es
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Ir al canal en Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

El canal Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 377 suscriptores, ocupando la posición 5 568 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 195 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 377 suscriptores.

Según los últimos datos del 04 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 23, y en las últimas 24 horas de -1, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 22.11%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 9.42% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 401 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 449 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 20.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 05 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 377
Suscriptores
-124 horas
-107 días
+2330 días
Archivo de publicaciones
#ጾመ_ነቢያት_ (#የገና_ጾም_) የ2013 ዓ.ም. የገና (የነቢያት) ጾም፤ ፠ #ጾሙ_ኅዳር_15_ይጀምራል_!! #Share l ፠ ከ7ቱ አጽዋማት (ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ፍልሠታ፣ ጾመ ሐዋርያት፣ ጾመ ነቢያት፣ ጾመ ድኅነት፣ ጾመ ነነዌ ና ጾመ ገሃድ) መካከል አንዱ ነው፡፡ ፠ ኅዳር 15 ቀን ተጀምሮ እስከ ልደት ለአርባ ሦስት ቀናት የሚጾም ጾም ነው፡፡ ፠ ይህንን ጾም በዘመነ ብሉይና በዘመነ ሐዲስ ብዙ ቅዱሳን ጾመውታል፤ በዚህም ምክንያት የሚከተሉት ስያሜዎች አሉት፡፡ እነርሱም፤ † ፩. #ጾመ_አዳም_፤ አዳም ዕፀ በለስን በልቶ ከገት ከተባረረ በኋላ; በፈጸመው በደል አዝኖ ፥ ተክዞ፤ አለቀሰ (እንባ ቢያልቅበት እዥ እስከሚያፈስ፤ እዥ ቢያልቅበት ደም በዓይኑ እስከሚፈስና ዓይኑ ይቡስ ወይም ደረቅ እስከሚሆን ድረስ አለቀሰ) ፥ ጾመ፣ ጸለየ፡፡ ከልብ የሆነ ጸጸቱን፣ ዕንባውን፣ በራሱ መፍረዱንም እግዚአብሔር አይቶ ተስፋ ድኅነት ሰጠው፡፡ ‹‹ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ፣ በደጅህ ድኼ፣ በዕፀ መስቀል ተሰቅዬ፣ ሞቼ አድንሃለሁ፡፡›› የሚል ነው፡፡ /ገላ. ፬፥፬፣ መጽ.ቀሌምንጦስ/ ስለዚህ ጾሙ የተሰጠው ተስፋ ፥ የተቆጠረው ሱባኤ ስለተፈጸመበት ‹‹ጾመ አዳም›› ይባላል፡፡ † ፪. #ጾመ_ነቢያት_፤ ነቢያትም የምሥጢረ ሥጋዌ ነገር ተገለጦ ስለታያቸው፣ ክርስቶስ ለሰው ልጅ የሚከፍለውን የፍቅር ዋጋ በትንቢት ተመልክተው ጾመውታልና ጾመ ነቢያት ይባላል፡፡ ይህ ጾም ከአባታችን አዳም እስከ መጥምቁ ዮሐንስ ድረስ የተነሱ አበውና እናቶች: ድኅነትንና ረድኤትን ሲሹ የጾሙት ጾም ነው:: በተለይ አባታችን አዳም: ቅዱስ ሙሴ: ቅዱስ ኤልያስ፣ ቅዱስ ዳንኤል ና ቅዱስ ዳዊት በጾማቸው የተመሰከረላቸው ቅዱሳን ናቸው:: (ዘዳ 9:19, ነገ. 19:8, ዳን. 9:3፣ መዝ. 68:10, 108:24) ቅዱሳን ነቢያት በጭንቅ በመከራ ሆነው የጾሙት ጾም ወደ መንበረ ጸባኦት ደርሶ: ወልድን ከዙፋኑ ስቦታል:: ለሞትም አብቅቶታል:: † ፫. #ጾመ_ሐዋርያት_፤ ሐዋርያት ‹‹ትንሣኤን ዐቢይ ጾምን ጾመን እናከብራለን፣ ልደትን ምን ሥራ ሠርተን እናከብረዋለን?›› ብለው ከልደተ ክርስቶስ በፊት ያሉትን ፵፫ ዕለታት ጾመዋልና፡፡ † ፬. #ጾመ_ማርያም_፤ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እግዚአብሔር አምላክ ቅድስናዋን አይቶ በቅዱስ ገብርኤል ብሥራት ወልደ አምላክን ያለ ሰስሎተ ድንግልና በግብረ መንፈስ ቅዱስ ጸንሳ እንደምትወልደው ቢነግራትም የትሕትና እናት ናትና ‹‹ምን ሠርቼ የሰማይና ምድርን ፈጣሪ እችለዋለሁ?›› ብላ ጌታን ከመውለዷ አስቀድማ ጾማለችና ‹‹ጾመ ማርያም›› ይባላል፡፡ † ፭. #ጾመ_ፊልጶስ_፤ ሐዋርያው ፊልጶስ በአረማውያን ዘንድ ገብቶ እያስተማረ ሳለ በሰማዕትነት ሲሞት፤ አስክሬኑ ከደቀመዛሙርቱ ስለተሰወረ፤ እግዚአብሔር የተሰወረውን የመምህራቸውን አስክሬን እንዲገለጽላቸው ከኅዳር ፲፮ ጀምረው ጾመው በሦስተኛው ቀን የመምህራቸው አስክሬን ተመልሶላቸዋል፤ ነገር ግን አስከሬኑ ቢመለስላቸውም ጾሙን ግን እስከ ልደት ቀጥለዋል፡፡ † ፮. #ጾመ_ስብከት_፤ የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን ያስተማሩበት፥ የሰው ልጆች ተስፋ የተመሰከረበት፥ የምስራች የተነገረበት ስለሆነ ጾመ ስብከትም ይባላል፡፡ † ፯. #ጾመ_ልደት_፤ የጾሙ መጨረሻ (መፍቻ) በዓለ ልደት ስለሆነ ‹‹ጾመ ልደት›› ይባላል፡፡ ጾምን ትእዛዝ ስለሆነ ብቻ ሳይሆን የፍቅርና የበረከት ምንጭ በመሆኑ ጭምር ደስ እያለን ብንጾመው የቅዱሳኑ በረከት ያድርብናል፡፡ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ፡፡ https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w https://t.me/medihanaelem

#አንኳን_ለቅዱስ_አግዚአብሔር አብ በዓልና_ለአእላፍ_መላእክት_በዓለ_ሢመት እንዲሁም #ቅዱስ_ሚካኤል ለሰው ልጆች ምሕረትን ከኅዳር 12 ጀምሮ እስከ 13 ድረስ ከአምላኩ ምሕረትን ለሚለምንበት) በዓል በሰላም አደረሳቹህ፡፡ ፨ ፨ ፨ #ኀዳር_13 ቀን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሊቃውንት #አእላፍ መላእክት እየተባለ ይጠራል ፤ 99ኙ ነገደ መላእክት በአንድ ላይ የሚከብሩብት ቀን ነው እንዚህም ሥጋ የሌለቸው ረቂቃንና ለዓለም ሁሉ የሚማልዱ ናቸው ፡፡ #Share ያድርጉ እግዚአብሔር ቅዱሳን መላእክትን ሲፈጥራቸው በነገድ 100 በክፍለ ነገድ 10 አድርጓቸዋል ፡፡ በ3 ሰማያትና በ10 ዓለማት ላይም ይገኛሉ፡፡ መላእክት ያሉባቸው ከተሞች #ኢዮር #ራማ #ኤረር ይባላሉ ፡፡ አሥሩ ነገዶች ከነአለቆቻቸው አንዲህ ናቸው 1. #አጋዕዝት (ቀድሞ አለቃቸው ሳጥናኤል የነበረ ፤ አሁን የተረፉት በቅዱስ ሚካኤል ስር ናቸው) 2. #ኪሩቤል (አለቃቸው ቅዱስ #ኪሩብ ፤ ለበለጠ ኀዳር 7 የጻፍነውን ይመልከቱ) 3. #ሱራፌል (አለቃችወ ቅዱስ #ሲራፊ ፤ ለበለጠ ኀዳር 24 ይጠብቁን) 4. #ኃይላት (አለቃቸው ቅዱስ #ሚካኤል ) 5. #አርባብ (አለቃቸው ቅዱስ ገብርኤል ) 6. #መናብርት (አለቃቸው ቅዱስ ሩፋኤል) 7. #ሥልጣናት (አለቃቸው ቅዱስ ሱርያል ) 8. #መኳንንት (አለቃቸው ቅዱስ ሰዳካኤል ) 9. #ሊቃናት (አለቃቸው ቅዱስ ሰላታኤል) 10. #መላእክት (አለቃቸው ቅድስ አናንኤል) ናችው፡፡ ከእነዚህም ፨ አጋዕዝት ፣ኪሩቤል ፣ ሱራፌልና ኃይላት መኖርያቸው በኢዮር(3ኛው ሰማይ ) ነው ፡፡ ፨አርባብ ፣መናብርትን ሥልጣናት መኖርያቸው በራማ ነው ፡፡ ፨መኳንንት ፣ሊቃናት ፣ መላእክት ደግሞ የሚኖሩት በኤረር ነው (1ኛው ሰማይ ) ———- (ከእልፍ አእላፋት አለቃዎች ስሞች በጥቂቱ)፡፡ ጸሎትነ ትብጻሕ (ሰላም ለክሙ) ለመላእክተ ምሕረት፤ #ሚካኤል_ወገብርኤል፥ #ሱራፌልወኪሩቤል/፬ቱ እንስሳ/፥ #ዑር(ራ)ኤል_ወሩፋኤል /፳፬ቱ ካህናተ ሰማይ/፥ #ሱርያል_ወፋኑኤል፥ #አፍኒን_ወራጕኤል፥ #ሳቁኤል_ወአቅናኤል፥ #ብርናኤል_ወሱባኤል፥ #ፍናኤል_ወሰላታኤል፥ #ሰዳካኤል_ወኤልናኤል፥ #አናንኤል_ወኢየሩማኤል፥ #ግርማኤል_ወድርማኤል ፥ #ድማህኤል_ወአድማኤል፥ #ሙራኤል_/ምናቴር_አብያቴር/፥ #ሱታ(ስቱ)ኤል_ወሱርያል፤ ……. ፨ ፨ ፨ ፨ የመላእክት ተፈጥሮ እመኀበ አልቦ ኀበ ቦ (ካለመኖር ወደመኖር ) ነው ፡፡ አይራቡም አይጠሙም ፤አይዋለደሙ ፣ አይሞቱም ፣ ዕረፍት የላቸውም ፤ምስጋናቸው እረፍታቸው ፤እረፍታቸው ምስጋናችው ነው አንጂ(አኮቴቶሙ ዕረፍቶሙ ወዕረፍቶሙ አኮቴቶሙ) እንዲል፡፡ ተፈጥሯቸው እጅግ ረቂቅ ነው፡፡ ተግባረቸውም ዘውተር እግዚአብሄርን ማመስገን ነው፡፡ —— #መላአክ ማለት ተላላኪ (አገልጋይ ) ነውና ከፈጣሪ ወደ ሰው ልጆች ለምሕረትም ፤ ለመዓትም ይላካሉ፡፡ ምሕረትን ያወረዳሉ ፡፡ ልመናን ያሳርጋሉ ቅጡ ሲባሉም ይቀጣሉ አንዲዚሁም ሁሉ ወቅትንም የሚቆጣጠሩ አሉ ፤ ስለ ሰው ልጆች ይማልዳሉ (ዘካ 1÷12 ) ምሥጢርም የሚገልፁም አሉ(ዳን 9÷21) መላእክት ተራዳኢም ናቸው (ኢያ 5÷13)፣ እነዳንሰናክል ይጠብቁናል (መዝ 90÷11 ) ፣ያድናሉ ( መዝ 33÷7 ) ፣የፀጋ ስግደትም ይገባቸዋል (መሳ 13÷20) በፍርድ ቀንም ኀጥአንን ከጻድቃን ያለያያሉ (ማቴ 25 ÷31) እነሆ እግዚአብሄር ይፈርድዘንድ ቅዱሳን መላእክቶቹን አስከትሎ ይመጣል እንዲል ፡፡ /የቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ፨፨፨ እልፍ አእላፋት ወትእልፊት ቅዱሳን ንጹሐን መላእክት ቆሙ በአገልግሎት ጸንተው በአንድነት ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ አምላክ በማለት፡፡ ምልጃቸው እና ጠብቆታቸው አይለየን አሜን ፡፡ —————— ኀዳር 13 ክብረ በዓሉ ከሚከበርባቸው ቦታዎች ጥቂቶቹ፤ ከፎቶ ጋር …. 1. ግሸን ደብረ ከርቤ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (መስቀሉ የሚገኝበት)፤ 2. ጠዳ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (ጎንደር፤ ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ)፤ 3. ጎርዶማ እግዚአብሔር አብ ቤተክርስቲያን (በሰሜን ሸዋ)፤ 4. ደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (አዲስ አበባ)፤ 5. ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤ.ክ (አዲስ አበባ) 6. ቦሌ ቡኒ ደብረ ቤቴል ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤ.ክ (አዲስ አበባ) /የቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/ #Share ያድርጉ https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

በመዲና ከተማችን የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል የሚከብርባቸው ገዳማትና አድባራትን እንጠቁማችሁ፡፡ /ፎቷቸውን ያልለጠፍናቸውና ስማቸውን ያልጠቀስናቸውን እንድትልኩልን በሊቀ መልአኩ ስም እንጠይቃለን) 1) *የካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን (ሾላ፤ መገናኛ) 2) *አንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል /ጭቁኑ/፤ ፈረንሳይ 3) *ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል (አዲሱ ሚካኤል)፤ አውቶብስ ተራ 4) *ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል፤ /ቦሌ/ 5) *ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል፤ /ላፍቶ/ 6) *ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል፤ (መካኒሣ) 7) *ኮተቤ ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል /ሳጠራው/ (ቀድሞ ኮተቤ አሁን ሲምሲ) 8) *ደብረ ምሕረት ሚካኤል (ቀድሞ ወህኒ ቤት ሚካኤል) 9) *መካነ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል 10) *ገነተ አምባ ቅዱስ ሚካኤል 11) *ደብረ ኢዮር ቅዱስ ሚካኤል 12) *ካራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤልና 24ቱ ካህናተ ሰማይ 13) *ሐያት ጨፌ ኢያሪኮ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን (በ1980ዓ.ም ጽላቱ ከነ ድርሳናቱ ተቀብሮ የተገኘበት) 14) *መንበረ ክብር ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም /ኋላ ወቅድስት አርሴማ በሚል እየተጠራ የሚገኝ/፤ (በቀጨኔ በአዲሱ ገበያና በእንጦጦ መሃል ጉብታ ላይ የሚገኝ) እንዲሁም በድርብነት 15) *እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት 16) *መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ (ስድስትኪሎ) 17) *ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ (መስቀል አደባባይ) 18) *ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ቤ.ክ (ኋላ ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል በሚል እየተጠራ የሚገኘው)፤ (ኢምግሬሽን አጠገብ) 19) *ደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ (ኋላ ወመካነ ጎልጎታ ቅድስት ድንግል ማርያም በሚል እየተጠራ የሚገኝ)

#አንኳን_አደረሳቹህ ኅዳር ፲፪፤ #ቅዱስ_ሚካኤል በእልፍ አእላፍ መላእክት ላይ የተሾመበትና እስራኤልን የመራበት ክብረ በዓል ነው፡፡ #በዓለ_ሢመቱ_፥#ወበዓለ_መራኄ_ፍኖቱ_ለቅዱስ_ሚካኤል_ሊቀ_መላእክት_፨ ፨፨፨ #Share ያድርጉ ኅዳር ፲፪ ለሰው ወገን የሚያዝንና የሚራራ፥ በእግዚአብሔር የጌትነት ዙፋን ፊት ሁልጊዜ ለምስጋና የሚቆም፥ ለፍጥረት ሁሉ የሚማልድ፥ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በዓለ ሢመቱና እስራኤላውያንን በባሕረ ኤርትራ ያሸገረበት በዓል ነው፡፡ (እንኳን አደረሳችሁ) ፠ #፩ በዓለ ሢመቱ፤ ሚካኤል ማለት ማን እንደ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡ ከሌሎች መላእክት ጋር በእለተ እሑድ ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ የተፈጠረ ሲሆን፤ እርሱም መጀመሪያ ከ100ው ነገደ መላእክት የ10ሩ ነገደ መላእክት (የኃይላት) አለቃቸው ነበር፤ በተጨማሪም ከሳጥናኤል ውድቀት በኋላ የኃይላት አለቅነቱን እንደያዘ የአጋእዝትን ነገድም (ሳጥናኤል/ሰማልያል/) ይመራቸው የነበሩትን 10 ነገዶችም በአለቅነት ደርቦ አለቃ ኾኗል፤ እንዲሁም በዛሬው ዕለት ለ100ውም(99ኙም) ነገደ መላእክት (ለእልፍ አእላፋት መላእክት) አለቃቸውም ቅዱስ ሚካኤል ኾኖ የተሾመበት ዕለት ነው፡፡ ልዑል ውእቱ ልዑለ መንበር ያሰኘውም ይኸው ነው፡፡ ቅ/ሚካኤል ለሰው ልጆች ምሕረትን ከኅዳር 12 (ከበዓለ ሢመቱ) ጀምሮ እስከ ኅዳር 13 (የአእላፍ መላእክት) በዓል ድረስ ከአምላኩ ለፍጥረታት ሁሉ ምሕረትን የሚለምንበት ዕለታት ናቸው፡፡ ፨፨፨ ፠#፪ እስራኤልን ከግብጽ ባርነት እየመራቸው ማውጣቱን የሚዘከርበት በዓል ነው፡፡ ይህም የሆነው ያዕቆብ በረሃብ 70 ኹኖ ወደ ግብፅ ከወረደ በኋላ ከ215 ዓመታት (አብርሃም ወደ ግብፅ በተሰደደ ከ430 ዓመታት) በኋላ፤ የዮሴፍን ዝና ያልሰማ፥ ዮሴፍን የማያውቅ ፈርዖን በግብፅ ነገሠ፡፡ እስራኤል ከእኛ ይልቅ በዝተዋል ጠላቶቻችን ቢነሱብን ከጣለቶቻችን ጋር ተደርበው ያጠፉናል በማለት አገዛዝ አጸናባቸው፥ ፍርድ አጓደለባቸው፡፡ የእስራኤል ሴቶች ልጅ ሲወልዱ ወንድ ከሆነ እንዲገደል በማድረግ መከራ አጸናባቸው፡፡ ለ215 ዓመታት በግብፅ በባርነት ከቆዩ በኋላ ከዕብራውያን ወገን የሆነችው ራሔል ጭቃ እያቦካች ምጥ በያዛት ጊዜ ከሥራዋ እንዲያሳርፏት ጠየቀች፤ ግብጻውያን ግን የሕፃናቱ ደም ጡቡን ያጠነክራል ርገጭ አሏት፡፡ ከማሕፀኗ የወጡ ሁለት መንትያ ልጆቿን እያየች ከጭቃ ጋር ረገጠች፤ ራሔልም መሪር ልቅሶን አለቀሰች፤ ስለ ልጆቿም መጽናናትን እንቢ አለች፡፡ የእስራኤል ንጉሥ ሆይ የሆነብንን እይ ስትል ራሷን ይዛ ታለቅስ ጀመር ፥ እንባዋንም ወደ ሰማይ ንጉሥ ወደ እግዚአብሔር ረጨች፡፡ የራሔል እንባዋ የሕዝበ እስራኤልን ሁሉ ጩኸት ፥ እሮሮ ይዛ ቅድመ እግዚአብሔር ደረሰች፡፡ “. . . ራሔል ስለ ልጆቿ አለቀሰች የሉምና ስለ ልጆቿ መጽናናት እንቢ አለች” /ኤር 31፥5፤ ማቴ 2፥17/ እንዲል፡፡ ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር ሙሴን አስነሳና፤ በሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል መሪነት፤ 10 ተዓምራትን በምድረ ግብፅ በ11ኛ ተዓምር ደግሞ በኅዳር 12 (ፈርዖንን ከነሠራዊቱ በኤርትራ ባሕር አስጥሞ) ወደ ተስፋይቱ ምድረ መራቸው፡፡ ባሕረ ኤርትራን እስራኤላውያን እንደተሻገሩም የእስራኤል ልጆች የሙሴ የአሮን እኅት ማርያም ከበሮ እየመታች ‹‹ንሴብሖ ለእግዚአብሔር ስቡሐ ዘተሰብሐ ፤ እግዚአብሔር ተዋጊ ነው ስሙም እግዚአብሔር ነው እያሉ፡፡›› ጠላታቸውን የመታላቸውን ፥ እነሱንም በተአምራቱ ያሻገራቸውን ፥ ከጠላታቸው እጅ ያዳናቸውን እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ ከዚህ በኋላ መጋቤ ብሉይ ቅዱስ ሚካኤል እየመራቸው ፥ መና ከሰማይ እያወረደላቸው ፥ ውሃ ከጭንጫ እያፈለቀላቸው ፥ ቀኑን በደመና ፥ ሌቱን በብርሃን መርቷቸው አርባ ዘመን ተጕዘው የቃል ኪዳን አገራቸው ምድረ ርስት ከነዓንን (የዛሬዋ ኢየሩሳሌምን) ወርሰዋል፡፡ /ዘጸ. 15/ ከሙሴ በኋላ እስራኤልን የመራው ነቢዩ ኢያሱም እስራኤልን በሚመራበት ጊዜ ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል እስራኤልን ይረዳቸው ነበር፡፡ ከጠላቶቻቸው ጋር ሲዋጉም ሰልፉን ይመራ የነበረው ቅዱስ ሚካኤል ነበር፡፡ ለምሳሌ እስራኤላውያን ከኢያሪኮ አጠገብ በነበሩበት ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦ ኢያሱን አነጋግሮታል፡፡ ኢያሱ በኢያሪኮ አጠገብ ሳለ ቀና ብሎ ሲመለከት የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ የያዘ አንድ ሰው ከፊቱ ቆሞ አየ፤ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ “ከእኛ ወገን ነህ ወይስ ከጠላቶቻችን?” ሲል ጠየቀው፡፡ እርሱም “አይደለሁም ነገር ግን የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ በመሆኔ መጥቻለሁ” ብሎታል /ኢያሱ 5፥13-15/፡፡ ይህ የተመዘዘ ሰይፍ ይዞ ከኢያሱ ፊት ለፊት የቆመው መልአክ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል (እንዲሁም መልአኩ ቅዱስ ራጕኤል) ነው፡፡ ይህን ለአብነት አነሣን እጅ እስራኤል በሚበድሉበት ጊዜ ሁሉ ወደ እግዚአብሔር የሚማልድላቸው ይህ ታላቅ መልአክ መጋቤ ብሉይ ቅ/ሚካኤል ነበር፤ እግዚአብሔር አምላክ በእደ መልአኩ ይጠብቀን፤ ከበዓሉ ረድኤት ፥ በረከት ይክፈለን፤ አሜን፨ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ #Share ያድርጉ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ኀዳር_11 በዚህችም ቀን አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለቅድስት ማርያም እናቷ የሆነች የተመሰገነች ቅድስተ ሐና ዐረፋቷ ነው፡፡ #share ያድርጉ #ቅድስት_ሐና በኢየሩሳሌም ከሌዊ ነገድ ከካህኑ አሮን ትውልድ የሌዊ የሜልኪ ልጅ ለሆነው የማጣት ልጅ ናት፡፡ ____ #ማጣትም 3 ልጆች አሉት እነርሱም ፤ #የመጀመሪያይቱ ስሟ ማርያም ናት፤ አዋላጅ የነበረች ስተሆን ቅድስት ሰሎሜን ወልዳለች ፤ ሰሎሜም እመቤታችን መድኃኒታችን ከተወለደችው ጀምሮ በስደቷም ወራት ከአረጋዊ ዮሴፍ ጋር እመቤታችንን ያገለገለቻት ናት፡፡ #ሁለተኛይቱ ስሟ ሶፍያ ፤ ይህቺ ቅድስተ ለመጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እናት የሆነችውን ቅድስት ኤልሳቤጥን ወለደች፡፡ #ሦስተኛይቱም ስሟ ሐና ነው፤ ይህች ቅድስት ሐና ከይሁዳ ነገድ ለሆነ ጻድቅ ስሙም ኢያቄም ከሆነ ጋር ተጋብታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ወለደቻት፡፡ ሰሎሜና ቅድስት ኤልሳቤጥ የእመቤታችን እናት ለሆች ለቅድስት ሐና እኀትማማች ናቸው፡፡ _____ ቅድስት ሐና መካነ እያለች አምላክን ልጅ እንዲሰጣት እጅግ አብዝታ ትለምን ነበር፡፡ እግዚአብሄርም በእርሷ ለዓለም ሁሉ ድኀነት የተደረገባትን ይቺን የተባረከችን የከበረች ልጅን ሰጣት እርሷም አምላክን የወለደች እመቤታችን ድንግል ማርያም ናት፡፡ ቅድስት ሐና ከሴቶች ሁሉ የምትከብርና የምትበልጥ መሆኗን አምላክን ለወለደችልን ለቅድስት እናታችን ድንግል ማርያም እናት ሆና አይተናል፤ ከሴቶች ሁሉ የሚበልጥ ትሩፋትና ተጋድሎ ባይኖራት ይህ ጸጋ ባልተገባት ነበር፡፡ _____ ምልጃዋ አይለየን ፡፡ ሃገራችንን ቅድስት ኢትዮጵያን እና ቅድስት ቤተክርስቲያናችንን ትጠብቅልን አሜን! በቦታው ሄዳቹ በዓሉን ማክበር ለምትፈልጉ👇🏼 ፎቶዎቹ፤ በአ.አ. ና በሌሎች የሚገኙ የቅድስት ሐና አብያተ ክርስቲያናት ... ፠ ጽርሐ ንግሥት ቅድስት ሐና ቤ/ክ ፠ ኮተቤ መካነ ቀረዱሳን ኢያቄም ወሐና ቤ/ክ እንዲሁም፡ ፠ ደብረ ንግስት መንዝ ቅድስት ሐና:: ሌሎች በዓሉ የሚከብሩባቸውን ቦታዎች ይጠቁሙን ፨፨፨ https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት - Estadísticas y analítica del canal de Telegram @finotehiwott