es
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Ir al canal en Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

El canal Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 411 suscriptores, ocupando la posición 5 577 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 191 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 411 suscriptores.

Según los últimos datos del 11 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 64, y en las últimas 24 horas de 24, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 24.26%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 9.47% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 737 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 458 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 23.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 12 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 411
Suscriptores
+2424 horas
+237 días
+6430 días
Archivo de publicaciones
ጾመ ሐዋርያት (የሰኔ ጾም) ፤ ከባለ 3 ገጹ የፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት ላይ የተወሰደ፡፡

(ከታች ያሉትን 2ት ፍሬ ነገሮች ለታሪክ ማስታወሻነት እንዲሆኑ፤ በፈለጋችሁት የቅኔ መንገድና የቅኔ ቤት ዝረፏት /አሰናኟት/፡፡) #አቡነ_ኤልሳዕን_ባሰብን_ጊዜ_፤ _ ፩#ነቢዩ ኤልሳዕ በሠረገላ ከተጓዘው ከመምህሩ ከኤልያስ የዮርዳኖስ ባሕርን ተሻግሮ በረከትን እንደተቀበለ፤ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕም በገላውዴዎስ ታቦት ሠረገላ ከሚባርኩት ከመምህሮቹ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት (ቅዱስ ፓትርያርኩና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት) እጅ የዐባይን ወንዝ ተሻግሮ /በበዓለ ዕረፍቱ ቀን/ በረከትን ተቀበለ፤ በዓለ ዕረፍቱን አስባረክ፡፡ ፪#፠ፓትርያርኩና ጳጳሳቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባን አቋርጠው አቡነ ኤልሳዕ ዕድሜ ዘመናቸውን ይወዱት ወደ ነበረውና ወዳሠሩት የቅዱስ ገላውዴዎስ ቤ/ክ በመሄድ በመገረምና በመደነቅ እንዲህ እያሉ በውዳሴና በቅዳሴ፤ በቡራኬና በማኅሌት ሥርዐተ ግብዐተ መሬቱን አከናወኑ፤ * ታላቁ አባታችን ሆይ ተለይህን!? * መምህራችን ሆይ ዝም አልክን!? * መካሪያችን ሆይ ጸጥታን መረጥክን!? ፠ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በጎን እያለቀሱ ፥ በጎን የያሬድን ዜማ እያፈሰሱ ሸኟቸው፤ ፠ ምእመናን ተክዘው ፤ ጉንጫቸው የዕንባ ሸለቆ ሁኖ ተሰናበቷቸው፤ ፠ አንዳንዱም የሆነውን ባለማመን የሚደረጉትን ሁኔታዎች በማየት ደንግጦ የሚደረጉትን ድርጊቶች በማየት ተሰናበታቸው፡፡ ፠፠፠እርሳቸው ለካ ጕዞ ኑሯቸው የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባን በሚከተሉት ሁኔታዎች ረስተው ወደ ጕዟቸው አመሩ፤ * በጎንደር ሆስፒታል ሐኪሞች ፍቅር ተስበው፤ * ከጎንደር ከተማ ወደ ደቡብ ጎንደር በሠረገላ (በመኪና) ጕዞ እንቅልፍ አሸልበው፤ * በመካነ ሰማዕት ገባሬ መንክራት ቅዱስ ገላውዴዎስ ታቦተ ሕግ ዑደት ቡራኬ ያሉበትን ረስተው፤ * በፓትርያርኩ ቡራኬና ተባርከው፤ ‹የሰላም አባት› በሚል ማዕረግና ሽልማት ተደስተው፣ * በፓትርያርኩና በጳጳሳቱ ቅዳሴና ዕጣን ተመስጠው፣ * በጕዟቸውም በየከተሞቹ፤ ከጎንደር ከተማ እስከ ደብረ ታቦር፤ ከቆማ ፋሲለደስ እስከ ገላውዴዎስ በቅዱስ ያሬድና በተከታዮቹ ደባትር ካህናት ዜማና ጸሎተ ፍትሐት ተማርከውና ፈዘው፣ (ወተቀበልዎ መላእክት በስብሐት ውስተ ሰማያት /ለብጹዕ ኤልሳዕ/፤ ወአብእዎ ኢየሩላሌም ሰማያዊት በፍሐ ወበሐሴት፡፡ (መላእክት በሰማያት በምሥጋና ብጹዕ ኤልሳን ተቀበሉት፤ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ወደተባለች ለጊዜው ገነት ለመጨረሻው መንግሥተ ሰማያት በደስታና በእልልታ አስገቡት፡፡) በሚለው ፈዘው * በመንግሥት አካላት እጀባ ኮርተው፤ * በምእመናን ዕንባና ሐዘን ተታለው፤ ******** አልተመለሱም፤ ወደ ወዲያኛው ዓለም፤ ይመኙት ወደነበረው፤ ወዳገለገሉት አምላክ አመሩ እንጂ።

የመልስ መርሐ ግብር ጥሪ፡፡ ለ .................................... የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ትቤት፤ ከዚህ በፊት ጋብቻቸውን ለፈጸሙ እኅቶቻችን፣ ወንድሞቻችንና ማኅበረ ካህናት የሚኾን ልዩ የመልስ መርሐ ግብር እሑድ ሰኔ 2/፳፻፲፩ ዓ.ም. ከቀኑ በ7፡30 ላይ አዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል፤ በመኾኑም ከ ባለቤትዎ/ባልተቤትዎ/ ጋር እንዲገኙልን በማክበር ጠርተንዎታል፡፡ ፠፠ለበዓሉ ድምቀት፤ ወደ መርሐ ግብሩ ሲመጡ ሥርዐተ ቤተክርስቲያንን የጠበቀ የሃገር ባህል ልብስ ወይም የተሞሸሩበትን የሃገር ባህል ልብስ ለብሰው እንዲመጡ በትህትና እናሳስባለን፡ ‹‹በእናንተ ዘንድ ሁሉ በፍቅር ይሁን፡፡›› ዕብ. ፲፥፳፭ ሰዓት በማክበር የበኩልዎን አስተዋጽዖ ያድርጉ፡፡ የፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት/ቤት፡፡

በእንተ ግብረ ሰዶም፤ እምጥንቱ እስከ ተፍጻሜቱ፡፡ /ክፍል ፩/ በመጪው ነሐሴ በጉብኝት ስም ወደ ኢትዮጵያ እንመጣለን ያሉ ግብረ ሰዶማውያንን #መሬቷና_ሕዝቡ_እንዳይቀበሏቸው_ቅዱስ_ሲኖዶስ_አወገዘ፨ ***የግብረ ሰዶም ድርጊት፤ ፠በሃይማኖት ኀጢአት የሆነ፤ ፠በባህል ነውርና አጸያፊ የሆነ፣ ፠በተፈጥሮ እንስሳት (ቊንጫ እንኳን የማትፈጽመው) አስጸያፊ ነውር የሆነ፤ ፠በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 629 ወንጀል የሆነ ነው፡፡ ፠በምንም ተኣምር በመጪው ነሐሴ ወር በቶቶ ቱርስ አስተባባሪነት ግብረ ሰዶማውያን በቱሪዝም ሽፋን ቅዱሳት መካናትን እንዳይረግጡ ለመንግሥት ማሳሰቢያ እንዲጻፍ አዘዘ፡፡ **መንግሥትም ይህን ድርጊት እንዲያወግዝ፤ በወንጀል አድራጎቱ የሚያዙ ግለሰቦችን በቀላል ቅጣት መለቀቅ እንደሌለባቸውና የወንጀል ሕጉን በማጥበቅ ቁርጠኝነቱን እንዲያሳይ ጠየቀ፡፡ **ለጋባዡ ፥ ለቪዛ ፈቃጁ ለኢትዮጵያ መንግሥትም ጠበቅ ያለ ማሳሰቢያና ማስጠንቀቂያ እንዲጻፍም ሲኖዶሱ አዟል። **ይህ ወንጀል መሆኑንና የሚያሳስር የሚያስቀጣ መሆኑን እያወቀ የጉብኝቱን ቪዛ የፈቀደው በአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በሕግ መጠየቅ እንዳለበትም ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ የሕግ ባለሙያዎች እየጠቆሙም ይገኛሉ። **የፌደራል ፖሊስ ልክ ቦሌ ላይ ሀሺሽ፣ ሕገ ወጥ መሣሪያዎችን ሲገቡ ይዞ ወደ ሕግ ጥላ ሥር እንደሚያውለው ሁሉ እነዚህን በግልጽ ግብረ ሶዶማዊያን ነን ብለው እያወጁ ኢትዮጵያ ለመምጣት የወሰኑትን በኢትዮጵያ ወንጀል በመሆኑ እንዲያስርና በሕግ እንዲጠየቁም ያደረግ ዘንድም ብዙዎችም በመጠየቅ ላይ ናቸው፡፡ ከሡራኄ (Surahe) ገጽ የተወሰደ፡፡ https://t.me/Surahe

#የክርስቶስ_ዕርገት_በትምህርተ_ሐዋርያት ጌታ ኢየሱስም ከእነርሱ ጋር ከተነጋገረ በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ፡፡ ማር.16፥19 ‹‹እስከ ቢታንያ አወጣቸው እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ እነርሱም ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደኢየሩሳሌም ተመለሱ፤ ዘወትርም እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እየባረኩ በመቅደስ ኖሩ፡፡›› ሉቃ.24፥50 ‹‹ይህንም ከተናገረ በኋላ እነርሱ እያዩት ከፍ ከፍ አለ ደመናም ከዐይናቸው ሰውራ ተቀበለችው፤ እርሱም ሲሄድ ወደ ሰማይ ትኩር ብለው ሲመለከቱ ሳሉ እነሆ ነጫጭ ልብስ ለብሰው ሁለት ሰዎች /መላእክት/ በአጠገባቸው ቆሙ ደግሞም ‹‹የገሊላ ሰዎች ሆይ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት ዳግመኛ ይመጣል፡፡›› አሏቸው›› ሐዋ.1፥9-12 በማለት ሐዋርያት የክርስቶስን ዕርገት ከመላእክት ጋር ሆነው እንደተመለከቱ ደስታውን እንደተካፈሉ ቅዱስ ሉቃስ ጽፎልናል፡፡ በትንሣኤው ነጭ ልብስ ለብሰው የታዩ መላእክት የደስታ ዘመን ነው ሲሉ በእርገቱም ነጭ ልብስ ለብሰው የዕርገቱን የምሥራች ለሐዋርያት አብስረዋል፡፡ /ምንጭ፤ የቃል ትምህርትና በመምህር ምሥጢረ ሥሳሴ ማናየ/ የአምላካችን ቸርነቱ ረድኤቱ አይለየን፡፡፠ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፠

ዕርገተ እግዚእ እንኳን ለጌታችን በዓለ ዕርገት ሐሙስ ግንቦት 29/2011ዓ.ም. አደረሳችሁ፥ አደረሰን፤ በዓሉን የሚመለከት ጽሑፍና ሥርዐተ ማኅሌቱን እንደተለመደው አቅርበንላችኋል፡፡ መልካም ንባብ፤ መልካም የምሥጋና ማኅሌት፡፡ /ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ሰሌዳ መጽሔት በማሳጠር የተወሰደ/ ‹‹አልቦ ዘዓርገ ውስተ ሰማይ ዘእንበለ ዘወረደ እምሰማይ ወልደ ዕጓለመሕያው፤ ከሰማይ ከወረደው የሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም፡፡›› ዮሐ.3፥13 ከሰማይ ከወረደው የሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም፡፡ እርሱም በሰማይ የሚኖረው ነው፡፡ ይህ ኃይለ ቃል ክብር ምስጋና ይግባውና ስለጌታችን፣ አምላካችን፣ መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማየ ሰማያት መውረድ ከድንግል ማርያም መወለድ እና የሰውነቱን ሥራ ጨርሶ በክብር ወደ ሰማይ ማረጉን የሚገልጽ ነው፡፡ እንደሚታወቀው አምላካችን ስለሁለት ዐቢይ ጉዳዮች ሰው ሆኗል፡፡ 1. *ለቤዛነት /ዓለምን ለማዳን/ 2. *ለአርአያነት /ምሳሌነት/ የሰውን ልጅ በመውደዱ ልዑል ባሕርዩን ዝቅ አድርጎ ከሰማይ ወረደ ሥጋ ለበሰ በምድር ላይ ተመላለሰ፤ ምድርን በኪደተ እግሩ ቀደሰ፤ ድውያንን ፈወሰ፤ ፍጹም ሰው እንደ መሆኑ ተራበ ፍጹም አምላክ መሆኑንም ያስረዳ ዘንድ አምስት ገበያ ሕዝብ በአምስት እንጀራ በሁለት ዓሣ አጠገበ ማቴ.14፥19 ለእኛ አርአያና ምሳሌ ለመሆን ዝቅ ብሎ የደቀ መዛሙርቱን እግር አጠበ ዮሐ.13፥14 እኛም ፍለጋውን እንከተል ዘንድ አንትሙኒ ከመዝ ግበሩ ለቢጽክሙ እናንተም ለባልንጀሮቻችሁ እንዲሁ አድርጉ ብሎ አዘዘ፡፡ መምሕረ ትሕትና ነውና በዚህ ዓይነት መልኩ ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር በዚህ ዓለም ኖረ ለሐዋርያት ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ወንጌልን አስተማራቸው ትምህርት በሚገባ ከተረዳለት በኋላ ለድኅነተ ዓለም በማዕከለ ምድር በቀራንዮ ተሰቀለ፡፡ #ወገብረ_መድኀኒተ_በማዕከለ_ምድር_እንዲል_በምድር_መካከል_መድኀኒትን_አደረገ_መዝ.73፥12 ‹‹እስመ ኢይደልዎ ለነቢይ መዊት በአፍአ ዘእንበለ በኢየሩሳሌም፤ ነቢይ በኢየሩሳሌም ነው እንጂ በውጭ ሊሞት አይገባውም፡፡›› ብሎ እንደተናገረ፡፡ ሉቃ.13፥33 በሞቱ ዓለምን አድኖ ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በከርሰ መቃብር አድሮ ሙስና መቃብርን አጥፍቶ ብርሃነ መለኮቱን ገልጾ ተነሣ፡፡ ነቢያት እንደተናገሩ ‹‹እግዚአብሔር ይነሣል ጠላቶቹም ይበተናሉ›› መዝ.67፥1 ‹‹እኔ ተኛሁ አንቀላፋሁ እግዚአብሔርም አስነሥቶኛልና ተነሣሁ፡፡›› መዝ.3፥5 ‹‹እግዚአብሔር አሁን እነሣለሁ ይላል መድኀኒትንም አደርጋለሁ በዕለቱም እገለጣለሁ›› መዝ.11፥5፡፡ ‹‹ሥጋየ ደግሞ በተስፋ /በትንሣኤ/ ታድራለች ነፍሴን በሲዖል /በመቃብር/ አትተዋትምና/ እነሣለሁ ቅዱስህንም መበስበስን ያይ ዘንድ አትተወውም፡፡›› መዝ.15፥9 ‹‹አቤቱ ንቃ ለምንስ ትተኛለህ ተነሥ ለዘወትርም አትጣለን›› መዝ.43፥23 ‹‹እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ›› መዝ.77፥65 ተብሎ የተተነበየውን ትንቢት ፈጽሞ ተነሣ፡፡ በሞቱ ሞታችንን ሻረልን፤ በመቀበሩም ሙስና መቃብርን አጠፋልን፡፡ ‹‹በሞቱ ሞትን አጠፋው›› እንዲል መጽሐፈ ኪዳን፡፡ ሕንፃ መነኮሳት ‹እርሱ በሁሉ ምሉዕ ሲሆን በመቃብር ለመቀበር ዮሴፍ ኒቆዲሞስ ገንዘውት ታየ፡፡ ከመሬት ውስጥ በመቀበሩም ሙስና መቃብርን አጠፋ፤ ከሥሩም ነቀለው ከተነሣ በኋላ ትንሣኤውን መጀመሪያ ለማርያም መግደላዊት ገለጸ ማር.16፥9፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ስለ ትንሣኤው ሲመሰክር ‹‹ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፤ ተቀበረም፤ መጽሐፍ እንደሚል፤ በሦስተኛው ቀን ተነሣ፡፡ ለኬፋም ታየ በኋላም ለአሥራ ሁለቱ ከዚያም በኋላ ከአምስት መቶ ለሚበዙ ወንድሞች በአንድ ጊዜ ታየ፡፡ ከዚያም በኋላ ለያዕቆብ ኋላም ለሐዋርያት ሁሉ ታየ›› 1ቆሮ.15፥3-8 ብሎ ክርስቶስ ትንሣኤውን ለተከታዮቹ በሙሉ የገለጠ መሆኑን መስክሯል፡፡ የሚያምኑ ፈሪሳውያንም ‹‹ትንሣኤው ምትሐት ነው›› እንዳይሉ እየታየ እያስተማረ እስከ 40 ቀን ድረስ መቆየቱን ይገልጽልና፡፡ በዚህም የአርባ ቀን ከትንሣኤ በኋላ ቆይታው ሦስት ቀን ጉባኤ አድርጎ ደቀ መዛሙርቱን እንዳስተማረ ቅዱስ ወንጌል ይነግረናል፡፡ ኢየሱስ ከሙታን ከተነሣ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ ሲገለጥላቸው ይህ ሦስተኛ ጊዜ ነበረ እንዲል ዮሐ.21፥14 ይህንም ሊቃውንት አባቶቻችን፡- 1. *የትንሣኤ 2. *የአግብኦተ ግብር /ዳግም ትንሣኤ/ 3. *የጥብርያዶስ ነው ብለው አስቀምጠውታል በዚህ 40 ቀን ቆይታ መጽሐፈ ኪዳንን ለደቀ መዛሙርቱ አስተምሯል፡፡ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስም ዕርገቱን ለመናገር ከሰማየ ሰማያት መውረዱን አስቀድሞ ከሰማይ ከወረደው ከሰው ልጅ በቀር ማንም ወደ ሰማይ የወጣ የለም እርሱም በሰማይ የሚኖረው ነው ብሎ ከዕርገቱ በኋላ በየማነ አብ፤ በዘባነ ኪሩብ በአምላክነት ሥልጣን ለመኖር ወደሰማይ የወጣ ከእርሱ በቀር ሌላ እንደሌለ አስረግጦ ነገረን፡፡ ሲጀምር ከሰማይ መውረዱን ማስቀደሙ ወረደ ብሎ ዐረገ ለማለት ይመቻል፡፡ ተጸነሰ ተወለደ ለማለት ጥንቱ ከሰማያት ወረደ ማለት እንደሆነ ሁሉ፤ ‹‹ተሰቀለ፤ ሞተ፤ ተቀበረ፤ ተነሣ'››ለማለት ‹‹ጥንቱ:- ተጸነሰ፤ ተወለደ፤ አደገ ተመላለሰ ሠላሳ ዓመት ኖረ›› የሚለው ነው፡፡ ስለሆነም ቅዱስ ዮሐንስ ጠርዝና ጠርዙን ይዞ ተናገረ፡፡ ‹‹ወረደ ዐረገ›› የሚሉት ሁለት ቃላት የዓለም ድኅነት መነሻና መድረሻ ናቸው፤ እነዚህን ሁለት ቃላት ስናይ በሁለቱ መካከል የተፈጸሙትን የአምላክ ሥራዎች ልብ ማለት ይገባል፡፡ ቤት በመሠረት ይጀመራል በጣሪያ ይፈጸማል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ይህን የቤዛነት ሥራ ሲያስረዳ በዮሐ.1፥14 ‹‹ቃል ሥጋ ኮነ፤ ቃል ሥጋ ሆነ›› ብሎ ጀምሯል ይህንም ቃል ‹‹ከሰማይ ከወረደው የሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም›› በማለት ሰው መሆኑን ብቻ ሳይሆን በአርያም የሚኖር መሆኑን አስተማረን፡፡ እንግዲህ ጌታችን ዕርገት እንዲሁ እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ውኃ ፈሳሽ አለመሆኑን ቀድሞ በነቢያት የተነገረ ኋላም በሐዋርያት የተመሰከረ መሆኑን ማወቅ ያስፈለጋል፡፡ #የክርስቶስ_ዕርገት_በትንቢተ_ነቢያት ‹‹ሰማዮችን ዝቅ ዝቅ አደረገ ወረደም ጨለማ /ዲያብሎስ/ ከእግሩ በታች ነበር በኪሩቤል ላይ ተቀምጦ በረረ በነፍሳትም ክንፍ በረረ›› መዝ.17፥9 ‹‹አምላክ በእልልታ እግዚአብሔር በመለከት ድምጽ ዐረገ መዝ.46፥5 ወደላይ ዐረግህ፥ ምርኮን ማረክህ ፥ስጦታንም ለሰዎች ሰጠህ›› መዝ.67፥18፡፡ ‹‹ዘምሩ ለእግዚአብሔር ዘዓርገ ውስተ ሰማይ ዘመንገለ ጽባሕ፤ በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ›› መዝ.67፥33፡፡

እንኳን ለአምላካችንና ፈጣሪያችን ቅዱስ አማኑኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን ፥ አደረሳችሁ፡፡ ክብረ በዓሉ ከሚከበርባቸው ገዳማትና አድባራት ዐበይቶቹ (እናንተም የምታውቋቸውንና በአቅራቢያችሁ ያሉትንከነፎቷቸው ጨምሩበት) ፠ ኦፍና አማኑኤል፤ መርሐ ቤቴ፥ አለም ከተማ፤ በ4ኛው ክፍለ ዘመን የተመሠረተ ጥንታዊ ቤ.ክ. ፠ ኤነር አማኑኤል፤ ምድረ ጕራጌ፤ እጅግ በጣም ጥንታዊ ገዳም ፠ ደብረ መንክራት በጎል ሰከበ ሚጣቅ ቅዱስ አማኑኤል፤ ከደብረ ብርሃንና አንኮበር መሃል ላይ የሚገኝ፤ በንጉሥ ሣህለ ሥላሴ የተመሠረተ፤ እጅጉን በጣም ፈዋሽ የኾነ ጠበል የሚገኝበትና የቅዱሳን መናኸሪያ የኾነ፡፡ ፠ ጫገል ቅዱስ አማኑኤል /በደብረ ሊባኖስ ገዳም ከሚተዳደሩ አብያተ ክርስቲያናት አንዱ/ ፠ ደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል፣ አዲስ አበባ፤ መርካቶ መሳለሚያ ፠ ባሶ ወረዳ ጣፎ ደብረ ሰላም ቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን፤ ከጢያ ከተማ ወደ አጠገብ የሚገኝ፡፡

#_ግንቦት_26_ኢትዮጵያዊው_ጻድቅ_አቡነ_ሀብተ_ማርያም_ልደታቸው_ነው፡፡ ፠፠በማዕጠንታቸው የታወቁ፤ ፠፠በጽድቅ ሥራቸው የተደነቁ፤ ፠፠5ት መቅሰፍቶችን የሚያርቁ፨ ፠በመራ ውዕይ (ሸዋ ፥ ቡልጋ) ከአባታቸው ፍሬ ቡሩክና ከእናታቸው ቅድስት ዮስቴና ነው የተወለዱት፡፡ ወላጆቹ በተለይም እናቱ ከማግባቷ በፊት መንና ነበር፡፡ ጻድቁን እንደምትወልድ በበቃ ባሕታዊ ተነግሯት ጻድቁን ወልዳ በጽድቅ ኑሮ ኑራ 7 አክሊላትን ተቀብላ በክብር አርፋለች፡፡ ፠አቡነ ሀብተማርያም በሕፃንነታቸው ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ ‹‹እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ›› ሲባል ይሰማሉ፤ በሕፃን አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ ‹‹ማረን እባክህን›› እያሉ ይሰግዱ ነበር፡፡ ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ፡፡ ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው ብዙ ተአምራትን ሠርተዋል፤ ጓደኞቻቸው የሌላ ሰው እሸት እየነቀሉ ሲበሉ እርሳቸው ግን አይበሉም ነበር፡፡ የፈጣሪውን ስም ያቃለለውን አንድ እረኛም በአየር ላይ ሰቅለው አውለውታል፡፡ ፠ወደ ት/ቤት ገብተው ትምህርትን ከቀሰሙ በኋላ ለአካለ መጠን ሲደርሱ ቤተ ሰቦቻቸው ሚስት አጩለት፤ እርሱ ግን ወደ አፋር ከአባ ሳሙኤል ዘንድ ሂዶ ለ12 ዓመታት ረድዕ ሆኖ ተቀመጠ፡፡ ከአፋርም ወደ ምኔት ወደሚባል ቦታ መጥቶ በታላቁ አባት በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሰ፤ ከአፋር ወደ ይነውፋ፥ ከይነውፋ ወደ ጉሐርብ ወደሚባል ሃገር ሂዶ ምናኔን፣ ትሩፋትንና ተጋድሎን ሠራ፡፡ ለአብነትም፤ *ባሕር ውስጥ ሰጥሞ 500 ጊዜ ይሰግዳል፤ *በየቀኑ 4ቱን ወንጌልንና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያል፤ *በ40 ቀናት ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባል፤ *ምግቡ ደግሞ ሣርና ቅጠል ብቻ ነው፤ *በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርል፤ *ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላል፥ ክቡር ደሙን ይጠጣል፤ *በልቡ ውስጥ በፍጹም ቂምን፣ መከፋትን አያሳድርም፡፡ *የብረት ሰንሰለት በወገቡ ታጥቆ ይሰግዳል ይጸልያልም፡፡ *"ጽድቅና ትሩፋት እንደ ሀብተ ማርያም" የተባለለት ታላቅ አባት ነው፡፡ ፠ዲቁናን ከጳጳሱ አቡነ ይስሐቅ ዘንድ ተቀበሎ ወደ በዓቱ ተመለሰ፡፡ ፠ኋላ ቆይቶም እንደገና ከአቡነ ይስሐቅ ዘንድ ቅስናን ተቀበለ፡፡ ወደ ጓና ወደ ምትባል ሀገርም ሂዶ ተቀመጠ፡፡ ቀጥሎም ጐላጐት ወደ ምትባል አገር ሂዶ ተቀመጠ፡፡ *የአፄ ናዖድ የንስሐ አባት ነበረና ንጉሡን ያስተምረውና ይገስጸውም ነበር፡፡ ፠ጌታችንም ለጻድቁ የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቶት በዚያ እየበረረ ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ተለያዩ ቦታዎች ይሔድ ነበር፡፡ ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በኋላም የክብር ባለቤት መድኀኒታችን ክርስቶስ አእላፍ መላእክትን አስከተትሎ መጥቶ እንዲህ አላቸው:: "*ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ: *ስለ ምናኔሕ: *ስለ ተባረከ ምንኩስናህ: *ስለ ንጹሕ ድንግልናህ: *ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ: *ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ: *ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን እሰጥሃለሁ::" "በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን: 500 የዕንቊ ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ:: በስምህ የሚለምኑ: በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ 'አማንየ በርእስየ' ብዬሃለሁ" አላቸው:: +ቅዱሳን መላእክትም "ሀብተ ማርያም ወንድማችን" ሲሉ አቀፏቸው:: ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ሳማቸው:: ከፍቅሩ ጽናትም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች:: በዝማሬም ወሰዷት::  ከተሰጣቸው ቃል ኪዳኖች ውስጥ አምስት መቅሰፍቶች የማስወገድ ሥልጣን ተሰጧቸዋል፡፡ እነርሱም፤ 1. #_መብረቅ፣ 2. #_ቸነፈር፣ 3. #_ረሃብ፣ 4.#_ወረርሽኝ፣ 5.#_የእሳት ቃጠሎ ናቸው፡፡ ፨በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትዕዛዝ ቦታውን ሲባርክ ሦስት አጋንንት በጸሎቱ ሥልጣን የታሠሩለት ታላቅ ጻድቅ ነው፡፡ በግንቦት 26 ተወልዶ፤ በ1490 ዓ.ም. በወርኀ ኅዳር 26 ባረፈ ጊዜም፤ ካህናት በመልካም ልብስ ገንዘው በዝማሬ በማኅሌት ከቅዱስ አባታችን ከአቡነ ተክለሃይማኖት አጽም ጋር በደብረ ሊባኖስ ቀበሩት፡፡ (ከወርቅ ንፁህ ከብርም የጠራ ከሁሉ የሚበልጥ የተመረጠ ሃብተማርያም መልአክ ዘበምድር ነው መልካሙ ዜናው እስከ አጽናፍ ተሰማ፡፡) #ሰላም_ለጽንሰትከ_እማኅፀነ_ቅድስት_ዮስቴና፤ #በብሥራተ_ጻድቅ_ባሕታዊ_ሠናየ_ዜና፡፡ #ሀብተማርያም_ጴጥሮስ_ሐዋርያ_ወልደ_ዮና፤ #መሐረኒ_ምግባረ_ጽድቅ_ወጸግወኒ_ልቡና፤ #አፍቅሮ_ቢጽ_እኅሥሥ_ዘምስለ_ፍጽመት_ትሕትና፡፡ ፎቶ ላይ የሚታዩት ገዳሞቹ፤ ፨ብሔረ ብፁዓን ድበረ ይሰበይ አቡነ ሀብተማርያም ገዳም፤ ደብረ ሊባኖስ አጠገብ ፨ቃሌ ተራራ ደብረ መድኀኒት አቡነ ሀብተማርያም ገዳም፤ አዲስ አበባ ከዊንጌት ትምህርት ቤት አጠገብ፡፡

‹‹ከእግዚአብሔር የኾነ የእግዚአብሔርን ቃል ይሰማል፡፡››፤ በልዩ አቀራረብና በአዲስ የሥርዐተ ትምህርት ዝግጅት፡፡ /ለትምህርቱ የምትመዘገቡ ካሁኑ ዝጅት አድርጉ፤ እንደ አስፈላጊነቱ የመግቢያ ፈተና ሊኖር ይችላል!!፡፡/

#ግንቦት_24_በዓተ_ግብጽ_፤ እመቤታችን እመ አምላክ ድንግል ማርያም ከልጇና ከአረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍ ጋር ለ3 ዓመት ከ6 ወር ከተሰደዱ በኋላ ወደ ግብጽ ሃገር ገብታ በሰላም ያረፈችበት ቀን ነው፡፡ ዖፍኒ ረከበት ላቲ ቤተ፤ ወፍም ቤቷን ሰራች፡፡ መዝ. ፹፫፥፫ *በአዲስ አበባ ታቦተ ሕጉ የሚነግሥባቸው ቦታዎች፤ ፠እንጦጦ መንበረ ንግሥት ቅድስት ቊስቋም ማርያም፡፡ (365ት ቀናት ሙሉ ዝክር በማኅበረ መድኀኔ ዓለም አዳራሽ የሚዘከርባት ቤ/ክ) ፠ደብረ ናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ ቤተ ክርስቲያን፡፡ (የቤ/ክርስቲያኑ ዐጸድ እጅጉን ልብን የሚገዛና የሚማርክ)

#የ100ኛ_ዓመት_መዝጊያ_መርሐ_ግብር_በደብረ_ናዝሬት_ቅዱስ_ዮሴፍ_ቤተ_ክርስቲያን፡፡ ፠እድሳት የተደገለት ሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ (ከ፻ ዓመት ዓመታት በፊት በ፲፻፱፲ ዓ.ም. በሰብዮን ኀይለ ማርያም የተመሠረተው) ዐርብ ግንቦት 23 በ9 ሰዐት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ይመረቃል፡፡ ፠ግንቦት 24/2011 ታቦቱ ወጥቶ ይነግሳል፡፡ ፠ከግንቦት 23-27፤ ከ10፡30 ጀምሮ ልዩ የዐውደ ምሕረት ጕባኤ ይካሄዳል፡፡ #ጻድቁ_ዮሴፍ_፤ **የጌታችን ከእመቤታችን መጸነስ በመንፈስ ቅዱስ ግብር መሆኑን በመልአክ የተገለጸለት **የእመቤታችን የድንግል ማርያም ጠባቂዋ፤ **ከእመቤታችንና ከልጇ ከአምላካችን ጋር ለ3 ዓመት ከ6 ወር አብሮ በበረሃ የተሰደደ **በድንግልና ለወለደችው መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ አባት ተብሎ የተጠራ **በእረፍቱ ጊዜ አባት ተብሎ በተጠራለት በመድኀኔ በክርስቶስ እጅ የገነዘ ✤#_ሊቁ_አባ_ጽጌ_ድንግል_በሰቈቃወ_ድንግል ድርሰቱ እንዲህ ብሎ ያመሰገነው፡፡ ጐየ ዮሴፍ ብሔረ ግብጽ ተንሢኦ እምንዋሙ፤ መልአከ እግዚአብሔር ሌሊተ በከመ ነገሮ በሕልሙ፡፡ ነሢኦ ሕፃነ ዘምስለ ማርያም እሙ፤ ይእቲ ትበኪ ወትቤ ቀቲሎትየ ይቅድሙ፤ እምእርአይ ለወልድየ ዘይትከዐው ደሙ፡፡ (የእግዚአብሔር መልእክተኛ የኾነ ቅዱስ ገብርኤል ሌሊት በሕልሙ እንደነገረው ዮሴፍ ከእንቅልፉ ነቅቶ ሕፃኑን ከእናቱ ከድንግል ማርያም ጋራ ይዞ ወደ ግብፅ ሃገር ሸሸ፤ ድንግል ማርያምም የልጄ ደም ሲፈስ ከማይ ይልቅ የሄሮድስ ሠራዊት እኔን አስቀድመው ይግደሉኝ እያለች አለቀሰች፡፡ / ሰቈቃወ ድንግል፣ ማቴ.2፥13/ ፠ደብሩ፤ ደብረ ናዝሬት ተብሎ የተሠየመው ጌታ በቤተ ልሔም ተወልዶ ወደ ግብጽና ኢትዮጵያ ተሰዶ ሲመለስ ወደ ቤተ ልሔም ሳይኾን ናዝሬት ገብቶ ነው ያደገው፤ እንዲሁም ናዝሬት አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ የተቀመጠባትና ብዙ ምሥጢራት ያየባት በመኾኗ ደብረ ናዝሬት ተብሎ ደብሩ ተሰይመሟል፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ በደጃዝማች መርዕድ መንገድ ላይ፤ ከቦሌ ወደ ሳሪስ አቦ በሚወስደው ቀለበት መንገዱ ዳር ላይ ይገኛል፡፡ (የታክሲ ትራንስፖርት፤ ከላጋር፣ ከፒያሣ፣ ከ4ኪሎ ቃሊቲ መናኸሪያ በቦሌ /በቀለበት መንገድ/ ብለው በሚጭኑት በቶሎ ቤተ ክርስቲያኑ በር ድረስ ያደርስዎታል፡፡)