es
Feedback
Finote Hiwot ዹቀጹኔ ደብሚ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብሚ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኀል ቀተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቀት

Finote Hiwot ዹቀጹኔ ደብሚ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብሚ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኀል ቀተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቀት

Ir al canal en Telegram

ዹቀጹኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቀት ነሐሮ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠሚተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot ዹቀጹኔ ደብሚ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብሚ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኀል ቀተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቀት

El canal Finote Hiwot ዹቀጹኔ ደብሚ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብሚ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኀል ቀተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቀት (@finotehiwott) en el segmento lingÌístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 366 suscriptores, ocupando la posición 5 631 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 191 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el МевіЎПЌП, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 366 suscriptores.

Según los últimos datos del 20 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -39, y en las últimas 24 horas de -5, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 22.39%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 7.98% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 441 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 226 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 22.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“ዹቀጹኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቀት ነሐሮ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠሚተ።”

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 21 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 366
Suscriptores
-524 horas
+297 días
-3930 días
Archivo de publicaciones
ፍቅሹ ድንግል በዹነ ዓሊ 1928 - 2016 ፣ዓ.ም ሥርዓተ ቀብራ቞ው በቀጹኔ መድኀኔ ዓለም ኹ5-6 ይፈጾማል ። ፍቅሹ ድንግል በዹነ ዓሊ ኚንቡሚ ዕድ በዹነ ዓሊ እና ኚወይዘሮ ሰላመ ድንግል ተክለጊዮ
ፍቅሹ ድንግል በዹነ ዓሊ 1928 - 2016  ፣ዓ.ም ሥርዓተ ቀብራ቞ው በቀጹኔ መድኀኔ ዓለም ኹ5-6 ይፈጾማል ። ፍቅሹ ድንግል በዹነ ዓሊ ኚንቡሚ ዕድ በዹነ ዓሊ እና ኚወይዘሮ ሰላመ ድንግል ተክለጊዮርጊስ በ 1928 ተወለዱ ። አቅማቾውም እስኚደኚመ ድሚስ ፥  ኚአባታ቞ው  ኚንቡሚ ዕድ ጋር በመሆን  በተለይ በዘመነ ጜጌ ላይ እንዲኁም  በዐቢይ ፆም  እሑድ ፥ መወድስ  በመቀኘት  ለሹጅም ጊዜ አገልግለዋል ። በልዩ ዹቅኔ አዋቂነታ቞ው  ይታወቁ ነበር ። ዹፍቅሹ ድንግልን ነፍስ ኚአብርሃም ኚይስሐቅ  ጋር ይደምርልን ።

#ሰማዕቱ_ቅዱስ_መርቆሬዎስ_በሥዕሉ_ላይ_አድሮ_ቅዱሳን_ዹሆኑ_ባስልዮስንና_ጎርጎርዮስን_በመርዳት_ኚሃዲውን_ንጉሥ_ዑልያኖስን_ዚገደለበት_ዕለት_ነው፡፡ #ራሱን_ዹሾጠው_ቅዱስ_ጎጥሮስ_ዕሚፍቱ_ነው፡፡ #ኚበሬ_ጋር_ተጠምደው_በማሚስ_ሰማዕትነትን_ዚተቀበሉት_አቡነ_ሕፃን_ሞዐ_ልደታ቞ው_ነው፡፡ **ዳግመኛም በዚህ ዕለትፀ #ስብስትያኖስ_ሰባስትያኖስ_ሰማዕት_ጥር_25 ፠ በሕመም፥ በጭንቅ፥ በመኚራ፥ በስቃይ፥ #በደዌ_ዳኛ፥ #በአልጋ_ቁራኛ_ላይ_ያላቜሁ_ሁሉ በእምነት ዚሰማዕቱ ዚቅዱስ ስብስትያኖስን ስሙን ጥሩት፥ ገድሉን አድምጡ ተሻሹ፥ እምነቱን ተቀቡ፥ ቀተ ክርስቲያኑን ተሳለሙ #ፈዋሜ_ሰማዕት_ነው፡፡ #ፈትለ_ሥላሎ በመባል በሚጠራው ቀ.ክ. (ኚአዲስ አበባ በሞጣ/በደብሚ ድማኅ/ በኩል ወደ ባሕር ዳር ሲሄዱ አዎት ኹተማ ኚመድሚስዎ በፊት ዠማ ወንዝ ለመድሚስ ሲቃሚቡ ያገኙታል)፡፡ ጥር 25 ዓመታዊ ክብሚ በዓሉ ይኚበራል፡፡ እንዲሁም በጥንታውያን ታላላቅ ገዳማትና አድባራት ዚብራና ገድሉ ስላለ አስነብቡ፥ ተሻሹፀ ፍጹም ፈውስን ታገኛላቜሁ፡፡ ፠ ሰባ(ስብ)ስትያኖስ ሰማዕትፀ በስዕሉ ላይ እንደምንመለኚተው በጜኑ ሕማምና ስቃይ ሰማዕትነትን ዹተቀበለ ነው፡፡ በተለይም በሕመምፀ በጭንቅ መኚራፀ በስቃይ ውስጥ ኟኖ ያለ ሰው አምላኹ ሰብስትያኖስ ብሎ ለጠራኝ እደርስለታለሁ ብሎ በማይታበል ቃሉ እግዚአብሔር አምላካቜን ቃል ኪዳን ዹሰጠው ሰማዕት ሲኟን ለጠሩትም ፈጥኖ ዚሚደርስ ሰማዕት ነው፡፡ ፠ ዚስብስትያኖስ አባቱ ዚሮሙ ንጉሥ ሲሆን ሃይማኖቱ ዹቀናና እግዚአብሔርንም ዚሚወድ ስለነበር ልጁን ዚቀተ ክርስቲያንን ትምህርት እያስተማሚ ፈሪሃ እግዚአብሔርን እያስተማሚ አሳደገው፡፡ አባቱም ኹሞተ በኋላ ኚሃዲያኑ ዲዮቅልጥያኖስና መክስምያኖስ ነገሡ፡፡ ቅዱስ ስብስትያኖስንም አገሹ ገዥ አድርገው ሟሙትና እንደ አባቱ እጅግ አድርገው አኚበሩት፡፡ ፠ ቅዱስ ስብስትያኖስ በጥበብና በማስተዋል ዹሚጓዝ ነው፡፡ በተጋድሎ ሕይወቱ ዹተመሰገነ ሆነ፡፡ እግዚአብሔርም በእጆቹ ዚተለያዩ ተአምራትን ገለጠ፡፡ ድውያንን ይፈውሳልፀ በጞሎቱም ዚዕውራንን ዐይኖቜ ያበራል፡፡ በእንዲህም ዓይነት በተጋደሎ ሲኖር ዲዮቅልጥያኖስ እግዚአብሔርን ክዶ በዓለም ላይ ያሉ ክርስቲያኖቜን እያሳሚደ አብያተ ክርስቲያናትንም ማቃጠል ጀመሚ፡፡ ይኾውም ኚሃዲ አገሹ ገዥ አድርጎ ሟሞትና በእጅጉ አክብሮት ዹነበሹውን ቅዱስ ስብስትያኖስን አሁን ለጣዖት እንዲሰግድ ግድ አለው፡፡ ፠ ቅዱስ ስብስትያኖስ ግን ዚኚሃዲውን ንጉሥ ትእዛዝ ቾል በማለት በፊቱ ቆሞ ዚጌታቜንን ዚመድኃኒታቜንን ዚኢዚሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰኚሚፀ ጣዖታቶቹንም ሚገመበት፡፡ ንጉሡም በዚህ ጊዜ በታላቅ ቁጣ ሆኖ ቅዱስ ስብስትያኖስን ብዙ አሠቃዚው፡፡ ኚግንድ ጋር አሥሮ በብዙ ፍላጻዎቜ(ቀስቶቜ) ሰውነቱን አስነደፈውፀ በዚህም ጊዜ እንደሞተ አስበው ትተውት ሄዱ፡፡ ምእመናንም ሥጋውን ለመውሰድ በሌሊት ቢመጡ በሕይወት አገኙትና ወስደው በደሎት መካኚል አስቀመጡት፡፡ ፠ ዲዮቅልጥያኖስም ዚቅዱስ ስብስትያኖስን በሕይወት መኖር ሲሰማ ድጋሚ አስመጣውና በብሚት ዘንጎቜ ሲያስደበድበው ዋለ፡፡ ለብዙ ቀናትም እንዲሁ በብሚት ዘንግ ሲያስደበድበው ቆዚ፡፡ ቅዱስ ስብስትያኖስም በጥር 25 ቀን ነፍሱ ኚሥጋው ተለዚቜና ዚሰማዕትነት ፍጻሜው ሆነ፡፡ ጌታቜንም መታሰቢያውን ለሚያደርግና ስሙን ለሚጠራ ዹቾነፈር ሕመም፥ ዹሕመም ስቃይና መኚራ እንዳይቀርበው ቃልኪዳን ሰጥቶታል፡፡ ቅዱስ ስብስትያኖስም ካሚፈ በኋላ ውሉዱስና ለምትባል ለአንዲት ቅድስት ሎት ተገለጠላትና ቅዱስ ሥጋው ያለበትን ነገራት፡፡ እርሷም ወደ ኚበሩ ቅዱሳን ጎጥሮስና ጳውሎስ መቃብር ወስዳ ቀበሚቜው፡፡ /በቀጹኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኀል ቀ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቀት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል ዹተዘጋጀ ::/    #share  .Telegram... https://t.me/medihanaelem      www.finotehiwotsundayschool.com .Facebook...  https://youtu.be/3o4wj7Qqcaw... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w http://tiktok.com/@finotehiwot #ቅዱሳን  #Saints  #ክብሚ_በዓላት #Feasts

#ስብስትያኖስ_ሰባስትያኖስ_ሰማዕት_ጥር_25 ፠ በሕመም፥ በጭንቅ፥ በመኚራ፥ በስቃይ፥ #በደዌ_ዳኛ፥ #በአልጋ_ቁራኛ_ላይ_ያላቜሁ_ሁሉ በእምነት ዚሰማዕቱ ዚቅዱስ ስብስትያኖስን ስሙን ጥሩት፥ ገድሉን አድምጡ ተሻሹ፥ እምነቱን ተቀቡ፥ ቀተ ክርስቲያኑን ተሳለሙ #ፈዋሜ_ሰማዕት_ነው፡፡ #ፈትለ_ሥላሎ በመባል በሚጠራው ቀ.ክ. (ኚአዲስ አበባ በሞጣ/በደብሚ ድማኅ/ በኩል ወደ ባሕር ዳር ሲሄዱ አዎት ኹተማ ኚመድሚስዎ በፊት ዠማ ወንዝ ለመድሚስ ሲቃሚቡ ያገኙታል)፡፡ ጥር 25 ዓመታዊ ክብሚ በዓሉ ይኚበራል፡፡ እንዲሁም በጥንታውያን ታላላቅ ገዳማትና አድባራት ዚብራና ገድሉ ስላለ አስነብቡ፥ ተሻሹፀ ፍጹም ፈውስን ታገኛላቜሁ፡፡ ፠ ሰባ(ስብ)ስትያኖስ ሰማዕትፀ በስዕሉ ላይ እንደምንመለኚተው በጜኑ ሕማምና ስቃይ ሰማዕትነትን ዹተቀበለ ነው፡፡ በተለይም በሕመምፀ በጭንቅ መኚራፀ በስቃይ ውስጥ ኟኖ ያለ ሰው አምላኹ ሰብስትያኖስ ብሎ ለጠራኝ እደርስለታለሁ ብሎ በማይታበል ቃሉ እግዚአብሔር አምላካቜን ቃል ኪዳን ዹሰጠው ሰማዕት ሲኟን ለጠሩትም ፈጥኖ ዚሚደርስ ሰማዕት ነው፡፡ ፠ ዚስብስትያኖስ አባቱ ዚሮሙ ንጉሥ ሲሆን ሃይማኖቱ ዹቀናና እግዚአብሔርንም ዚሚወድ ስለነበር ልጁን ዚቀተ ክርስቲያንን ትምህርት እያስተማሚ ፈሪሃ እግዚአብሔርን እያስተማሚ አሳደገው፡፡ አባቱም ኹሞተ በኋላ ኚሃዲያኑ ዲዮቅልጥያኖስና መክስምያኖስ ነገሡ፡፡ ቅዱስ ስብስትያኖስንም አገሹ ገዥ አድርገው ሟሙትና እንደ አባቱ እጅግ አድርገው አኚበሩት፡፡ ፠ ቅዱስ ስብስትያኖስ በጥበብና በማስተዋል ዹሚጓዝ ነው፡፡ በተጋድሎ ሕይወቱ ዹተመሰገነ ሆነ፡፡ እግዚአብሔርም በእጆቹ ዚተለያዩ ተአምራትን ገለጠ፡፡ ድውያንን ይፈውሳልፀ በጞሎቱም ዚዕውራንን ዐይኖቜ ያበራል፡፡ በእንዲህም ዓይነት በተጋደሎ ሲኖር ዲዮቅልጥያኖስ እግዚአብሔርን ክዶ በዓለም ላይ ያሉ ክርስቲያኖቜን እያሳሚደ አብያተ ክርስቲያናትንም ማቃጠል ጀመሚ፡፡ ይኾውም ኚሃዲ አገሹ ገዥ አድርጎ ሟሞትና በእጅጉ አክብሮት ዹነበሹውን ቅዱስ ስብስትያኖስን አሁን ለጣዖት እንዲሰግድ ግድ አለው፡፡ ፠ ቅዱስ ስብስትያኖስ ግን ዚኚሃዲውን ንጉሥ ትእዛዝ ቾል በማለት በፊቱ ቆሞ ዚጌታቜንን ዚመድኃኒታቜንን ዚኢዚሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰኚሚፀ ጣዖታቶቹንም ሚገመበት፡፡ ንጉሡም በዚህ ጊዜ በታላቅ ቁጣ ሆኖ ቅዱስ ስብስትያኖስን ብዙ አሠቃዚው፡፡ ኚግንድ ጋር አሥሮ በብዙ ፍላጻዎቜ(ቀስቶቜ) ሰውነቱን አስነደፈውፀ በዚህም ጊዜ እንደሞተ አስበው ትተውት ሄዱ፡፡ ምእመናንም ሥጋውን ለመውሰድ በሌሊት ቢመጡ በሕይወት አገኙትና ወስደው በደሎት መካኚል አስቀመጡት፡፡ ፠ ዲዮቅልጥያኖስም ዚቅዱስ ስብስትያኖስን በሕይወት መኖር ሲሰማ ድጋሚ አስመጣውና በብሚት ዘንጎቜ ሲያስደበድበው ዋለ፡፡ ለብዙ ቀናትም እንዲሁ በብሚት ዘንግ ሲያስደበድበው ቆዚ፡፡ ቅዱስ ስብስትያኖስም በጥር 25 ቀን ነፍሱ ኚሥጋው ተለዚቜና ዚሰማዕትነት ፍጻሜው ሆነ፡፡ ጌታቜንም መታሰቢያውን ለሚያደርግና ስሙን ለሚጠራ ዹቾነፈር ሕመም፥ ዹሕመም ስቃይና መኚራ እንዳይቀርበው ቃልኪዳን ሰጥቶታል፡፡ ቅዱስ ስብስትያኖስም ካሚፈ በኋላ ውሉዱስና ለምትባል ለአንዲት ቅድስት ሎት ተገለጠላትና ቅዱስ ሥጋው ያለበትን ነገራት፡፡ እርሷም ወደ ኚበሩ ቅዱሳን ጎጥሮስና ጳውሎስ መቃብር ወስዳ ቀበሚቜው፡፡ #ሰላም_ለዝክሹ_ስምኚ_ዘይትበደር እምብሩርፀ ወይጥዕም እም ሶኚር፡፡ ሰባስትያኖስ ንጹሕ ትሩፈ ምግባርፀ በዝክሹ ስምኚ ተማኅጞንኩ ኢትኅድገኒ ለገብርፀ አመ ትወፅዕ ነፍስዚ እምሥጋ በግብር፡፡ #ሰላም_ዕብል_ለፍጜምኚ_መአድምፀ በስመ ሥላሎ ኅቱም፡፡ ሰባስትያኖስ አቡዚ ሰላም ሰላም፡፡ በፍጜምኚ ተማኅጞንኩ ኢይቅርበኒ ሕማምፀ ማዕተበ ፍጜምኚ በፍጜምዚ ሢም፡፡ #ሰላም_ለመልክዕኹ_ዝብጠታተ ኀጺን ዘተወክፋፀ ወትዕግስታተ አዝለፋ፡፡ ሰባስትያኖስ ጻማዊ ሱታፌ ሕማሙ ለዘልፋፀ መልክዐ ገጜኚ ኀበ ተጜሕፋ፥ ለመለክዕዹ ጞሐፋፀ ውስተ ምዕራፍኚ ሚሲ ምዕራፋ፡፡ **ዳግመኛም በዚህ ዕለትፀ #ሰማዕቱ_ቅዱስ_መርቆሬዎስ_በሥዕሉ_ላይ_አድሮ_ቅዱሳን_ዹሆኑ_ባስልዮስንና_ጎርጎርዮስን_በመርዳት_ኚሃዲውን_ንጉሥ_ዑልያኖስን_ዚገደለበት_ዕለት_ነው፡፡ #ራሱን_ዹሾጠው_ቅዱስ_ጎጥሮስ_ዕሚፍቱ_ነው፡፡ #ኚበሬ_ጋር_ተጠምደው_በማሚስ_ሰማዕትነትን_ዚተቀበሉት_አቡነ_ሕፃን_ሞዐ_ልደታ቞ው_ነው፡፡ Facebook  https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube    https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem

እንኳን አደሚሳቹሁ #ጥር21_አስተርእዮ_ማርያም_ ( #በዓለ_ዕሚፍታ_ለማርያም_(ለሶልያና ) #እመቀታቜን_በ64_ዓመቷ_ጥር_21_በ49ዓም_ያሚፈቜበት_ዕለት_መታሰቢያ_ክብሚ_በዓል_ነው፡፡ #ተናገራ_ዕዝራ_ተናገራ_ዳዊት_ዘመራፀ #ዕዝራ_በመሰንቆ_ዳዊት_በበገና_እያጫወቷትፀ #ሳታውቀው_አለፈቜ_ያንን_መራራ_ሞት፡፡ ፠ ጌታቜን ለእናታቜን ለቅድስት ማርያም ብዙ ቃልኪዳንን ኚገባላት በኋላፀ ቅድስት ነፍሷን ኚክብርት ሥጋዋ ለይቶ በቃለ አቅርንት፥ በዝማሬ መላእክት አሳሚጋት፡፡ ደቀመዛሙርቱንም ኚያሉበት ደመና ጠቅሶ እመቀታቜሁን ቅበሩ አላ቞ው፡፡ በአጎበር አድርገው እናትና  አባቷ  ወደተቀበሩበት  ወደ ጌቮ  ሮማኒ  ሲወስዷት  አይሁድ  አይተውፀ  ልጇ ተነሳ፥ አሹገ  እያሉ ሲያውኩን ኖሩ አሁን ደግሞ እሷ ተነሳቜ፥ አሚገቜ እያለ ሉያውኩን አይደለምን? ንዑ ናዓውያ ሥጋሃ ለማርያም /ኑ ሥጋዋን እናቃጥልባ቞ው/ ብለው ተነሱፀ ለዚሁም ኚመካኚላ቞ውም ታውፊኒያ ዚተባለውን ዹጎበዝ አለቃ መሚጡፀ እርሱም ዹአልጋዋን ሞንኮር ሊያቃጥል ሲይዝ ዚታዘዘ መልአክ መጥቶ ሁለት እጁን በሰይፍ ቀጣው፡፡ በድያለሁ ማሪኝ ብሎ ቢማፀናት እራሷን ዘምበል አድርጋ ቅዱስ ጎጥሮስን እንደነበሚው  አድርግለት ብላ አዘዘቜውፀ እርሱም እጁን አድኖለታል፡፡ ኹዚህ  በኋላ ጌታቜን ኚመካኚላ቞ው ነጥቆ ኚገነት ኹዕፀ ሕይወት ስር አኑሯታል፡፡ 
.. ሐዋርያት ዚቀበሯት ግን ኹ6 ወር በኋላ በነሐሮ 14 ነው  ----›እርሱን እዚህ ያንብቡ ----›https://t.me/medihanaelem/6840ፀ ‹‹ሞት በጥር ነሐሮ መቃብር እንዲሉ፡፡››ሚፍታ ለሶልያና(ለማርያም) ወሹደ ወልድ ዲበ እምዲበ ልዕልና ወሚደ፡፡ #ሶልያና_ዚእመቀታቜን_ዚማርያም_ሌላ_ስሟ_ነው፡፡ *ዚእመቀታቜንን ዕሚፍት ሊቁ ቅዱስ  ያሬድም  ‹‹ሞትሰ  ለመዊት ይደሉ፥  ሞታ  ለማርያም ዚአጜብ ለኵሉ፡፡ /ሞት ለሚሞት ሰው ሁለ ዚተገባ ነው፥ ዚማርያም ሞት ግን ሁለን ያስደንቃል፡፡›› በማለት አደንቆ ጜፏል፡፡ *እንደዚደብራቜሁ ይትበሃል ትጠቀሙበት ዘንድ ዹላይ ቀት (ዹግምጃ ቀት ማርያም) አብነትና ዚታቜ ቀት(ዚበዓታ) አብነትን ሁለቱንም አዘጋጅተንላቜኋል፡፡ መልካም ክብሚ በዓል፡፡ **ክብሚ በዓሉ በሃገራቜንና በዓለማቜን ክፍሎቜ ባሉ ዚእመቀታቜን አብያተ ክርስቲያናት ዚሚኚብሩ ቢሆንም ግንፀ በልዩ ሁኔታ እንደ ጎንደር አዘዞ ሎዛ ማርያም ባሉት አብያተ ክርስቲያናት ግን እንደ ጥምቀት በዓልፀ ኹዋይዜማው ጀምሮ ወደ ጥምቀተ ተወርዶ በማደር ክብሚ በዓሉ በልዩ ሁኔታ መኚበሩን ልብ ይሏል:: /በቀጹኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኀል ቀ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቀት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል ዹተዘጋጀ ::/    #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot      www.finotehiwotsundayschool.com #ቅዱሳን  #Saints  #ክብሚ_በዓላት #Feasts   #Our_mother_Virgin_mary #እመቀታቜን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም https://youtu.be/3o4wj7Qqcaw...

Finote Hiwot ዹቀጹኔ ደብሚ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብሚ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኀል ቀተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቀት - Estadísticas y analítica del canal de Telegram @finotehiwott