ከአጋንንት ጋር እየተጋደለ በውስጡ 60 ዓመት ኖረ፡፡ ባረፈም ጊዜ ቅዱሳን መላእክት በታላቅ ክብር ቀበሩት፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡
+ + + + + | 91 |
| 20 | لا يوجد نص... | 104 |
