es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 695 suscriptores, ocupando la posición 8 016 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 154 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 695 suscriptores.

Según los últimos datos del 30 agosto, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 145, y en las últimas 24 horas de 2, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 31.28%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 16.96% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 909 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 661 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 10.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 31 agosto, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 695
Suscriptores
+224 horas
+187 días
+14530 días
Archivo de publicaciones
‎ለዞኑ አስተማማኝ ኤሌክትሪክ ኃይል ለማቀረብ የሚያስችል ተንቀሳቃሽ የማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ ጀመረ፤ ‎......///..... ‎በኦሮሚያ ክልል ለባሌ ዞን አስተማማኝ ኤሌክትሪክ ኃይል ለማቀረብ የሚያስችል ባለ 132/15 ኪሎ ቮልት ተንቀሳቃሽ የማከፋፈያ ጣቢያ ተከላ ሥራ ተጠናቆ ሥራ መጀመሩን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። ‎ ‎በተቋሙ የደቡብ አንድ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ንጉሴ እንደገለጹት ቀደም ሲል በሮቤ ከተማ የነበረው ባለ 66 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ አቅም አነስተኛ በመሆኑ ምክንያት አካባቢው ለሁለት ዓመት በላይ ኤሌክትሪክ በፈረቃ ሲያገኝ ቆይቷል። ‎ ‎በአካባቢው የነበረውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ችግር ለመፍታት ተቋሙ ወደ ያዶት ከሚሄደው የ132 ኪሎ ቮልት ማስተላለፊያ መስመር ላይ ታፕ በማድረግ ባለ132/15 ኪሎ ቮልት ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ ተከላ ስራ ሲያከናውን መቆየቱን ተናግረዋል ‎ ‎ተቋሙ የተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያውን የተከላ ሥራ በማጠናቀቅ ከታህሣሥ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ገልጸዋል። ‎ ‎ይህም የዞኑ መቀመጫ ባሌ ሮቤ ከተማን ጨምሮ በአካባቢው ለሚገኙ ወረዳዎች በፈረቃ ሲሰጥ የነበረውን የኃይል አቅርቦት ሙሉ ለሙሉ እንደሚያስቀር አስገንዝበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ታህሳስ 25 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

“የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን ለማስፋፋት ባለፉት ዓመታት ሰፊ ኢንቨስትመንት ተካሂዷል። ለአምራች ኢንዱስትሪው የሚቀርበው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትም ከፍተኛ ለውጥ አሳይቷል። የሕዳሴ የኃይል ማመን
“የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን ለማስፋፋት ባለፉት ዓመታት ሰፊ ኢንቨስትመንት ተካሂዷል። ለአምራች ኢንዱስትሪው የሚቀርበው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትም ከፍተኛ ለውጥ አሳይቷል። የሕዳሴ የኃይል ማመንጫን ጨምሮ ሌሎች በጅምር ያሉና በሚገባ አገልግሎት እየሰጡ ያልነበሩ ማመንጫዎችን ወደ መሥመር ለማስገባት ተችሏል። በዚህም ሀገራችን ለአምራች ኢንዱስትሪው የሚያስፈልጋትን የኃይል አቅርቦት በሚገባ መሸፈን ችለናል።” የመደመር_መንግሥት (ገጽ 206) 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ታህሳስ 25 ቀን 2018 ዓ.ም

የኒውክሊየር ልማት የኢነርጂ ደህንነትን ለማረጋገጥ ሚናው የጎላ ነው …..///….. የኒውክሊየር ልማት የኃይል ስብጥሩን በማሳደግ የኢነርጂ ደህንነትን ለማረጋገጥ ሚናው የጎላ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክ
የኒውክሊየር ልማት የኢነርጂ ደህንነትን ለማረጋገጥ ሚናው የጎላ ነው …..///….. የኒውክሊየር ልማት የኃይል ስብጥሩን በማሳደግ የኢነርጂ ደህንነትን ለማረጋገጥ ሚናው የጎላ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ገለጸ፡፡ በዘርፉ የኢነርጂ ሀብት ልማት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ያለውአይቀር ማንደፍሮ እንደገለጹት የኢትዮጵያ መንግሥት የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን ጨምሮ በርካታ ጥቅሞች ያሉትን የኒውክሊየር ኃይል ለማልማትና ለመጠቀም ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ገብቷል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኒውክሊየር-ልማት-የኢነርጂ-ደህንነትን&lang=am   💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ታህሳስ 25 ቀን 2018 ዓ.ም

ሪጅኑ በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሚስተዋለውን የኃይል ጭነት መጨናነቅ ለመቅረፍ እየሰራ ነው ‎....///.... ‌‎በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚስተዋለውን የኤሌክትሪክ ጭነት መጨናነቅ ለመቅረፍ እየ
+3
ሪጅኑ በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሚስተዋለውን የኃይል ጭነት መጨናነቅ ለመቅረፍ እየሰራ ነው ‎....///.... ‌‎በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚስተዋለውን የኤሌክትሪክ ጭነት መጨናነቅ ለመቅረፍ እየሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 3 ሪጅን መምሪያ አስታወቀ። ‎ ‎የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ እስማኤል ሙዘይን እንደገለፁት ሪጅኑ ከሚያስተዳድራቸው 20 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች መካከል አስራ አንዱ የሚገኙት በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ሪጅኑ-በማከፋፈያ-ጣቢያዎች-ላይ-የሚስተዋ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ታህሳስ 24 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ ፕሮጀክቶችን በራሱ ፋይናንስ ለመገንባት የሚያስችል አቅም እየፈጠረ ነው …….///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን በራሱ የፋይናንስ አቅም ለመገንባት የሚያ
ተቋሙ ፕሮጀክቶችን በራሱ ፋይናንስ ለመገንባት የሚያስችል አቅም እየፈጠረ ነው …….///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን በራሱ የፋይናንስ አቅም ለመገንባት የሚያስችል ቁመና ላይ መድረሱን በተቋሙ የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የፋይናንስ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አለማየሁ መንግሥቱ እንዳስታወቁት የተቋሙ የፋይናንስ ቁመና በመጠናከሩ ፕሮጀክቶችን በራስ የገቢ ምንጭ የመሸፈን አቅም በከፍተኛ ሁኔታ እየተሻሻለ መጥቷል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-ፕሮጀክቶችን-በራሱ-ፋይናንስ-ለመገ&lang=am   💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ታህሳስ 23 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን በማስወገድ ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ አገኘ ……///….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት 6 ወራት አገልግሎት ከማይሰጡ ንብረቶችን በሽያጭ በማስወገድ 8
ተቋሙ አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን በማስወገድ ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ አገኘ ……///….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት 6 ወራት አገልግሎት ከማይሰጡ ንብረቶችን በሽያጭ በማስወገድ 82 ነጥብ 25 ሚሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን የንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ዘርፍ ገለጸ። በዘርፉ የንብረት አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ አቶ ታምራት ገብረመድህን እንደገለጹት ተቋሙ በ2018 በጀት ዓመት ከቁርጥራጭ ብረቶች፣ ካገለገሉ ተሸከርካሪዎችና ጎማዎች፣ ከበርሜሎች፣ ከኤሌክትሪክ ገመዶች፣ ከተለያዩ ባትሪዎችና መሰል ንብረቶች ሽያጭ ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለማግኘት አቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-አገልግሎት-የማይሰጡ-ንብረቶችን-በ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ታህሳስ 23 ቀን 2018 ዓ.ም

ለጥገና ሥራ የሚቋረጥ ኃይል እሁድ ታህሳስ 26 ቀን 2018 ዓ.ም በቃሊቲ ጂአይ ኤስ የኃይል ማከፋፈያ ጣብያ የጥገና ሥራ ይከናወናል፡፡ ስለሆነም ከጠዋቱ 1:00 እስከ ቀኑ 8፡00 ድረስ በካዲስኮ፣
ለጥገና ሥራ የሚቋረጥ ኃይል እሁድ ታህሳስ 26 ቀን 2018 ዓ.ም በቃሊቲ ጂአይ ኤስ የኃይል ማከፋፈያ ጣብያ የጥገና ሥራ ይከናወናል፡፡ ስለሆነም ከጠዋቱ 1:00 እስከ ቀኑ 8፡00 ድረስ በካዲስኮ፣ በሃና ማርያም፣ በኃይሌ ጋርመንት፣ በአፍሪካ ሲዲሲ፣ በሰፈራ ኮንዶሚኒየም፣ በማሰልጠኛ፣ በቡልቡላ፣ በገላን ጉራ፣ በኢንዱስትሪ አካባቢ፣ በአዲስ አበባ ምድር ባቡር እና አካባቢው ኤሌክትሪክ ተቋርጦ ስለሚቆይ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ከወዲሁ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል!!

የተቋሙ የፋይናንስ ሥርዓት ጤናማ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ …….///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፋይናንስ ሥርዓት በብዙ አመላካቾች ጤናማ የሚባል ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የተቋሙ የፋይናን
የተቋሙ የፋይናንስ ሥርዓት ጤናማ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ …….///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፋይናንስ ሥርዓት በብዙ አመላካቾች ጤናማ የሚባል ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የተቋሙ የፋይናንስ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስፈፃሚው አቶ አለማየሁ መንግሥቱ እንደገለፁት የተቋሙ የፋይናንስ ሥርዓት ወደጤናማ ሥርዓት የተሸጋገረው በመንግሥት የተደረጉ ድጋፎችና በተቋሙ የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች ውጤት በማስገኘታቸው ነው፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙ-የፋይናንስ-ሥርዓት-ጤናማ-ደረጃ-ላ&lang=am ‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ታህሳስ 22 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ ለዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ትግበራ ትኩረት ሰጥቷል .........///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ትግበራ ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱን በተቋሙ የዲጂታል ትራንስፎርሜ
+5
ተቋሙ ለዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ትግበራ ትኩረት ሰጥቷል .........///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ትግበራ ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱን በተቋሙ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በበለጸገው የፈተና ሥርዓት አስተዳደር መተግበሪያ ላይ የልምድ ልውውጥ አካሂደዋል። የዘርፉ ተወካይ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ጽዮን በቀለ በልምድ ልውውጥ መድረኩ ላይ እንደገለጹት መተግበሪያው በውስጥ አቅም ለምቶ ወደ ሥራ መግባቱ ተቋሙ ለዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ትግበራ የሠጠውን ትኩረት ያሳያል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-ለዲጂታል-ትራንስፎርሜሽን-ትግበራ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ታህሳስ 21 ቀን 2018 ዓ.ም

ሥልጠናው የአመራር ክህሎትን በማሳደግ የኦፕሬሽን ሥራዎችን ለማሳለጥ የሚያስችል ነው፤ ‎.....///.... ‎በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢትዮጵያ ፓወር አካዳሚ ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና የአመራር ክህሎትን በማሳደግ በሥራ ሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታትና የኦፕሬሽን ሥራዎችን ለማሳለጥ ምቹ መደላድል የሚፈጥር መሆኑን ሠልጣኝ አመራሮች ገለጹ። ‎ የኢትዮጵያ ፓወር አካዳሚ ከኃይል ማመንጫዎች፣ ሪጅኖችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለተውጣጡ የሥራ መሪዎች በ10 ዙር የሰጠው የአመራር ክህሎት ሥልጠና ተጠናቋል፡፡ ‎ ‎የደዴሳ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ተሰማ ገብሬ እና የሚዛን ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ጽጌነሽ ሞላ እንደገለጹት ሥልጠናው የአመራር ክህሎታቸውን በማጎልበት የኦፕሬሽን ሥራዎችን ለማሳለጥ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። ‎ ‎የማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጆች አብዛኞቹ የቴክኒክ ሠራተኞች በመሆናቸው ‎ከሠው ኃይል አስተዳደር፣ ከፋይናንስ፣ ከጊዜ አጠቃቀምና ከኦፕሬሸን ሥራዎች ጋር በተያያዘ የሚያጋጥሙ አስተዳደራዊ ጉዳዮችን በፍጥነት ለመፍታት ሥልጠናው እንዳገዛቸው አብራርተዋል። ‎ ተመሳሳይ የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎች ተቋማዊ ግቦችን ለማሳካት ትልቅ ተሳነሽነት የሚፈጥሩ መሆናቸውን የጠቆሙት ሰልጣኝ አመራሮቹ ሠራተኛውም በአስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ በቂ ግንዛቤ ኖሮት ሥራውን ውጤታማ በሆነ መልኩ እንዲፈጽም ሥልጠናው እስከ ታች ድረስ ሊሰጥ እንደሚገባ አሳስበዋል። ‌‎ ከህክምና፣ ከውሃ፣ ከመኪና፣ ከግብዓት ከመለዋወጫ ዕቃ አቅርቦት፣ ከሥልጠናና ልምድ ልውውጥ፣ ከሀብት አያያዝና አጠቃቀም፣ ከደንብ ልብስና ከበርሃ አባል ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች በሰልጣኝ አባላቱ ቀርበው በሚመለከታቸው አካላት ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ በተቋሙ የኢትዮ ፓወር አካዳሚ የአመራር ልማት ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ተናኜ መኮንን በሥልጠናው ማጠቃለያ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ፓወር አካዳሚው ከአመራር ክህሎትና ከአስተዳደራዊ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት፣ ብቁ የሥራ መሪዎችን ለማፍራት እና ተቋማዊ ግቦችን ለማሳካት በሚያስችሉ 7 ርዕሰ ጉዳዮች ላይ መሰጠቱን አብራርተዋል፡፡ ‎ ‎ወ/ሮ ተናኜ አክለውም ሥልጠናው በአመራሮች መካከል የልምድ ልውውጥ እንዲኖር እድል ከመፍጠሩም ባሻገር በኃይል ማመንጫዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚስተዋሉ ችግሮችን በመለየት የሥራ ክፍሎች ችግሮችን ለመፍታት በዕቅድ አካተው እንዲሰሩ ሥልጠናው የጎላ ሚና እንዳለውም ተናግረዋል፡፡ ‎  💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ታህሳስ 20 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠር ለሠራተኞች ውጤታማነትና ምርታማነት ወሳኝ መሆኑ ተጠቆመ ‎......///..... ‌‎በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠር ለሠራተኞች ውጤታማነትና ምርታማነት
+9
ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠር ለሠራተኞች ውጤታማነትና ምርታማነት ወሳኝ መሆኑ ተጠቆመ ‎......///..... ‌‎በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠር ለሠራተኞች ውጤታማነትና ምርታማነት ወሳኝ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡ ‎ ‎በተቋሙ የኮርፖሬት ገቨርናንስና ኮምፕሊያንስ ዘርፍ ሥር የሚገኙ የሥራ ክፍሎች በሆለታ ባለ 500 እና በገፈርሳ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የመስክ ምልከታ አድርገዋል። ‎ ‎በዚህ ወቅት በተቋሙ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ደረጀ አጥናፌ  እንደገለፁት የመስክ ምልከታው በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎቹ ውስጥ እየሰሩ የሚገኙ ሠራተኞች ያሉባቸውን የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመለየት እና  ሰላማዊና ውጤታማ የሥራ አካባቢ መኖሩን ለማረጋገጥ ያለመ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ምቹ-የሥራ-አካባቢ-መፍጠር-ለሠራተኞች-ውጤ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ታህሳስ 18 ቀን 2018 ዓ.ም

በዘርፉ ያለውን የሴቶች ተሳትፎ ለማሳደግ ከታዳጊ ህፃናት ጀምሮ መስራት ይገባል፤ ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ ….///…. በኤሌክትሪክ ኃይል ዘርፍ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለማሳደግ መስራት እንደሚገባ በኢ
+9
በዘርፉ ያለውን የሴቶች ተሳትፎ ለማሳደግ ከታዳጊ ህፃናት ጀምሮ መስራት ይገባል፤ ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ ….///…. በኤሌክትሪክ ኃይል ዘርፍ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለማሳደግ መስራት እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ገለጸፀ። ከደጃዝማች ወንድይራድ ትምህርት ቤት የተወጣጡ ሴት ተማሪዎች በተቋሙ የመስክ ምልከታ አካሂደዋል፡፡ በጉብኙቱ ላይ የተገኙት የመምሪያው ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ የኃይል ዘርፉን ለማሳደግ ብቃት ያለው እና በሥርዓተ ፆታ የተመጣጠነ ባለሙያ ቢያስፈልግም አሁን ላይ በዘርፉ የተሰማሩ ሴቶች ቁጥር አነስተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በዘርፉ-ያለውን-የሴቶች-ተሳትፎ-ለማሳደግ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ታህሳስ 16 ቀን 2018 ዓ.ም

አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለኢንዱስትሪ ልማት የልብ ትርታ ነው - ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) .......///........ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለኢንዱስትሪ ልማትና ለኢኮኖሚያዊ እድገት ወሳኝ
+5
አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለኢንዱስትሪ ልማት የልብ ትርታ ነው - ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) .......///........ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለኢንዱስትሪ ልማትና ለኢኮኖሚያዊ እድገት ወሳኝ መሆኑን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) ገለጹ። ዋና ስራ አስፈፃሚው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በጉባ ባዘጋጀው "ስለ ኢትዮጵያ" መድረክ የፓናል ውይይት ላይ እንደገለፁት ኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት በኃይል መሰረተ ልማት ግንባታ ላይ ያደረገችው ኢንቨስትመንት ለዛሬው ኢኮኖሚያዊ ለውጥ መሠረት ሆኗል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=አስተማማኝ-የኃይል-አቅርቦት-ለኢንዱስት&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ታህሳስ 16 ቀን 2018 ዓ.ም

ህዳሴ ለሀገር ውስጥ የኃይል አቅርቦት እና ለጎረቤት ሀገራት የኃይል ትስስር ትልቁን ሚና እየተወጣ ነው - ኢንጂነር አሸብር ባልቻ .......///...... ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለሀገር ውስ
+2
ህዳሴ ለሀገር ውስጥ የኃይል አቅርቦት እና ለጎረቤት ሀገራት የኃይል ትስስር ትልቁን ሚና እየተወጣ ነው - ኢንጂነር አሸብር ባልቻ .......///...... ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለሀገር ውስጥ የኃይል አቅርቦት እና ለጎረቤት ሀገራት የኃይል ትስስር ትልቁን ሚና እየተወጣ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ገለፁ። "ሕዳሴ ለኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ  የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በጉባ ባዘጋጀው "የስለ ኢትዮጵያ" መድረክ ላይ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለኃይል መሰረተ ልማት አቅም እና ለቀጣናዊ ትስስር በሚል ርዕስ የውይይት መነሻ ሀሳብ አቅርበዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ህዳሴ-ለሀገር-ውስጥ-የኃይል-አቅርቦት-እና&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ታህሳስ 16 ቀን 2018 ዓ.ም

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ ትስስር .....///..... ትልቅ የታሪክ እጥፋት የፈጠረ፣ ለኢትዮጵያውያን የጋራ አንድነት ማረጋገጫ የሰጠና የታሪካዊ ድሎች ትልቅ ማሳያ መሆ
+5
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ ትስስር .....///..... ትልቅ የታሪክ እጥፋት የፈጠረ፣ ለኢትዮጵያውያን የጋራ አንድነት ማረጋገጫ የሰጠና የታሪካዊ ድሎች ትልቅ ማሳያ መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አስታወቁ። "ሕዳሴ ለኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ  የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ያዘጋጀው "የስለ ኢትዮጵያ" መድረክ በጉባ እየተካሄደ ይገኛል። የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን በመድረኩ መክፈቻ ላይ እንደተናገሩት፤ ግድቡ የሕብረ ብሔራዊ አብሮነት ማጠናከሪያ፣ የብልጽግና አይቀሬነት ማሳያና የኢትዮጵያ የማንሰራራት ምልክት ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ታላቁ-የህዳሴ-ግድብ-ለምስራቅ-አፍሪካ-ትል&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ታህሳስ 16 ቀን 2018 ዓ.ም

በኃይል መሠረተ ልማት ላይ ስርቆት የፈጸሙ ተጠርጣሪዎች በሕግ በቁጥጥር ስር ዋሉ ....///.... በጎፋ ዞን ደምባ ጎፋ ወረዳ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ ስርቆት የፈጸሙ ተጠርጣሪዎች በሕግ ቁጥ
+3
በኃይል መሠረተ ልማት ላይ ስርቆት የፈጸሙ ተጠርጣሪዎች በሕግ በቁጥጥር ስር ዋሉ ....///.... በጎፋ ዞን ደምባ ጎፋ ወረዳ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ ስርቆት የፈጸሙ ተጠርጣሪዎች በሕግ ቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የወረዳው ፖሊስ ጽሕፈት ቤት ገለጸ። የጽ/ቤቱ አዛዥ ተወካይ ዋ/ሣጅን ያዕቆቦ ካሳሁን እንደገለጹት ተጠርጣሪዎቹ ጨለማን ተገን በማድረግ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ብረቶችን በቡድን በመስረቅ ወንጀል  ተጠርጥረው በኦፕሬሽን ሥራ በሕግ  ቁጥጥር ስር ውለዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በኃይል-መሠረተ-ልማት-ላይ-ስርቆት-የፈጸሙ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ታህሳስ 16 ቀን 2018 ዓ.ም

በተቋሙ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በጥናት ላይ ተመስርቶ መፍታት ይገባል - አቶ ሙላት ገዛኸኝ ……..///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚያጋጥሙ ችግሮችን በጥናት ላይ ተመስርቶ መፍታት እንደሚገባ
+4
በተቋሙ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በጥናት ላይ ተመስርቶ መፍታት ይገባል - አቶ ሙላት ገዛኸኝ ……..///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚያጋጥሙ ችግሮችን በጥናት ላይ ተመስርቶ መፍታት እንደሚገባ የተቋሙ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ ገለፀ፡፡ የኢትዮ ፓወር አካዳሚ ከአዲስ አባባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር “በኢትዮ ኬኒያ ከፍተኛ ቮልቴጅ የቀጥታ መስመር ላይ ያሉ የኦፕሬሽን ተግዳሮቶች እና መፍትሄዎች” በሚል ርዕስ በተዘጋጀ ጥናታዊ ጽሑፍ ዙሪያ አውደ ጥናት ተካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በተቋሙ-የሚያጋጥሙ-ችግሮችን-በጥናት-ላይ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ታህሳስ 14 ቀን 2018 ዓ.ም

ህዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም