en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 553 subscribers, ranking 8 395 in the Technologies & Applications category and 2 164 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 553 subscribers.

According to the latest data from 22 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 5 over the last 30 days and by 1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.99%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.38% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 043 views. Within the first day, a publication typically gains 2 393 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 23 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 553
Subscribers
+124 hours
+47 days
+530 days
Posts Archive
አመራሩ ለውጥ ለማምጣት መረባረብ አለበት ~ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ‎.....///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራር በኃይል ልማት ዘርፉ መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት መረባረብ እንዳለበት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሳሰቡ። ‎ ‎ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ይሄን የተናገሩት ተቋሙ የ2018 በጀት የመጀመሪያውን ሩብ  ዓመት የጀነሬሽን እና የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፎችን ዕቅድ አፈጻጸም በገመገመበት መድረክ ላይ ነው። ‎ ‎ተቋሙ የፕሮጀክቶች አፈጻጸምን በማሻሻል እና የኦፕሬሽን ሥራዎችን በማቀላጠፍ በዘርፉ መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የመዋቅር ማሻሻያ አድርጎ ወደ ሥራ መግባቱን አስታውሰዋል። ‎ ‎ተቋሙ አዳዲስ የኃይል መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ከመገንባት ባሻገር ያለውን ሲስተም አስጠብቆ ለተጠቃሚው አስተማማኝ ኃይል ተደራሽ ማድረግ ዋነኛ ተልዕኮው መሆኑን ጠቁመዋል። ‎ ‎ሆኖም አመራሩ የተናበበ ዕቅድ አቅዶ በትብብር ባለመስራቱና ሀብትን በአግባቡ ባለማስተዳደሩ በተቋሙ ለሚስተዋለው የፕሮጀክቶች መዘግየት ምክንያት እየሆነ ነው ብለዋል። ‎ ‎በዚህም በሩብ ዓመቱ በኦፕሬሽንና በፕሮጀክቶች አፈጻጸም ላይ በታዩ ጉድለቶች ሳቢያ ለኃይል መቆራረጥና ተቋሙን ለተጨማሪ ወጪ መዳረጉን አብራርተዋል። ‎ ‎እንደ ኢንጂነር አሸብር ገለፃ የባለሙያዎችን አቅም ከመገንባትና ተጠያቂነትን ከማስፈን አንጻር ክፍተት በመኖሩ በኦፕሬሽን ሥራዎች ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድሯል። ‎ ‎በመሆኑም የተቋሙ አመራር የገቢ አማራጮችን በማስፋት አዳዲስ ፕሮጀክቶች እንዲጀመሩ እንዲሁም በግንባታ ሒደት ላይ የሚገኙትም በጊዜ ተጠናቀው የተቀላጠፈ የኦፕሬሽን ሥራ ለማከናወን እንዲቻል በትብብርና በጊዜ የለኝም መንፈስ መስራት እንደሚጠቅበት አሳስበዋል። ‎ ‎በተቋሙ የሰለጠነ የሰው ኃይል ከማፍራት አንፃር የሚስተዋለውን ክፍተት ለመሙላትም መጠነ ሰፊ የአቅም ግንባታ ሥራዎች ማከናወን እንደሚገባ በአፅዕኖት ገልፀዋል። ‎ ‎በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ውስጥ በሥራ ላይ የሚገኙ ትራንስፎርመሮችን ደህንነት ለማስጠበቅ የሚያስችል ጠንካራ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት እንደሚያስፈልግም ነው ያብራሩት። ‎ ‎የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን በዕቅድ ላይ ተመስርቶ የዕድሳትና መልሶ ግንባታ ሥራዎች ማከናወን እንደሚገባ የተናገሩት ዋና ሥራ አስፈጻሚው አመራሩ አዳዲስ ሀሳቦችን በማመንጨትና በመተግበር ጭምር በኃላፊነትና ቁርጠኝነት መስራት እንዳለበት አስገንዝበዋል። ‎ ‎ሪጅኖች የተቋሙ አምባሳደሮች በመሆናቸው ከየአካባቢው የመንግሥት መስተዳድር አካላት ጋር በቅርበት መስራት እንደሚጠበቅባቸውም ነው የጠቆሙት። ‎ ‎በፕሮጀክቶች እና ጣቢያዎች ውስጥ የሚገኙ ጥቅም ላይ የማይውሉ ቁርጥራጭ ብረቶችና ዕቃዎች ለስርቆት መንስዔ እየሆኑ መምጣታቸውን የጠቆሙት ኢንጂነር አሸብር ዕቃዎቹን በአግባቡ መዝግቦ የማደራጀት እና የማስወገድ ሥራ በአፋጣኝ መከናወን እንዳለበት ተናግረዋል። ‎ ‎ከመረጃ አያያዝ፣ ከሪፖርት አቀራረብ እና ከቅንጅታዊ አሰራር እንዲሁም ከሀብት አጠቃቀም ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ሰፊ ክፍተቶች እንዳሉ የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈጻሚው እነዚህና በሩብ ዓመቱ የተስተዋሉ ሌሎች ችግሮች የሚስተካከሉበት የድርጊት መርሀ ግብር ዘርፎቹ አቅደው ማምጣትና መፈጸም እንዳለባቸው አቅጣጫ ሰጥተዋል። ‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

ተቋሙ በሩብ ዓመቱ ወደ 27 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ገቢ አግኝቷል ‎........///....... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት ሦስት ወራት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገራት ከቀረበ የኃይል ሽያጭ እና ተጓዳኝ አገልግሎቶች ከ26 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን ገለጸ። ‎ ‎በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አንዷለም ሲዓ እንደተናገሩት በሩብ ዓመቱ ከኃይል ሽያጭ 24 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ 26 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ገቢ  ተገኝቷል። ‎ ‎በሩብ ዓመቱ 7 ነጥብ 88 ቴራ ዋት ሰዓት ኃይል በመሸጥ በብር 10 ነጥብ 1 ቢሊዮን እንዲሁም በውጭ ምንዛሬ 117 ነጥብ 1 የአሜሪካን ዶላር ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል። ‎ገቢው ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ96 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑንም ተናግረዋል። ‎ ‎እንደ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ በሩብ ዓመቱ የተሸጠው የኃይል ምርት ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ47 በመቶ ወርሃዊ ዕድገት አለው። ‎ ‎በመጀመሪያው ሩብ ዓመት ለሽያጭ ከቀረበው ኃይል 93 በመቶ ለሀገር ውስጥ እንዲሁም 7 በመቶ ደግሞ ለውጭ ሀገራት የቀረበ መሆኑን ተናግረዋል። ‎ ‎ለሀገር ውስጥ ከቀረበው የኃይል ሽያጭ ውስጥ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 53 ነጥብ 6 በመቶ፣ የከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች 4 ነጥብ 6 በመቶ እንዲሁም የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች 34 ነጥብ 6 በመቶ ድርሻ እንዳላቸው ጠቁመዋል። ‎ ‎በተመሳሳይ ለጎረቤት ሀገራት ከቀረበው የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ውስጥ ኬንያ እና ታንዛኒያ 4 ነጥብ 6 በመቶ እንዲሁም ጅቡቲ 2 ነጥብ 2 በመቶ ድርሻ አላቸው ብለዋል። ‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

ማህበሩ  ከ62 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ትርፍ አገኘ ‎....///..... ‎የኢትዮ ኤሌክትሪክ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የሕብረት ሥራ ማህበር ጠቅላላ ጉባዔ 2ኛ መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው። ‎የማህበሩ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ አንበሴ ግዛቸው እንደገለጹት የመደበኛ ጠቅላላ ጉባዔው ስብሰባ ዓላማ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የኦዲት ሪፖርት እንዲሁም የ2018 በጀት ዓመት የበጀት ማሻሻያ ለጉባዔው አባላት አቅርቦ ማጽደቅ ነው፡፡ በተመሳሳይ የብድር ጣሪያ እና የመክፈያ ጊዜን ጨምሮ ማሻሻያ የተደረገባቸው ደንቦች በስብሰባው ላይ ቀርበው እንደሚፀድቁ ተናግረዋል፡፡ ‎ ‎በስብሰባው ላይ ከሐምሌ 1 ቀን 2016 ዓ.ም እስከ ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ያለው የማህበሩ የኦዲት ሪፖርት ቀርቧል። ‎ ‎በሪፖርቱ ማህበሩ በተጠቀሰው ጊዜ ከአገልግሎት፣ ከባንክ ወለድ፣ ከኢንቨስትመንት እና ከሌሎች ገቢዎች 159 ሚሊዮን 18 ሺህ 87 ብር ከ98 ሳንቲም ገቢ ማግኘቱ ተጠቅሷል፡፡ ‎ ‎ማህበሩ ለአስተዳደርና ለተለያዩ ጉዳዮች 96 ሚሊዮን 619 ሺህ 800 ብር ከ87 ሳንቲም ወጭ ማድረጉንም በኦዲት ሪፖርቱ ተመልክቷል። ‎ የማህበሩ የተጣራ ትርፍ 62 ሚሊዮን 398 ሺህ 287 ብር ከ11 ሳንቲም መሆኑንና ከዚህ ውስጥ በአዋጁ መሰረት 30 በመቶው መጠባበቂያ እና 10 በመቶው ለልዩ ልዩ አስተዳደራዊ ወጭዎች በማስቀመጥ ቀሪው ለአባላት እንደሚከፋፈል ተነግሯል፡፡ ‎በቀረበው የኦዲት ሪፖርት ላይ በጠቅላላ ጉባዔው አባላት ከገንዘብ አሰባሰብ፣ ከወጭ፣ ከኢንቨስትመንት፣ ከመጠባበቂያ ተቀማጭና ያልተከፋፈለ ትርፍ ጋር ተያይዞ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተዋል። ‎ለተነሱ ጥያቄዎችን ማብራሪያዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበት የኦዲት ሪፖርቱ በአብላጫ ድምጽ ጸድቋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+5

‎ተቋሙ በሩብ ዓመቱ ከ9 ሺህ ጊጋ ዋት ስዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል ‎......///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከ9 ሺህ በላይ ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማምረቱን የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ። ‎ ‎የዘርፉ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ኪዳን እንደገለፁት በሩብ ዓመቱ 10 ሺህ 354 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማምረት ታቅዶ 9 ሺህ 208 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማምረት ተችሏል። ‎ ‎ይህም የዕቅዱ 89 በመቶ መሳካቱን የሚያሳይ ሲሆን በ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከተመረተው ኃይል ጋር ሲነፃፀር ግን የ2 ሺህ 707 ጊጋ ዋት ሰዓት ብልጫ ያለው መሆኑን አብራርተዋል። ‎ ‎እንደ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ በሩብ ዓመቱ ከመነጨው ኃይል ውስጥ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ 4 ሺህ 549 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም 49 ነጥብ 4 በመቶ እንዲሁም የጊቤ ሦስት የኃይል ማመንጫ ጣቢያ 1 ሺህ 694 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም የ18 ነጥብ 4 በመቶ በማመንጨት ከፍተኛ ድርሻ እንደነበራቸው ተጠቅሷል። ‎ ‎በሩብ ዓመቱ ከመነጨው ኃይል 9 ሺህ 27 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም 98 በመቶ ከውሃ እንዲሁም 180 ነጥብ 6 ጊጋ ዋት ሰዓቱ  ወይም 2 በመቶ ከንፋስ የተገኘ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡  ‎ ‎በሩብ ዓመቱ የታላቁ ህዳሴ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ በመጠናቀቁ እና 22 የአሰላ ንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ተርባይኖች ወደ ኦፕሬሽን በመግባታቸው የማመንጨት አቅም በ2017 በጀት ዓመት ከነበረበት 7 ሺህ 919 ሜጋ ወደ 9 ሺህ 554 ሜጋ ዋት ከፍ ማለቱን ጠቅሰዋል። ‎ ‎የባለሙያዎችን አቅም በማሳደግ ጠንካራና ቀጣይነት ያላቸው የጥገና ሥራዎች በማከናወን እንዲሁም በማዕቀፍ ግዥ ጭምር የመለዋወጫ ዕቃዎች ሲቀርቡ መቆየቱንም አንስተዋል።  ‎ ‎በሩብ ዓመቱ የኃይል ማመንጫ አቅምን ከመጠቀም አንጻር የተሻለ አፈጻጸም የተመዘገበ መሆኑን የጠቆሙት ኢንጂነር ኤፍሬም የህዳሴ ኃይል ማመንጫን አቅም በተሻለ ለመጠቀም እና የግሪድ አስተማማኝነትን ለማሳደግ ተጨማሪ የማጠናከሪያ ሥራዎች መከናወን አለባቸው ብለዋል። ‎ ‎በቀጠይ 9 ወራት አማካይ የኃይል ጭነትን በማሻሻል ለበጀት ዓመቱ የታቀደውን የኃይል ምርት ግብ ለማሳካት እንደሚሰራም ተናግረዋል:: 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4

‎ተቋሙ የሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እየገመገመ ነው ‎.....///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የ2018 በጀት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ከሥራ መሪዎች ጋር በሸራተን አዲስ ሆቴል መገምገም ጀምሯል። ‎ ‎በዚህ ወቅት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለጹት የግምገማ መድረኩ በሩብ ዓመቱ የተመዘገቡ ስኬቶችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በመለየት ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ነው። ‎ ‎በ2018 በጀት ዓመት ሕዳሴን ማስመረቅ ጨምሮ ትልልቅ ስኬቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። ‎ ‎በሩብ ዓመቱ ያጋጠሙ እጥረቶች ላይ የተቋሙ አመራር የጋራ መረዳት በመያዝ ለተሻለ ውጤት መስራት እንዳለበት አሳስበዋል። ‎ ‎ በግምገማ መድረኩ ሁሉም ዘርፎች የሩብ ዓመቱን ዕቅድ አፈጻጸም የሚያቀርቡ ሲሆን እኛም እየተከታተልን መረጃውን የምናደርሳችሁ ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም

‎ተቋሙ የሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እየገመገመ ነው፤ ‎.....///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የ2018 በጀት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ከሥራ መሪዎች ጋር በሸራተን አዲስ ሆቴል መገምገም ጀምሯል። ‎ ‎በዚህ ወቅት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለጹት የግምገማ መድረኩ በሩብ ዓመቱ የተመዘገቡ ስኬቶችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በመለየት ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ነው። ‎ ‎በ2018 በጀት ዓመት ሕዳሴን ማስመረቅ ጨምሮ ትልልቅ ስኬቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። ‌‎ተቋሙ የሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እየገመገመ ነው ‎.....///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የ2018 በጀት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ከሥራ መሪዎች ጋር በሸራተን አዲስ ሆቴል መገምገም ጀምሯል። ‎ ‎በዚህ ወቅት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለጹት የግምገማ መድረኩ በሩብ ዓመቱ የተመዘገቡ ስኬቶችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በመለየት ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ነው። ‎ ‎በ2018 በጀት ዓመት ሕዳሴን ማስመረቅ ጨምሮ ትልልቅ ስኬቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። ‎ ‎በሩብ ዓመቱ ያጋጠሙ እጥረቶች ላይ የተቋሙ አመራር የጋራ መረዳት በመያዝ ለተሻለ ውጤት መስራት እንዳለበት አሳስበዋል። ‎ ‎ በግምገማ መድረኩ ሁሉም ዘርፎች የሩብ ዓመቱን ዕቅድ አፈጻጸም የሚያቀርቡ ሲሆን እኛም እየተከታተልን መረጃውን የምናደርሳችሁ ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+5

የአራት ጥናቶች ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ተካሄደ፤ ‎....///.... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር የሚያሰራቸው አራት ጥናቶች ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ተካሂዷል። ‎ ‎አራቱ ጥናቶች የሠራተኞችና የባለድርሻ አካላት እርካታ፣ በተቋማዊ ባህል እና የሠራተኞች ለሥራ መሰጠት ላይ የሚያተኩሩ ናቸው። ‎ ‎በፕሮግራሙ ላይ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደገለጹት እንደሀገር ሁሉን አቀፍ እድገት ለማምጣት የኃይል አቅርቦቱን እና ተደራሽነቱን ማሳደግ ወሳኝ ነው። ‎ ‎ለዚህም ተቋሙ በጥናት ላይ ተመስርቶ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻልና ተልዕኮውን ለማሳካት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጋር በአቅም ግንባታና በጥናትና ምርምር ጨምሮ በተለያዩ መስኮች በትብብር እየሠራ መሆኑን አብራርተዋል። ‎ ‎ጥናቱ በአጭር ጊዜ ተጠናቆ ወደ ተግባር በመቀየር በተቋሙ ዘላቂ ለውጥ ለማምጣት የሥራ አመራሩ ዝግጁ መሆኑንና አስፈላጊውን ትብብር እንደሚያደርግ አስገንዝበዋል። ‎ በተቋሙ የጥናትና ምርምር ሥራ አስኪያጅ አቶ ቢትወደድ ገብረአሊፍ በበኩላቸው የውይይቱ ዓላማ ዩኒቨርሲቲው ጥናት ለማድረግ ከስምምነት በተደረሰባቸው በአራቱ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ጥናቱ መጀመሩን ለማብሰርና ባለድርሻ አከላትም ይሄን አውቀው ትብብር እንዲያደርጉ ለማሳወቅ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ጥናቱ ተቋሙ ከሠራተኞችና ባለድርሻ አካላት እርካታ፣ ከተቋማዊ ባህል እና የሠራተኞች ለሥራ መሰጠት አንጻር አሁን ላይ ያለበትን ነባራዊ ሁኔታ በመለየት በቀጣይ መሻሻልና መለወጥ ያለባቸውን ጉዳዮች የሚያመላክት መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ‎ጥናቶች በምን መልኩ እንደሚካሄዱ የመነሻ ጽሁፍ በጥናቱ ተሳታፊና በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢነርጅ ኢኮኖሚ መምህር በሆኑት አቶ ኤፍሬም አንዳርጌ ቀርቧል። ‎ ጥናቱ ሀገሪቱ በኃይል ልማት ዘርፉ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም የኃይል ተደራሽነቱን ለማስፋት እና የአፍሪካ ሀገራትን በኃይል ለማስተሳሰር የተያዘውን እቅድ ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ዩኒቨርሲቲው የራሱን ድርሻ እንዲወጣ የሚያስችለው ነው ብለዋል።‎ ‎እንደ አቶ ኤፍሬም ገለጻ የጥናት ማስጀመሪያ ውይይቱ በጥናቱ ሂደት ላይ በተቋማቱ መካከል የጋራ መረዳት እንዲኖር የሚያስችል ነው፡፡ ዩኒቨርስቲው ጥናቱን በአጭር ጊዜ አጠናቆ ለማቅረብ ከተቋማቱና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡ የጥናት ማስጀመሪያ ውይይቱ ተሰታፊዎች ጥናቱ መደረጉ በጣም ጠቃሚ መሆኑን በመጥቀስ የደንበኛ እርካታ ለብቻው ተካቶ የሚሰራበት መንገድ ቢኖር የሚል ሀሳብ አቅርበዋል። ‎ ‎በተጨማሪም ከናሙና አመራረጥና መጠን፣ ለርዕሰ ጉዳዮቹ ከተሰጣቸው ጊዜ፣ ከጥናቱ ሞዴል፣ ከመረጃ አሰባሰብ ዘዴዎች ጋር በተያያዘም ጥያቄዎችና አስተያየቶችን አንስተው ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

photo content
+9

ማሳሰቢያ .....///..... የገናሌ ዳዋ 3ኛ የኃይል ማመንጫ ግድብ ውሃ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በመምጣቱ ምክንያት የግድቡን ደህንነት ለማስጠበቅ ሲባል ውሃውን ከጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም.
ማሳሰቢያ .....///..... የገናሌ ዳዋ 3ኛ የኃይል ማመንጫ ግድብ ውሃ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በመምጣቱ ምክንያት የግድቡን ደህንነት ለማስጠበቅ ሲባል ውሃውን ከጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ላልተወሰኑ ቀናት መልቀቅ አስፈልጓል፡፡ ስለሆነም በሊበን እና መዳወላቡ ወረዳዎች ኮባዲ፣ ሚኤሳ፣ መዳ፣ ኦዳ ቦጂ፣ እና ቢድሬ ቀበሌዎች እና በአካባቢያቸው ያሉ ነዋሪዎች የሚለቀቀው ደራሽ ውሃ በሰውም ሆነ በእንሰሳት ላይ ጉዳት እንዳያደርስ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ በአክበሮት እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም

በሩብ ዓመቱ ዘርፉ የተቋሙን ጥቅም የሚያስጠብቁ ሥራዎችን አከናውኗል ………///…….. በ2018 የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የተቋሙን ጥቅም የሚያስጠብቁ የተለያዩ ተግባራት ማከናወኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮምፕሊያንስና ገቨርናንስ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ ገለጹ፡፡ ሥራ አስፈጻሚው አቶ ዱጉማ ነዳ እንደገለጹት ዘርፉ የተቋሙን ስትራቴጅክ ዕቅድ መሰረት በማድረግ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድን በሥሩ በሚገኙ መምሪያዎች እስከ ባለሙያ ድረስ በማውረድ ወደ ሥራ ገብቷል፡፡ በዚህም በመጀመሪያው ሩብ ዓመት የተቋሙን ገጽታ ከመገንባት፣ ብልሹ አሰራሮችን ከመከላከል፣ የተቋሙን ጥቅም ከማስጠበቅ፣ ግልጸኝነትንና ተጠያቂነትን ከማስፈን እንዲሁም የሴቶችን ተሳትፎ ከማሳደግ አንጻር የተለያዩ ሥራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ተናግረዋል፡፡ በሩብ ዓመቱ የባለሙያዎችን በፍርድ ቤት ተከራክሮ የመርታት አቅም በማጎልበት ከ13 ነጥብ 78 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማዳን መቻሉን ገልጸዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት 8 ቢሊዮን ብር የገንዘብ መጠን ያላቸው 260 የሚሆኑ የፍትሐ ብሔር እና የአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ እንዲሁም 108 የወንጀል ጉዳይ መዝገቦች በክርክር ሂደት ላይ እንደሚገኙም አብራርተዋል፡፡ የመንግስትንና የሕዝብን ጥቅም የማስጠበቅ ኃላፊነት በአዋጅ ከተሰጠው ከፍትህ ሚኒስቴር ጋር በመነጋገር ግምታቸው ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ በሆኑ የካሳ ጉዳዮች ዙሪያ ተቋሙን ወክሎ እንዲከራከር ስምምነት ተደርሶ ወደ ሥራ መገባቱን አቶ ዱጉማ ጠቁመዋል፡፡ በሩብ ዓመቱ በሥራ ቦታ ሥነ-ምግባር እንዲሁም በስልታዊ ኮሙዩኒኬሽን ጽንሰ ሀሳብና አስፈላጊነት ዙሪያ ለተቋሙ የሥራ መሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና መሰጠቱን አመልክተዋል፡፡ የሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ምስጢራዊነቱን በጠበቀ መልኩ ለመጠቆም የሚያስችል መተግበሪያ ወደ ሥራ መግባቱንና በዚህም 18 የሙስና ጥቆማዎች ቀርበው ምርመራ እየተካሄደባቸው እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡ የተለያዩ የኮሙዩኒኬሽን መሣሪያዎችን እንዲሁም ሁሉንም የሚዲያ አማራጮች በመጠቀም የተቋሙን ገጽታ ለመገንባት የተለያዩ ሥራዎች መከናወናቸውን የገለጹት ሥራ አስፈጻሚው ከ4 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ወጭ በማድረግ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች መከናወናቸውንም ጠቁመዋል፡፡ በተቋሙ የሚሰሩ ሴቶችን ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሥርዓተ ፆታና በአመራር ክህሎት ዙሪያ ከ200 በላይ ለሆኑ ሴት ሠራተኞችና አመራሮች ሥልጠና መሰጠቱንም አንስተዋል፡፡ የሰው ኃይል እጥረት፣ ሥልጠና በተያዘለት ጊዜ ያለማግኘት እና የሥራ ኃላፊዎች ለሚቀርብላቸው የመረጃ ጥያቄዎች በሚፈለገው ጊዜና ጥራት መረጃ ያለመስጠት ችግሮች በሩብ ዓመቱ የታዩ ችግሮች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የተቋሙን ጥቅሞች ከሚጎዱ ብልሹ አሰራሮች በመራቅ እንዲሁም ግልጸኝነትንና ተጠያቂነትን በማስፈን የተቋሙን መልካም ስም ለመገንባት ሁሉም ተቋማዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

በማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የጤና ምርመራ አገልግሎት ተሰጠ ………///……… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ዊንግስ ኦፍ ሂሊንግ ከተባለ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር በመተባበር በፅዳትና በግቢ ውበት ለተሰማሩ ሴት ሰራተኞች የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራና የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጥቷል፡፡ በተቋሙ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ እንደተናገሩት በዋና መ/ቤት በፅዳትና በግቢ ውበት ለተሰማሩ ሴት ሰራተኞች የማኀፀን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራና የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት መሰጠቱ ለሰራተኞቹ ትልቅ የጤና በረከት ነው፡፡ የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅ መሆኑን የገለፁት ወ/ሮ ሌንሴ አቅም የሌላቸው ሴት ሠራተኞች በነፃ ምርመራ እንዲያገኙ መደረጉ ሴት ሠራተኞች ከበሽታው ራሳቸውን ቀድመው ለመከላከል እንደሚያስችላቸው ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም ሴቶች በበሽታው ዙሪያ ያላቸውን ግንዛቤ  እንዲያሳድጉ ይረዳቸዋል ነው ያሉት፡፡ የዊንግስ ኦፍ ሂሊንግ ድርጅት የጤና ትምህርት አስተባባሪ ዶክተር መቅደስ መኮንን በበኩላቸው የግንዛቤ ማስጨበጫና የምርመራ አገልግሎት መሰጠቱ ለተቋሙ የሥራ ስኬት ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ በዓመት 8 ሺህ ሴቶች በበሽታው እንደሚጠቁ እንዲሁም 6 ሺህ የሚሆኑት ደግሞ ለሞት እንደሚዳረጉ ገልፀዋል፡፡ የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር በዓለማችን ሴቶችን ከሚያጠቁ የካንሰር ዓይነቶች አራተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ መሆኑን የጠቀሱት ዶክተር መቅደስ በሽታውን በህክምና መከላከል መቻሉ ከሌሎች የተለየ ያደርገዋል ፡፡ በዕለቱ 25 ለሚሆኑ ሠራተኞች በተቊሙ ዋና መ/ቤት በሚገኘው መካከለኛ ክሊኒክ የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ ተደርጎላቸዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4

የፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራ 70 በመቶ መድረሱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለፁ ……..///……. የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የሲቪል ሥራ 70 በመቶ መድረሱን የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ተናገሩ። በዛሬው ዕለት ከሚኒስትሮቻቸው ጋር የኮይሻ ፕሮጀክትን በመጎብኘት የ100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማ መጀመራቸውንም  ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው የገለፁት። ፕሮጀክቱ ከባለፈው ጉብኝት ጋር ሲነፃፀር የሚለካ የሥራ እድገት የታየበት መሆኑን እና ይህ ስኬት ለኃይል ምንጭ ዋስትና ለሚደረገው  ያላሰለሰ ጥረት ምስክር መሆኑን አስታውቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባጋሩት መረጃ እንዳስታወቁት የግድቡ ከፍታ ከመሰረቱ 128 ሜትር ደርሷል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም