es
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Ir al canal en Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

El canal Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 411 suscriptores, ocupando la posición 5 577 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 191 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 411 suscriptores.

Según los últimos datos del 11 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 64, y en las últimas 24 horas de 24, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 24.26%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 9.47% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 737 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 458 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 23.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 12 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 411
Suscriptores
+2424 horas
+237 días
+6430 días
Archivo de publicaciones
#ዐርብ_ግንቦት_23_2011 ዓ.ም.#131ኛ_ሳምንት_የዐርብ_ጕባኤ_ከ12-2ሰዓት፤ ውዳሴ ማርያም በዜማ ይደርሳል:: ትምህርት ይሰጣል::
#ዐርብ_ግንቦት_23_2011 ዓ.ም.#131ኛ_ሳምንት_የዐርብ_ጕባኤ_ከ12-2ሰዓት፤ ውዳሴ ማርያም በዜማ ይደርሳል:: ትምህርት ይሰጣል::

አርእይኒ ገጸ ዚአኪ ማርያም ምዕረ፤ ዘኢይሰምዖ ካልእ እንግርኪ ነገረ፡፡ #ማርያም_ሆይ_ለሌላ_የማልነግረው_( #_ሌላ_የማይሰማው)#ነገርን_እነግርሽ_ዘንድ_አንድ_ጊዜ_ፊትሽን_ግለጪልኝ_፡፡

እንኳን አደረሳችሁ፡፡ #ግንቦት_21_ደብረ_ምጥማቅ_ማርያም_የምናከብርበት_ምክንያቱና_ሥርዐተ_ማኅሌት_ዘግንቦት_21፡፡ ግብጻውያን ክርስቲያኖች ከግንቦት 21 እስከ 25 የእመቤታችንን በዓል (አጎበር ጥለው፥ ድንኳን ተክለው፥ ድባብ ዘርግተው ያከብራሉ፤ እመቤታችንም ከቅዱሳን ጋር በመገኘት ትባርካቸዋለች፡፡) እነዚህ 5ት ቀናትም ከእመቤታችን 33ቱ በዓላት 5ቱን ከተ.ቊ 25ኛ እስከ 29ኛ ያለውን ይይዛሉ፡፡ እነርሱም፤ ፠25ኛ. ግንቦት 21 ቀን በግብጽ ሃገር ደብረ ምጥማቅ በተባለ ቤተክርስቲያን ለተሰበሰቡት ምዕመናን በግልጽ የታየችበት ነው፡፡ ፠26ኛ. ግንቦት 22 ቀን በግብጽ ሃገር ደብረ ምጥማቅ በተባለ ቤተክርስቲያን ለተሰበሰቡት ምዕመናን በግልጽ የታየችበት ነው፡፡ ፠27ኛ. ግንቦት 23 ቀን ደብረ ምጥማቅ በተባለች ቦታ የታየችበት ነው፡፡ ፠28ኛ. ግንቦት 24 ተሰዳ ግብጽ የገባችበት ነው፤ /ኢሣ.1 9፥11፣ ማቴ.2፥13-15/ ፠29ኛ. ግንቦት 25 ልጇ መድኀኔዓለም ክርስቶስ የደረቁ በትሮችን ተክሎ ያለመለመበት በዓል ነው፡፡ እነዚህ ከላይ ያየናቸውን የደብረ ምጥማቅ በዓላት (ከግንቦት 21-25) በአፄ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተነሥቶ የነበረው የግብፁ ንጉሥ እንዳያከብሩ በመከልከሉ፤ ኢትዮጵያውያንም ይህንን በዓል ለማክበር ይሄዱ ነበርና አፄ ዘርዐ ያዕቆብ ለመጽናኛ እንዲሆን በሃገራችን የደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያምን መሠረተ፤ እመቤታችንም ብዙ ቃል ኪዳንን ሰጠችው፤ ይኸው ቃል ኪዳኗ ሳይታጠፍ በጻድቃኔ ማርያም ዛሬ ድረስ ስፍር ቊጥር የሌለው ብዙ ተዓምራትና የምሕረት ሥራ የሚፈጸምባት ቅዱስ ቦታ ኾና ትገኛለች፡፡ እስካሁን ባለን መረጃ በሃገራችንም ግንቦት 21 የደብረ ምጥማቅ ክብረ በዓል በዋነኛነት!!! (በዋነኛነት!!!) የሚከበርባቸው ቦታዎች የሚከተሉት ናቸው፤ *1ኛ) #ደብረ_ምጥማቅ_ጻድቃኔ_ማርያም_ገዳም፡፡ /ሰሜን ሸዋ/ *2ኛ) ሐመረ ብርሃን ደብረ ምጥማቅ ቤተ ክርስቲያን /ጎንደር ከተማ/ *3ኛ) ደብረ ምጥማቅ ሰዓሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም /አዲስ አበባ/ (ሥርዐተ ማኅሌቱን ላልደረሰው በ Facebook, Telegram, Email, Viber, Xender, Bluetooth በማድረስ ይተባበሩ፡፡) ኦ አበው ወእማት አኃው ወአኃት ኢትርስዑነ በጸሎተክሙ (በዘጸለይክዋ በዝንቱ ሥርዐተ ማኅሌት) ለትምህርተ ቤትነ ቀ.ደ.ሰ.መድኀኔዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት፡፡

አዲስ ቤተ ክርስቲያን ሲሰራ (ቅዳሴ ቤት ሲከበር) ወይም ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ታንጾ ሲመረቅ የሚባለውን #ሥርዐተ_ማኅሌት እነሆ አቅርበንላችኋል፡፡ (ቤተ ክርስቲያኑ የቅዱስ ገብርኤል ከሆነ የሚቆመው ማኅሌት ከሌሎቹ ሁሉ ስለሚለይ የማኅሌቱን ጽሑፍ ያለ ሐረግ አዘጋጅተነዋል፡፡) #ግንቦት_21_2011_ዓም_የሚመረቁ_አብያተ_ክርስቲያናትን_እንጠቁማችሁ #እናንተም_ጨምሩባቸው፤ #ደቡብ_ወሎ_ደሴ_ወረኢሉ_ካቤን_ሰኞ_ገበያ_ወይብላ_ማርያም (በ8 ወር ተሰርታ የተጠናቀቀች) /የቀ.ደ.ሰ መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ. ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት/

ኢትዮጵያን አይርሱ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የአምላክ ጳጳሱ፣ በሰማዩ መቅደስ ሰዓታት ሊያደርሱ፣ ከርክበ ካህናት አቋርጠው ተነሡ፤ በሞት ሠረገላ የሕይወት ፈረሱ፣ እንደ አባ ገሪማ ሔዱ ገሰገሱ። በስብሐተ ፍቁር በዘይነግሡ፣ አባ ኤልሳዕ አደራ ኢትዮጵያን አይርሱ፤ እኛም እንዳንጠፋ ዘወትር ያስታውሱ። ©ዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው

፠በሃገራችን ብቸኛ የኾነውንና በድርቡሽ ጠፍ ሁኖ ለ126ዓመታት የቆየውን የሠለስቱ ምዕት ቤ/ክን ያስከፈቱ፤ ፠ለ41 ዓመታት ከኤጲስ ቆጶስነት እስከ ቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊነት ያገለገሉ፤ ፠በኹለት ቅዱሳን ፓትርያርኮች ምርጫ በዕጩነት የቀረቡ፤ ፠በእግራቸውና በበቅሎ ገጠር ከመንደር እየዘዋወሩ ያስተማሩ ሕንፃ ቤ/ክን የባረኩ (ፎቶውን ይመልከቱ)፤ ፠ለበርካታ ሺህ ካህናትና ዲያቆናት የክህነት አባት የኾኑ፤ ፠ቤተ ክርስቲያን፣ ምዕመናንና ሊቃውንት ሲበደሉ ማንንም (መንግሥትም) ቢኾን የማይፈሩ፤ በዚህም እስከ እስር የተዳረጉ፡፡ ፠የፍቅርና የትሕትና አባት፤ የዋሁና ደጉ፤ የሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ ዐረፉ፡፡ ፠በጎንደር ክፍለ ሀገር፣ ደብረ ታቦር አውራጃ በመካነ ሰማዕት ቅዱስ ገላውዴዎስ ደብር፣ ከአባታቸው አቶ ፈንታ ወልድየ እና ከእናታቸው ወ/ሮ ወለተ ተክለ ሃይማኖት፣ ግንቦት 29 ቀን በ1927 ዓ.ም. ተወለዱ #የትምህርት_ሁኔታቸው_፤ *ዕድሜያቸው ለትምህርት እንደ ደረሰ፣ በተወለዱበት ደብር በመካነ ሰማዕት ቅዱስ ገላውዴዎስ የድጓ መምህር ከነበሩት መምህር ሙሉጌታ ኀይሉ የቃል ትምህርት እና ጾመ ድጓ ተምረዋል፡፡ *ከዚያም ወደ ሸዋ ክፍለ ሀገር መጥተው በደብረ ብርሃን አውራጃ በናስ ማርያም ከአለቃ ቤተ ማርያም ድጓ፣ በምግልዋሻ ገብርኤል ከአለቃ ኀይለ ጊዮርጊስ ቅኔ ተምረዋል፤ እንዲሁም በተለያዩ ቦታዎች ከሚገኙ ልዩ ልዩ መምህራን ዘንድ እየተዘዋወሩ አቋቋም እና ቅኔ ተምረዋል፡፡ ድጓውንና ዝማሬ መዋስዕቱን ጽፈው አመልክተው በመምህርነት ተመርቀዋል፡፡ *ቀጥሎም በደብር ቅዱስ ደብረ ጽጌ ማርያም ገዳም ከመምህር ገብረ ሕይወት ሐዲስ፥ ፍትሐ ነገሥት፣ ትርጓሜ ዳዊት፣ ኪዳን፣ ትምህርተ ኅቡአት፣ ባሕረ ሐሳብ፣ የውዳሴ ማርያምና የቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ ተምረዋል፡፡ እንዲሁም ከአለቃ መርዓዊ ዝማሬ መዋሥዕት፣ ከአለቃ አፈ ወርቅ ዜማን በማሻሻል፣ ከመሪጌታ ልዑል ቅዳሴ፣ ከመሪጌታ ቀለም ወርቅ ተምረዋል፡፡ በአጠቃላይ የቤተ ክርስቲያን ትምህርትን እንደ ንህብ የቀሰሙ፤ ቢዘምሩ ቢቀድሱ፣ ቢሰብኩ ቢናገሩ፣ ቢተቹ ቢፈርዱ የሚያምርባቸው፤ ሊቅነት ከደግነት የተባበረላቸው ሙሉ አባት ናቸው፡፡ #ክህነት_፤ *በ1945 ዓ.ም. ከብፁዕ አቡነ ሚካኤል ዲቁና፣ *በ1964 ዓ.ም. በደብረ ሊባኖስ ገዳም ምንኩስናን ተቀብለዋል፡፡ *በ1965 ዓ.ም. ከብፁዕ አቡነ ሚካኤል ቅስና፣ *በ1969 ዓ.ም. ከብፁዕ አቡነ ሰላማ ቁምስናን ተቀብለዋል፡፡ #አገልግሎት_፤ *በደብር ቅዱስ ደብረ ጽጌ ማርያም ገዳም፣ በትምህርት ላይ እንዳሉ፥ በቅዳሴ፣ በመዘምርነትና በልዩ ልዩ የገዳም ሥርዓቶች፣ ለዐሥራ አምስት ዓመታት ያኽል አገልግለዋል፡፡ *በጋሞጎፋ ክፍለ ሀገር በመምህርነት በማገልገል እንዳሉ ለኤጲስ ቆጶስነት ማዕርግ ተመረጡት፡፡ ጥር 8 ቀን 1971 ዓ.ም. በመንበረ ፓትርያርኩ የተካሔደው ምርጫ፣ ከ14ቱም ክፍለ ሀገር እና ከአዲስ አበባ፣ ከቀረቡት 21 ቆሞሳት 12ቱ በድምፅ ብልጫ ማለፋቸውንና በሰሜን አሜሪካ ኦርቶዶክሳውያን ምእመናን በከፍተኛ ድምፅ የተመረጡት አባ ላዕከ ማርያም ማንደፍሮ በኋላ ብፁዕ አቡነ ይሥሓቅ ተጨምረው በጠቅላላ 13 አባቶች ለሢመተ ጵጵስና ቀርበው በጥር 13 ቀን 1971 ዓ.ም. በሦስተኛው ፓትርያርክ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንብሮተ እድ ሥርዐተ ጵጵስና ተከናወኖላቸዋል፡፡ ይህም በአንድ ጊዜ 13 ጳጳሳት ሲሾሙ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕድ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከፍተኛውና የመጀመሪያው ነው፤” የእኒህ 13 ኤጲስ ቆጶሳት መመረጥም ለስብከተ ወንጌል መስፋፋት፣ ስለ ሰበካ ጉባኤ መጠናከር፣ ቤተ ክርስቲያን ለወጣቶች ማድረግ ስላለባት መልካም አቀባበልና ስለ ዓለም አብያተ ክርስቲያናት ግንኙነትና ስለሌላው የቤተ ክርስቲያን የአስተዳደር ይዘት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ #በጵጵስና_አገልግሎት፤ በቀድሞው ስማቸው መምህር ቆሞስ አባ ኅሩይ ፈንታ ይባሉ የነበሩ አቡነ ኤልሳዕ ጵጵስና ከተቀበሉ በኋላ ለ41 ዓመታት በሚከተሉት አህጉረ ስብከቶችና ኃላፊነቶች በትጋትና በንቃት፥ በብርታትና በታማኝነት፤ ገጠር ከተማ ሳይለዩ፤ በበቅሎና በአግራቸው አቀበት ዳገቱን እየወጡ እየወረዱ አገልግለዋል፡፡ ፠ ከ1971 እስከ 1976 ዓ.ም. የጅማ፣ ፠ ከ1976 እስከ 1978 ዓ.ም. የካፋ፣ ፠ ከ1978 እስከ 1981 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ ፠ ከ1981 እስከ 2001 ዓ.ም. የደቡብ ጎንደር፣ ፠ ከ2001 እስከ 2011 ዓ.ም. የሰሜን ጎንደር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመኾን፣ ቤተ ክርስቲያንን ለ41 ዓመታት በትጋት አገልግለዋል፡፡ ፠ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ዘመነ ክህነት፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የካህናት የበላይ ጠባቂ ኾነው ሠርተዋል፡፡ ፠የራብዓይ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ እና የስድስተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የፕትርክና ምርጫ በተከናወነበት ወቅት፣ በዕጩነት ከቀረቡት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትም አንዱና ግንባር ቀደሙ ናቸው፡፡ በተለይም ከ1986 ዓ.ም. አንሥቶ፣ በግፍ እስር ታፍነው የሚገኙትን ሊቁን እንደሥራቸው አግማሴን ለማስፈታት ቅዱስ ሲኖዶስንና መንግሥትን ሳይሰለቹ በመወትወትና በሀገረ ስብከታቸው የሚፈጸሙ ኢሰብአዊ ተግባራትን በመቃወማቸው ምክንያት፣ በኮማንድ ፖስት እስከ መታሰርና በተለያየ መልክ የሚገለጽ መገፋት የደረሰባቸው መኾኑ የሚታወስ ነው፡፡ በታኅሣሥ ወር 2006 ዓ.ም.፣ “አራቱ ኀያላን” የተሰኘውን መጽሐፉን በጎንደር ባስመረቀበት መርሐ ግብር ላይ፥ “ሙሐዘ ጥበባት” የሚለው ስመ ማዕርግ ለጸሐፊና የነገረ ቤተ ክርስቲያን ተመራማሪ ዲን. ዳንኤል ክብረት ሰጥተውታል፡፡ ገጠር ሳይመረጡ በትጋት፣ በደግነትና በሰላማዊነት አባታዊ ሓላፊነታቸውን ተወጥተዋል፡፡ (ፎቶው ይሄንኑ ይመሰክራል) የብፁዕ አቡነ ገሪማ ሐዘን ሳይረሳ ሌላ ደግ አባታችንን ግንቦት 17 ቀን 2011 ዓ.ም. ሠርክ ላይ በተወለዱ በ84 ዓመት ዕድሜያቸው አጣን፤ ሰኞ ግንቦት 19 በጎንደር መስቀል ዐደባባይ የስንብትና የሽኝት መርሐ ግብር ተደርጎ፤ ሥርዓተ ቀብራቸው፥ ማክሰኞ ግንቦት 20 በኑዛዜ ቃላቸው መሠረት በታላቁ ደብር በደራ ወረዳ አፈር ውኃ እናት በመካነ ሰማዕት ቅ/ገላውዴዎስ በ7፡00 ሰዐት እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ይፈጸማል፡፡ ከ40 ዓመት በኋላ ዛሬ፣ በቅዱስ ሲኖዶስ አባልነት ካሉን 70 ያኽል ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ውስጥ፣ በሹመት ቀዳሚዎቹ በ1971 ዓ.ም. የተቀቡቱ ሲኾኑ፣ ዓረፍተ ዘመን እየገታቸው እየተለዩን ናቸው፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስንና ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስን ጨምሮ በዐጸደ ሥጋ የቀሩን የዘመኑ ተሿሚ አባቶች ከሦስት አይበልጡም፡፡ ካረፉት አባቶች በረከት ይክፈለን፤ ያሉትንም በጤናና በዕድሜ፤ በብርታትና በኀያል ጠብቆ የአበው አምላክ መድኀኔ ዓለም ያቆይልን፡፡ የብፁዕነታቸው በረከት ይድረሰን፤ አሜን፡፡ (ፎቶዎቹ፤ ፠ በሰሜን ተራሮች ታስ ደጀን አጠገብ የታላቁን ገዳም የደብረ ሐዊ ቅዱስ ያሬድ ቤ.ክና የቅዱስ ያሬድ የዜማ ትምህርቶችን በአንድ ላይ ይዞ እንዲሠራ ለታሰበው የመሠረት ድንጋይ ለመጣል ሲጓዙ፤ ፠ በጵጵስና ቀደምት ተሽዋሚ በመሆናቸው ከአቡነ ናትናኤል ጋር በመሆን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስን ሲሾሙ፡፡ ፠ ሆስፒታል ተገኝተው ሕሙማንን ሲጠይቁ፤ ፠ በሃገር አቀፍ የሰበካ ጕባኤ ስብሰባ ላይ፡፡ ፠ በጎንደር ለሚገኙ ሙስሊም ወንድሞቻችን የምስከር ወረቅት ሲያበረክቱ፡፡)

እንኳን ለታላላቆቹ አባቶች ለአቡነ ዓቢየ እግዚእና ለአቡነ ዮሴፍ ዓመታዊ በዓል (ግንቦት 19) በሰላምና በጤና አደሳችሁ፡፡ /#በጻድቃን_ተዓምራት_ማድረግ_ለምትጠራጠሩ፤ #ጻድቃን_ከበዓለ_ዕረፍታቸው_በኋላ_ዛሬም_ከማማለድም_አልፈው_በቃልኪዳናቸው_ተዓምራት_እንደሚያደርጉ_ኑና_እዩ_ተመልከቱ፡፡ ተዓምራትን ማየት ለምትፈልጉ ኹሉ ሂዳችሁ እዩ!!!!!)፡፡ ክብረ በዓላቸው (የአቡነ ዓቢየ እግዚእ በተንቤን መረታ ደብረ መድኃኒት፣ በጎንደር ከተማ ጥንታዊ በኾነው በዓቢየ እግዚእ ኪዳነምሕረት፣ በመቀሌ እንዳ ገብርኤል /እንዳ አቡነ ዓቢየ እግዚእ/፣ በአዲስ አበባ ሞጆ አካባቢ ባለው ቤ.ክ በድምት ይከበራል፡፡) እንዲሁም (የአቡነ ዮሴፍ በላስታ ላሊበላ በቅርብ ርቀት በሚገኘውና ወደ ላለበላ የሚጓዝ ኹሉ ሊያየው በሚችል በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘውና በኢትዮጵያ በከፍታ ከራስ ደጀን ተራራ ቀጥሎ በሚገኘው የዋሻ ገዳማቸው ይከበራል)፡፡ ሁለቱም ቅዱሳን አስካሁን ጊዜ ድረስ የሚታይ ባለ አስደናቂ የቃልኪዳን ተዓምራት አላቸው፤ አቡነ ዮሴፍ ከላሊበላ በቅርብ ርቀት በሚገኝ ገዳማቸው ጭላዳ እህል ጠባቂ ሳያሻው እህል እንዳይበላ ገዝተውታል፤ አቡነ ዐቢየ እግዚእ ቃል ኪዳን በተሰጣቸው ቦታ (ለምሳሌ በጎንደር ከተማ) አሁንም ድረስ ጅብ እንስሳቶችን እንዳይበላ ገዝተዋል፡፡ #አቡነ_ዮሴፍ_ዘእንጂፋቱ (በወሎ ላስታ ሰውንና ዝንጀሮን በቃልኪዳን ያስተሳሰሩ #እስከዛሬ_ድረስ_ዝንጀሮ_እህል_እንዳይበላ_የገዘቱ፤ እመቤታችን ዕጣን እየሰጠቻቸው፤ ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር የሥላሴን መንበር ያጠኑ (እንደ አቡነ ተክለሃይማኖት፣ አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባና አቡነ ዘርዓ ቡሩክ) ናቸው፤ ገዳማቸው በላሊበላ በቅርበት አቡነ ዮሴፍ ተራራ ተብሎ በሚጠራ ተራራ ቦታ ላይ የዋሻ ቤ.ክ አላቸው፡፡ #አባ_ዓቢየ_እግዚእ_፤ አባ ዓቢየ እግዚእ የተወለዱት በ14ኛው መቶ ክ/ዘመን ትግራይ ተንቤን (መረታ) ውስጥ ነው:: የተባረኩ ወላጆቻቸው ያፍቅረነ እግዚእ እና ጽርሐ ቅድሳት ይባላሉ:: አጥምቀው 'ዓቢየ እግዚእ' ሲሉ ስም ያወጡላቸው የወቅቱ ዻዻስ ሰላማ መተርጕመ መጻሕፍት ናቸው:: ትርጉሙም "በጌታ ዘንድ ታላቅ ሰው" ማለት ነው:: ዓቢየ እግዚእ በሕጻንነታቸው ሌሊት ሌሊት ባሕር ውስጥ ሰጥመው ሲጸልዩ አድረው ቀን ቀን እየተማሩ ብሉይ ከሐዲስ ጠነቀቁ:: ገና በወጣትነታቸው ወደ ታላቁ መነኮስ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ደብረ በንኮል ሔደው መንኵሰዋል:: በገዳሙ በጾም በጸሎትና በስግደት ተወስነው ከኖሩ በኋላ ወደ ዋልድባ ሔደው የተሰወረች ቤተ ክርስቲያን አግኝተዋል:: በጊዜው በ40 ቀን አንዲት ቅጠል ብቻ ለቁመተ ሥጋ ይበሉ ነበር:: ከዚያም ወደ ሃገራቸው ተንቤን ተመልሰው ዛሬም ድረስ ድንቅ ሆኖ የሚታየውን ገዳም መሥርተው ብዙ መናንያንን አፍርተዋል:: ዓቢየ እግዚእ ገዳማዊና ጻድቅ ብቻ ሳይሆን ሐዋርያዊ አባትም ነበሩ:: ከትግራይ እስከ ደንቢያ ሃገረ ስብከታቸው ነው:: አንድ ጊዜ ደቀ መዛሙርትን አስከትለው ለስብከት ሲንቀሳቀሱ ተከዜ ወንዝ አካባቢ ደረሱ:: ቀኑ ነሐሴ 10 ነውና ተከዜ እስከ ገደፉ ሞልቶ ለ3 ቀናት ባለመጉደሉ ከ1,000 በላይ ሰዎች ሲያለቅሱ ደረሱ:: ጻድቁ ባካባቢው የነበሩት ኢ-አማንያን (አሕዛብ) ቢሆኑም ራርተዋልና "አምላከ ሙሴ" ብለው ጸልየው ወደ ጥልቁ ውስጥ ገቡ:: ቅዱስ ሚካኤል አብሯቸው ነበርና ተከዜ ግራና ቀኝ ተከፍሎ መሃሉ የብስ ሆነ:: ይሕን ድንቅ ያዩ ከ1,000 በላይ አሕዛብም አምነው በጻድቁ እጅ ተጠምቀዋል:: ይህም ዘወትር ነሐሴ 10 ቀን በቤተ ክርስቲያናቸው (ጐንደር) ይከበራል:: ከዚያም እያስተማሩ ጐንደር ደረሱ:: ያኔ ጐንደር በቀሃና አንገረብ ወንዞች የታጠረች አንዲት መንደር ነበረች:: ጻድቁ ቀን ቀን እየሰበኩ ማታ ዛሬ ቤተ ክርስቲያናቸው የታነጸበት ሥፍራ ላይ ሲጸልዩ ያድሩ ነበር:: በዚያ ዘመን ጐንደር ውስጥ ጅብ: እባብና መሰል አራዊት ገብተው ሕዝቡን ጨረሱት:: ይህንን የተመለከቱት አባ ዓቢየ እግዚእ ወደ እግዚአብሔር አለቀሱ:: በፍጹም ልባቸውም ስለ ሕዝቡ ለመኑ:: የለመኑትን የማይነሳ ጌታ ወደ ጻድቁ ቀርቦ "በስምሕ የተማጸኑ: በቃል ኪዳንህ ያመኑ: በምድር አራዊት አይሠለጥኑባቸውም:: በሰማይም እሳትን አያዩም:: ጐንደርንም አራዊት ገብተው ሰውን አይጐዱም::" ብሏቸው አርጉዋል:: ጻድቁም የወንጌል አገልግሎታቸውን ፈጽመው ወደ ገዳማቸው ተንቤን ተመልሰዋል:: አባ ዓቢየ እግዚእ በገዳማቸው ተንቤን ለብዙ ዘመናት በቅድስና ኑረው፥ 3 ሙታንን አስነስተው፥ ብዙ ድውያንን ፈውሰው፥ ብሔረ ብጹዓንን ጎብኝተው፥ የድኅነት ቃል ኪዳንም ተቀብለው፥ በ140 ዓመታቸው ግንቦት 19 ቀን አርፈዋል:: የጻድቁ ክብር ለሁሉ ነውና እባካችሁ እናስባቸው:: ** አምላካችን በወዳጆቹ ምልጃ ሃገራችንን ከክፉው ሁሉ ይሠውርልን:: ሥርዐተ ማኅሌቱን ላልደረሰው በ Facebook, Email, Viber, Xender, Bluetooth በማድረስ ይተባበሩ፡፡ ኦ አበው ወእማት አኃው ወአኃት ኢትርስዑነ በጸሎተክሙ (በዘጸለይክዋ በዝንቱ ሥርዐተ ማኅሌት) ለትምህርተ ቤትነ ቀ.ደ.ሰ.መድኀኔዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት፡፡ /ሥርዐተ ማኅሌቱን ሳንለጥፍ በማዘግየታችን ይቅርታ፡፡/

መልአከ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ሆይ ከዘመን መንሱት፤ ከዕለት እኪት አድነን፡፡ መልአኬን አታስቈጡት!!፤ በቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ላይ በቀረቡ የአብያተ ክርስቲያናት መቃጠልና …. በሰማን ጊዜ ይህን ጻፍን፡፡ (የዛሬው የደብራችን ውሎ ይህን ይመስላል)፡፡

ንዑ ንሑር ኀበ ደብረ ይባቤ፤ ንዑ ንሑር ኀበ ዉሉደ ያሬድ፡፡ ደብራችንን ጨምሮ በሃገር ውስጥና በውጭ ሲካሄዱ ለነበሩት በግንቦት ወር ለተካሄዱት የ‹‹ዝከረ ቅዱስ ያሬድ›› መርሐ ግብሮች ማጠቃለያ የሚሆነውን መርሐ ግብር እሑድ ግንቦት 18 በደብረ ይባቤ በዉሉደ ያሬድ ሰ/ት/ቤት ከጠዋቱ 3፡30 ጀምሮ በመገኘት በአንድነት እናክብር፡፡ እግረ መንገዳችንንም የወንድሞቻችንንና እኅቶቻችንን የዉሉደ ያሬድ ሰ/ት/ቤት 50ኛ ዓመት የምሥረታ የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል አብረን እናከብር፡፡ /ቦታው፤ ጎተራ አጎና ሲኒማ ጋር ነው፡፡/