ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 554 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 397,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 165

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 554 名订阅者。

根据 21 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 10,过去 24 小时变化为 1,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.74%。内容发布后 24 小时内通常能获得 14.94% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 003 次浏览,首日通常累积 2 323 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 22 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 554
订阅者
+124 小时
+87
+1030
帖子存档
ማህበሩ  ከ62 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ትርፍ አገኘ ‎....///..... ‎የኢትዮ ኤሌክትሪክ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የሕብረት ሥራ ማህበር ጠቅላላ ጉባዔ 2ኛ መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው። ‎የማህበሩ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ አንበሴ ግዛቸው እንደገለጹት የመደበኛ ጠቅላላ ጉባዔው ስብሰባ ዓላማ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የኦዲት ሪፖርት እንዲሁም የ2018 በጀት ዓመት የበጀት ማሻሻያ ለጉባዔው አባላት አቅርቦ ማጽደቅ ነው፡፡ በተመሳሳይ የብድር ጣሪያ እና የመክፈያ ጊዜን ጨምሮ ማሻሻያ የተደረገባቸው ደንቦች በስብሰባው ላይ ቀርበው እንደሚፀድቁ ተናግረዋል፡፡ ‎ ‎በስብሰባው ላይ ከሐምሌ 1 ቀን 2016 ዓ.ም እስከ ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ያለው የማህበሩ የኦዲት ሪፖርት ቀርቧል። ‎ ‎በሪፖርቱ ማህበሩ በተጠቀሰው ጊዜ ከአገልግሎት፣ ከባንክ ወለድ፣ ከኢንቨስትመንት እና ከሌሎች ገቢዎች 159 ሚሊዮን 18 ሺህ 87 ብር ከ98 ሳንቲም ገቢ ማግኘቱ ተጠቅሷል፡፡ ‎ ‎ማህበሩ ለአስተዳደርና ለተለያዩ ጉዳዮች 96 ሚሊዮን 619 ሺህ 800 ብር ከ87 ሳንቲም ወጭ ማድረጉንም በኦዲት ሪፖርቱ ተመልክቷል። ‎ የማህበሩ የተጣራ ትርፍ 62 ሚሊዮን 398 ሺህ 287 ብር ከ11 ሳንቲም መሆኑንና ከዚህ ውስጥ በአዋጁ መሰረት 30 በመቶው መጠባበቂያ እና 10 በመቶው ለልዩ ልዩ አስተዳደራዊ ወጭዎች በማስቀመጥ ቀሪው ለአባላት እንደሚከፋፈል ተነግሯል፡፡ ‎በቀረበው የኦዲት ሪፖርት ላይ በጠቅላላ ጉባዔው አባላት ከገንዘብ አሰባሰብ፣ ከወጭ፣ ከኢንቨስትመንት፣ ከመጠባበቂያ ተቀማጭና ያልተከፋፈለ ትርፍ ጋር ተያይዞ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተዋል። ‎ለተነሱ ጥያቄዎችን ማብራሪያዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበት የኦዲት ሪፖርቱ በአብላጫ ድምጽ ጸድቋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+5

‎ተቋሙ በሩብ ዓመቱ ከ9 ሺህ ጊጋ ዋት ስዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል ‎......///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከ9 ሺህ በላይ ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማምረቱን የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ። ‎ ‎የዘርፉ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ኪዳን እንደገለፁት በሩብ ዓመቱ 10 ሺህ 354 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማምረት ታቅዶ 9 ሺህ 208 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማምረት ተችሏል። ‎ ‎ይህም የዕቅዱ 89 በመቶ መሳካቱን የሚያሳይ ሲሆን በ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከተመረተው ኃይል ጋር ሲነፃፀር ግን የ2 ሺህ 707 ጊጋ ዋት ሰዓት ብልጫ ያለው መሆኑን አብራርተዋል። ‎ ‎እንደ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ በሩብ ዓመቱ ከመነጨው ኃይል ውስጥ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ 4 ሺህ 549 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም 49 ነጥብ 4 በመቶ እንዲሁም የጊቤ ሦስት የኃይል ማመንጫ ጣቢያ 1 ሺህ 694 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም የ18 ነጥብ 4 በመቶ በማመንጨት ከፍተኛ ድርሻ እንደነበራቸው ተጠቅሷል። ‎ ‎በሩብ ዓመቱ ከመነጨው ኃይል 9 ሺህ 27 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም 98 በመቶ ከውሃ እንዲሁም 180 ነጥብ 6 ጊጋ ዋት ሰዓቱ  ወይም 2 በመቶ ከንፋስ የተገኘ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡  ‎ ‎በሩብ ዓመቱ የታላቁ ህዳሴ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ በመጠናቀቁ እና 22 የአሰላ ንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ተርባይኖች ወደ ኦፕሬሽን በመግባታቸው የማመንጨት አቅም በ2017 በጀት ዓመት ከነበረበት 7 ሺህ 919 ሜጋ ወደ 9 ሺህ 554 ሜጋ ዋት ከፍ ማለቱን ጠቅሰዋል። ‎ ‎የባለሙያዎችን አቅም በማሳደግ ጠንካራና ቀጣይነት ያላቸው የጥገና ሥራዎች በማከናወን እንዲሁም በማዕቀፍ ግዥ ጭምር የመለዋወጫ ዕቃዎች ሲቀርቡ መቆየቱንም አንስተዋል።  ‎ ‎በሩብ ዓመቱ የኃይል ማመንጫ አቅምን ከመጠቀም አንጻር የተሻለ አፈጻጸም የተመዘገበ መሆኑን የጠቆሙት ኢንጂነር ኤፍሬም የህዳሴ ኃይል ማመንጫን አቅም በተሻለ ለመጠቀም እና የግሪድ አስተማማኝነትን ለማሳደግ ተጨማሪ የማጠናከሪያ ሥራዎች መከናወን አለባቸው ብለዋል። ‎ ‎በቀጠይ 9 ወራት አማካይ የኃይል ጭነትን በማሻሻል ለበጀት ዓመቱ የታቀደውን የኃይል ምርት ግብ ለማሳካት እንደሚሰራም ተናግረዋል:: 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4

‎ተቋሙ የሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እየገመገመ ነው ‎.....///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የ2018 በጀት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ከሥራ መሪዎች ጋር በሸራተን አዲስ ሆቴል መገምገም ጀምሯል። ‎ ‎በዚህ ወቅት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለጹት የግምገማ መድረኩ በሩብ ዓመቱ የተመዘገቡ ስኬቶችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በመለየት ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ነው። ‎ ‎በ2018 በጀት ዓመት ሕዳሴን ማስመረቅ ጨምሮ ትልልቅ ስኬቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። ‎ ‎በሩብ ዓመቱ ያጋጠሙ እጥረቶች ላይ የተቋሙ አመራር የጋራ መረዳት በመያዝ ለተሻለ ውጤት መስራት እንዳለበት አሳስበዋል። ‎ ‎ በግምገማ መድረኩ ሁሉም ዘርፎች የሩብ ዓመቱን ዕቅድ አፈጻጸም የሚያቀርቡ ሲሆን እኛም እየተከታተልን መረጃውን የምናደርሳችሁ ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም

‎ተቋሙ የሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እየገመገመ ነው፤ ‎.....///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የ2018 በጀት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ከሥራ መሪዎች ጋር በሸራተን አዲስ ሆቴል መገምገም ጀምሯል። ‎ ‎በዚህ ወቅት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለጹት የግምገማ መድረኩ በሩብ ዓመቱ የተመዘገቡ ስኬቶችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በመለየት ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ነው። ‎ ‎በ2018 በጀት ዓመት ሕዳሴን ማስመረቅ ጨምሮ ትልልቅ ስኬቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። ‌‎ተቋሙ የሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እየገመገመ ነው ‎.....///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የ2018 በጀት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ከሥራ መሪዎች ጋር በሸራተን አዲስ ሆቴል መገምገም ጀምሯል። ‎ ‎በዚህ ወቅት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለጹት የግምገማ መድረኩ በሩብ ዓመቱ የተመዘገቡ ስኬቶችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በመለየት ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ነው። ‎ ‎በ2018 በጀት ዓመት ሕዳሴን ማስመረቅ ጨምሮ ትልልቅ ስኬቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። ‎ ‎በሩብ ዓመቱ ያጋጠሙ እጥረቶች ላይ የተቋሙ አመራር የጋራ መረዳት በመያዝ ለተሻለ ውጤት መስራት እንዳለበት አሳስበዋል። ‎ ‎ በግምገማ መድረኩ ሁሉም ዘርፎች የሩብ ዓመቱን ዕቅድ አፈጻጸም የሚያቀርቡ ሲሆን እኛም እየተከታተልን መረጃውን የምናደርሳችሁ ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+5

የአራት ጥናቶች ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ተካሄደ፤ ‎....///.... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር የሚያሰራቸው አራት ጥናቶች ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ተካሂዷል። ‎ ‎አራቱ ጥናቶች የሠራተኞችና የባለድርሻ አካላት እርካታ፣ በተቋማዊ ባህል እና የሠራተኞች ለሥራ መሰጠት ላይ የሚያተኩሩ ናቸው። ‎ ‎በፕሮግራሙ ላይ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደገለጹት እንደሀገር ሁሉን አቀፍ እድገት ለማምጣት የኃይል አቅርቦቱን እና ተደራሽነቱን ማሳደግ ወሳኝ ነው። ‎ ‎ለዚህም ተቋሙ በጥናት ላይ ተመስርቶ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻልና ተልዕኮውን ለማሳካት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጋር በአቅም ግንባታና በጥናትና ምርምር ጨምሮ በተለያዩ መስኮች በትብብር እየሠራ መሆኑን አብራርተዋል። ‎ ‎ጥናቱ በአጭር ጊዜ ተጠናቆ ወደ ተግባር በመቀየር በተቋሙ ዘላቂ ለውጥ ለማምጣት የሥራ አመራሩ ዝግጁ መሆኑንና አስፈላጊውን ትብብር እንደሚያደርግ አስገንዝበዋል። ‎ በተቋሙ የጥናትና ምርምር ሥራ አስኪያጅ አቶ ቢትወደድ ገብረአሊፍ በበኩላቸው የውይይቱ ዓላማ ዩኒቨርሲቲው ጥናት ለማድረግ ከስምምነት በተደረሰባቸው በአራቱ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ጥናቱ መጀመሩን ለማብሰርና ባለድርሻ አከላትም ይሄን አውቀው ትብብር እንዲያደርጉ ለማሳወቅ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ጥናቱ ተቋሙ ከሠራተኞችና ባለድርሻ አካላት እርካታ፣ ከተቋማዊ ባህል እና የሠራተኞች ለሥራ መሰጠት አንጻር አሁን ላይ ያለበትን ነባራዊ ሁኔታ በመለየት በቀጣይ መሻሻልና መለወጥ ያለባቸውን ጉዳዮች የሚያመላክት መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ‎ጥናቶች በምን መልኩ እንደሚካሄዱ የመነሻ ጽሁፍ በጥናቱ ተሳታፊና በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢነርጅ ኢኮኖሚ መምህር በሆኑት አቶ ኤፍሬም አንዳርጌ ቀርቧል። ‎ ጥናቱ ሀገሪቱ በኃይል ልማት ዘርፉ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም የኃይል ተደራሽነቱን ለማስፋት እና የአፍሪካ ሀገራትን በኃይል ለማስተሳሰር የተያዘውን እቅድ ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ዩኒቨርሲቲው የራሱን ድርሻ እንዲወጣ የሚያስችለው ነው ብለዋል።‎ ‎እንደ አቶ ኤፍሬም ገለጻ የጥናት ማስጀመሪያ ውይይቱ በጥናቱ ሂደት ላይ በተቋማቱ መካከል የጋራ መረዳት እንዲኖር የሚያስችል ነው፡፡ ዩኒቨርስቲው ጥናቱን በአጭር ጊዜ አጠናቆ ለማቅረብ ከተቋማቱና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡ የጥናት ማስጀመሪያ ውይይቱ ተሰታፊዎች ጥናቱ መደረጉ በጣም ጠቃሚ መሆኑን በመጥቀስ የደንበኛ እርካታ ለብቻው ተካቶ የሚሰራበት መንገድ ቢኖር የሚል ሀሳብ አቅርበዋል። ‎ ‎በተጨማሪም ከናሙና አመራረጥና መጠን፣ ለርዕሰ ጉዳዮቹ ከተሰጣቸው ጊዜ፣ ከጥናቱ ሞዴል፣ ከመረጃ አሰባሰብ ዘዴዎች ጋር በተያያዘም ጥያቄዎችና አስተያየቶችን አንስተው ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

photo content
+9

ማሳሰቢያ .....///..... የገናሌ ዳዋ 3ኛ የኃይል ማመንጫ ግድብ ውሃ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በመምጣቱ ምክንያት የግድቡን ደህንነት ለማስጠበቅ ሲባል ውሃውን ከጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም.
ማሳሰቢያ .....///..... የገናሌ ዳዋ 3ኛ የኃይል ማመንጫ ግድብ ውሃ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በመምጣቱ ምክንያት የግድቡን ደህንነት ለማስጠበቅ ሲባል ውሃውን ከጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ላልተወሰኑ ቀናት መልቀቅ አስፈልጓል፡፡ ስለሆነም በሊበን እና መዳወላቡ ወረዳዎች ኮባዲ፣ ሚኤሳ፣ መዳ፣ ኦዳ ቦጂ፣ እና ቢድሬ ቀበሌዎች እና በአካባቢያቸው ያሉ ነዋሪዎች የሚለቀቀው ደራሽ ውሃ በሰውም ሆነ በእንሰሳት ላይ ጉዳት እንዳያደርስ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ በአክበሮት እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም

በሩብ ዓመቱ ዘርፉ የተቋሙን ጥቅም የሚያስጠብቁ ሥራዎችን አከናውኗል ………///…….. በ2018 የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የተቋሙን ጥቅም የሚያስጠብቁ የተለያዩ ተግባራት ማከናወኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮምፕሊያንስና ገቨርናንስ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ ገለጹ፡፡ ሥራ አስፈጻሚው አቶ ዱጉማ ነዳ እንደገለጹት ዘርፉ የተቋሙን ስትራቴጅክ ዕቅድ መሰረት በማድረግ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድን በሥሩ በሚገኙ መምሪያዎች እስከ ባለሙያ ድረስ በማውረድ ወደ ሥራ ገብቷል፡፡ በዚህም በመጀመሪያው ሩብ ዓመት የተቋሙን ገጽታ ከመገንባት፣ ብልሹ አሰራሮችን ከመከላከል፣ የተቋሙን ጥቅም ከማስጠበቅ፣ ግልጸኝነትንና ተጠያቂነትን ከማስፈን እንዲሁም የሴቶችን ተሳትፎ ከማሳደግ አንጻር የተለያዩ ሥራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ተናግረዋል፡፡ በሩብ ዓመቱ የባለሙያዎችን በፍርድ ቤት ተከራክሮ የመርታት አቅም በማጎልበት ከ13 ነጥብ 78 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማዳን መቻሉን ገልጸዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት 8 ቢሊዮን ብር የገንዘብ መጠን ያላቸው 260 የሚሆኑ የፍትሐ ብሔር እና የአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ እንዲሁም 108 የወንጀል ጉዳይ መዝገቦች በክርክር ሂደት ላይ እንደሚገኙም አብራርተዋል፡፡ የመንግስትንና የሕዝብን ጥቅም የማስጠበቅ ኃላፊነት በአዋጅ ከተሰጠው ከፍትህ ሚኒስቴር ጋር በመነጋገር ግምታቸው ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ በሆኑ የካሳ ጉዳዮች ዙሪያ ተቋሙን ወክሎ እንዲከራከር ስምምነት ተደርሶ ወደ ሥራ መገባቱን አቶ ዱጉማ ጠቁመዋል፡፡ በሩብ ዓመቱ በሥራ ቦታ ሥነ-ምግባር እንዲሁም በስልታዊ ኮሙዩኒኬሽን ጽንሰ ሀሳብና አስፈላጊነት ዙሪያ ለተቋሙ የሥራ መሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና መሰጠቱን አመልክተዋል፡፡ የሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ምስጢራዊነቱን በጠበቀ መልኩ ለመጠቆም የሚያስችል መተግበሪያ ወደ ሥራ መግባቱንና በዚህም 18 የሙስና ጥቆማዎች ቀርበው ምርመራ እየተካሄደባቸው እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡ የተለያዩ የኮሙዩኒኬሽን መሣሪያዎችን እንዲሁም ሁሉንም የሚዲያ አማራጮች በመጠቀም የተቋሙን ገጽታ ለመገንባት የተለያዩ ሥራዎች መከናወናቸውን የገለጹት ሥራ አስፈጻሚው ከ4 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ወጭ በማድረግ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች መከናወናቸውንም ጠቁመዋል፡፡ በተቋሙ የሚሰሩ ሴቶችን ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሥርዓተ ፆታና በአመራር ክህሎት ዙሪያ ከ200 በላይ ለሆኑ ሴት ሠራተኞችና አመራሮች ሥልጠና መሰጠቱንም አንስተዋል፡፡ የሰው ኃይል እጥረት፣ ሥልጠና በተያዘለት ጊዜ ያለማግኘት እና የሥራ ኃላፊዎች ለሚቀርብላቸው የመረጃ ጥያቄዎች በሚፈለገው ጊዜና ጥራት መረጃ ያለመስጠት ችግሮች በሩብ ዓመቱ የታዩ ችግሮች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የተቋሙን ጥቅሞች ከሚጎዱ ብልሹ አሰራሮች በመራቅ እንዲሁም ግልጸኝነትንና ተጠያቂነትን በማስፈን የተቋሙን መልካም ስም ለመገንባት ሁሉም ተቋማዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

በማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የጤና ምርመራ አገልግሎት ተሰጠ ………///……… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ዊንግስ ኦፍ ሂሊንግ ከተባለ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር በመተባበር በፅዳትና በግቢ ውበት ለተሰማሩ ሴት ሰራተኞች የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራና የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጥቷል፡፡ በተቋሙ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ እንደተናገሩት በዋና መ/ቤት በፅዳትና በግቢ ውበት ለተሰማሩ ሴት ሰራተኞች የማኀፀን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራና የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት መሰጠቱ ለሰራተኞቹ ትልቅ የጤና በረከት ነው፡፡ የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅ መሆኑን የገለፁት ወ/ሮ ሌንሴ አቅም የሌላቸው ሴት ሠራተኞች በነፃ ምርመራ እንዲያገኙ መደረጉ ሴት ሠራተኞች ከበሽታው ራሳቸውን ቀድመው ለመከላከል እንደሚያስችላቸው ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም ሴቶች በበሽታው ዙሪያ ያላቸውን ግንዛቤ  እንዲያሳድጉ ይረዳቸዋል ነው ያሉት፡፡ የዊንግስ ኦፍ ሂሊንግ ድርጅት የጤና ትምህርት አስተባባሪ ዶክተር መቅደስ መኮንን በበኩላቸው የግንዛቤ ማስጨበጫና የምርመራ አገልግሎት መሰጠቱ ለተቋሙ የሥራ ስኬት ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ በዓመት 8 ሺህ ሴቶች በበሽታው እንደሚጠቁ እንዲሁም 6 ሺህ የሚሆኑት ደግሞ ለሞት እንደሚዳረጉ ገልፀዋል፡፡ የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር በዓለማችን ሴቶችን ከሚያጠቁ የካንሰር ዓይነቶች አራተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ መሆኑን የጠቀሱት ዶክተር መቅደስ በሽታውን በህክምና መከላከል መቻሉ ከሌሎች የተለየ ያደርገዋል ፡፡ በዕለቱ 25 ለሚሆኑ ሠራተኞች በተቊሙ ዋና መ/ቤት በሚገኘው መካከለኛ ክሊኒክ የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ ተደርጎላቸዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4

የፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራ 70 በመቶ መድረሱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለፁ ……..///……. የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የሲቪል ሥራ 70 በመቶ መድረሱን የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ተናገሩ። በዛሬው ዕለት ከሚኒስትሮቻቸው ጋር የኮይሻ ፕሮጀክትን በመጎብኘት የ100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማ መጀመራቸውንም  ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው የገለፁት። ፕሮጀክቱ ከባለፈው ጉብኝት ጋር ሲነፃፀር የሚለካ የሥራ እድገት የታየበት መሆኑን እና ይህ ስኬት ለኃይል ምንጭ ዋስትና ለሚደረገው  ያላሰለሰ ጥረት ምስክር መሆኑን አስታውቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባጋሩት መረጃ እንዳስታወቁት የግድቡ ከፍታ ከመሰረቱ 128 ሜትር ደርሷል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+7

የሥራ መሪዎች መሰረታዊ  የአመራር እውቀት በመያዝ የተሰጣቸውን ኃላፊነት ሊወጡ ይገባል …..…///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በየደረጃው የሚገኙ የሥራ መሪዎች መሰረታዊ  የአመራር እውቀት በመያዝ የተሰጣቸውን ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ በተቋሙ የኢትዮ ፓወር አካዳሚ የአመራር ልማት ሥራ አስኪያጅ  አሳሰቡ፡፡ ሥራ አስኪያጇ ወ/ሮ ተኛኘ መኮንን ከሁሉም የኃይል ማመንጫ እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች  ለተወጣጡ  የኦፕሬሽን የሥራ ኃላፊዎች እየተሰጠ ባለው መሰረታዊ የአመራር አቅም ማሳደጊያ ስልጠና  ላይ ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ሥራ አስኪያጇ በመልዕክታቸው እንደገለፁት ሥልጠናው የተዘጋጀው የሥራ መሪዎች የአመራርነት ክህሎትን በማዳበር በተቋሙ በሁሉም ዘርፎች ብቁ በመሆን  የተቋሙን ስትራቴጂ፣ ራዕይ እና ተልተኮ በብቃት እንዲያሳኩ ለማስቻል ነው፡፡ ለስደስት ቀናት የሚቆየው ይህ ስልጠና  በፋይናንስ አስተዳደር፣ በሥራ ላይ ደህንነት፣በተቋማዊ ሥነ-ምግባር እና በህግ ጉዳዮች ላይ መሰረታዊ  የአመራር አቅም ግንባታ ሥልጠዎች እንደሚሰጡ ጠቁመዋል፡፡ የሚሰጠው ሥልጠና በአመራርነት ክህሎት ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት እና ራስን ለማብቃት እንደሚያግዝ የተናገሩት ወ/ሮ ተናኘ ሠልጣኖች ሥልጠናውን በትኩረት በመከታተል በሚያገኙት ግብዓት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡  በተቋሙ በራስ አቅም በሚሰጠው በዚህ ስልጠና ከሁሉም ሪጅን የማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ከኃይል ማመንጫዎች የተወጣጡ 25 የኦፕሬሽን የሥራ መሪዎች  እየሰለጠኑ ይገኛሉ፡፡ ስልጠናው በቀጣይ በአስር ዙሮች እንደሚቀጥል የተናገሩት ሥራ አስኪያጇ በዚህም በየደረጃው የሚገኙ የሁሉም የኃይል ማመንጫዎች፣  የማከፋፋያ ጣቢያዎች እና ማስተላፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን የሥራ መሪዎች የአቅም ግንባታውን ስልጠና እንደሚወስዱ  ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+5

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የቀድሞ ፕሬዝደንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እንገልጻለን ………..///……….. የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅ
በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የቀድሞ ፕሬዝደንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እንገልጻለን ………..///……….. የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የቀድሞ ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ትናንት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡ ታላቁ የሃይማኖት አባት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ባጋጠማቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡ ሐጂ ዑመር በአመራር ዘመናቸው የተለያዩ ወገኖች ወደ አንድነት እንዲመጡ እና የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በሕግ ዕውቅና እንዲኖረው ከፍተኛ አስተዋጽዖ አድርገዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ቤተሰቦች እንዲሁም ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ መፅናናትን ይመኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም