es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 697 suscriptores, ocupando la posición 8 062 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 174 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 697 suscriptores.

Según los últimos datos del 01 septiembre, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 139, y en las últimas 24 horas de 1, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 28.75%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 16.42% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 513 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 578 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 10.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 02 septiembre, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 697
Suscriptores
+124 horas
+277 días
+13930 días
Archivo de publicaciones
የአይሻ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን የፋይናንስ ሥምምነት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው …..///….. በመንግሥት እና የግል አጋርነት ማዕቀፍ ለሚገነባውና 300 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ላለው
+6
የአይሻ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን የፋይናንስ ሥምምነት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው …..///….. በመንግሥት እና የግል አጋርነት ማዕቀፍ ለሚገነባውና 300 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ላለው የአይሻ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የፋይናንስ ሥምምነት ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ ከገንዘብ ሚኒስቴር እና ከዋና ዋና የልማት አጋሮች ጋር በመተባበር የከፍተኛ ደረጃ የአበዳሪዎች የቅድመ ኢንቨስትመንት ምርመራ ስብሰባ በሸራተን አዲስ ሆቴል ተካሂዷል፡፡ በስብሰባው ላይ የተገኙት የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ የማክሮ ኢኮኖሚ እና የውጭ ምንዛሪ ማሻሻያዎችን በማድረግ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት መንግሥት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የአይሻ-1-የንፋስ-ኃይል-ማመንጫ-ፕሮጀክትን&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 8 ቀን 2018 ዓ.ም

@9:00

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ አገኘ .....///…... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ቀደም ሲል የነበረበትን ከፍተኛ የዕዳ ጫና በመቋቋም እና አሠራሩን በማዘመን ለመጀመሪ
+1
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ አገኘ .....///…... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ቀደም ሲል የነበረበትን ከፍተኛ የዕዳ ጫና በመቋቋም እና አሠራሩን በማዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ትርፋማነት መሸጋገሩን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ አስታወቀ። የኢንቨስትመንት ሆልዲንጉ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ብሩክ ታዬ ( ዶ/ር) እንደገለፁት ተቋሙ በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ከ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ አስመዝግቧል፡፡ አሁን ላይ የተመዘገበው ትርፍ ተቋሙ ካለበት የብድር ጫና ወጥቶ ራሱን እንዲችል መንገድ የሚከፍት መሆኑ ጠቁመዋል። ተቋሙ የነበረበት ከፍተኛ የብድር ጫና ወደ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መተላለፉ፣ በመንግሥት የተተገበረው የኢኮኖሚ ሪፎርም እና የተደረገው የታሪፍ ማሻሻያ ለትርፉ መመዝገብ ድርሻው የጎላ መሆኑን ዶ/ር ብሩክ አብራርተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 8 ቀን 2018 ዓ.ም

ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ለከተማዋ የኃይል አቅርቦት ቁልፍ ድርሻ ያበረክታል ……...///…….... በባህር ዳር ከተማ እየተገነባ የሚገኘው ባለ 230 ኪሎ ቮልት ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሲጠናቀቅ
+6
ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ለከተማዋ የኃይል አቅርቦት ቁልፍ ድርሻ ያበረክታል ……...///…….... በባህር ዳር ከተማ እየተገነባ የሚገኘው ባለ 230 ኪሎ ቮልት ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሲጠናቀቅ በከተማዋ እና በአካባቢው አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ተሻገር እንደገለፁት በከተማዋ አንድ ባለ 400/230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ የሚገኝ ቢሆንም ጣቢያው የነዋሪውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ጥያቄ በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል አልነበረም፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ፕሮጀክቱ-ሲጠናቀቅ-ለከተማዋ-የኃይል-አቅ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም

አካዳሚው ዲጂታል የምዘና ስርዓት ተግባራዊ ማድረግ ጀመረ .......///...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዲጂታል የምዘና ስርዓት መጀመሩን የኢትዮ ፓወር አካዳሚ አስታወቀ። በአካዳሚው የዕውቀት
+1
አካዳሚው ዲጂታል የምዘና ስርዓት ተግባራዊ ማድረግ ጀመረ .......///...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዲጂታል የምዘና ስርዓት መጀመሩን የኢትዮ ፓወር አካዳሚ አስታወቀ። በአካዳሚው የዕውቀት አስተዳደርና ብቃት ምዘና ተወካይ ስራ አስኪያጅ አቶ ፈቃዱ አለማየሁ እንደተናገሩት ተቋሙ ከታህሳስ 2018 ዓ.ም ጀምሮ የዲጂታል ምዘና ስርዓት በይፋ ጀምሯል። የምዘና ሥርዓቱ ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ በ18 የሥራ መደቦች ለ91 የተቋሙ ሠራተኞች የዲጂታል ፈተና ያለምንም ችግር መስጠት መቻሉን ገልፀዋል። በመጀመሪያው ዙር የደረጃ ዕድገት እና ዝውውር ለሚወዳደሩ የተቋሙ ሠራተኞች በዋና መስሪያ ቤት፣ በደሴ፣ በሠመራ፣ በወላይታ፣ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እና በጣና በለስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የዲጂታል ምዘና በስኬት መከናወኑንም ነው አቶ ፈቃዱ የገለፁት። በቀጣይም ሌሎች የዲጂታል ምዘናዎች ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጠናቀቃቸውንም ተናግረዋል። የዲጂታል የምዘና ስርዓት ከዚህ ቀደም በሠራተኞች ይቀርብ የነበረውን የፈተና አወጣጥ የተአማኒነት ቅሬታ በእጅጉ እንደሚቀርፍ ታምኖበታል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ስድስት የኢትዮጵያ የፋይናንስ ተቋማት በጋራ ባዘጋጁት የፋይናንስ ኮንፈረንስ እየተሳተፉ ነው። የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ
+4
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ስድስት የኢትዮጵያ የፋይናንስ ተቋማት በጋራ ባዘጋጁት የፋይናንስ ኮንፈረንስ እየተሳተፉ ነው። የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ሌሎች የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት እና “የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ” በሚል በተሰናዳው ኮንፈረንስ ስድስት የሀገራችን የፋይናንስ እና የገቢ ሥርዓት በመምራት ላይ ያሉ ዐበይት ተቋማት አፈፃፀማቸውን ያቀርባሉ። እነዚሁ ተቋማት ለሚቀጥሉት አምስት አመታት የሚኖራቸውን ስትራቴጂያዊ የቅድሚያ ምልከታ ለታዳሚው የሚያቀርቡ ይሆናል። መረጃው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ነው 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም

ፕሮጀክቶቹን በተያዘላቸው ጊዜ እና በጀት ለማጠናቀቅ ነቅቶ መስራት ይገባል …….///……. አስተማማኝ ኃይል ለማመንጨት እና የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜና በጀት ለማጠናቀቅ ሁሉም የዘ
+8
ፕሮጀክቶቹን በተያዘላቸው ጊዜ እና በጀት ለማጠናቀቅ ነቅቶ መስራት ይገባል …….///……. አስተማማኝ ኃይል ለማመንጨት እና የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜና በጀት ለማጠናቀቅ ሁሉም የዘርፉ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞችኛ በንቃትና በመተባበር መስራት እንደሚጠበቅባቸውት የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወልደኪዳን አሳሰቡ፡፡ ዘርፉ በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸምን በሥሩ ከሚገኙ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ሲገመግም እንደተናገሩት ከፕሮጀክቱ የተገኙ ተሞክሮዎችንና ያጋጠሙ ችግሮችን ለቀጣይ ፕሮጀክቶች ግብዓት በሚሆን መልኩ አደራጅቶ ማስቀመጥ ይገባል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ፕሮጀክቶቹን-በተያዘላቸው-ጊዜ-እና-በጀት&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም

የተቋሙን መሠረተ ልማቶች ለመጠበቅ የተገኙ ተስፋ ሰጭ ውጤቶችን ማጠናከር ያስፈልጋል …….///……. በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀመውን ስርቆት በዘላቂነት ለመፍታት የታዩ ተስፋ ሰጪ ጅምሮች
+9
የተቋሙን መሠረተ ልማቶች ለመጠበቅ የተገኙ ተስፋ ሰጭ ውጤቶችን ማጠናከር ያስፈልጋል …….///……. በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀመውን ስርቆት በዘላቂነት ለመፍታት የታዩ ተስፋ ሰጪ ጅምሮችና የተገኙ ውጤቶችን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚያስፈልግ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋም ደህንነት መምሪያ አስታወቀ። መምሪያው ከሪጅን ኃላፊዎችና ከመሠረተ ልማት ደህንነት የጥበቃ አባላት ኃላፊዎች ጋር በኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማት ደህንነት ዙሪያ የተከናወኑ ሥራዎችን አስመልክቶ ሲያካሂድ የቆየውን ግምገማ አጠናቋል። በግምገማው ላይ በሁሉም የተቋሙ ሪጅኖች የተመደቡ የመሰረተ ልማት ጥበቃ የሥራ ኃላፊዎች ሥራ ከጀመሩበት ጊዜ አንስቶ ባከናወናቸው ሥራዎች ላይ የታዩ ጠንካራና ደካማ ጎኖች ቀርበው ተገምግመዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙን-መሠረተ-ልማቶች-ለመጠበቅ-የተገ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም

የኮምቦልቻ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ለኢንዱስትሪ መስፋፋት ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል …….///……… የኮምቦልቻ ቁጥር 1 ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው ኢንዱስትሪዎች እንዲስፋፉ
+4
የኮምቦልቻ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ለኢንዱስትሪ መስፋፋት ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል …….///……… የኮምቦልቻ ቁጥር 1 ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው ኢንዱስትሪዎች እንዲስፋፉ ከፍተኛ ሚና መጫወቱን የጣቢያው ኃላፊ ተናገሩ፡፡ ኃላፊው አቶ ደምሴ ሣህለማርያም እንደተናገሩት የኮምቦልቻ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ለኮምቦልቻ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ኃይል ለማቅረብ ታስቦ በ1976 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረ ነው፡፡ ጣቢያው በወቅቱ ከሸዋሮቢት ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ተቀብሎ በሰባት ባለ 15 እና በአንድ ባለ 66 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ለጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካው፣ ለኮምቦልቻና ለደሴ ከተሞች ኃይል ሲያቀርብ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኮምቦልቻ-ቁጥር-1-ማከፋፈያ-ጣቢያ-ለኢንዱ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል ማመንጫዎችን የኦፕሬሽን አቅም ለማሳደግ እና የሥራ ላይ ደህንነትን ለማስጠበቅ እንደሚሰራ ተገለፀ …….///…….. በሁሉም የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን አቅምን ለማሳደግ እና የሥራ ላይ
+7
የኃይል ማመንጫዎችን የኦፕሬሽን አቅም ለማሳደግ እና የሥራ ላይ ደህንነትን ለማስጠበቅ እንደሚሰራ ተገለፀ …….///…….. በሁሉም የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን አቅምን ለማሳደግ እና የሥራ ላይ ደህንነት መስፈርቶችን ለማስጠበቅ እንደሚሰራ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወልደኪዳን የተመራ የባለሙያዎች ቡድን በአዋሽ 2 እና 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የመስክ ምልከታ አድርጓል። የመስክ ምልከታው በጣቢያዎቹ ወቅታዊ የኦፕሬሽን አፈፃፀም፣ በማመንጨት ሂደት ላይ በሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች እና በሌሎች የዘርፉ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለመወያየት ያለመ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-ማመንጫዎችን-የኦፕሬሽን-አቅም-ለ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም

ዘርፉ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት እየሰራ ነው ……..///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሀገር አቀፍ ደረጃ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት የተለያዩ ሥራዎችን እያከና
+2
ዘርፉ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት እየሰራ ነው ……..///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሀገር አቀፍ ደረጃ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን የጀኔሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወልደኪዳን ተናገሩ። ዘርፉ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀሙን እየገመገመ ይገኛል። ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር ኤፍሬም በግምገማው ላይ እንዳሉት ዘርፉ ተቋሙ የተሰጠውን ተልዕኮና የነደፈውን ስትራቴጂክ ዕቅድ ለማሳካት ቀደም ሲል በተናጠል ሲሰሩ የነበሩት የኃይል ማመንጫ ግንባታ እና የኦፕሬሽን የሥራ ክፍሎችን በአንድ ላይ በማድረግ የተቋቋመ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ዘርፉ-እያደገ-የመጣውን-የኃይል-ፍላጎት-ለ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 5 ቀን 2018 ዓ.ም

ፕሮጀክቱ ሁሉን አቀፍ ዕድገት በማስመዝገብ ተወዳዳሪ ከተማ ለመፍጠር ያስችላል - ከንቲባ ሳሙኤል ሞላልኝ …….///……… በደሴ ከተማ አካባቢ በግንባታ ላይ የሚገኘው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከ
+5
ፕሮጀክቱ ሁሉን አቀፍ ዕድገት በማስመዝገብ ተወዳዳሪ ከተማ ለመፍጠር ያስችላል - ከንቲባ ሳሙኤል ሞላልኝ …….///……… በደሴ ከተማ አካባቢ በግንባታ ላይ የሚገኘው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የከተማዋን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ በማሳደግ ከሌሎች ከተሞች ጋር ተወዳዳሪ እንድትሆን ያስችላታል ሲሉ የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተናገሩ፡፡ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ እንደተናገሩት በአሁኑ ወቅት የደሴ ከተማና አካባቢው የኤሌክትሪክ አቅርቦት የሚያገኙት በከተማዋ ለረጅም ጊዜ አገልግሎት ሲሰጥ ከቆየው የ66 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ነው፡፡ ሆኖም ከከተማዋ መስፋፋት እና ከህዝብ ቁጥር መጨመር ጋር ተያይዞ ጣቢያው በየጊዜው እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ጥያቄ በአግባቡ እየመለሰ አለመሆኑን ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ፕሮጀክቱ-ሁሉን-አቀፍ-ዕድገት-በማስመዝገ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 5 ቀን 2018 ዓ.ም

ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ቀጣናውን እያስተሳሰረች ነው - አምባሳደር ጀማል በከር (ዶ/ር) ‎....///.... ‎ኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ማዕከል በመሆን የምስራቅ አፍሪካን ቀጣና እያስተሳሰረች መሆኑን
+4
ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ቀጣናውን እያስተሳሰረች ነው - አምባሳደር ጀማል በከር (ዶ/ር) ‎....///.... ‎ኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ማዕከል በመሆን የምስራቅ አፍሪካን ቀጣና እያስተሳሰረች መሆኑን አምባሳደር ጀማል በከር (ዶ/ር) ገለጹ። ‎ በተባበሩት ዐረብ ኢምሬት አቡዳቢ ከጥር 03 እስከ ጥር 04 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ "Powering Humanity: Renewable Energy for Shared Prosperity" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ በሚገኘው 16ኛው የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኤጀንሲ (IRENA) ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ በመሳተፍ ላይ ትገኛለች። ‎ ‎አምባሳደር ጀማል በጉባኤው ባቀረቡት የኢትዮጵያ ብሔራዊ መግለጫ ሀገሪቱ የምትጠቀመው ኃይል ከ98 በመቶ በላይ ከታዳሽ የኃይል ምንጮች የሚገኝ መሆኑን ጠቁመዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ኢትዮጵያ-በታዳሽ-ኃይል-ቀጣናውን-እያስተ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 4 ቀን 2018 ዓ.ም

የመሠረተ ልማቶች ስርቆት በሀገር ላይ ከኢኮኖሚ የዘለለ ጉዳት ያስከትላል ….....///……. በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ ጉዳቶች ከኢኮኖሚ የዘለለ እንድምታ እንዳላቸው በኢትዮጵያ ኤሌክ
+4
የመሠረተ ልማቶች ስርቆት በሀገር ላይ ከኢኮኖሚ የዘለለ ጉዳት ያስከትላል ….....///……. በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ ጉዳቶች ከኢኮኖሚ የዘለለ እንድምታ እንዳላቸው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ ገለፁ፡፡ በተቋሙ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈጸሙ ስርቆቶችን በመከላከል ሂደት የተከናወኑ ሥራዎች ተገምግሟል። በተቋሙ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደገለጹት በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ ጉዳቶች ከኢኮኖሚ ጥቅም ባሻገር ፓለቲካዊ አንድምታ ይኖራቸዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የመሠረተ-ልማቶች-ስርቆት-በሀገር-ላይ-ከኢ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 4 ቀን 2018 ዓ.ም

የኮምቦልቻ ቁጥር 3 ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት በመጠናቀቀ ላይ ይገኛል …….///…… የባህርዳር - ወልዲያ ኮምቦልቻ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክ
+8
የኮምቦልቻ ቁጥር 3 ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት በመጠናቀቀ ላይ ይገኛል …….///…… የባህርዳር - ወልዲያ ኮምቦልቻ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት አካል የሆነው የኮምቦልቻ ቁጥር 3 ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ሥራ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ የጣቢያው የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች ተቆጣጣሪ ተናገሩ፡፡ ተቆጣጣሪው አቶ ኃይለኢየሱስ ስንታየሁ እንደተናገሩት ማከፋፈያ ጣቢያው በ400 ኪሎ ቮልት በኩል 1000 ሜጋ ቮልት አምፒር ኃይል የመሸከም አቅም ያላቸው ሁለት አውቶ ትራንስፎርመሮች እንዲሁም በ230 ኪሎ ቮልት በኩል 300 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ሁለት ፓወር ትራንስፎርመሮች አሉት፡፡ በተጨማሪም ጣቢያው 20 ባለ 33 እና ሁለት ባለ 230 ኮሎ ቮልት ወጭ መስመሮች እንዳሉት ገልፀዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኮምቦልቻ-ቁጥር-3-ባለ-400-ኪሎ-ቮልት-የኃይል&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 4 ቀን 2018 ዓ.ም

የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቱ ከ40 በመቶ በላይ ደርሷል ………///……. ለደሴ ከተማና አካባቢው አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ታስቦ እየተገነባ የሚገኘው የደሴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ
+9
የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቱ ከ40 በመቶ በላይ ደርሷል ………///……. ለደሴ ከተማና አካባቢው አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ታስቦ እየተገነባ የሚገኘው የደሴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት አጠቃላይ አፈፃፀሙ 40 ነጥብ 7 በመቶ መድረሱን የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አስታወቁ፡፡ አስተባባሪው አቶ አብዲ ኪያር እንዳስታወቁት የፕሮጀክቱ የአፈር ቆረጣና ልል አፈር የማንሳት ሥራ ከተያዘለት ጊዜ በላይ ቢወስድም ሥራውን በታቀደለት ጊዜና ጥራት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የማከፋፈያ-ጣቢያ-ፕሮጀክቱ-ከ40-በመቶ-በላይ_&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 4 ቀን 2018 ዓ.ም

የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቱ ከ40 በመቶ በላይ ደርሷል ………///……. ለደሴ ከተማና አካባቢው አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ታስቦ እየተገነባ የሚገኘው የደሴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት አጠቃላይ አፈፃፀሙ 40 ነጥብ 7 በመቶ መድረሱን የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አስታወቁ፡፡ አስተባባሪው አቶ አብዲ ኪያር እንዳስታወቁት የፕሮጀክቱ የአፈር ቆረጣና ልል አፈር የማንሳት ሥራ ከተያዘለት ጊዜ በላይ ቢወስድም ሥራውን በታቀደለት ጊዜና ጥራት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የማከፋፈያ-ጣቢያ-ፕሮጀክቱ-ከ40-በመቶ-በላይ_&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 4 ቀን 2018 ዓ.ም

“የፕሮጀክቶች አፈጻጸም ወጭ ቆጣቢ፣ የሥራ ጥራት እና ቅልጥፍና መለያቸው እንዲሆነ እየተሰራ ነው፤” ኢንጅነር ውድነህ የማነ .…///.… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚከናወኑ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ወ
+8
“የፕሮጀክቶች አፈጻጸም ወጭ ቆጣቢ፣ የሥራ ጥራት እና ቅልጥፍና መለያቸው እንዲሆነ እየተሰራ ነው፤” ኢንጅነር ውድነህ የማነ .…///.… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚከናወኑ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ወጭ ቆጣቢ፣ የሥራ ጥራት እና ቅልጥፍና መለያቸው እንዲሆነ እየተሰራ መሆኑን በተቋሙ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ኢንጅነር ውድነህ የማነ ገለጹ። ‎ዘርፉ የ2018 በጀት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸሙን ሲገመግም ኢንጂነር ውድነህ እንደተናገሩት ባለፉት ስድስት ወራት በኢንጅነሪንግ ዲዛይን፣ በመነሻ ዲዛይን፣ በፕሮጀክቶች ክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም በኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ተግባራት ላይ አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የፕሮጀክቶች-አፈጻጸም-ወጭ-ቆጣቢ፣-የሥ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 1 ቀን 2018 ዓ.ም

ፕሮጀክቶች የተሻለ አፈጻጸምና ቁመና እንዲኖራቸው በቁርጠኝነት መስራት ይገባል ‎.....////..... ‎በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚከናወኑ ፕሮጀክቶች የተሻለ የግንባታ አፈጻጸምና የፋይናንስ ቁመ
+3
ፕሮጀክቶች የተሻለ አፈጻጸምና ቁመና እንዲኖራቸው በቁርጠኝነት መስራት ይገባል ‎.....////..... ‎በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚከናወኑ ፕሮጀክቶች የተሻለ የግንባታ አፈጻጸምና የፋይናንስ ቁመና እንዲኖራቸው ሠራተኛው በቁርጠኝነት መስራት እንዳለበት በተቋሙ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ ገለጸ። ‎ ‎ዘርፉ በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያ በሥሩ ከሚገኙ የሥራ ክፍል ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር ውይይት እያካሄደ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ፕሮጀክቶች-የተሻለ-አፈጻጸምና-ቁመና-እን&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 1 ቀን 2018 ዓ.ም

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ የተቋማችን ሠራተኞች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሠላም አደረሳችሁ እያልኩ ልባዊ ምኞቴን እገልፃለሁ። ተቋማችን ሀገራችን ኢትዮጵያ ለጀመረችው ሁለንተናዊ ዕድገት
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ የተቋማችን ሠራተኞች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሠላም አደረሳችሁ እያልኩ ልባዊ ምኞቴን እገልፃለሁ። ተቋማችን ሀገራችን ኢትዮጵያ ለጀመረችው ሁለንተናዊ ዕድገት ያለው አበርክቶ ከፍተኛ ነው። የቤት ውስጥ ኃይል ተጠቃሚው፣ ኢንደስትሪው፣ አገልግሎት ሰጪው፣ ሁሉም ዘርፍ ከኤሌክትሪክ ኃይል ውጪ መንቀሳቀስ የማይችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል። በዚህ ሂደት ውስጥ ሁሉም የተቋማችን ሠራተኞች ጉልህ ድርሻ ያላችሁ በመሆኑ ልትኮሩና ለላቀ ውጤት በትጋት ልትሰሩ ይገባል። ሀገራችን ለጀመረችው ሁለንተናዊ ብልጽግና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ወሳኝ በመሆኑ የኃይል ተደራሽነትን ለማስፋት እና አስተማማኝነቱን ለማረጋገጥ በጋራ እንድንረባረብ ጥሪ እያቀረብኩ በዓሉ የሠላም፣ የፍቅርና የመተሳሰብ  እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ። ኢንጂነር አሸብር ባልቻ፣ ዋና ሥራ አስፈፃሚ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ታህሳስ 28 ቀን 2018 ዓ.ም