es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 553 suscriptores, ocupando la posición 8 395 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 164 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 553 suscriptores.

Según los últimos datos del 22 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 5, y en las últimas 24 horas de 1, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 25.99%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 15.38% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 043 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 393 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 9.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 23 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 553
Suscriptores
+124 horas
+47 días
+530 días
Archivo de publicaciones
በበጀት ዓመቱ በፕሮጀክቶች ላይ የተሻለ አፈጻፀም ተመዝግቧል ........///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የ2017 በጀት ዓመት የፕሮጀክቶች አፈፃፀም የተሻለ እንደነበር የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ገለፁ። ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በተቋሙ የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀምና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድን በተመለከተ ለመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ በሰጡበት ወቅት እንደገለፁቱ እያደገ ለመጣው የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠትና በመላ ሀገሪቱ የኃይል ተደራሽነትን ለማሳደግ የኃይል ማመንጫ፣ ከፍተኛ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን እና የማስተላለፊያ መስመሮችን በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ በበጀት ዓመቱ አራት የኃይል ማመንጫ እና 20 የማከፋፈያ ጣቢያ፣ ማስተላለፊያ መስመርና ተያያዥ ፕሮጀክቶች በግንባታ ላይ እንደነበሩ ገልፀዋል። የበጀት ዓመቱ አፈጻፀማቸውም የተሻለ እንደነበር ኢንጂነር አሸብር ጠቁመዋል፡፡ በዚህም በበጀት ዓመቱ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ፕሮጀክት ለማጠናቀቅ በተደረገው ርብርብ ለምረቃ ዝግጁ መሆኑን  በመጥቀስ አሁን ላይም በዘጠኝ ተርባይኖች 3 ሺህ 400 ሜጋ ዋት ኃይል እያመነጨ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በተመሳሳይ በአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የጀት ዓመቱን ዕቅድ በማሳካት በ12 የንፋስ ተርባይኖች 41 ሜጋ ዋት እያመነጨ በመሆኑ በተያዘው በጀት ዓመት ለምረቃ እንደሚበቃም ገልፀዋል፡፡ የአይሻ የንፋስና የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች የፋይናንስ ተግዳሮት ገጥሟቸው እንደነበር ያስታወሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ችግሩን በመንግስት እገዛና በተቋሙ ጥረት በማቃለል የግንባታ ሥራቸው በተሻለ ደረጃ ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡ የፕሮጀክቶቹን የግንባታ አፈጻፀም ለማሻሻል ተቋሙ ለአይሻና ለኮይሻ ጨምሮ ለማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ከራሱ ፋይናንስ 261 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዶላር ክፍያ መፈፀሙን በመግለጫቸው አመልክተዋል፡፡ በዚህም የኮይሻ ፕሮጀክት 71 ነጥብ 4 በመቶ እንዲሁም የአይሻ ከ85 በመቶ በላይ እንዲደርስ ማስቻሉን በመግለፅ ፕሮጀክቶቹ በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ  ከፋይናንስ ጋር በተያያዘ የተስተዋለውን ችግር በዘላቂነት  ለመፍታት እየተሰራ ስለመሆኑም አስታውቀዋል። በበጀት ዓመቱ ከኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ባለፈ የኃይል ተደራሽነትን የሚያሳድጉ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች የግንባታ ሥራ ትኩረት ተሰጥቷቸው ሲከናወኑ እንደነበር አስረድተዋል፡፡ እንደ ኢንጂነር አሸብር ገለፃ በበጀት ዓመቱ በግንባታ ላይ ከነበሩ የማከፋፈያ ጣቢያ፣ ማስተላለፊያ መስመርና መሰል ፕሮጀክቶች መካከል የአምስት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ማብቃት ተችሏል፡፡ ከተጠናቀቁት መካከልም የደብረ ታቦርና በቆጂ ማከፋፈያ ጣቢያዎች፣ የለገጣፎ-አላማጣ-ኮምቦልቻ ማስተላለፊያ መስመር እና የጫካ ፕሮጀክት የኃይል አቅርቦት ተጠቃሾች ናቸው፡፡ የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን እና የደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክቶችን አፈፃፀም በበጀት ዓመቱ  ከ75 በመቶ በላይ ለማድረስ ታቅዶ በቅደም ተከተል 79 እና ከ80 በመቶ በላይ ማድረስ መቻሉንም አመልክተዋል፡፡ በኃይል ልማት ዘርፉ የሚከናወኑ ሥራዎች ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት የሚኖራቸውን ሚና በመገንዘብ ተቋሙ በፕሮጀክት አስተዳደር ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሆነና በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 01 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ ከኃይል ሽያጭና ገቢ ጋር በተያያዘ ያነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች 📌 በ2017 በጀት ዓመት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገራት ከቀረበ የኃይል ሽያጭ እንዲሁም ከተለያዩ የገቢ ምንጮች 75 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ገቢ ተገኝቷል። 📌 ከዚህ ውስጥ 74 ነጥብ 05 ቢሊየን ብሩ  ከኃይል ሽያጭ 1 ነጥብ 41 ቢሊየን ብሩ ደግሞ ከተጓዳኝ አገልግሎቶች የተገኘ ነው። 📌 ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭ ከተገኘው ገቢ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 35 በመቶ፣ የዳታ ማይኒንግ 39 በመቶ እንዲሁም የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች የ4 በመቶ ድርሻ አላቸው። 📌ለውጭ ሀገራት ከቀረበው የኃይል ሽያጭ የተገኘው ገቢ የኬኒያ የ15 በመቶ እንዲሁም የጅቡቲ  5 በመቶ ድርሻ ያለው ነው ። 📌በበጀት ዓመቱ ለደንበኞች በአጠቃላይ 25 ሺህ 180 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ተሽጧል። 📌ከዚህ ውስጥ 93 በመቶ ለሀገር ውስጥ እንዲሁም 7 በመቶ ለውጭ ሀገራት የቀረበ ነው። ይህም ተቋሙ ለሀገር ውስጥ ፍጆታ ቅድሚያ እየተሰጠ ለመሆኑ ማሳያ ነው። 📌ከሽያጭ ከቀረበው ኃይል ውስጥ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 60 በመቶ፣ የዳታ ማይኒንግ 27 በመቶ፣  ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች 6 በመቶ ፣ ለኬኒያ የ5 በመቶ እንዲሁም ለጅቡቲ  2 በመቶ የቀረበ ነው። 📌የተቋሙ ገቢ ከጊዜ ወደ ጊዜ ዕድገት እያሳየ ነው።  ለአብነትም በ2015 በጀት ዓመት ከነበረበት 22 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በ2017 በጀት ዓመት 75 ነጥብ 4 ቢሊዮን ደርሷል። 📌የተቋሙ ገቢ እያደገ በመሄዱ ለፕሮጀክቶች የሚያስፈልጉ ወጭወችን በራስ አቅም መሸፈን ተጀምሯል። በዚህም በበጀት ዓመቱ 261 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዶላር በራስ አቅም ለፕሮጀክቶች ውሏል። 📌 በበጀት ዓመቱ ከኤሌክትሪክ የኃይል ሽያጭ 338 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ተገኝቷል። ይህም በ2016 በጀት ዓመት ከተገኘው የ140 ሚሊዮን ዶላር ጋር ሲነፃፀር 135 በመቶ ብልጫ ያለው ነው። 📌በበጀት ዓመቱ ለተገኘው ገቢ እና የውጭ ምንዛራ አፈፃፀም ዕድገት ምክንያቶች:- 📌 የታሪፍ ማሻሻያ መደረጉ፣ 📌የዳታ ማይኒንግና የውጭ የኃይል ሽያጭ ገቢ ማደጉ 📌 በሀገር ውስጥ ለዳታ ማይኒንግ ኃይል በዶላር መሸጡ የ2018 በጀት ዓመት ገቢ ዕቅድ በተመለከተ 📌ተቋሙ በ2018 በጀት ዓመት  ከ109 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለማግኘት አቅዷል 📌በተያዘው የበጀት ዓመት ከውጭ ምንዛሪ 420 ሚሊዮን ዶላር  ለማግኘት ዕቅድ ይዟል ፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 01 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

‎ተቋሙ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት  ከ29 ሺ ጊጋ ዋት ስዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል ‎......///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት 29 ሺ 480 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማምረቱን አስታወቀ። ‎ ‎ተቋሙ በ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ዙሪያ ለመገናኛ ብዙኃን በስካይ ላይት ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጠ ነው። ‎ ‎የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ መግለጫውን በሰጡበት ወቅት እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ 25 ሺ 423 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማምረት ታቅዶ 29 ሺ 480 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማምረት ተችሏል። ‎ ‎ይህም ከዓመታዊ ዕቅዱ የ16 በመቶ ወይም 4 ሺ 56 ጊጋ ዋት ሰዓት እንዲሁም በ2016 በጀት ዓመት ከተመረተው 20 ሺ 596 ጊጋ ዋት ሰዓት የ43 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑን አብራርተዋል። ‎ ‎እንደ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ በበጀት ዓመቱ ከመነጨው ውስጥ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት 9 ሺ 798 ጊጋ ዋት ስዓት ወይም የ33 ነጥብ 2 በመቶ እንዲሁም የጊቤ ሦስት የኃይል ማመንጫ ጣቢያ 7 ሺ 148 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም የ24 ነጥብ 2 በመቶ በማመንጨት ከፍተኛ ድርሻ ነበራቸው። ‎ ‎በበጀት ዓመቱ ከመነጨው ኃይል 28 ሺ 682 ጊጋ ዋት ሰዓቱ ወይም 97 ነጥብ 3 በመቶ ከውኃ እንዲሁም 789 ጊጋ ዋት ሰዓቱ  ወይም 2 ነጥብ 7 በመቶ ከንፋስ የተገኘ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡  ‎ ‎የህዳሴ ግድብ እና የአሰላ ንፋስ የተወሰኑ ተርባይኖች ወደ ኦፕሬሽን መግባት፣ የባለሙያዎችን አቅም በማሳደግ ጠንካራና ቀጣይነት ያላቸው የጥገና ሥራዎች መከናወን፣ የመለዋወጫ ዕቃ አቅርቦቱ መሻሻል ለዕቅድ አፈጻጸሙ ከፍ ማለት በምክንያትነት አንስተዋል። ‎ ‎ተቋሙ በበጀት ዓመቱ ያስመዘገበውን ስኬት እንደመነሻ በመጠቀም በቀጣይ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ዓለም አቀፍ እውቅና ካላቸው የሲስተም ኦፕሬተሮች ጋር በጥገናና ኦፕሬሽን ሥራዎች ላይ አብሮ በመስራት፣ የማመንጫ ጣቢያዎችን አቅም በማሻሻልና በማዘመን እንዲሁም የክትትልና ድጋፍ ሥርዓቱን በማጠናከር እንደሚሰራም ገልጸዋል። ‎ ‎ህዳሴን እና አሰላ ኃይል ማመንጫዎችን ሙሉ በሙሉ ወደ ኦፕሬሽን በማስገባት በ2018 በጀት ዓመት 38 ሺ 124 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማምረት መታቀዱን ተናግረዋል፡፡  💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 01 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የተቋሙ ለመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጠ ነው ....///.... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተቋሙ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ዙሪያ ለመገናኛ ብዙኃ
የተቋሙ ለመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጠ ነው ....///.... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተቋሙ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ዙሪያ ለመገናኛ ብዙኃን በስካይ ላይት ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጠ ይገኛል። መግለጫውን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እየሰጡ ነው። ጋዜጣዊ መግለጫው በ2017 በጀት ዓመት የኃይል ሽያጭና የገቢ አሰባሰብ፣ በኃይል ማመንጨት የኦፕሬሽን ሥራ አፈፃፀም፣ በማመንጫ፣ ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክቶች አፈፃፀም እንዲሁም በ2018 ዋና ዋና ዕቅዶች ላይ ትኩረት ያደርጋል። እኛም በጋዜጣዊ መግለጫው የሚነሱ ሀሳቦችን እየተከታተልን በሁሉም የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን የምናደርሳችሁ ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 01 ቀን 2017 ዓ.ም

የችግኝ ተከላ መርሀ ግብሩ ለኃይል ማመንጫ ግድቦች ደህንነት መጠበቅ ሚናው የጎላ ነው .....///..... የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የተቋሙን የኃይል ማመንጫ ግድቦችን ደህንነት ለማስጠበቅ የጎላ ሚና እንዳለው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፓወር ግሪድ ኦፕሬሽን መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ዛሬ የችግኝ ተከላ ሲያከናውኑ የመምሪያው ዳይሬክተር ኢንጂነር ሚኪያስ ወንድሙ እንደገለጹት በየዓመቱ እየተከናወነ ያለው የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ግድቦችን ከደለል በመከላከል ደህንነታቸውን ለማስጠበቅ የሚያስችል ነው። መርሀ ግብሩ ወቅቱን የጠበቀ ዝናብ እንዲኖር በማድረግ ተቋሙ የታዳሽ ኃይል አማራጮችን በመጠቀም አስተማማኝና ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይልን ለማቅረብ የያዘውን ተልዕኮ ለማሳካት ጉልህ አበርክቶ እንዳለው ገልጸዋል፡፡ የመምሪያው ሠራተኞች የተከሏቸውን ችግኞች በእኔነት ስሜት በመንከባከብ የመጽደቅ ምጣኔያቸውን ለማሳደግ መስራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል። በችግኝ ተከላው ላይ የተገኙት የቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሱራፌል ቢያብል በበኩላቸው በወረዳው በሚገኘው የተቋሙ ግቢ ውስጥ ችግኞች በመተከላቸውና ወረዳውም ተሳታፊ በመሆኑ ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ ‎መርሀ ግብሩ አካባቢውን ፅዱና አረንጓዴ ከማድረጉ በተጨማሪ እየተተከሉ የሚገኙ ችግኞች ለምግብነት የሚውሉ በመሆኑ የምግብ ዋስትናዋን ያረጋገጠች ሀገር ለትውልድ ለማስተላለፍ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ብለዋል። ‎በቀጣይም በአረንጓዴ ልማት አሻራ መርሀ ግብሩና በሌሎች ጉዳዮች አስተዳደሩ ከተቋሙ ጋር በትብብር እንደሚሰራ አረጋግጠዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 29 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

በበጀት ዓመቱ የሴቶችን የአመራር ሰጪነት ሚና ለማሳደግ እንደሚሰራ ተገለፀ .......///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በበጀት ዓመቱ የሴቶችን የአመራር ሰጪነት ሚና ለማሳደግ እንደሚሰራ አስታወቀ፡፡ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ከፓዎር አካዳሚ ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን የምክክር መድረክ ሲከፍቱ እንደተናገሩት የሴቶችን የአመራር ሰጪነት ሚና የማሳደግ ሥራ በአመራሩ ትኩረት ተሰጥቶታል፡፡ ሴቶች በባለሙያነትም ሆነ በኃላፊነት በተመደቡበት ቦታ ሁሉ የተሰጣቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ራሳቸውን ማዘጋጀት አለባቸው ብለዋል። በመድረኩ ላይ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢትዮ ፓዎር አካዳሚ ዳይሬክተር ወንድወሰን ካሳ ( ዶ/ር) የተቋሙን የሴቶች አቅም እና የአመራር ሰጭነት ሚና ለማሳደግ በሚያስችሉ ሀገራዊ እና ዓለምቀፋዊ አሰራሮች ላይ ያተኮረ የመወያያ ጽሁፍ አቅርበዋል፡፡  ምንም እንኳን ሴቶች በአመራር ሰጭነት እና በተቋማዊ የሥራ አፈፃፀም ክንውን ጉልህ ድርሻ ቢኖራቸውም በአብዛኛዎቹ የአፍሪካ ሀገራት ተሳትፏቸው አነስተኛ መሆኑ በቀረበው ጽሁፍ ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሴቶችን ተሳታፊ የሚያደረግ ፖሊሲ እና የአሰራር ማዕቀፎችን ቀርፆ ቢንቀሳቀስም ተሳትፎአቸው ከ18 በመቶ እንዳልዘለለ ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ በተቋሙ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ በበኩላቸው ሴቶችን ለማብቃት እና ተሳትፏቸውን ለማሳደግ የተቋሙ የሥራ መሪዎች ትኩረት እንዲሰጡ ጠይቀዋል፡፡   ሴቶችም ተጠቃሚነታቸውን እና ተሳትፎኣቸውን ለማሳደግ የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በመድረኩ ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች የተውጣጡ መካከለኛ እና የበላይ አመራሮች የተሳተፉ ሲሆን ሴቶች ለራሳቸው እና ሌሎች ለሴቶች የሚሰጡት የተሳሳተ ግምት እንዲሁም ሴቶችን ማዕከል ያላደረጉ ፖሊሲ እና የሥራ አካባቢዎች እንዲስተካከሉ፤  ለሴቶች የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች በልዩ ሁኔታ እንዲዘጋጁ፣ የሴቶችን ተጠቃሚነት እና አካታችነት የሚያረጋግጡ አስራሮች ተግባራዊ እንዲደረጉ ጠይቀዋል፡፡‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 29 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የግድቡ መጠናቀቅ ባለመጨረስ የባሕል ልምምድ ላይ የተሰነዘረ መዶሻ ነው ‎....///..... ‎የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ ለምርቃት ዝግጁ መሆን ትልልቅ ፕሮጀክቶችን ጀምሮ ያለመጨረስ የባሕል ልምምድ ላይ የተሰነዘረ መዶሻ መሆኑን የአፍሪካ ሥራ አመራር አካዳሚ ፕሬዝዳንት ዛዲግ አብርሃ ተናገሩ። ‎ ‎ፕሬዚደንቱ ይህን የተናገሩት ለሕዳሴ ግድብ ምክር ቤት ከፍተኛ አመራሮች እና ባለሙያዎች  በሰጡት ስልጠና ላይ ነው። ‎ ‎እንደ አቶ ዛዲግ ገለጻ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ፉክክርን ወደ ትብብር በመቀየር ትልልቅ ፕሮጀክቶችን ጀምሮ የመፈጸም ሀገራዊ መሰረት የተጣለበት እንዲሁም ብሔራዊ ማንነታችንንና የፍላጎታችንን አዋጅ የተነገረበት ነጋሪት ጋዜጣ ነው። ‎ ‎የግድብ ግንባታው የመሰረት ድንጋይ ሲቀመጥ ቦንድ የገዛውና ገንዘብ የለገሰው ሕዝብ በወቅቱ ይታየው የነበረው የመሰረት ድንጋይ ሳይሆን የመነጨ የኤሌክትሪክ ኃይል እና ብርሃን ነበር ብለዋል። ‎ ‎ሕዝቡ ከመንግስት ጋር በመተባበር በጨለማ እየኖረ በቅርብ ላላየው ብርሃን ታጋይ ሆኖ የዘመኑ አደዋ የሆነውን የሕዳሴ ግድብ ግንባታን የማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ እንዲደርስ ማድረጉን ገልጸዋል። ‎ ‎የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ መጠናቀቅ የአባይ ምንጭ የነበረችዋን ኢትዮጵያ 5 ሺ 150 ሜጋ ዋት ኃይል በማመንጨት የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል እንድትሆን መደላድል የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል። ‎ ‎እንደ አቶ ዛዲግ ገለፃ ግድቡ አፍሪካ ያላትን ፀጋ በራሷ ልጆች ዕውቀት፣ ጉልበትና ገንዘብ ወደ ሀብት በመቀየር መልማት እንደምትችል ለዓለም ያሳየ የአደባባይ ትዕምርት ነው። ‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 29 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ....///.... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ Junior Electrical Engineer እና በ Junior Mechanical Engineer የስራ መደቦች ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ሚያዚያ 09 ቀን 2017 ዓ.ም  የውጭ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረት ከላይ ስማችሁ የተገለጸ አመልካቾች በJunior Electrical Engineer ነሐሴ 06 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት  በJunior Mechanical Engineer ነሐሴ 07 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ  ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በዋናው መ/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 28 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ ስርቆት የፈፀሙ አካላት በፅኑ እስራት ተቀጡ ….///…. ከእንጦጦ ፓርክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የኤሌክትሪክ ገመዶችን በመቁረጥ የሰረቁ ተከሳሾች እስከ 23 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት መቀጣታቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገለፀ፡፡ መልካሙ ማቴዎስ፣ ቢኒያም ካሳሁን፣ ደረጄ ተሰማ፣ ቶፊቅ ዓለሙ፣ አማኑኤል አቡ፣ አስመላሽ ትዕግስቱ እና ዓለሙ ተመስገን የተባሉ ተከሳሾች የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት ጥቅምት 4 ቀን 2016 ዓ.ም በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ልዩ ቦታው እንጦጦ ፓርክ ውስጥ ነው። ተከሳሾች አባሪ ተባባሪ በመሆን ለእንጦጦ ፓርክ አገልግሎት እንዲውል የተዘረጋ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ገመድ ቆርጠው በኮድ1 ላዳ ተሽከርካሪ ጭነው ለመውሰድ ሲሉ በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ ሲካሄድባቸው ቆይቷል፡፡ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ያጠናቀረውን የምርመራ መዝገብ አቃቤህግ  ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ልዩ ልዩ የወንጀል ጉዳዮች ችሎት አቅርቧል፡፡ ፖሊስ በምርመራ መዝገቡ ተከሳሾቹ በተለያዩ ጊዜያት በሌሊት እንጦጦ ፓርክ ግቢ ውስጥ በመግባት የተዘረጉ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ገመዶችን እየቆረጡ በተሽከርካሪ በመጫን ሰርቀው በመውሰድና ሸጠው በመከፋፈል ተግባር መሰማራታቸውን ገልጿል፡፡ ፍርድ ቤቱም እንደ ወንጀሉ አፈፃፀምና ተሳትፏቸው መጠን ተከሳሾችን ያስተምራል፣ ሌሎች ወንጀል ፈፃሚዎችን ያስጠነቅቃል ሲል ከ6 ዓመት ከ9 ወር እስከ 23 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ የፍርድ ውሳኔ ሰጥቶባቸዋል። የመረጃ ምንጫችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ነው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 28 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ኃይል ሳይቋረጥ ሲከናወን የቆየው የኮንዳክተር ገመድ ቅየራ ሥራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቀቀ ….//…. በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ተከስቶ በነበረው የፀጥታ ችግር ሳቢያ ጉዳት የደረሰበትን የኮምቦልቻ- አላማጣ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ ሁለተኛ ሰርኪዩት መስመር ኃይል ሳይቋረጥ በአዲስ የኮንዳክተር ገመድ የመቀየር ሥራ ሙሉ በመሉ መጠናቀቁን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽን ቢዝነስ አስታወቀ። በትራንስሚሽን ቢዝነስ የፕሮጀክት ማኔጂመንት 1 ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ ሙሉ ብርሃን እንዳስታወቁት 114 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው ከኮምቦልቻ- አላማጣ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ሁለተኛ ሰርኪዩት የኮንዳክተር ሽቦ ዝርጋታ ሥራ ተጠናቆ በዛሬው ዕለት አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። የመስመሩ መጠናቀቅ በኮምቦልቻ እና አላማጣ እንዲሁም አጎራባች ከተሞች በኤሌክትሪክ መቋረጥ ሳቢያ ሊፈጠር የሚችለውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ለማስቀረት የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ብለዋል፡፡ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታው ከ2013 ዓ.ም በፊት ተጠናቆ ለፍተሻና ሙከራ ሥራ ዝግጁ እንደነበር ያስታወሱት ሥራ አስኪያጁ በወቅቱ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በነበረው ጦርነት ምክንያት መስመሩ መጎዳቱን ገልፀዋል፡፡ እንደ አቶ አሸናፊ ገለፃ ከዚህ በፊት ከለገጣፎ- ኮምቦልቻ 61 ኪሎ ሜትር የኃይል ማሰተላለፊያ መስመር የኮንዳክተር ገመድ ቅየራ ሥራ ተጠናቆ ለህብረተሰቡ ያልተቆራረጠ ኃይል ማቅረብ መጀመሩንም አስታውሰዋል። ከለገጣፎ- ኮምቦልቻ በተከናወነው የኮንዳክተር ገመድ ቅየራ ሥራ ከመስመሩ ኃይል ለሚያገኙ አካባቢዎች እና ለለሚ ሲሚንቶ ፋብሪካ እንዲሁም ለደብረ-ብርሃን ኢንዱስትሪ ዞን አስተማማኝ ኤሌክትሪክ ለማቅረብ ማስቻሉንም ነው የጠቀሱት። በአንድ ዓመት ውስጥ የተጠናቀቀው የኮንዳክተር ገመድ ቅየራ ሥራ የግሪድ ሥርዓቱን ከማረጋጋት ባሻገር ተጨማሪ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ማስቻሉንም ነው ያስረዱት። የመስመር ዝርጋታ ሥራውን ኃይል ሳይቋረጥ ማከናወን መቻሉ ለተቋሙ ትልቅ እምርታ መሆኑን ያብራሩት አቶ አሸናፊ ሥራው በተቋሙ የኮንስትራክሽን ማኔጂመንት መምሪያ ሠራተኞች አቅም በስኬት በመጠናቀቁ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1