es
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Ir al canal en Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

El canal Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 411 suscriptores, ocupando la posición 5 577 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 191 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 411 suscriptores.

Según los últimos datos del 11 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 64, y en las últimas 24 horas de 24, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 24.26%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 9.47% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 737 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 458 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 23.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 12 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 411
Suscriptores
+2424 horas
+237 días
+6430 días
Archivo de publicaciones
መሐሮሙ እግዚኦ ለነፍሳተ አግብርቲከ፤ ኀይለ ገብርኤል፣ ወልደ ጊዮርጊስ፣ ገብረ ኪዳነ ማርያም፣ ገብረ ሕይወት፣ ገብረ እግዚአብሔር፣ …፡፡ (አቤቱ አምላካችን ሆይ፤ የጄነራል ሰዐረ መኰንንን፣ የዶ.ር አምባቸው መኰንንን፣ የሜጀር ጄነራል ገዛኢ አበራን፣ የብርጋዴር ጄነራል አሳመነው ጽጌን፣ የእዘዝ ዋሴን፣ የምግባሩ ከበደን ነፍስ ይማርልን፤ ነፍስ ይማርልን፤ ከደጋጎቹ ከአብርሃም ከይስሐቅና ከያዕቆብ ጋራ ያኑርልን፡፡) ፠፠ስላላየነውና ስላልሰማነው፤ ስለማናውቀውና ስላልደረስንበት ነገር በእርግጠኝነት አናውራ!፤ አንናገርም!!፡፡ ‹‹በአፍህ ቃል ተጠመድህ፤ በአፍህ ቃል ተያዝህ፡፡›› መጽሐፈ ምሳሌ 6÷2/ ፨ ‹‹የእግዚአብሔር ጽኑ ቍጣ ከእኛ ዘንድ አልተመለሰምና ማቅ ልበሱ፥ አልቅሱም ዋይም በሉ፡፡›› ትንቢተ ኤርሚያስ 4፥8 ‹‹የኢትዮጵያ ድንኳኖች ሲጨነቁ አየሁ፡፡›› ትንቢተ ኤርምያስ 3÷7/ *‹‹በሚያልፈው ዓለም የማይለፈውን ፍቅር እንኑርበት፥ በሚያልፈው ዓለም የማይልፈውን ሰላም እንመላለስበት›› /ብፁዕ አቡነ አብርሃም/ *አክለክሙ ዘኀለፍክሙ መዋዕል::

ሥርዐተ ማኅሌት ወዜናሁ ዘሠኔ ፲፯፤ በዓለ አባ ገሪማ (ይስሐቅ) ዘመደራ፡፡ * በዓለም ላይ በእድሜ ረጅም ዓመታት (ከ1500ዓመታት በላይ) ያስቈጠረውን የብራና ወንጌል ጽፈው ያቆዩልን፤ * ዓድዋ የሚለውን ስያሜ ያወጡ፤ * አሁንም ድረስ ከደረቅ ዓለት ላይ ጠበል እንዲፈልቅ ቃል ኪዳን የተሰጣቸው፤ ሂዳችሁ እዩ!! * በአንድ ቀን ዘርተው ለ9 ሰዓት ቅዳሴ መሥዋዕት ያደረሱ፤ በዚህና በሌሎች ምግባሮቻቸው ወንድሞቻቸው የሚኾኑ ቅዱሳን ሳይቀር ገሪማ ገረምከን ብለው የመሰከሩላቸው፤ * የኢትዮጵያ ታሪክን የያዘ ታላቁን መደራ ገዳም የሠረቱ፤ የታላላቅ የአድዋ ጀግኖቻችን መሪያቸው ራስ አሉላ አባ ነጋን ጨምሮ አጽማቸው ያረፉበት ነው፡፡ (ክብረ በዓላቸው ሰኔ 17 በዐድዋ በሚገኘው በመደራና በአዲስ አበባ በካራ አሎ መድኀኔ ዓለም በታላቅ ድምቀት ይከበራል፡፡) #አባ_ገሪማ_(ይስሐቅ)#ዘመደራ (ክብረ በዓላቸው በዓድዋ በሚገኘው ገዳማቸው፣ በጎንደር ተክለሃይማኖት፣ በአዲስ አበባ ካራአሌ መድኀኔዓለም ወአቡነ ገሪማ ገዳም) በአልአሜዳ ዘመነ መንግሥት በ፬፻፹ ዓ.ም ወደ አገራችን ወደ ኢትዮጵያ በሃይማኖት ምክንያት ከሶርያና ከታናሽ እስያ ተሰደው ከመጡት ተስዓቱ (ዘጠኙ) ቅዱሳን መነኮሳት (አባ አሌፍ፣ አባ አረጋዊ፣ አባ አፍጼ፣ አባ ሊቃኖስ፣ አባ ገሪማ፣ አባ ጉባ፣ አባ ይምአታ፣ አባ ጰንጠሌዎን እና አባ ጽሕማ) መካከል በትምህርታቸው የላቁ፣ ቅዱስ ያሬድ በድጓው (በመዝሙር)፣ በዝማሬና በመዋሥዕት ድርሰቱ ውስጥ ‹‹ገሪማ ገረምከኒ አስኬማከኒ አልባቲ ሙስና፤ አባ ገሪማ አስገረምኸኝ፡፡ ለምንኵስናህም እንከን የለባትም›› በማለት የደረሰላቸውና አድዋ የሚለውን ስያሜ የሰየሙ፣ በዓለማችን ላይ እስካሁን ከተገኙት የብራና ወንጌሎች መካከል በእድሜው ረዥሙንና ባለሠንጠረዡን /ከ1400ዓመታት በላይ/ የጻፉ፣ እስከ አሁንም ድረስ የሚያስደንቅ ከደረቅ ዓለት ላይ እንደ እንባ የሚወጣው ፈዋሽ ጠበል ያፈለቁ አባ ገሪማ ዘመደራ ናቸው፡፡ እነዚህ ዘጠኙ ቅዱሳን በመላው ኢትዮጵያ ተዘዋውረው ወንጌልን ሰብከዋል፤ በወቅቱ ብሔራዊ ቋንቋ የነበረዉን ግእዝን በሚገባ አጥንተው ቅዱሳት መጻሕፍትን ከሱርስትና ከጽርዕ ቋንቋዎች ወደ ግእዝ ተርጕመዋል፡፡ እንደዚሁም ገዳማትንና አብያተ ክርስቲያናት አሳንጸዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያናችንም ከፈጸሟቸው መንፈሳውያን ተልእኮዎች፣ ካደረጓቸው ተአምራትና መልካም ሥራዎች አኳያ ቅዱሳን በሚል መዓርግ ትጠራቸዋለች፤ በስማቸውም ጽላት ቀርፃ በዓላቸውን ታከብርላቸዋለች፡፡ የአባ ገሪማ አባት መስፍንያኖስ የሮም አገር ንጉሥ ነበረ፤ ሚስቱም ሰፍንግያ ትባላለች፡፡ መካን ስለነበረች በቅድስት ድንግል ማርያም ስም በመማጸን ልጅ እንዲሰጣት እግዚአብሔርን ስትለምን ከኖረች በኋላ ወንድ ልጅ ወለደች፤ ስሙንም ይስሐቅ አለችው፡፡ የያን ጊዜው ይስሐቅ የኋላው አባ ገሪማ በመንፈሳዊ ሥርዓት ካደገ በኋላም የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ተምሮ በዲቁና ማገልገል ጀመረ፡፡ ይስሐቅ ወላጅ አባቱ ሲሞትም በአባቱ ዙፋን ተተክቶ ለሰባት ዓመታት ሮምን በንጉሥነት ሲያስተዳድር ከቆየ በኋላ በዋሻ ይኖሩ የነበሩት አባ ጰንጠሌዎን ዘጾማዕት ‹‹ይስሐቅ ሆይ፣ ሙታኖቻቸውን ይቀብሩ ዘንድ ሙታንን ተዋቸውና የማያልፈዉን የክርስቶስን መንግሥት ትሻ ዘንድ ወደ እኔ ና›› ብለው መልእክት ላኩበት፡፡ መልእክቱ እንደ ደረሰውም መንግሥቱን ትቶ በሌሊት ወደ አባ ጰንጠሌዎን ሲሔድ ቅዱስ ገብርኤል ተገልጾ በብርሃናውያን ክንፎቹ ተሸክሞ ዐሥር ወር የሚወስደዉን መንገድ በሦስት ሰዓታት አስጉዞ ከአባ ጰንጠሌዎን በዓት አደረሰው፡፡ አባ ይስሐቅ (አባ ገሪማ) በአባ ጰንጠሌዎን እጅ ከመነኰሱ በኋላ በጾም፣ በጸሎትና በስግደት ተጠምደው ቆዳቸው ከዐፅማቸው እስኪጣበቅ ድረስ ተጋድሎ ሲፈጸሙ ቆዩ፡፡ ከዚያ በኋላ ወደ መደራ ሔደው በእግዚአብሔር ኃይል ድንቆችንና ተአምራትን እየያደረጉ፣ በሽተኞችን እየፈወሱ፣ አጋንንትን እያስወጡ ብዙ ዓመታት ኖሩ፡፡ ካደረጓቸው ተአምራት መካከልም በጠዋት ሥንዴ ዘርተው፣ በሠርክ ሰብስበው መሥዋዕት ካሳረጉ በኋላ በማግሥቱ ከግራር ዛፍ ላይ በሬዎችን አውጥተው ሥንዴዉን አበራይተው ሰባ ሰባት የእንቅብ መሥፈሪያ መሰብሰባቸው አንደኛው ሲኾን፤ በዓለት ላይ የተከሏት ወይን ወዲያው በቅላ፣ አብባ ፍሬ እንድታፈራ ማድረጋቸውና በወይኑም መሥዋዕት ማሳረጋቸው ደግሞ ሌላኛው ተአምር ነው፡፡ አባ ገሪማ መጽሐፍ እየጻፉ ሳሉ ፀሐይ ሊጠልቅ በተቃረበ ጊዜ ጸሎት አድርሰው ጽሕፈታቸዉን እስኪፈጽሙ ድረስ እንደ ኢያሱ ፀሐይን በቦታው እንዲቆም ማድረጋቸውም በመጽሐፈ ስንክሳር ተመዝግቧል፡፡ ከእጃቸው የወደቀው ብርዕ ወዲያው በቅሎ፣ አቈጥቍጦ እንደ አደገ፤ ምራቃቸዉን ትፍ ያሉበት ሥፍራም እስከ ዛሬ ድረስ ሕሙማንን እንደሚፈውስ መጸሐፈ ስንክሳር ይናገራል፡፡ በአንዲት ዕለትም መቅኑናቸውን ተቀብለው ከመነኮሳት ጋር ሲሔዱ መንገድ ላይ ቤተ ክርስቲያን አግኝተው ሲጸልዩ ካህናቱ ቅዳሴ እንዲያሟሉላቸው ጠየቋቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ሌሎቹ ምግብ በልተው ነበርና ‹‹አንችልም›› ሲሉ አባ ይስሐቅ ምግብ አልተመገቡም ነበርና መቅኑናቸዉን አስቀምጠው ቅዳሴውን አሟሉ፡፡ ባልንጀሮቻቸው ግን በልተው የቀደሱ መስሏቸው ወደ አባ ጰንጠሌዎን መጥተው ‹‹ቀሲስ ይስሐቅ ከበላ በኋላ ቀደሰ›› ብለው ከሰሷቸው፡፡ አባ ጰንጠሌዎንም አባ ይስሐቅ ሲመለሱ ‹‹የምጠይቅህ ምሥጢር ስላለኝ ሰዎችን ከአጠገብህ ገለል አድርጋቸው›› ሲሏቸው አባ ይስሐቅም ‹‹ሰዎች ብቻ ሳይኾኑ ዕንጨቶችና ድንጋዮችም ገለል ይበሉ›› ብለው መለሱላቸው፡፡ ወዲያዉኑም ዕንጨቶችና ድንጋዮች አንድ ምዕራፍ ያህል ከቦታቸው ሸሹ፡፡ በዚህ ጊዜ አባ ጰንጠሌዎን ‹‹ኦ ወልድየ ይስሐቅ ገረምከኒ፤ ልጄ ይስሐቅ ሆይ! ገረምኸኝ›› እያሉ አደነቋቸው፡፡ አባ ገሪማን ሳያዉቁ የከሰሷቸው መነኮሳትም ይቅርታ ጠይቀዋቸዋል፡፡ አባ ገሪማ ተብለው መጠራት የጀመሩትም ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡ ይህንን መሠረት በማድረግ ‹‹ገሪማ ገረምከኒ አስኬማከኒ አልባቲ ሙስና፤ አባ ገሪማ አስገረምኸኝ፡፡ ለምንኵስናህም እንከን የለባትም›› በማለት ቅዱስ ያሬድ በመዝሙሩ አመስግኗቸዋል፡፡ ከዚያም በትግራይ ክፍለ ሀገር ልዩ ስሙ መደራ ከሚባል ቦታ ገብተው በዓት ሠርተው ለ፳፫ ዓመታት በትኅርምት ኖረው መልካም ተጋድሏቸውንና የቀና አካሔዳቸዉን በፈጸሙ ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰኔ ፲፯ ቀን ተገልጦ ስማቸውን የሚጠሩትን፣ መታሰቢያቸዉን የሚያደርጉትን፣ ገድላቸዉን የሚጽፉ፣ የሚያነቡና የሚተረጕሙትን፣ ቤተ ክርስቲያን የሚያንጹትንና የሚያገለግሉትን ስማቸውን በሕይወት መጽሐፍ እንደሚጽፍላቸው ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡ አባ ገሪማም ይህንን ታላቅ ሀብት የሰጣቸዉን እግዚአብሔርን አመስግነው ከተደሰቱ በኋላ በብርሃን ሠረገላ ተነጥቀው ብሔረ ሕያዋን ገብተዋል፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን በተለይ በገዳማቸው በመደራ አባ ገሪማ የተሠወሩበት ሰኔ ፲፯ ቀን በየዓመቱ በድምቀት ይከበራል፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይኹን፡፡ እኛንም በጻድቁ ጸሎት ይማረን፤ በረከታቸዉም ከእኛ ጋር ትኑር፤ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡ ሰአል ለነ አባ ገሪማ፤ ቅድመ መንበሩ ለንጉሠ ራማ፤ ሰአል ለነ አባ፤ ጸሎትከ ወትረ ይዕቀበነ:: ምንጭ፡- መጽሐፈ ስንክሳር፣ ሰኔ ፲፯ ቀን፡፡ መዝገበ ታሪክ ክፍል ፪፣ መ/ር ኅሩይ ኤርምያስ፣ ገጽ ፺፱-፻፡፡ የማኅበረ ቅዱሳን ድኅረ ገጽ ኦ አበው ወእማት አኃው ወአኃት ኢትርስዑነ በጸሎተክሙ ለትምህርተ ቤትነ ቀ.ደ.ሰ.መድኀኔዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት፡፡

ገሪማ ገረምከኒ (ገሪማ ሆይ ገረምከኝ) ፎቶዎቹ፤ ፠በዓለም በዕድሜ ብዛት ረጅም ዕድሜን ያስቈጠረውና 1500 ዓመታትን ያስቈጠረውን የ‹‹አባ ገሪማ ወንጌል››፤ መደራ፤ ዓድዋ አጠገብ የሚገኝ፡፡ ፠ከደረቅ ዓለት ላይ እንደ እንባ የሚፈልቀው የአቡነ ገሪማ አስደናቂና ደዋሽ ጠበል፡፡ (ክብረ በዓላቸው በዓድዋ በሚገኘው ገዳማቸው መደራ፣ በጎንደር ተክለሃይማኖት፣ በአዲስ አበባ ካራአሎ መድኀኔዓለም ወአቡነ ገሪማ ገዳም በደማቅ ሁኔታ ይከበራል፡፡)

ሃሌ ሃሌ ሉያ ለቤተ ክርስቲያን፤ ሐነፃ ላሊበላ ለቤተ ክርስቲያን፡፡ /ወረብ ዘሸዋ፤ በየካ ሚካኤል በሰኔ የሚወረብ የቤቱ የሸዋ ወረብ ቀለም/፤ ዛሬ የሐናፄ መቅዱስ ቅዱስ ላሊበላ(ላልይበላል) ክብረ በዓሉ ነው፡፡

ሰኔ ቅዱስ ሚካኤልና ሥርዐተ ማኅሌት፡፡ #ሰኔ_፲፪ #መከበሩ_ስለምንድን_ነው_ቢሉ_፤ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ የሚበር፤ ንሥረ አርያም የሚባል፥ ውዳሴው እንደ ማር የጣፈጠ፥ ንዑድ ክቡር የሆነ ፥ የመላእክት ሁሉ አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ፭ት ነገሮችን የፈጸመበት እለት ስለኾነና የሌሎችም ቅዱሳን መታሰቢያ ቀናቸው ስለኾነ ነው፡፡ እነርሱም፤ ፠፩. በዓለ ሲመቱ ለቅዱስ ሚካኤል፤ ፠፪. ባሕራንን ያዳነበት፤ ፠፫. የአስተራኒቆስ ሚስት ቅድስት አፎምያን ያዳነበት፤ በዓለ እረፍቷም በዚሁ እለት ነው፤ ፠፬. በግብፅ ሃገር ፓትርያርክ እለ እስክንድሮስ ቅዳሴ ቤቱን ያከበረበት፤ ፠፭. ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ነጥቆ ወስዶ ያሳየበት፤ ፠ሐናፄ መቅደስና በሰማያት ያለ ምሥጢርን የተመለከተ ቅዱስ ላሊበላ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ በዓለ ዕረፍቱ ነው፤ ፠67ኛ ሊቀ ጳጳስ ቄርሎስ ሊቀ ዻዻሳት ዘእስክንድርያ እረፍቱ ነው፤ ፠የእስክንድርያ 6ኛ ሊቃነ ጳጳሳት አባ ዮስጦስ (ወንጌላዊና ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ የክርስትና ጥምቀትን ያጠመቀው፥ ዲቁናና ቅስናን የሾመው) እረፍቱ ነው፡፡

ሰኔ ቅዱስ ሚካኤልና ሥርዐተ ማኅሌት፡፡ #ሰኔ_፲፪#መከበሩ_ስለምንድን_ነው_ቢሉ_፤ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ የሚበር፤ ንሥረ አርያም የሚባል፥ ውዳሴው እንደ ማር የጣፈጠ፥ ንዑድ ክቡር የሆነ ፥ የመላእክት ሁሉ አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ፭ት ነገሮችን የፈጸመበት እለት ስለኾነና የሌሎችም ቅዱሳን መታሰቢያ ቀናቸው ስለኾነ ነው፡፡ እነርሱም፤ ፠፩. በዓለ ሲመቱ ለቅዱስ ሚካኤል፤ ፠፪. ባሕራንን ያዳነበት፤ ፠፫. የአስተራኒቆስ ሚስት ቅድስት አፎምያን ያዳነበት፤ በዓለ እረፍቷም በዚሁ እለት ነው፤ ፠፬. በግብፅ ሃገር ፓትርያርክ እለ እስክንድሮስ ቅዳሴ ቤቱን ያከበረበት፤ ፠፭. ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ነጥቆ ወስዶ ያሳየበት፤ ፠ሐናፄ መቅደስና በሰማያት ያለ ምሥጢርን የተመለከተ ቅዱስ ላሊበላ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ በዓለ ዕረፍቱ ነው፤ ፠67ኛ ሊቀ ጳጳስ ቄርሎስ ሊቀ ዻዻሳት ዘእስክንድርያ እረፍቱ ነው፤ ፠የእስክንድርያ 6ኛ ሊቃነ ጳጳሳት አባ ዮስጦስ (ወንጌላዊና ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ የክርስትና ጥምቀትን ያጠመቀው፥ ዲቁናና ቅስናን የሾመው) እረፍቱ ነው፡፡

በመዲና ከተማችን የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል የሚከብርባቸው ገዳማትና አድባራትን እንጠቁማችሁ፡፡ /ፎቷቸውን ያልለጠፍናቸውና ስማቸውን ያልጠቀስናቸውን እንድትልኩልን በሊቀ መልአኩ ስም እንጠይቃለን) 1. *የካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን (ሾላ፤ መገናኛ) 2. *አንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል /ጭቁኑ/፤ ፈረንሳይ 3. *ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል (አዲሱ ሚካኤል)፤ አውቶብስ ተራ 4. *ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል፤ /ቦሌ/ 5. *ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል፤ /ላፍቶ/ 6. *ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል፤ (መካኒሣ) 7. *ኮተቤ ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል /ሳጠራው/ (ቀድሞ ኮተቤ አሁን ሲምሲ) 8. *ደብረ ምሕረት ሚካኤል (ቀድሞ ወህኒ ቤት ሚካኤል) 9. *መካነ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል 10. *ገነተ አምባ ቅዱስ ሚካኤል 11. *ደብረ ኢዮር ቅዱስ ሚካኤል 12. *ካራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤልና 24ቱ ካህናተ ሰማይ 13. *ሐያት ጨፌ ኢያሪኮ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን (በ1980ዓ.ም ጽላቱ ከነ ድርሳናቱ ተቀብሮ የተገኘበት) 14. *መንበረ ክብር ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም /ኋላ ወቅድስት አርሴማ በሚል እየተጠራ የሚገኝ/፤ (በቀጨኔ በአዲሱ ገበያና በእንጦጦ መሃል ጉብታ ላይ የሚገኝ) እንዲሁም በድርብነት 1. *እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት 2. *መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ (ስድስትኪሎ) 3. *ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ (መስቀል አደባባይ) 4. *ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ቤ.ክ (ኋላ ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል በሚል እየተጠራ የሚገኘው)፤ (ኢምግሬሽን አጠገብ) 5. *ደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ (ኋላ ወመካነ ጎልጎታ ቅድስት ድንግል ማርያም በሚል እየተጠራ የሚገኝ)

#በዓለ_ጰራቅሊጦስ፤ /ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ/ ሥርዐተ ማኅሌቱ በዓለ ጳራቅሊጦስ ከ፱ኙ ዐበይት በዓላተ እግዚእ አንዱ እንደመኾኑ በኹሉም ገዳማትና አድባራት ይከበራል፤ ነገር ግን ታቦተ ሕጉ ወጥቶ በተለያዩ የሃገራችን ክፍሎች በሐዋርያትና በመንፈስ ቅዱስ ስም በተሰየሙ አብያ ክርስቲያናት ይከበራል፤ ይልቁንም በአዲስ አበባ ብቸኛ በኾነው #በጽርሐ_ጽዮን_ሐዋርያት_መንፈስ_ቅዱስና_/ኋላ/#ጎላ_ሚካኤል_ (ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል አገብ) ቤተ ክርስቲያን ይከበራል፡፡ ጰራቅሊጦስ ማለት መንጽሒ (የሚያነጻ)፥ መጽንዒ (የሚያጸና)፥ መስተፈሥሒ (ደስታን የሚሰጥ)፣ መስተሥርይ (ኀጢአትን ይቅር የሚል)፣ ናዛዚ (የሚያረጋጋ)፣ ከሣቲ (ምሥጢርን የሚገልጥ) የሚል ትርጕምን ይሰጣል (መጻሕፍተ ሠለስቱ ሐዲሳት፣ ገጽ ፪፻፹፫)፡፡ ይኸውም መንፈስ ቅዱስ በኀጢአት ጭቃ የወደቁትንና የሚወድቁትን እንደሚያነጻቸው፤ በመንፈሳዊ ተጋድሎ ላሉት ኹሉ በፈተናቸውና በመከራቸው ኹሉ እንደሚያበረታቸው (እንደሚያጸናቸው)፤ የሚነዋወፁትን እንደሚያረጋጋቸው፤ ያዘኑትን እንደሚያጽናናቸው፤ የሚደክሙትን እንደሚያበረታቸው፤ የተከዙትንም ሐሴትን እንደሚሰጣቸው የሚያስገነዝብ ነው፡፡ ጻድቃንን ወደ ተጋድሎ፤ ሰማዕታትን ወደ ደም፣ መነኰሳትን ወደ ገዳም፣ ማኅበረ ክርስቶስንም ወደ ቤተ ክርስቲያን ልቡናቸውን የሚያነሣሣና የሚመራ እርሱ መንፈስ ቅዱስ ነው፤ /ዮሐ.፲፮፥፲፪/፡፡ #በዓለ_ሃምሳ_በብሉይ እስራኤል ዘሥጋ በዓለ ኃምሳን የሚያከብሩት ስለ ብዙ ምክንያት ነው፡፡ ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ያኽልም፤ ፩ኛ) ከምድረ ግብጽ ከወጡ በኋላ ምድረ ከነዓን ገብተው ለመዠመርያ ጊዜ እሸት የበሉበትን የሚዘክሩበት ነው፡፡ ዳግመኛም በበረኻ ሳሉ እግዚአብሔር ከሰማያት ኅብስተ መናን አውርዶ፥ ከጭንጫ ውኃን አመንጭቶ እንደመገባቸው ይዘክሩበታል፡፡ በመኾኑም በዚኽ በዓል ቀዳምያት፥ ዐሥራትና በኵራት እያወጡ፣ በየዓመቱ ከሚዘሩት እኽል እሸት (በብዛት ስንዴ) እየበሉ እግዚአብሔርን ስለ ምድር ፍሬ የሚያመሰግኑበት በዓል ነው፡፡ ፪ኛ) እግዚአብሔር ከግብጽ ባርነት ካወጣቸው በኋላ በሃምሳኛው ቀን በደብረ ሲና ሕገ ኦሪትን ስለተቀበሉበት ይኽን ያስቡበታል፡፡ ፫ኛ) እግዚአብሔር ከምድረ ግብጽ በታላላቅ ገቢረ ተአምራት ስላወጣቸው ይኽን ያስቡበታል፡፡ ከላይ ለመግለጥ እንደተሞከረው ይኽ በዓል እኽል በሚታጨድበት በመከር ወቅት የሚከበር በዓል ነው፡፡ መከር ሲገባ መጀመርያ ከሚሰበስቡት እኽል ለእግዚአብሔር መሥዋዕት እንዲያቀርቡ ታዝዘው ነበር /ዘጸ. ፳፫፡፲፮/፡፡ በመኾኑም ከበዓለ ፋሲካ ጀምረው ሰባት ሳምንታት (፵፱ ቀናት) በየዕለቱ አንድ መስፈርያ እኽል ይሰጡ ነበር፡፡ በ፶ኛው ቀን ደግሞ ሊቀ ካህኑ ከተሰበሰበው እኽል በትልቅ መስፈርያ አድርጎ ካቀረበ በኋላ መሥዋዕተ በግ ይሠዋ ስለነበር ታላቅ በዓል ኾኖ ይከበር ነበር /ዘሌ. ፳፫፥፲-፲፯፣ ዘዳ. ፲፪፥፭-፯/፡፡ ***አማናዊ ትርጓሜ - በሐዲስ ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ድኅነተ ዓለምን በፈጸመበት ዓመት ግን፥ እስራኤል ዘሥጋ ከላይ በገለጥነው መንገድ ከያሉበት ተሰባስበው በዓሉን በኢየሩሳሌም ሲያከበሩ፤ ለእሥራኤል ዘሥጋና ለእሥራኤል ዘነፍስ ብርሃን እንዲኾኑ የመረጣቸው ሐዋርያትም ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የነገራቸውን ተስፋ እየተጠባበቁ በደብረ ጽዮን በቅዱስ ማርቆስ እናት በማርያም ቤት ተሰባስበው ነበር /ሉቃ. ፳፬፡፵፱/፡፡ በዓለ ሃምሳ የተባለው ቀን በደረሰ ጊዜም ከወደ ሰማይ እንደ ዓውሎ ነፋስ ድምፅ ያለ ድምፅ ነጕዶ ተሰማ፤ መንፈስ ቅዱስ ነበር፡፡ በዚኽም ብሉይና ሐዲስ ተገናኙ፤ ተተካኩ፡፡ የነቢያት ትንቢታቸው፥ የሐዋርያትም ስብከታቸው የኾነው ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነቢያትንና ሐዋርያትን በደብረ ታቦር ተራራ እንዳገናኛቸው፥ በዚያም ክብረ መንግሥቱን፥ ብርሃነ መለኮቱን እንደገለጸላቸው የሚታወስ ነው /ማቴ. ፲፮፡፩-፯/፡፡ በምሴተ ኀሙስም በቤተ አልዓኣዛር የብሉይ ፋሲካን እንዳዘጋጁና እርሱም መሥዋዕተ ብሉይን በመሥዋዕተ ሐዲስ እንደተካው የተጻፈ ነው /ማቴ. ፳፮፡፲፯-፳፱/፡፡ በበዓለ ኃምሳ የኾነውም ልክ እንደዚኹ ነው /ሐዋ. ፪/፡፡ ይኽ ኹሉ በኢየሩሳሌም፣ በመዠመርያዪቱ ቤተ ክርስቲያን በተሰየመች በቤተ ማርያም (የማርቆስ እናት) ተፈጸመ፡፡ ቤተ ክርስቲያን ለፊተኞችም ለኋለኞችም እናታቸው እንደኾነችም ታወቀ፤ ተረዳ፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት በዲድስቅልያ ፴፩ ላይ፡- “ከዕርገቱ ቀን በኋላ ታላቅ በዓል ይደረግ፤ በዚኽች ቀን በሦስተኛው ሰዓት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጰራቅሊጦስን ልኮልናልና እኛም በርሱ ስጦታዎች ተሞላን፤ አዳዲስ ቋንቋም ተናገርን” በማለት በዓሉን በቤተ ክርስቲያን ልናከብረው እንዲገባ ሥርዐት ሐዋርያት የሠሩልንም ስለዚኹ ነው፡፡ በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት የታነጸችው ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችንም ይኽንኑ በዓል ከጌታችን ዘጠኝ ዐበይት በዓላት አንዱ በማድረግ በድምቀት ታከብረዋለች፡፡ #ርደተ_መንፈስ_ቅዱስ ጌታችን እንደነገራቸው መቶ ሃያው ቤተ ሰብእ በቤተ ማርያም ኀይልን ከአርያም እስኪለብሱ ድረስ ተሰብስበው ነበር፡፡ በትዕግሥት ከመጠበቅ ውጪ መንፈስ ቅዱስ መቼ እንደሚወርድም አያውቁም ነበር /ሐዋ. ፪፥፪/፡፡ ጌታችን ባረገ በዐሥረኛው ቀን ግን እኔና እናንተ እንደምንሰማው ዓይነት ያይደለ፥ ነገር ግን ከወደ ሰማይ እንደ ዓውሎ ነፋስ ድምፅ ያለ ድምፅ ነጕዶ ተሰማ፡፡ ያሉበትን ቤት ሞላው፡፡ ላንቃ ላንቃ ያለው እሳት ኾኖ ታያቸው፡፡ በበደልን ጊዜ ከእኛ ርቆ ነበርና አኹን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሞት ስለታረቅን በኹሉም አደረባቸው: /ማቴ. ፫፡፲፩/፡፡ ኀይል የሚኾናቸው ሀብትን፣ ሀብት የሚኾናቸው ዕውቀትን ገንዘብ አደረጉ፡፡ #መንፈስ_ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ ከሦስቱ አካላተ ሥላሴ አንዱ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ ጋር የሚሠለስ የሚቀደስ የባሕርይ አምላክ ነው፡፡ እንደ አብና ወልድ ፍጹም ገጽ፥ ፍጹም መልክዕ፥ ፍጹም አካል አለው፡፡ መንፈስ ቅዱስ አካላዊ እንጂ ሕጹጽ (ብትን፣ ዝርው) አይደለም፡፡ በተለየ ግብሩም መሥረፅ (መውጣት) ነው፤ መሥረጹም ከአብ ብቻ እንጂ አንዳንዶች (ካቶሊኮችና መካነ ኢየሱሶች) እንደሚሉት ከወልድም ጭምር አይደለም /ዮሐ.፲፭፡፳፮/፡፡ መንፈስ ቅዱስ ቢሠርፅ እንጂ አያሠርጽም፤ አይወልድም፤ አይወለድም፡፡ በባሕርይ፥ በመለኮት፥ በሥልጣን፥ በሕልውና፥ በአገዛዝ፥ ዓለማትን በመፍጠርና በማሳለፍ ከአብና ከወልድ ጋራ የተካከለ ነው /ጸሎተ ሃይማኖት/፡፡ ቀዳሚነትም ኾነ ተቀዳሚነት የሌለው ይልቁንም ከአብና ከወልድ ጋር የተካከለ (ዕሩይ) ነው፡፡ ከአብና ከወልድ ጋር ዓለም ሳይፈጠር ፥ ዘመን ሳይቈጠር ይህ ነው በማይበል ዘመን የነበረ ቀዳማዊ፤ ከአብና ከወልድ ጋር አሁንም ያለ ማዕከላዊ፤ ከአብና ከወልድ ጋር አብሮ ተካክሎ ይህ ነው ለማይባል ዘመን ወደፊት የሚኖር ደኃራዊ ነው፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/

ጾመ ሐዋርያት (የሰኔ ጾም) ፤ ከባለ 3 ገጹ የፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት ላይ የተወሰደ፡፡

ጾመ ሐዋርያት (የሰኔ ጾም) ፤ ከባለ 3 ገጹ የፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት ላይ የተወሰደ፡፡

(ከታች ያሉትን 2ት ፍሬ ነገሮች ለታሪክ ማስታወሻነት እንዲሆኑ፤ በፈለጋችሁት የቅኔ መንገድና የቅኔ ቤት ዝረፏት /አሰናኟት/፡፡) #አቡነ_ኤልሳዕን_ባሰብን_ጊዜ_፤ _ ፩#ነቢዩ ኤልሳዕ በሠረገላ ከተጓዘው ከመምህሩ ከኤልያስ የዮርዳኖስ ባሕርን ተሻግሮ በረከትን እንደተቀበለ፤ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕም በገላውዴዎስ ታቦት ሠረገላ ከሚባርኩት ከመምህሮቹ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት (ቅዱስ ፓትርያርኩና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት) እጅ የዐባይን ወንዝ ተሻግሮ /በበዓለ ዕረፍቱ ቀን/ በረከትን ተቀበለ፤ በዓለ ዕረፍቱን አስባረክ፡፡ ፪#፠ፓትርያርኩና ጳጳሳቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባን አቋርጠው አቡነ ኤልሳዕ ዕድሜ ዘመናቸውን ይወዱት ወደ ነበረውና ወዳሠሩት የቅዱስ ገላውዴዎስ ቤ/ክ በመሄድ በመገረምና በመደነቅ እንዲህ እያሉ በውዳሴና በቅዳሴ፤ በቡራኬና በማኅሌት ሥርዐተ ግብዐተ መሬቱን አከናወኑ፤ * ታላቁ አባታችን ሆይ ተለይህን!? * መምህራችን ሆይ ዝም አልክን!? * መካሪያችን ሆይ ጸጥታን መረጥክን!? ፠ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በጎን እያለቀሱ ፥ በጎን የያሬድን ዜማ እያፈሰሱ ሸኟቸው፤ ፠ ምእመናን ተክዘው ፤ ጉንጫቸው የዕንባ ሸለቆ ሁኖ ተሰናበቷቸው፤ ፠ አንዳንዱም የሆነውን ባለማመን የሚደረጉትን ሁኔታዎች በማየት ደንግጦ የሚደረጉትን ድርጊቶች በማየት ተሰናበታቸው፡፡ ፠፠፠እርሳቸው ለካ ጕዞ ኑሯቸው የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባን በሚከተሉት ሁኔታዎች ረስተው ወደ ጕዟቸው አመሩ፤ * በጎንደር ሆስፒታል ሐኪሞች ፍቅር ተስበው፤ * ከጎንደር ከተማ ወደ ደቡብ ጎንደር በሠረገላ (በመኪና) ጕዞ እንቅልፍ አሸልበው፤ * በመካነ ሰማዕት ገባሬ መንክራት ቅዱስ ገላውዴዎስ ታቦተ ሕግ ዑደት ቡራኬ ያሉበትን ረስተው፤ * በፓትርያርኩ ቡራኬና ተባርከው፤ ‹የሰላም አባት› በሚል ማዕረግና ሽልማት ተደስተው፣ * በፓትርያርኩና በጳጳሳቱ ቅዳሴና ዕጣን ተመስጠው፣ * በጕዟቸውም በየከተሞቹ፤ ከጎንደር ከተማ እስከ ደብረ ታቦር፤ ከቆማ ፋሲለደስ እስከ ገላውዴዎስ በቅዱስ ያሬድና በተከታዮቹ ደባትር ካህናት ዜማና ጸሎተ ፍትሐት ተማርከውና ፈዘው፣ (ወተቀበልዎ መላእክት በስብሐት ውስተ ሰማያት /ለብጹዕ ኤልሳዕ/፤ ወአብእዎ ኢየሩላሌም ሰማያዊት በፍሐ ወበሐሴት፡፡ (መላእክት በሰማያት በምሥጋና ብጹዕ ኤልሳን ተቀበሉት፤ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ወደተባለች ለጊዜው ገነት ለመጨረሻው መንግሥተ ሰማያት በደስታና በእልልታ አስገቡት፡፡) በሚለው ፈዘው * በመንግሥት አካላት እጀባ ኮርተው፤ * በምእመናን ዕንባና ሐዘን ተታለው፤ ******** አልተመለሱም፤ ወደ ወዲያኛው ዓለም፤ ይመኙት ወደነበረው፤ ወዳገለገሉት አምላክ አመሩ እንጂ።