es
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Ir al canal en Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

El canal Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 377 suscriptores, ocupando la posición 5 568 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 195 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 377 suscriptores.

Según los últimos datos del 04 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 23, y en las últimas 24 horas de -1, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 22.11%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 9.42% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 401 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 449 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 20.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 05 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 377
Suscriptores
-124 horas
-107 días
+2330 días
Archivo de publicaciones
እንኳን ለቅድስት ሐና በዓለ ዕረፍት አደረሳችሁ፡፡ ፎቶዎቹ፤ በአ.አ. የሚገኙ የቅድስት ሐና አብያተ ክርስቲያናት ፠ ጽርሐ ንግሥት ቅድስት ሐና ቤ/ክ ፠ ኮተቤ መካነ ቀረዱሳን ኢያቄም ወሐና ቤ/ክ እንዲሁም፡ ፠ ደብረ ንግስት መንዝ ቅድስት ሐና::

ኅዳር ፱፤ የሠለስቱ ምዕት (318ቱ ሊቃውንት) ክብረ በዓል ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያኑ ፎቶ፤ ሐመረ ኖኅ ሠለስቱ ምዕት ቤ.ክ፤ በሃገራችን በሠለስቱ ምዕት (በ318ቱ ሊቃውንት ስም) ብቸኛ የሆነውና በአሁኑ ሰዐት ከ4ቱ የመጻሕፍት ጕበኤያት በኢትዮጵያ ደረከጃ የመጻሕፍተ መነኰሳት ዋና ማስመስከሪያ የሆነ ነው፡፡ ፠ በሃገራችን በሠለስቱ ምዕት (በ318ቱ ሊቃውንት ስም) ብቸኛ የሆነውና ከ311 ዓመታት በፊት በአፄ ቴዎፍሎስ (ስመ መንግሥት አጽራር ሰገድ) ታንጾ የነበረ ሲኾን ንጉሡ ሲያንጹትም የሠለስቱ ምዕት የአእላፍ መላእክትና የነቢያት ቤተ ከርስቲያን አድርገው ነው፤ ድርቡሽ ጎንደርን ከ130 ዓመታት በፊት በወረረ ጊዜ ጠፍ ኹኖ ቆይቶ በ2007 ዓ.ም. ቤተ ክርስቲያኑ ድጋሚ ተሠርቶ፤ እነሆ ዘንድሮ ለ6ኛ ጊዜ ተከብሮ ውሏል፡፡ ፠ ይህ ቤተ ክርስቲያን ታላቅ ጕባኤ ቤትም ሲኖረው፤ ቀድሞ የ4ቱ ጕባኤያት ዋና ማስመስከሪያ ኹኖ ቆይቷል፤ ከአፄ ኀይለ ሥላሴ ዘመን ጀምሮ በኢትዮጵያ ደረጃ የመጻሕፍተ መነኰሳት ዋና ማስመስከሪያ ኹኖ ይገኛል፡፡ ፠ ፎቶ ላይ የምትመለከቱት የሠለስቱ ምዕት የመጻሕፍተ መነኰሳት ጕባኤ ቤት ከዋናውና ከጥንቱ የመጻሕፍተ መነኰሳት ጕባኤ ማሄጃ ብራና መጻሕፍት ጋር በእሳት አደጋ በተቃጠለበት ወቅት፤ በጎንደር የሚገኙ፤ በኢትዮጵያ ደረጃ ዋና የመጻሕፍተ ብሉያት ምስክር መምህር ዘዐቢየ እግዚዕ ኪዳነ ምሕረት (መምህር ኤልያስ)፤ በኢትዮጵያ ደረጃ ዋና የመጻሕፍተ ሐዲሳት ምስክር መምህር ዘግምጃ ቤት ማርያም (ሊቀ ማዕማራን ወመጋቤ ሐዲስ ወልደ ሰንበት ባይነሳኝ)፤ በኢትዮጵያ ደረጃ ዋና የመጻሕፍተ ሊቃውንት ምስክር መምህር ዘመንበረ መንግሥት መድኀኔ ዓለም (ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ) በአንድ ላይ ሁነው፤ ፠ በኢትዮጵያ ደረጃ ዋና የመጻሕፍተ መነኰሳት መምህር ዘሠለስቱ ምዕት የሆኑትን (መጋቤ ምሥጢር ወመጋቤ ምክር መምህር ተሾመ ታደሰን)ና ቀደ መዛሙርቶቻቸውን ሲያጽናኑ የሚያሳይ ነው፡፡ https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ኅዳር_፰ #ተዝካረ_አበው_(ኅዳር ፮-፰) share ያድርጉ ፠፠ በታላቁ ገዳም በዋልድባ/ዋሊ/ ብቻ ለሚደረገው የተዝካረ አበው (የዋልድባ አባቶች መታሰቢያ) አደረሳችሁ ፥ አደረሰን፨ በኢትዮጵያ በብቸ
#ኅዳር_፰ #ተዝካረ_አበው_(ኅዳር ፮-፰) share ያድርጉ ፠፠ በታላቁ ገዳም በዋልድባ/ዋሊ/ ብቻ ለሚደረገው የተዝካረ አበው (የዋልድባ አባቶች መታሰቢያ) አደረሳችሁ ፥ አደረሰን፨ በኢትዮጵያ በብቸኝነት ጌታችን በመሠረተው በዚህ ታላቅ ገዳም በዋልድባ ብቻ ከሚደረጉ ሥርዐቶች መካከል አንዱና ከቀድሞ አባቶች ሲወርድ ሲዋረድ ከመጣው መካከል፤ ከሰኔ ፳፩ ጀምሮ የወጣ ሳይገባ፥ የገባ ሳይወጣ (መርፌም ቢኾን ከሱባዔው በፊት ወደ ገዳሙ ካልገባ ሱባዔው እስኪያልቅ ጥቅም ላይ አይውልም)፨ የ158 ቀናት ሱባዔ ይደረጋል፤ ከ140 ቀናት በኋላ ከኅዳር ፮ - ፰ ተዝካረ አበው ይደረጋል፤ በሱባኤ የቆዩ አባቶች በማኅበር ደረጃ ይሰባሰባሉ፤ መልሰው ከኅዳር ፱ ጀምረው ደግሞ እስከ ኅዳር ፳፬ ወደ ሱባዔ ገብተው በ፳ወ፬ቱ ካህናተ ሰማይ ትልቁ ሱባዔ ያበቃል፤ ከኅዳር ፳፬ ጀምሮ ወደ ገዳም መግባት መውጣት ይፈቀዳል፨ በእነዚህ 158 የሱባኤ ቀናት (ከሰኔ ፳፩ - ኅዳር ፳፬ ድረስ)፤ ከቀባሪ በስተቀር ወደ ገዳሙ መግባትም አይቻልም፨ ሰላም ለዝክረ ስምክሙ ለዘይሴኒ እምወይን፤ ወእምነ ሐሊብ ጣዕሙ እንተ ይሠምዮ ልሣን፡፡ አበው ቀደምት ዘአብረንታንት ቅዱሳን፤ እለ ሕገክሙ ዘእንበለ ፍሬ ምኑን፤ ከመ ኢያብኡ እክለ በዛቲ መካን፡፡ ፠፠ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ከአርጋብ ጸዓድዒድ ቅዱሳን አበው አንድነት፥ ከአቡነ ሳሙኤል ልጅነት፥ ከገዳመ ዋሊ ረድኤት በረከት ይክፈለን፨ /ከዋልድባ ዋሊ ገጽ የተወሰደ/ https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

እንኳን ለበዓለ #አርባዕቱ እንስሳ ‹‹ኪሩቤል›› በሰላም አደረሳቹህ:: ኅዳር ፰፤ #አርባዕቱ_እንስሳ_(ኪሩቤል) share ያድርጉ ፨ ኪሩቤል ቃሉ ከአካድ/ጥንት ባቢሎናውያን ቋንቋ / የተወረሰ ሲሆን ትርጉሙም አማልጅ፣ኃያል፣ታላቅ ማለት ነው፡፡ #ኪሩቤል የብዙ ቁጥር ሲሆን በነጠላ #ኪሩብ ይባላል፡፡ ፨ መላእክት ሆነው ሳለ ‹‹አርባዕቱ እንስሳ›› የተባሉበት ምክንያት ለቅዱሳን ነቢያትና ሐዋርያት በእንስሳት አምሳል በመገለጻቸው ነው፡፡ ፨ ከመቶው ነገድ መላእክት የአስሩ ነገድ መጠሪያ ስም ነው ፨ ከ3ቱ መላእክተ ሰማያት በመጀመሪያይቱ በኢዮር ላይ ከአጋዝት በታች በ2ኛይቱ ከተማ የሰፈሩ ናቸው፡፡ ፨ አለቃቸው #ኪሩብ ሲባል (በጥንት እለት ሳጥናኤል ቦኃላ ቅዱስ ሚካኤል የተሾመበት) ፤በታች ነው፡፡ ፨ ከወገባቸው በላይ አራት አራት ከወገባቸው በታች አንድ አንድ እያደረገ ፈጥሯቸዋል ፨ ከእግር እስከ ራሳቸው በዓይን ተሸልመዋል - ዓይናቸውን እንደ ነብር ለምድ ዥንጉርጉር ነው፤አንድም እንደ መስታወት ስድ ነው ፤ ይኸውም ኪሩቤል ኃላፊያትንና መጻእያትን የማወቅ ክሂል ከልዑል አምላክ መቸራቸውን ያሳየናል ፤ ይህም የእግዚአብሄር ስራ ገደብ የማይጣልለት የቸርነት ሥራ ነው፡፡ መዝ 87፥ 35 ፨ ክንፋቸው እስከ ምድር እግራቸው እስከ በርባኖስ ይደርሳል ፡፡ ‹‹የክንፎቻቸው ብዛት ስድስት ነው፤ ክንፎቻቸውም ከላይ ተዘርግቶ ነበር የእያንዳንዱም ሁለት ሁለት ክንፋቸው የተያያዙ ነበሩ ፡፡ ሁለት ሁለቱም ገላቸውን ይከድኑ ነበር፡፡›› ሕዝ 1፥11 ፨ ገጻቸው ገጸ #ሰብእ እና ገጸ #አንበሳ ገጸ #ላሕም እና ገጸ #ንስር ነው በምሥራቅ በምዕራብና በሰሜን በደቡብ ጀርባቸው ወደ ውስጥ ፊታቸውን ወደ ውጭ አድርጎ አቁሟቸዋል ምን ጊዜም ገጽ ለገጽ አይተያዩም ፡ አገልግሎታቸውም የአጋዕዝተ ዓለም ሥላሴን መንበር መሸከም ነው፡፡ የካህናት የቀሳውስት አምሳል ናቸው 4ቱ እንስሳ የ4ቱ ወንጌላዉያን ምስሌ ናቸው ቅዱስ #ማቴዎስ በገጸ #ሰብእ ይመሰላል ቅዱስ #ማርቆስ በገጸ #አንበሳ ይመሳል ቅዱስ #ሉቃስ በገጸ #ላሕም ይመሰላል ቅዱስ #ዮሐንስ በገጽ #ንስር ይመሰላል 4ቱ እንሰሳ ለተወከሉበት መልክእ ቅድም እግዚአብሄር ጸሎት ያደርጋሉ #የሰው መልክ ያለው ኪሩብ #ለሰው ልጅ፣ #የአንበሳ መልክ ያለው ኪሩብ #ለአራዊት፣ #የላሕም መልክ ያለው ኪሩብ #ለቤት እንስሳት፣ #የንስር መልክ ያለው ኪሩብ ደግሞ #ለአእዋፍ ሁሉ እየጸለየ ሲጠብቃቸው ይኖራል፡፡ ምልጃቸው አይለየን ፡፡ https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ኅዳር ፯ #የሊቀ ስማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅዳሴ ቤቱ ነው)፨ መክብበ ሰማዕት ፥ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ ኰከበ ልዳ፥ ፀሐየ ፋርስ፤ ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ የኢትዮጵያ ገበዝ፤ ከአውሎ ነፋስ ይልቅ ፈጥኖ የሚደርስ ፈጥኖ ደራሽ ሰማዕት፤ እንደ እናቱ (እኅቱ) ቅድስት ማርያም ርኁሩህ የኾነ፡፡ ኅዳር 7 ቅዳሴ ቤቱ (ለመጀመሪያ ጊዜ የተሠራው ቤ.ክ የተመረቀበትና ቅዳሴ የተከናወነበት ክብረ በዓል) ነው፡፡ ———- ፨ ኅዳር ፯፤ (የአቡነ ገብረ እንድያስ በዓለ ዕረፍትና ነው)፨ ፠ ዕፁብ ድንቅ የኾነ ተዓምራትን የሚሠሩት (#እንጨቱ_ጸበላቸው_ውስጥ_ሲገባ_መቊጠሪያ_የሚያደርጉት፤ #በፎቶ_የምታዩት)፤ ፠ በጠበላቸው ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተዓምራትን የሚያደርጉት ፠ ፻ ትውልድ የሚያስምሩት፤ ፠ በደንጊያ ሠረገላነት የሚጓጓዙት፤ ፠ ከ፯ቱ ቅዱሳን ዘጋሥጫ አንዱ የኾኑት፤ #አቡነ_ገብረ_እንድርያስ_በዓለ_ዕረፍታቸው_ነው፨ ቦታቸውን ክርስቲያን የኾነ ኹሉ ሊያየው የሚገባ የተዓምራት ቦታ ነው፤ ✤✣✤ #ጻድቁ_አቡነ_ገብረ_እንድርያስ_ዘወለቃ_ወዘደብረ_ቆዘት_፤ ✤አባታቸው ተንሥአ ክርስቶስ፥ እናታቸው አርሴማ ሲባሉ፥ የትውልድ ሀገራቸው ወሎ፥ ቦረና፥ ጋሥጫ ሲኾን፤ የቀድሞ ስማቸው ንፍታሊም ይባል ነበር። ✤ ለትምህርት ሲሄዱ መምህራቸው ብዙኃኑን የምታድን ጻድቅ ትሆናለህ ብለው ትንቢት የተናገሩላቸው ሲኾን፤ የመጻሕፍትን ትርጓሜ በደንብ ካስተማሯቸው በኋላ ንፍታሊም ይባል የነበረውን የቀድሞ ስማቸውን ለውጠው ገብረ እንድርያስ አሏቸው። ✤ ጻድቁ በአቡነ ከማ ገዳም ለረጅም ጊዜ በታላቅ ተጋድሎ አገልግለዋል፤ ብዙ አባቶች ሱባኤ በሚይዙበት በስኮሩ ሥላሴ ቤተክርስትያን ጸሎት ሲያደርጉ ቅዱስ ዑር(ራ)ኤል በወርቅ ጽዋ ማየ ሕይወት አጠጥቷቸዋል። ✤ ጻድቁ አባታችን ሙታንን በማስነሳትና ድውያንን በመፈወስ ብዙ ተአምራትን ሲያደርጉ ኖረዋል። ✤ ጻድቁ ዐርብ ፥ ዐርብ የጌታችንን ቅዱስ ሥጋውን ና ክቡር ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም ይመላለሱ የነበረው በአየር ላይ ድንጋዩን እንደ ሰረገላ ፥ ዋርካውን እንደ ጥላ እየተጠቀሙበት ነበር። ይህ ሰረገላ የሆነው ድንጋይ በገዳማቸው ዛሬ ድረስ ይገኛል። (ፎቶውን ይመልከቱ) ✤ ጻድቁ አባታችን እግዚአብሔር ኀጥአንን እንዲምርላቸው ርቀት ወንዝ ከተሰኘው ቦታ በአንገታቸው ላይ በጣም ትልቅ ድንጋይ እየተሽከሙ ይጸልዩ ነበር። በዚህም ይጸልዩበት በነበረው ወንዝ ውስጥ በተአምራት መቊጠርያ የሚሰራ ጸበል ፈለቀላቸው፤ ጠበላቸው ውስጥም እንጨት ሲነከርበት እንጨቱ በተአምራት መቊጠርያ ሆኖ ይወጣል፤ ይኸውም መቊጠሪያ ለብዙ ሕመሞች መድኀኒት ነው፡፡ (ፎቶውን ይመልከቱ) ✤ ✤ ✤ አቡነ ገብረ እንድርያስና ሊቀ ሰማዕቱ ስለ ሃገራችን በተቀበሉት ቃል ኪዳን ሰላምና ጤና ያውርዱልን፤ ጠላታችንን ከሃገራችን ያባርሩልን፨ #ግጥም_በእንተ_ቅዱሳን_ወገዳማት_ዘወለቃ_ ✤ እባካችሁ ዝም አትበሉን እናንት ገዳማት፤! ዕድሜ ጠገቦቹ የዘመን አዝማናት፡፡ እነ አባ ያዕቆብ ፥ እነ ደብረ ጽጌ፤ እነ ቦሎ ዋሻ ፥ እነ ደብረ ሐይጌ፤ እነ ፍልፍሌ ጸዓዳ ፥ እነ ጅቦ ዋሻ፤ እነ ደብረ ቆዘት ፥ እነ ጊዮርጊስ ዋሻ፡፡ ታሪካችሁን ንገሩን እንያዝ ማሰታወሻ፤ ድንገት ብትጠፉብን እንዲሆን ማልቀሻ፡፡ ደብረ ቆዘት ጠርተን ገብረክረስቶስ አልን፤ የገዛዛን ታሪክ ለላሊበላ ሰጠን፤ ደበረ ከረቤ ብለን አባ ያዕቆብ አልን፤ የወለቃን ጉዳይ ለዘካርያስ ሰጠን፡፡ እነ ደብረ ሐይጌ እነ ጅቦ ዋሻ፤ የያጌ ጌጦች የታሪክ መናገሻ፤ የጎለሌው ዋሻ የተባለከው ፍልፍሌ፤ የቦሎ ቤቴክርስቲያን የጉርባው ቀበሌ፤ የጊዮርጊስ ዋሻ ነአኵቶ ድድምቱ፤ እስኪ ተናገሩ የታሪክ እውነቱ፡፡ ማን እንበላችሁ የመጠርያ ስማችሁ፤ እነማን ነበራችሁ የታለ ገድላችሁ? ያሁኑ ስማችሁስ ማን ሰየመላችሁ? * (በደቡብ ወሎ ወግዲ ወረዳ ለሚገኙ ከዘመናት ብዛት በመፈራረስ እና በመጥፋት ያሉ ታሪካቸው በአግባቡ ያልታወቁ 13 ጥንታዊያን ፍልፍል አብያተ ክርስቲያናት፡፡ 2001 ዓ.ም) (ከቦታው ድረስ በመሄድ አባቶችን በመጠየቅ ለዘገበልን ወንድማችን አምላከ አቡነ ገብረ እንድርያስ በበረከት ይጎብኝልን) /ከዋልድባ ዋሊ ገጽ የተወሰደ/ https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

፠ በኢትዮጵያ ደረጃ ኅዳር 6 የሚከበርባቸው ቦታዎች፤ ገዳመ አባ ጽጌ ድንግል፤ ደቡብ ወሎ፤ ወግዲ፡፡ ደብረ ፀሐይ ጎንደር ቋስቋም ማርያም፤ ጎንደር ከተማ ከሆስፒታል አጠገብ፡፡ ፠ በአዲስ አበባ ታቦተ
+6
፠ በኢትዮጵያ ደረጃ ኅዳር 6 የሚከበርባቸው ቦታዎች፤ ገዳመ አባ ጽጌ ድንግል፤ ደቡብ ወሎ፤ ወግዲ፡፡ ደብረ ፀሐይ ጎንደር ቋስቋም ማርያም፤ ጎንደር ከተማ ከሆስፒታል አጠገብ፡፡ ፠ በአዲስ አበባ ታቦተ ሕጉ የሚነግሥባቸው ቦታዎች፤ ፠እንጦጦ መንበረ ንግሥት ቅድስት ቊስቋም ማርያም፡፡ (#365ት_ቀናት_ሙሉ_ዝክር_በማኅበረ_መድኀኔ_ዓለም_አዳራሽ_የሚዘከርባት_ቤ/ክ) ፠ደብረ ናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ ቤተ ክርስቲያን፡፡ (የቤ/ክርስቲያኑ ዐጸድ እጅጉን ልብን የሚገዛና የሚማርክ) ፠ቃሊቲ ቊስቋም ማርያም ቤ/ክ፡፡ … ሌላም ካለ ይንገሩን.. /የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡/

#ኅዳር_6፤ ደብረ ቊስቋም፤ #እመቤታችን_ከልጇ_ጋርስ_ደትን_የጀመረችበት_ዕለት_ነው፡፡ **ድንግል ማርያም ከልጇና ከአረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍ ጋርለ3 ዓመታት ከ6 ወራት (ወይም ለ42 ወራት) (1275 ቀናት) ከተሰደደች በኋላ #ግንቦት_24_ደግሞ_በዓተ_ግብጽ_ (ወደ ግብጽ ወደ ደብረ ቊስቊም ገብታ ያረፈችበት ቀን ነው፡፡ ዖፍኒ ረከበት ላቲ ቤተ፤ ወፍም ቤቷን ሰራች፡፡ መዝ. ፹፫፥፫ ንጉሥ ተወልዷል መባሉን የሰማው ሔሮድስ 144,000 ሕጻናትን ሲፈጅ በቅዱስ ገብርኤል ትዕዛዝ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አንድ አምላክ ልጇን አዝላ፤ በአንዲት አህያ ላይ ተቀምጣ፤ ጥቂት ስንቅ ቋጥራ፤ ከዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ስደት ወጣች፡፡ ከገሊላ ተነሥታ በጭንቅ፣ በመከራ፣ በረሃብና በጥም፣ በሐዘንና በድካም፣ በእንባ ተጕዛ በዚህች ቀን ምድረ ግብፅ ገብታ በሥደት እጅግ ብዙ መከራ ተቀብላለች:: † የአምላክ እናቱ እሳትን አዝላ በብርድ ተንገላታለች:: † ለእኛ የሕይወት እንጀራን ተሸክማ እርሷ ተራበች:: † የሕይወትን ውሃ ተሸክማ ተጠማች:: † የሕይወት ልብስን ተሸክማ ተራቆተች:: † የሕይወት ፍስሐን ተሸክማ አዘነች:: † እመ አምላክ ተራበች፣ ተጠማች፣ ታረዘች፣ ደከመች፣አዘነች፣ አለቀሰች፣ እግሯ ደማ፣ ተንገላታች:: ለሚገባው ይሕ ሁሉ የተደረገው ለእኛ ድኅነት ነው:: በእውነት ይህንን እያወቀ ለድንግል ማርያም ክብር የማይሰጥ ሰይጣን ብቻ ነው:: አራዊት: ዕፀዋትና ድንጋዮች እንኳን ለአመላክ እናት ክብር ይሰጣሉ:: አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍና ቅድስት ሰሎሜ ደግሞ የክብር ክብር ይገባቸዋል:: ከአምላክ እናት ከድንግል ማርያምና ከቸር ልጇ ጋር መከራ መቀበልን መርጠዋልና:: #መድኃኔ_ዓለም_ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ_ለምን_ተሰደደ? #ለምን_ስደቱን_ወደ_ግብፅና_ኢትዮዽያ_አደረገ? 1. ፠ትንቢቱን ይፈጽም ዘንድ:: በፈጣን ደመና ወደ ግብፅ እንደሚወርድ ተነግሯልና(ኢሳ 19፥1፣ ዕን. 3፥7) 2. ፠ምሳሌውን ለመፈጸም፤ የሥጋ አባቶቹ እነ አብርሃም፥ ያዕቆብ (እሥራኤል):፥ ኤርምያስ ወደዚያው ተሰደዋልና:: 3. ከግብፅ ጣዖት አምልኮን ያጠፋ ዘንድ:: (ኢሳ. 19፥1) 4. የግብፅና የኢትዮዽያ ገዳማትን ይቀድስ ዘንድ:: 5. ሰው መሆኑ በአማን (በእውነት) እንጂ ምትሐት እንዳልሆነ ለማጠየቅ:: (ሰው ባይሆን ኑሮ አይሰደድም ነበር:: ሔሮድስ ቢያገኘው ደግሞ ሊገድለው አይችልም:: ያለ ፈቃዱና ያለ ዕለተ ዐርብ ደሙ አይፈስምና:: 6. ስደትን ለሰማዕታት ባርኮ ለመስጠት:: እና 7. የአዳምን ስደት በስደቱ ለመካስ ነው:: እመ ብርሃን ድንግል ማርያም ለ3 ዓመታት ከ6 ወራት (ወይም ለ42 ወራት) (1275 ቀናት) በስደት የቆየችባቸው ቦታዎች አሉ:: ፠ በመጀመርያ ድንግል ማርያም ከርጕም ሔሮድስ ስትሸሽ መጀመሪያ የሔደችው ከገሊላ ወደ ሶርያ ደንበር (ደብረ ሊባኖስ) ነበር:: በዚያም የሸሸጋት ቅዱስ ጊጋር መስፍኑ በሔሮድስ ሲገደል ወደ ምድረ ግብጽ ወረደች፡፡ ፠ በግብጽም ለብዙ ጊዜ ከአንዱ ወደ ሌላው ስትሸሽ ቆየች:: ‹‹እንዘ ከመ በግዕት ግድፍት አመ ሳኮይኪ ውስተ ምድረ በዳ፡፡›› እንዲል:: (እሴብሕ ጸጋኪ) ፠ ቀጥላም በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ገብታ ደብረ ቢዘን ላይ (አሁን ኤርትራ ውስጥ ነው) ዐረፈች፤ ፠ ከደብረ ቢዘን ደብረ ሐዊ፣ በደብረ ዳሞ፣ አኵሱም፣ ደብር ዐባይ፣ ዋልድባ አድርጋ እየባረከች ቆይታለች፤ ፠ በዋልባም ቆይታቸው ልጇ ገዳሙን በኢትዮጵያ በብጨኝነት ራሱ የገደመውን ገዳም መሥርቶ እየባረከ ወደ ጣና ሄደዋል፡፡ ፠ በጣና ገዳማትም፤ በተለይ በጣና ቂርቆስ ለ100 ቀናት ቆይታ ቀጥታ በጐጃም ወደ ሸዋ ሔዳ ደብረ ሊባኖስን ቀድሳለች:: ፠ ቀጥላም እስከ ደብረ ወገግና ደብረ ሐዘሎ ደርሳለች፤ በእግሯ ያልደረሰችባቸውን የሀገራችን ክፍሎች በደመና ተጭና ዐይታ ባርካቸዋለች፡፡ ፠ በደብረ ኤረር ተራራ ላይም ከልጇ ኢትዮጵያን በዐሥራትነት ተቀብላለች፡፡ ሔሮድስ መሞቱን መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል የነገራትም እዚሁ ኢትደዮዽያ ውስጥ መሆኑን ትውፊት ያሳያል:: እመቤታችን የሄሮድስን ሞት ከሰማች በኋላ ቊስቋም ከሚባል ተራራ ላይ ሆና ደስታዋን አብረዋት መከራን ከተቀበሉት ከዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር አከበረች፡፡ ከሃገራችን ሰዎች (ከሰብአ ኦፌር) የተቀበለችውን ስንቅና ስጦታ በ5 ግመሎች ጭና ከቅዱሳኑ ዮሴፍና ሰሎሜ ጋር ኅዳር 6 ቀን ቊስቋም ውስጥ ገብተው ከድካም ዐርፈዋል፤ ሐሴትንም አድርገዋል:: #ግብጽ_ደብረ_ቊስቋም_፤ ከክርስቶስ ስደት 400 ዓመታት በኋላ በዚህች ቀን የግብጿ ደብረ ቊስቋም ታንጻ ተቀድሳለች፤ የቅዱሳን ማደሪያም ሆናለች፡፡ ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ፤ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በ390ዎቹ አካባቢ ድንግል እናቱን፣ ቅዱሳን ሐዋርያትን፣ አእላፍ መላእክትን፣ ጻድቃን ሰማዕታትን፣ አስከትሎ ወረደ፡፡ የወቅቱ የግብጽ ፓትርያርክ ቅዱስ ቴዎፍሎስና ሊቁ ቅዱስ ቄርሎስ ቤተ ክርስቲያኑን አንጸው፤ ሕዝቡን ሰብስበው ይጠብቁት ነበርና ወርዶ ቀድሶላቸው ታላቅ ደስታ ኾኗል:: ይህቺ ቀን ለእኛ ለክርስቲያኖች ሁሉ እጅግ የደስታ ቀን ነውና ሐሴትን እናድርግ፤ የሰማይና የምድር ጌታ ለእኛ ሲል ካደረገው ስደቱ ኅዳር 6 ተመልሷልና:: ስደቷን አስበን ካዘንን: መመለሷን አስበን ደስ ልንሰኝ ይገባልና:: ‹‹አብርሒ አብርሒ ናዝሬት ሃገሩ፤ ንጉሥኪ በጽሐ ዘምስለ ማርያም መጾሩ›› ልንልም ይገባል፡፡ ***ኅዳር 5 ለኅዳር 6 ከዋይዜማው ጀምሮ የሚባለውን ሙሉ ሥርዐተ ማኅሌትም እነሆ ብለናል፤ መልካም የማኅሌት ሌሊት ይሁንልን፡፡ /የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡/