es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 696 suscriptores, ocupando la posición 8 017 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 152 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 696 suscriptores.

Según los últimos datos del 31 agosto, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 142, y en las últimas 24 horas de 2, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 30.85%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 16.42% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 842 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 578 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 10.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 01 septiembre, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 696
Suscriptores
+224 horas
+237 días
+14230 días
Archivo de publicaciones
photo content
+7

በዘርፉ የሴቶችን ተሳተፎ ማሳደግ እንደሚገባ ተገለፀ …….///….… በኢትዮጵያ የኢነርጂ ዘርፍ ውስጥ የሴቶችን ተሳትፎ እና የውሳኔ ሰጪነት ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሴቶች የኢነርጂ ባለሙያዎች ማህበር (EWiEN) ለአምስተኛ ጊዜ በኢነርጂ ዘርፍ ላይ ያተኮረ ዓመታዊ መርሃግብር በሒልተን ሆቴል እያካሔደ ይገኛል። በመርሃግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተወካይ ወንድወሰን ካሳ (ዶ/ር) እንደተናገሩት ተቋሙ ሴቶች በኢነርጂ ዘርፉ ውስጥ የሚኖራቸውን ሚና እና ተፅዕኖ ፈጣሪነት ለማሳደግ እየሰራ ይገኛል። ተቋሙ የኢትዮጵያ ሴቶች የኢነርጂ ባለሙያዎች ማህበር ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱን ገልፀዋል። እንደ ወንድወሰን(ዶ/ር) ገለፃ መርሃግብሩ ሴቶች በዘርፉ ላገኙት ስኬት ዕውቅና ከመስጠት ጎን ለጎን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የአቅም ማሳደግ ሥራዎችን ለመስራት ያግዛል። ማህበሩ በዘርፉ የሴት ባለሙያዎችን ዕድገት እና ተሳትፎ ከፍ ለማሳደግ እያደረገ ያለውን ጥረት እንደሚያደንቁ ገልፀው ተቋሙ በሁሉም ደረጃዎች የሴት ባለሙያዎችን ቁጥር ለመጨመር በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። በመርሃግብሩ ላይ በኢነርጂ ዘርፍ ላይ የተሳተፉ ተቋማትና ድርጅቶች ምርታቸውንና አገልግሎታቸውን የሚያስተዋውቁበት አውደርዕይ የተከፈተ ሲሆን በዘርፉ የሴቶች ተሳትፎ ዕድገት ላይ ትኩረቱን ያደረገ የፓናል ውይይትም እየተካሔደ ይገኛል። ማህበሩ በዓመቱ በኢነርጂ ዘርፍ ላይ በፈጠራና በአስተዳደር እንዲሁም በልዩ ልዩ ደረጃዎች ተፅዕኖ ለፈጠሩ ሴቶች ዕውቅና ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል። የኢትዮጵያ ሴቶች የኢነርጂ ባለሙያዎች ማህበር (EWiEN) በኢነርጂ ዘርፍ ያለውን የሥርዓተ-ፆታ ክፍተት ለማመጣጠን በማሰብ በአምስት ሴት ባለሙያዎች የተመሠረተ ለትርፍ ያልተቋቋመና መንግሥታዊ ያልሆነ ማህበር ነው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+7

ጣቢያው ተጨማሪ ደንበኞችን እየጠበቀ ነው …….///……. የቀብሪደሃር ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ተጨማሪ የኃይል ፈላጊ ደንበኞችን እየጠበቀ እንደሚገኝ አስታወቀ፡፡ የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ኢብራሂም ሰዒድ እንደገለፁት ጣቢያው 22 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት ኃይል የመጫን አቅም ቢኖረውም በአሁኑ ወቅት ለደንበኞች እያቀረበ ያለው 3 ነጥብ 3 ሜጋ ዋት ኃይል ብቻ ነው፡፡ ቀሪው 19 ነጥብ 2 ሜጋ ዋት ኃይል አዲስ ደንበኞችን እየጠበቀ እንደሚገኝ ነው ሥራ አስኪያጁ የተናገሩት፡፡ ሥራ አስኪያጁ እንደገለፁት በቀብሪደሃር ከተማና በዙሪያው የሚገኙ አስራ ሁለት ቀበሌዎች ከጣቢያው የኤሌክትሪክ ኃይል እየቀረበላቸው ሲሆን ሽላቦ፣ ላሰንከሪ እና ዋርዴር ከተሞች ከማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል በማግኘት ላይ ናቸው፡፡ በ2012 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረው የቀብሪደሃር ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ከጎዴ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ 132 ኪሎ ቮልት ገቢ መስመር ኃይል የሚቀበል ሲሆን አንድ ባለ 25 ሜጋ ቮልት አምፒር አንድ የኃይል ትራንስፎርመር አለው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+5

🌍 Africa’s rivers are unlocking a clean-energy revolution! …….///……. Africa holds 17% of the world’s hydropower potential, yet only a small portion has been developed. This means the power to transform our future is already flowing across the continent. Ethiopia is at the forefront with landmark projects like GERD, Gibe III, Koysha, and Genale Dawa III—turning natural water resources into reliable, renewable energy that lights homes, drives industries, and strengthens regional cooperation. Hydropower delivers more than electricity: 💧 Stabilizes solar and wind 💧 Strengthens climate resilience 💧 Fuels economic growth 💧 Expands access to electricity 💧 Supports peace & regional integration Africa’s rivers shaped our history—now they can shape a cleaner, brighter, net-zero future for all. ⚡️ 👉 Read the full article here: https://www.eep.com.et/?article=the-conductors-current-how-africas-rivers-are-powering-a-net-zero-future #AfricaEnergy #Hydropower #Ethiopia #SustainableDevelopment #CleanEnergyFuture 💡 "Clean Energy for a Better Life!" 📌Facebook: https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌Telegram: https://t.me/EEPCommuication 📌Twitter: https://twitter.com/EEPethiopia 📌 LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power-የኢትዮጵያ-ኤሌክትሪክ-ኃይል 📌YouTube: https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌TikTok: https://tiktok.com/@ethio_power 📌 Website: https://www.eep.com.et ህዳር 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

ጣቢያው ለጅግጅጋና አካባቢው ነዋሪዎች አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ ነው ……///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጅግጅጋ ማከፋፈያ ጣቢያ ለአካባቢው ነዋሪዎች እና በከተማዋ ዙሪያ ለሚገኙ ኢንዱስትሪዎች አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ፡፡ የጣቢያው ኃላፊ አቶ ደምለው ተሾመ እንዳስታወቁት 60 ሜጋ ዋት የመጫን አቅም ያለው የማከፋፈያ ጣቢያው በስምንት ወጪ መስመሮች ለክልሉ ዋና ከተማ ጅግጅጋና ለአካባቢው ከተሞች 30 ሜጋ ዋት ኃይል እያቀረበ ይገኛል፡፡ ጣቢያው በ 33 ኪሎ ቮልት ለፋፈም፣ ለቶጎ ጫሌ፣ ለቀብሪበያህ፣ ለጭናክሰን እና በአከባቢው ለሚገኙ ከተሞች አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ጣቢያው ካለው አቅም 30 ሜጋ ዋት የሚሆነው ደምበኞችን በመጠባበቅ ላይ በመሆኑ  ባለሀብቶች በአቅራቢያቸው የተዘጋጀላቸውን ኃይል እንዲጠቀሙበት ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል፡፡ እንደ አቶ ደምለው ገለፃ ጣቢያው አንድ ባለ 25 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመር እና ሁለት ባለ 31 ነጥብ 5 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች አሉት፡፡ የጅግጅጋ ማከፋፈያ ጣቢያ በ132 ኪሎ ቮልት ከሐረር ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ተቀብሎ መልሶ በ132 ኪሎ ቮልት ለደገሀቡር ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ያስተላልፋል፡፡ ጣቢያው ከ1997 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም ለማሳደግና ለማዘመን እየተሰራ ነው .....///...... የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም ለማሳደግና ለማዘመን እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡ በተቋሙ የማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን ወ/ማርያም እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ በ24 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የ15 አና 33 ኪሎ ቮልት ስዊችጊሮችን ለማዘመን ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል። በበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት በሆርማት፣ አዋሽ 7 ኪሎ፣ ወልቂጤ፣ ኮምቦልቻ፣ ወላይታ ሶዶ አንድ እና ዓለም ከተማ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የማዘመን ሥራው ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን አብራርተዋል። ተጨማሪ ደንበኞችን ማስተናገድ የማይችሉ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በመለየት የአቅም ማሳደግ ሥራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኙ ዳይሬክተሩ አንስተዋል። በአሁኑ ወቅትም በሱሉልታ፣ ኮምቦልቻ ሁለት፣ ለገጣፎ፣ ጅማ እንዲሁም በሚዛን እና ባሌ ሮቤ ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ከ50 እስከ 250 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮች እየተተከሉ እንደሚገኙ አብራርተዋል፡፡ የአቅም ማሳደግ ያስፈልጋቸዋል ተብለው በተለዩ ሌሎች የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ተመሳሳይ ሥራዎችን ለማከናወን የትራንስፎርመር ግዥ በሂደት ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ለጥገና አገልግሎት የሚያገለግሉ መለዋወጫ ዕቃዎች፣ የ15 እና 33 ኪሎ ቮልት ብሬከሮች፣ ባትሪዎች እንዲሁም የሆለታ እና ደዴሳ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የቮልቴጅ መዋዥቅ ለማስተካከል የሚረዳ የSVC መለዋወጫ ዕቃዎች እና የከፍተኛ ቮልቴጅ መለዋወጫ ዕቃዎች በተቋሙ መጋዘን መኖራቸውን ገልፃዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ የዕቃ ማንሻ ክሬኖችን ጨምሮ ለኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች አስፈላጊ የሆኑ ሌሎች የመለዋወጫ ዕቃዎችንና መሣሪያዎችን ለማሟላት በግዥ ሂደት ላይ ይገኛሉ፡፡ በማከፋፈያ ጣቢያዎች ያለአግባብ የተቀመጡ ንብረቶችን በሥርዓት ለማስቀመጥ የሚያስችሉ 17 የዕቃ ግምጃ ቤቶች በስምንት ሪጅኖች ላይ እየተሰሩ ሲሆን ከነዚህም መካከል የከምሴ፤ ኮምቦልቻ ሁለት፤ አንፎ ሜዳ፤ ጅጅጋ እና የሐዋሳ ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያ የዕቃ ግምጃ ቤቶች መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል። በመጀመሪያው ሩብ ዓመት የአደጋ ጊዜ የከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን (emergency restoration tower) ወደ ሥራ ለማስገባት የባለሙያዎችን አቅም የሚያሳድግ የተግባር ላይ ሥልጠና በመስጠት አሁን ላይ ሥራው ሙሉ በሙሉ በራስ አቅም እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። ለተቋሙ ፈተና የሆነውን የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ የብረት ምሰሶ ስርቆት ለመከላከልና በግሪድ ሥርዓቱ ላይ የሲስተም መረበሽ እንዳያጋጥም ችግሩ በስፋት የሚስተዋልባቸው ቦታዎችን በመለየት የፍተሻ ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡ ተቋሙ በ13 ሪጅኖች 145 ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ያስተዳድራል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 16 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+1

ጣቢያው ከዕቅድ በላይ ማመንጨቱን ገለፀ …….///…….       የግልገል ጊቤ 1 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት አራት ወራት 440 ነጥብ 3 ጊጋ ዋት ሠዓት ኤሌክትሪክ ማመንጨቱን አስታወቀ፡፡ የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ንጉሳ እንደገለጹት ጣቢያው 425 ነጥብ 7 ጌጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ለማመንጨት አቅዶ 440 ነጥብ 3  ጌጋ ዋት ሰዓት በማመንጨት ከዕቅዱ በላይ 3 ነጥብ 42 በመቶ አሳክቷል፡፡ ጣቢያው ያመነጨው ኃይል ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት  ጋር ሲነጻጸር የ24 በመቶ ብልጫ ማሳየቱን አቶ ደሳለኝ   ገልፀዋል፡፡ አስፈላጊ የጥገና ሥራዎች ቀድመው በመከናወናቸው፣  ሁሉም ተርባይኖች በሙሉ አቅማቸው በመስራታቸው  እና ግድቡ በቂ የውሃ በመያዙ አፈፃፀሙን ከፍ ማለቱን አቶ ደሳለኝ አክለው ተናግረዋል ። እንደ ኃላፊው ገለፃ የጣቢያውን ደህንነት ለመጠበቅና  በበጀት ዓመቱ የታቀደውን የኤሌክትሪክ ኃይል ምርት ለማምረት የሚያስችሉ በቂ የጥገና ሥራዎች ተሰርተዋል፡፡ ለበጀት ዓመቱ የታቀደው የኃይል ምርት ለማሳካት ግድቡ በቂ ውሃ መያዙን  ጠቁመዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 16 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+2

የስኳር ህመምን ለመከላከል ጤናማ የኑሮ ዘይቤ መከተል ይገባል .......///........ የስኳር ህመምን ለመከላከል ጤናማ የኑሮ ዘይቤ መከተል እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል  የጤና አገልግሎት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ክሊኒኩ የዓለም የስኳር ህመም ቀንን አስመልክቶ ከአዲስ ህይወት ጠቅላላ ሆስፒታል ጋር በመተባበር ነፃ የስኳር ህመም እና ተዛማጅ በሽታዎች የቅድመ ልየታ ምርመራ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቶችን በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት እና በአዲስ አበባ ዙሪያ ለሚገኙ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ሰጥቷል። የተቋሙ የጤና አገልግሎት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ መሠረት ሙሉጌታ  እንደገለፁት የቅድመ ልየታ ምርመራ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቱ ለድንገተኛ ህልፈት በሚዳርጉ የስኳር እና ሌሎች ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች የሚጠቁ ሠራተኞችን ቁጥር ለመቀነስ ያለመ ነው። በዓለም አቀፍ ደረጃ ለድንገተኛ ህልፈት በሚዳርጉ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች የሚጠቁ የህብረተሰብ ክፍሎች ቁጥር እየጨመረ መጥቷል። የቅድመ ልየታ ምርመራው የስኳር ህመም እና ተዛማጅ በሽታዎችን አስቀድሞ በመለየትና አስፈላጊውን የህክምና ክትትል በማድረግ መከላከል እንዲያስችል መሆኑንም ተናግረዋል። ክሊኒኩ ሠራተኞች ጤንነታቸው ተጠብቆ በሥራቸው ውጤታማ እንዲሆኑ ለማስቻል የተለያዩ ጤና ተኮር መርሃ ግብሮችን ቀርፆ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝም ነው የተናገሩት። በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል ጠቅላላ ሐኪም ዶ/ር ሜሮን ደበበ እንደተናገሩት በዓለም ላይ በስኳር ህመም የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ይገኛል። የስኳር ህመም የሚከሰተው ሰውነት አስፈላጊውን ስኳር በትክክል መጠቀም ሳይችል ሲቀር መሆኑን ያነሱት ዶ/ር ሜሮን ታካሚዎች አስፈላጊውን ህክምና እና እንክብካቤ ካገኙ በተሟላ ጤንነት የመኖር ዕድል እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡ የስኳር ህመም ዓይነት አንድ፣ ዓይነት ሁለትና በእርግዝና ጊዜ የሚከሰት በመባል በሦስት እንደሚከፈል ገልፀው የዓይነት አንድ የስኳር ህመም ቆሽት የተባለው የሰውነት ክፍል የሚያመርተው የኢንሱሊን ንጥረ ቅመም አነስተኛ መሆን አሊያም ማምረት ሲያቆም የሚከሰት እንደሆነ አብራርተዋል፡፡ እንደ ዶ/ር ሜሮን ገለፃ የስኳር ህመም ከተከሰተ በኋላ ተገቢውን ህክምናና ክትትል አለማድረግ ለልብ፣ ለኩላሊት እና ለነርቭ እንዲሁም ለዐይነ ስውርነት ሊያጋልጥ ይችላል፡፡ ከፍተኛ የሆነ የካርቦሃይድሬት መጠን ያላቸውን እና በፋብሪካ የተመረቱ ምግቦችን አብዝቶ መመገብ፣ ቅባትነት ያላቸውን ምግቦች ማዘውተር፣ አልኮል አብዝቶ መጠጣት እና ሲጋራ ማጨስ እንዲሁም የሰውነት ክብደት ደረጃን አለመቆጣጠር ለስኳር በሽታ አጋላጭ መሆናቸውንም ነው የገለፁት፡፡ ሰውነታችን ያለውን የስኳር መጠን በማወቅ፣ የመከላከያ ዘዴዎችን በመጠቀም፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማድረግ እንዲሁም ጤናማ ሥርዓተ ምግብን በመከተል የስኳር ሕመምን መከላከል እንደሚገባም ዶ/ር ሜሮን አመልክተዋል።                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                        💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 12 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ቀድሞ መከላከል እንደሚያስፈልግ ተገለፀ ……///….. ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ሥርጭት ለመቀነስ የመከላከያ ዘዴዎችን ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጤና አገልግሎት ቢሮ አስታወቀ፡፡ ለአዳማ አንድ እና ሁለት ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሠራተኞች ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን አስመልክቶ የምርመራና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ ላይ የጤና አገልግሎት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ መሠረት ሙሉጌታ እንደተናገሩት እንደ ስኳር እና ደም ግፊት ያሉ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ሥርጭት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ ይገኛል፡፡ ከ70 በላይ ለሚሆኑ የሁለቱ ኃይል ማመንጫ ሠራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና የሰጡት የዮያ አጠቃላይ ሆስፒታል የማርኬቲንግ ኃላፊ እና ጠቅላላ ሐኪም ዶክተር ሮሒ ከበደ በየጊዜው እያደገ የመጣውን የስኳር በሽታ ቀድሞ ለመከላከል የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ እና የተመጣጠነ የአመጋገብ ስርዓት መከተል እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የስኳር በሽታ የተለያዩ ደረጃዎች እንዳሉት የገለፁት ዶክተር ሮሒ ቶሎ ቶሎ የሽንት መምጣት፣ የምግብ ፍላጎት መጨመር እና የዐይን ብዥታ ዋና ዋና የስኳር በሽታ ምልክቶች መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡ የስኳር በሽታ እና የደም ግፊት በሽታዎች ተወራራሽ ባህሪ ያላቸው በመሆናቸው እንደጋንግሪን፣ የልብ ህመም እና የኩላሊት በሽታዎችን ስለሚያስከትሉ አስቀድሞ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡ የሆስፒታሉ አስተዳደር ኃላፊና የማህበረሰብ ጤና ስፔሻሊስት ንጉሴ ከበደ በበኩላቸው ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ለመከላከል ከአልኮል መጠጥ መራቅ፣ አትክልት ፍራፍሬ አዘወትሮ መመገብ፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረግ እና ሲጋራ አለማጨስ ወሳኝ እርምጃዎች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ቀድሞ መከላከል ተመራጭ ዘዴ መሆኑን የገለፁት ኃላፊው በበሽታው የተያዙ ሰዎች ለስኳር በሽታም ሆነ ለደም ግፊት የሚታዘዙ መድሃኒቶችን በአግባቡ መውሰድ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት፡፡ በአዳማ አንድ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በተካሄደው በዚህ መርሐ ግብር ለ52 ሠራተኞች የደም ግፊት እና የስኳር በሽታ ምርመራ ተከናውኗል፡፡                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                        💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 11 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

𝗧𝗵𝗲 𝗘𝗮𝗿𝘁𝗵’𝘀 𝗣𝘂𝗹𝘀𝗲: 𝗛𝗼𝘄 𝗘𝘁𝗵𝗶𝗼𝗽𝗶𝗮 𝗶𝘀 𝘁𝗮𝗽𝗽𝗶𝗻𝗴 𝗶𝗻𝘁𝗼 𝗚𝗲𝗼𝘁𝗵𝗲𝗿𝗺𝗮𝗹 𝗣𝗿𝗼𝗺𝗶𝘀𝗲 What if the key to a sustainable future lies deep beneath our feet? Ethiopia is answering that question with visionary policy and bold investment in geothermal energy turning the Earth’s inner heat into a beacon of clean power. Read more 👇 https://www.linkedin.com/feed/update/urn:li:activity:7397234113319059456 💡 "Clean Energy for a Better Life!" 📌Facebook: https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌Telegram: https://t.me/EEPCommuication 📌X: https://twitter.com/EEPethiopia 📌 LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power-የኢትዮጵያ-ኤሌክትሪክ-ኃይል 📌YouTube: https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌TikTok: https://tiktok.com/@ethio_power 📌 Website: https://www.eep.com.et

ተቋሙ በአደጋ ሰለባ ለሆኑ ቤተሰቦች ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለፀ ……..///…..… ከወራት በፊት ወደ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሲጓጓዝ ወድቆ በነበረው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ትራንስፎርመር ህይታቸውን ላጡ እና የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች እና ቤተሰቦቻቸው ድጋፍ ለማድረግ መወሰኑን በተቋሙ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደገለፁት በአዲስ አበባ መውጫ እንጦጦ ፍተሻ አካባቢ ከወራት በፊት በደረሰው አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በሁለት ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡ የደረሰውን ጉዳት ተከትሎ የዕቃ አቅራቢ ኩባንያው በወቅቱ  ለአደጋው ሰለባዎች እና ቤተሰቦች የካሳ ክፍያ መፈፀሙን ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልም እንደ ተቋም ማህበራዊ ኃላፊነቱን ከመወጣት አንፃር ለተጎጂ ቤተሰቦች ድጋፍ እንዲያደርግ በተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ይሁንታ ማግኘቱን ገልፀዋል፡፡ እንደ ኃላፊው ገለፃ የተጎጂ ቤተሰቦችን የኑሮ ሁኔታ እና በሥራ ላይ ያሉ የካሳ ክፍያ ህጎችን ባገናዘበ መልኩ  ተቋሙ ለተጎጂዎች እና ለቤተሰቦቻቸው ከአምስት ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ወስኗል፡፡ በተጨማሪም ለተጎጂ ቤተሰቦች እና ልጆቻቸው በተቋሙ የሥራ ዕድል እንዲመቻችላቸው እንዲሁም በትምህርት ላይ ያሉ ልጆቻቸው ትምህርታቸውን  እስኪያጠናቅቁ ድረስ  ዘለቄታዊ ድጋፍ ለማድረግ ተቋሙ እንደሚሰራ ጠቁመዋል፡፡   እንደ አቶ ሙላት ገለፃ የተጎጂ ቤተሰቦች ህጋዊ የወራሽነት መብታቸውን የሚያረጋግጥላቸውን የፍርድ ቤት ውሳኔ ለተቋሙ ሲያቀርቡ የተፈቀደው ድጋፍ ተግባራዊ ይደረግላቸዋል፡፡                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                        💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 10 ቀን 2018 ዓ.ም