EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 555 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 397,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 165 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 555 名订阅者。
根据 21 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 10,过去 24 小时变化为 1,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.74%。内容发布后 24 小时内通常能获得 14.94% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 003 次浏览,首日通常累积 2 323 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 22 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 555
订阅者
+124 小时
+87 天
+1030 天
帖子存档
15 555
የተሽከርካሪ ስምሪት እና ቁጥጥርን ለማዘመን እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ውጤት እየተገኘባቸው ነው
………///……….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሸከርካሪ ስምሪት እና ቁጥጥርን ለማዘመን የተገበራቸው የአሰራር ስርዓቶች ውጤት እየተገኘባቸው መሆኑን በተቋሙ የተሽከርካሪ አስተዳደር ቢሮ ገለፀ።
የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደገለፁት ተቋሙ የተሸከርካሪዎችን ስምሪት ለማሳለጥ እና የቁጥጥር ስርዓቱን ለማዘመን የጂ.ፒ.ኤስ ቴክኖሎጂ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል፡፡
የጂ.ፒ.ኤስ ቴክኖሎጂ ተግባራዊ ከመደረጉ በፊት ተሽከርካሪዎች የመስክ ሥራቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ያለ ሥራ የሚቀመጡበት ጊዜ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
ይህም የተሸከርካሪ እጥረት እንዲከሰት በማድረግ የሥራ ክፍሎች ሥራቸውን በዕቅዳቸው መሰረት እንዳያከናውኑ እንቅፋት ሆኖ እንደነበር አቶ ዋለ ተናግረዋል፡፡
በተሸከርካሪ ስምሪት እና ቁጥጥርን ላይ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በአሁኑ ወቅት በተቋሙ ካሉ 1 ሺህ 40 ተሸከርካሪዎች መካከል 500 በሚሆኑት ላይ ጂ.ፒ.ኤስ መገጠሙንም ነው ያስታወቁት፡፡
ተሸከርካሪዎችን በቴክኖሎጂ በመከታተል ሥራቸውን ጨርሰው ሲመለሱ ለሌላ ስምሪት ዝግጁ በማድረግ እና የተቋሙን ሥራ ውጤታማ ለማድረግ የራሱ የሆና አስተዋጽዖ እንዳለው አስረድተዋል፡፡
የጂፒኤስ ቴክኖሎጂው ሥራን ከማቀላጠፍ በተጨማሪ ከዚህ በፊት ከነዳጅ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የነበሩ ችግሮችን በማቃለል ተቋሙን ከተጨማሪ ወጭ እየታደገው ይገኛል ብለዋል፡፡
እንደ አቶ ዋለ ገለፃ ማሻሻያው በአሃዝ የተደገፈ ግልጽ መረጃ ለማግኘት ከማስቻሉም ባለፈ ተሸከርካሪዎች ከተመደቡበት መስመር ሲወጡና ከፍጥነት ወሰን በላይ ሲጓዙ መልዕክት ወደ ማዕከል ያደርሳል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መስከረም 7 ቀን 2018 ዓ.ም
15 555
+2
#vacancy
የፈተና ውጤት ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጀማሪ ኤሌክትሪካል መሐንዲስ እና በጀማሪ መካኒካል መሐንዲስ የስራ መደብ ለመቅጠር ነሐሴ 07 እና ነሐሴ 08 ቀን 2017 ዓ.ም የጽሁፍ ፈተና መስጠቱ ይታወቃል፡፡
ስለሆነም በጀማሪ ኤሌክትሪካል መሐንዲስ የስራ መደብ የጽሁፍ ፈተና ተፈትናችሁ ከተራ ቁጥር 1 እስከ 15 እንዲሁም በጀማሪ መካኒካል መሐንዲስ የስራ መደብ ከተራ ቁጥር 1 እስከ 4 ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በተሰጠው የፅሁፍ ፈተና አብላጫ ውጤት ያመጣችሁ በመሆኑ ከመስከረም 19 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ቅጥርና ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃ ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ ቀርባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈጽሙ እያሳወቅን፤ ስማችሁ ያልተገለጸው አመልካቾች የማለፊያ ውጤት ያላመጣችሁ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መስከረም 5 ቀን 2017 ዓ.ም
15 555
እንኳን ለ2018 አዲስ ዓመት በሠላም አደረሳችሁ!
አዲስ ዓመት ሁሌም ተስፋ ይዞ የሚመጣ የበዓላት ሁሉ በኩር ነው፡፡ የዘመን መቀየር ተስፋችንን የሚያለመልም እና ወደፊት እንድናስብ የሚያደርግ ከመሆኑም ባሻገር በአዲስ ዓመት ዋዜማ ለምርቃት የበቃው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ደግሞ ተስፋችንን ምሉዕ ያደርገዋል፡፡ እንደ ተቋም ብቻ ሳይሆን እንደሀገር ለምናቅዳቸው ሥራዎች መሳካት ትልቅ አቅም እንደሚሆን እምነቴ የፀና ነው፡፡ ስለሆነም በአዲሱ ዓመት "የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል" የመሆን ራዕያችንን እውን ለማድረግ የምንሠራበት፣ ሁለንተናዊ ተቋማዊ ስኬት የምናስመዘግብበት እንዲሁም በግል ያቀድናቸውን ውጥኖች ከግብ የምናደርስበት የሠላም፣ የደስታና የስኬት ዘመን እንዲሆን እመኛለሁ!!
መልካም አዲስ ዓመት!
አሸብር ባልቻ (ኢንጂነር)
ዋና ሥራ አስፈፃሚ
15 555
በቅርቡ የኃይል ትስስር ሊፈረም ይችላል
........///.......
ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ለመውሰድ የሚያስችላትን ስምምነት በቅርቡ እንደምትፈጽም ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት አስታወቁ ፡፡
ፕሬዚዳንቱ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት ግድቡ ከኢትዮጵያ አልፎ የቀጣናውን ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡
ሀገራቸው ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ማግኘት የሚያስችላትን ስምምነት በቅርቡ እንደምትፈፅም ገልፀዋል፡፡
ሁለቱ ሀገራት የኃይል ሽያጭ ለማከናወን የመግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸውና ባለሙያዎቻቸው አስፈላጊውን ጥናት እያካሄዱ መቆየታቸው ይታወሳል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም
15 555
ግድቡ አፍሪካዊ አጀንዳዎችን ለማሳካትና ቀጣናዊ ትስስርን ለማሳደግ የሚያስችል ነው
…....///…......
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አፍሪካዊ አጀንዳዎችን ለማሳካት እና ቀጣናዊ ትስስርን ለማሳደግ እንደሚያስችል የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ገለፁ፡፡
ሊቀመንበሩ ሙሐሙድ አሊ ዩሱፍ በግድቡ ምርቃት ላይ ባደረጉት ንግግር ግድቡ በትውልድ ቅብብሎሽ ተገንብቶ ለምረቃ በመብቃቱ ለመላው ኢትዮጵያውያን እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
ግድቡ የሀገር ውስጥን ፍላጎት ከማሟላት ባሻገር ቀጣናውን በኃይል ልማት ዘርፍ ለማስተሳሰር የጎላ ሚና እንዳለው ተናግረዋል፡፡
ፕሮጀክቱ ለአየር ንብረት የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ በመገንባት ኢትዮጵያንና ቀጣናውን ተጠቃሚ የሚያደርግና ከአህጉራዊ አጀንዳዎች ጋር የሚጣጣም መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡
ኢትዮጵያ ግድቡን በራስ አቅም ገንብታ ማጠናቀቋ ለአህጉሩ መነሳሳትን የሚፈጥርና የሕብረቱን 2063 አጀንዳን ለማሳካት የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል፡፡
ከሴኔጋል ወንዝ ጋር በተያያዘ በሴኔጋል፣ ማሊ እና ሞሪታኒያ መካከል የተደረገውን የሦስትዮሽ ትብብር የጠቀሱት ሊቀመንበሩ ድንበር ተሸጋሪ ወንዞችን በጋራ ተጠቃሚነት ላይ በተመሰረተ መርህ በሰላማዊ መንገድ የመጠቀም ልምምድ መጎልበት እንደሚገባው ገልፀዋል፡፡
የጅቡቲ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኢትጵያውያን ብቻ ሳይሆን የዓለምን ሕዝብ ያስደነቀ የመላ አፍሪካውያን የጋራ ፕሮጀክት ነው ብለዋል፡፡
የግድቡ መሳካት ለኢትዮጵያ ወዳጆች ሁሉ ድል በመሆኑ የከበረ አድናቆት አለን ያሉት ፕሬዝዳንቱ የግድቡ ግንባታ በኢትዮጵያውያን ሙያተኞች ለፍጻሜ በመብቃቱ እጅግ የተለየ አድናቆት የሚቸረው መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
የግድብ ግንባታውን በራስ አቅም በማጠናቀቅ ኢትዮጵያውያን እንደገና አፍሪካን የሚያኮራ ሥራ መስራታቸውን የተናገሩት ደግሞ የኢስዋቲኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ሩሴል ሚሶ ድላሚኒ ናቸው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም ሀገራቸው ኢስዋቲኒን ጨምሮ በርካታ የምዕራብ አፍሪካና በጥቅሉ አፍሪካውያን መሪዎች ህዳሴን መሰል ትውልድ ተሸጋሪ ሥራዎችን እንዴት መስራት እንደሚቻል የሚያስተምር ነው ብለዋል፡፡
የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሐመድ በበኩላቸው የግድቡ መመረቅ ለቀጣናው ኩራት እንዲሁም ለጋራ ዕድገትና ቀጣናዊ ትብብር ወሳኝ ስለመሆኑም ገልፀዋል፡፡
የግድቡ መጠናቀቅ ኢትዮጵያ በራሷ አቅም ያከናወነችው ትልቅ ታሪክ እና የብልጽግናዋ ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑንም አንስተዋል።
ፕሮጀክቱ ከአንድ ግድብነት ያለፈ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ በትብብር ለመልማትና ለማደግ የሶማሊያ ሕዝብና መንግስት ዝግጁ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም
15 555
የግድቡ ግንባታ ጠንካራ የሥራ ባህል እና ጽናት የታየበት ነው- ፔትሮ ሳሊኒ
…....///…..
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ጠንካራ የሥራ ባህል እና ጽናት የታየበት እንደሆነ የፕሮጀክቱ ሥራ ተቋራጭ የጣሊያኑ ዊ ቢውልድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፔትሮ ሳሊኒ ተናገሩ፡፡
ሥራ አስፈጻሚው በግድቡ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት ላይ የግድብ ግንባታው ተጠናቆ ሲታይ ቀላል ቢመስልም በርካታ ፈተናዎችን እና ውጣ ውረዶችን በጽናት ማለፉን ተናግረዋል፡፡
ግድቡ አሁን ላይ የሚያስፈልገውን ውሃ መያዙን እና የሀገሪቱን የማመንጨት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ በማሳደግ በርካታ ኢትዮጵያውያን የኃይል ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ለጎረቤቶቿ በመሸጥ ትብብሯን ለማጠናከር ጉልህ ሚና እንደሚጫወት አስገንዝበዋል::
የህዳሴ ግድብ በዓለማችን ደህንነታቸው ከተጠበቁ ፕሮጀክቶች አንዱ ነው ያሉት ሥራ አስፈጻሚው በግንባታው ላይ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በጽናትና በቁርጠኝነት የተሳተፉበት እንዲሁም የእውቀት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ያገኙበት መሆኑንም አብራርተዋል፡፡
የግድብ ግንባታው መጠናቀቅ የኔ እና የኢትዮጵያ ህልም እውን የሆነበት ነውም ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያውያን በፈተናዎችና በችግሮች ሳይበገሩ ግድቡ እንዲጠናቀቅ ትልቅ ሚና መጫወታቸውን የጠቆሙት ፔትሮ ሳሊኒ ለግድብ ግንባታው እውን መሆን አሻራቸውን ላሳረፉ ሠራተኞችም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በግድቡ ግንባታ ሥራ ላይ እየተሳተፉ በነበረበት ወቅት በተለያዩ አደጋዎች ሕይወታቸውን ላጡ ሠራተኞች ክብር እንደሚሰጡ እና በኅሊና እንደሚያስቧቸው ተናግረዋል።
የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ለመንግሥታቸው የላኩትን የደስታ መግለጫ መልዕክትም አቅርበዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም
15 555
ከፊታችን ለሚጠብቀን ከባድ ሥራ ታጥቀን ልንነሳ ይገባል
.......///.......
ኢትዮጵያዊያን በሰራነው ገድል ሳይሆን ከፊታችን ለሚጠብቀን ከባድ ሥራ ታጥቀን ልንነሳ እንደሚገባ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አሳስበዋል፡፡
ዶ/ር ዐቢይ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ ባደረጉት ንግግር ከዛሬ በኋላ ዳግም ዓድዋ ጉባ ላይ በመሰራቱ የኢትዮጵያ የልመና፣ የስንፍናና የእንጉርጉሮ ዘመን አብቅቶ እንደ ልኳ የምትመዘንበት ዘመን ከፊታችን መዘርጋቱን ገልፀዋል፡፡
ኢትዮጵያ ተረጅነቷ ቀርቶ ረጂ ትሆናለች ያሉት ዐቢይ አህመድ በኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን የመጀመሪያው ቀን የተገኙ ወዳጆች ኢትዮጵያ ወዳጅነት ብቻ ሳይሆን ከሀብቷ፣ ከብልጽግናዋ፣ ከተስፋዋ፣ ከእውቀቷ ከልምዷ የምታቋድሳቸው እንደምትሆን አረጋግጠዋል፡፡
"የኢትዮጵያ ብልጽግና የማይሳካ ለሚመስላቸው ለቅርብና ለሩቅ ጠላቶቻችን እኛ ኢትዮጵያዊያን የማይሞት ስም እንጅ የማይሞት አካል የለንም፤ አካላችን ሞቶ የማይሞት ስም ለማስቀረት፤ የማይሞት አሻራ ለማኖር የምንተጋ ህዝቦች ነን" ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡
ህዳሴ ጥቁሮች እንደምንችልና እንደምናሳካ በጥቁር ዘር ታሪክ የመጀመሪያው ታላቅ ሥራ ነው ያሉት ዶ/ር ዐቢይ ህዳሴን በንግግር፣ በፎቶና በተንቀሳቃሽ ምስል ብቻ መግለጽ ስለማይቻል የህዳሴን ልክ ለመገንዘብ መላው ኢትዮጵያዊያንና አፍሪካዊውያን ግድቡን በመጎብኘት የተሰራውን ገድል እንድገነዘቡም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ከእንግዲህ የህዳሴ ፋይል ተዘግቷል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አምስትና ስድስት ዓመታት በአጠቃላይ ከ30 ቢሊዮን ዶላር በላይ ሀብት የሚፈስባቸው የአፍሪካን ልጆች ቀና የሚያደርጉ እና የኢትዮጵያን ብልጽግና የሚያሰምሩ የተለያዩ ሜጋ ፕሮጀክቶችን ለመገንባት ዕቅድ እንዳላት አብስረዋል፡፡
የኢትዮጵያ የታሪክ እጥፋት፣ የብልጽግና መሰረት እና የማንሰራራት ዘመን ዛሬ በሁሉም አቅጣጫ መታወጁን በመጠቆም ኢትዮጵያን ለማቅናት ሁሉም በአንድ ልብና በአንድ መንፈስ በጋራ በመቆም የኢትዮጵያን ብልጽግና እውን ማድረግ እንደሚጠበቅበትም አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ብልጽግና እውን መሆኑን ኢትዮጵያ ዳግም አደዋን ደጋግማ ለጥቁር ህዝቦች ማሳየቷ አይቀሬ ነው ያሉት ዶ/ር ዐቢይ የጥቁር ህዝቦች ከልመና በመውጣት ለመበልጸግ በአንድ ላይ ሊቆሙ እንደሚገባም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም
15 555
ግድቡ ከብሔራዊ ፕሮጀክትነት ባለፈ የፓን አፍሪካ አቅምን በተግባር ያሳየ ነው -ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ
….///….
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከብሔራዊ ፕሮጀክትነት ባለፈ የፓን አፍሪካ አቅምን በተግባር ያሳየና የአፍሪካ መር መሰረተ ልማት ግንባታ መገለጫ መሆኑን የኬኒያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ተናገሩ፡፡
በዛሬው ዕለት የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት ላይ የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ (ዶ/ር)፣ የጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦመር ጊሌህ፤ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ (ዶ/ር)፣ የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫኪር ማየርዴት፣ የባርባዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚያ አሞር ሞትሊ፣ የኢስዋቲኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ሩሴል ሚሶ ድላሚኒ፣ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበር መሀመድ አሊ ዩሱፍ፣ በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ፀሐፊ ክላቨር ጋቴቴ እና ሌሎችም ተገኝተዋል።
በምርቃት ሥነሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ እንደተናገሩት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምርቃት ትልቅ ታሪካዊ አንድምታ ያለው መሆኑን እና አፍሪካ የራሷን እጣ ፈንታ በራሷ የመወሰን አቅም እንዳላት የሚያሳይ ታላቅ ፕሮጀክት ነው፡፡
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የምህንድስና ሥራ ሳይሆን አፍሪካ የራሷን መጻኢ እድል በራሷ መወሰን እንደምትችል የሚያሳይ በመሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ እና መንግስት ለዚህ ታሪካዊ ስኬት እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ ብለዋል።
አፍሪካውያን የራሳቸውን የብልጽግና መሻት በራሳቸው ማካሳት እንደሚችሉም የሚያመላክት መሆኑን የጠቆሙት ፕሬዝዳንቱ ፕሮጀክቱ የአፍሪካ ቀንድ እና የናይል ተፋሰስ ሀገራት ለጋራ ትብብር ያለንን ቁርጠኝነት በግልጽ እያሳየን መሆኑንም በንግግራቸው አንስተዋል፡፡
ኢትዮጵያ በኢነርጂ ራሷን ለመቻል እና ኢኮኖሚዋን ለመለወጥ እያደረገች ያለውን ጥረትም አድንቀዋል።
የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫኪር ማየርዲት በበኩላቸው ግድቡ ሕዝብ በተባበረ ክንድ ምን መስራት እንደሚችል ያሳየ የአንድነትና የመስዋዕትነት ምልክት መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የደቡብ ሱዳን ሕዝብና መንግስት ከኢትዮጵያውያን ጋር የጋራ ታሪክ እና ሕልም ያላቸው መሆኑን ጠቅሰው ለግድቡ ግንባታ መጠናቀቅ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡
የባርባዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚያ አሞር ሞትሊ በበኩላቸው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአድዋ ድል ተምሳሌት ሆኖ በኢንጅነሪንግ ጥበብ ዳግም የተገለጠበት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ግድቡ ኢትዮጵያውያ ለመላው አፍሪካውያን መቻላቸውን ያሳዩበት ፕሮጀክት መሆኑንም አብራርተዋል፡፡
ሌሎችም መሪዎችም የግድቡ ግንባታ መጠናቀቅ ለአፍሪካና ለቀጠናው የሚኖረውን በጎ ሚና በማውሳት የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም
15 555
ገደሉን ተሻግረን በሕዳሴ ገድል አትመናል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
….///…..
የገጠሙንን ፈተናዎችና ችግሮች ተጋፍጠን ገደሉን ተሻግረን የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታን በማጠናቀቅ ገድል አትመናል ሲሉ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ይህን የተናገሩት የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ ባደረጉት ንግግር ነው፡፡
ሕዳሴ የትላንት ቁጭት ማሰሪያ የመጭው ንጋት ማብሰሪያ እንዲሁም ለመላ ኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለጥቁር ሕዝቦች ሁሉ ታሪክ ሆኖ የሚኖር ገድል ነው ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ ሕዳሴን የሰራችው የታችኛውን ተፋሰስ ሀገራት ጨምሮ አፍሪካውያንን በኃይል ለማስተሳሰር እንጂ የጎረቤት ሃቅን ለማስቀረትና ለመጉዳት አለመሆኑንም አረጋግጠዋል፡፡
ስለሕዳሴ በመናገር ጊዜ አናባክንም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሕዳሴን ግድብ የሚስተካከል ለሠላማዊ ዓላማ ብቻ የሚውል የኒኩሌር ኃይል ማመንጫን ጨምሮ የአየር ማረፊያ ግንባታ፣ የማዳበሪያ እና የጋዝ ፋብሪካዎችን ሥራ በቅርቡ እንደምታስጀምርም ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን በሁሉም አቅጣጫ በሕዳሴ መጀመሩንም አብስረዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም
15 555
በግድብ ግንባታ ላይ አበርክቶ የነበራቸው አመራሮች ተሸለሙ፤
…....///….....
በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ምርቃት ላይ በግድብ ግንባታው ወቅት በአመራርነት አበርክቶ የነበራቸው አመራሮች በጠቅላይ ሚኒስቴር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የክብር ኒሻን ተሸልመዋል፡፡
የክብር ኒሻን የተሸለሙት ኢንጂነር ኤፍሬም ወልደኪዳን አማካለኝ ከህዳር 2004 ዓ.ም ጀምሮ ጥር 14 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ የፕሮጀክቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ፣
ኢንጂነር ከማል አህመድ ሱለይማን ከሚያዚያ 2013 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ የፕሮጀክቱ የኦፕሬሽን ሥራ አስኪያጅ
አቶ በላቸው ካሳ ወልዴ በምክትል ሥራ አስኪያጅ ማዕረግ የፕሮጀክቱ ሳይት አስተባባሪ
ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ናቸው፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
