es
Feedback
የጥበብ ማዕድ

የጥበብ ማዕድ

Ir al canal en Telegram

ዝም ብለህ ተቀላቀል!

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram የጥበብ ማዕድ

El canal የጥበብ ማዕድ (@yetbebmead_ab) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 974 suscriptores, ocupando la posición 5 411 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 116 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 974 suscriptores.

Según los últimos datos del 25 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 604, y en las últimas 24 horas de -23, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 2.64%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 2.10% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 419 visualizaciones. En el primer día suele acumular 334 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 10.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
ዝም ብለህ ተቀላቀል!

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 26 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 974
Suscriptores
-2324 horas
+1447 días
+60430 días
Archivo de publicaciones
የአክስቴን ቤት ከረጅም ጊዜ በኋላ ትናንትና ሄድኩኝ ። ቤታቸው ስገባ አላመኑኝም ። በተለይ አክስቴና ልጇ ( ቃልኪዳን ) እግሬ በራቸውን እንደረገጠ ነው መጥተው ጥምጥም ያሉብኝ ። ሰላም ከተባባልን በኋላ ቤቱ ሞቅ ሞቅ አለ ። በተለይ የአክስቴ ፊት ሎተሪ እንደወጣለት እድለኛ ተፍነክንካለች ። ልጇ ቃልኪዳን የ ስድስት ዓመት ህፃን ናት ። ማንም ሰው እነሱ ቤት እንደማይመጣ ያወኩት ደስታቸውን ካየሁ በኋላ ነው ። " እና አክስቴ ኑሮ እንዴት ነው " ? አልኩ ድምፄን ከፍ አድርጌ ( ማዕድ ቤት ናት ) " እግዚአብሔር ይመስገን " አለች " ቃልዬ ደሞ አድጋልሻለች " አልኩ እቅፌ ውስጥ ያለችውን ቃልን እያየሁ .. "አዎን !! ይመስገን እ..... ግን " ብላ ዝም አለች " ግን ምን ? አክስቴ ? " አልኩ ግርምት ይሁን ድንጋጤ በማላውቀው ስሜት ፊቴን ቅጭም አርጌ ። " አይይይ!! ብሩኬ ልጄ እኮ በዘመዶቿ ናፍቆት እየከሳች ነው ። አንተም ይሀው እዚ ቤት ከመጣህ ዛሬ ድፍን ሶስት አመቱ ። ልጄ ሰው ያስፈልጋታል አንተም ይህ ስሜት ይገባሃል ብየ ነበረ ግን አንተም ያው ነህ ። " አለችኝ ንግግሯ ምክር ይሁን ዘለፋ ባላውቅም ግን ልቤን ነው የነካችው ። የልጇን ፊት አየሁ ፤ እውነትም ሰው ናፍቋታል ። እኔ ሃሳቤ ደርሼ በቶሎ ለመመለስ ነበረ ። ግን የቃልዬን ደስታ እንዴት ላጨልመው ? አንድ ሰው ሎተሪ ደርሶት ከተደሰተ በኋላ ይቅርታ ተሳስተን ነው ባለ ዕድሉ ሌላ ሰው ነው ሲባል የሚሰማው ስሜት አለ አይደል ። የኔም በቶሎ መመለስ ለቃልዬ እንደሱ መስሎ ታየኝ ። " ቃልዬ ምን ልግዛልሽ " ? አልኳት አቅፌ ፀጉሯን እያሻሸሁ " ልትሄድ ነው እንዴ " ? አለች በሚጣፍጥ አንደበቷ " አረ !! አልሄድም ለምን እንደዚ አልሽ" ? አልኳት " የ ማሚ ጓደኛ መስከለም አዚ መጥታ ልትሄድ ሽትል ነው ብል ምትሸጠኝ " አለች " ልሂድ ወይስ እዚ ልቆይ" ? አልኳት " እኛ ጋ አብለህ ኑል የትም አትሂድ " ብላ ጥብቅ አርጋ አቀፈችኝ ። እሺ ለዚች ትንሺዬ ልጅ ምን ልበል ? ነገ እመጣለሁ ብዬ በውሸት ተስፋ ሆዷን ልሙላ ? ስራ ምሰራው ከሰኞ - ቅዳሜ ነው ያለኝ የእረፍት ቀን እሁድ ነው እሱም አብዛኛውን እሁድ ማሳልፈው በስብሰባ ነው ስለዚህ አይመቸኝም ብዬ ግልፁን ላውራ ? ከራሴ ጋ ሙግት ገጠምኩ ። በመጨረሻም አንድ ነገር ወሰንኩ !! እንደምንም ብዬ አሁድ እሁድ ለመምጣት ለራሴ ቃል ገባሁ ። ✍ Henok

መብራት የጠፋ ለት የቤተሰቦችህ ልብ በርቶ ታገኘዋለህ።

ደስታዋ ማደጓን ማሳየት ነበረ!      የተሻለ ያገኘች ቀን ፍጥነቷ ራሱ ልቧ ምን ያህል እንደፈካ ይገልጽ ነበር።      በዚህ የተነሳ ማጣትን ረገምኩት ሁሌ ፊቷ ላይ ደስታን ስላሳጣኝ!!!

እንድታወራቸው ፈቀዱልህ ማለት ያደረካቸውን ረሱልህ ማለት አይደለም!!! እንደውም መንቀሳቀስህን የሚጠብቅ ፈንጂ ላይ እንደቆምክ ቁጠረው!!!

በ እናት ሆድ ውስጥ ጥጋብ ነው ርሀብ የለም::በ እናት ሆድ ውስጥ ሙቀት ነው ብርድ የለም። ከሁሉም በላይ ግን በ እናት ሆድ ውስጥ ጣዕር የለም ። መስራትም የለም። በምቾት መንፈላሰስ እና በለስላሳ ውሀ ውስጥ መንሳፈፍ ነው። ይህ ሁሉ ድሎት በተወለድንበት ቅፅበት ይለወጣል። ወተንፈስ ግድ ይላል ርሐብን ለማስታገስ መጥባት እንጀምራለን። ይበርደናል ሙቀት ለማግኘት ከሌላው እንጠጋለን ለመኖር አለበለዚያ መኖር የለም መታፈን በርሀብ አለንጋ መቆላትና በብርድ ቆርፍዶ መሞት። የፍርሐታችን ሁሉ መነሻ ይሆናል በእናታችን ማህፀን የምናውቀው መኖር ብቻ ነው። መወለድ አለመኖርን አመልካች ነው ። 📖 አለመኖር !

" ሜሉዬ" አልኩኝ ( ፊቷን አንገቴ ውስጥ ቀብራ ጥብቅ ! አድርጋ አቅፋኛለኝ ) " እእእእእ " አለች ( በእንቅልፍ ሰመመን ውስጥ ሁና ) " ነገ በጠዋቱ ቁርስ እንድትሰሪልኝ እሺ " አልኳት " እእ
" ሜሉዬ" አልኩኝ ( ፊቷን አንገቴ ውስጥ ቀብራ ጥብቅ ! አድርጋ አቅፋኛለኝ ) " እእእእእ " አለች ( በእንቅልፍ ሰመመን ውስጥ ሁና ) " ነገ በጠዋቱ ቁርስ እንድትሰሪልኝ እሺ " አልኳት " እእእእእእእ " አለች እእእ ብለሻል አዎ ! አልሰማሁም እንዳትይ " ኡፍፍፍፍፍፍፍ !!! እሺሺሺ" አለች ተናዳ😡 እኔም ስልክ ማፍጠጤን ትቼ በሃሳብ ባቡር ተሳፈርኩ ። ለካ ብዙ ከማውራት " እእእእእእእ" ብሎ ማለፍ ይቻላል ። እንዴት ነው " እእእእእእእ " መልስ ሚሆነው ? እንዴት ነው በ " እእእእእእእ" መግባባት ሚቻለው ? እእእእእእእ ራሱ ምንኛ ነው ? እኔና ሜሉ ግን በ እእእእእእ ተግባባን ። እኔ ብዙ አወራለሁ እሷ እእእእእ ትላለች ። በአላዋቂነት ብዙ ከማውራት በአዋቂነት እእእእእእእ ማለት ብዙ ያግባባል ። ብዙ ከማወራ ብዙ ባስብ ይሻላል ። የበዛ ወሬ ውሸትን ይወልዳል ውሸት ደግሞ ውዱን የሰውን ልጅ ርካሽ ያደርጋል ። " እእእእእእእ" ✍ Henok

ቤተሰብ ይህ ሁሉ የቤተሰብ ቁጥር ይዘን ተመልካችም እያለ ስለምን የወደዱትን ፣ ያነበቡትን ሐሳብ አስተያየት ለምን አትሰጡበትም እንዲሁም ማበረታቻ ይሆን ዘንድ ለምን #like አያደርጉትም?! ካልወደዱትም እንደዛው…

. . አንቺ ጋር ስጣላ... መንግስትን ተሳደብ ፣ ተሳደብ ይለኛል ከሰደብኩት ደሞ ፣ አስሮ ይገርፈኛል ከገረፈኝ ደሞ... ለጊዜውም ቢሆን ፣ አንቺን ያስረሳኛል! ከረሳሁሽ ደሞ... አጣኋትኝ ብዬ  ፣ አላስብም ቅንጣት ተሳድቦ መገረፍ.... ሳይሻል አይቀርም፣ አፍቅሮ ከማጣት፡፡ (በላይ በቀለ ወያ)

አንዳንድ ሰው ሐሳብና ችግሩ ሸክም ሆኖበት እንኳን ለሰው ደስታ ይደክማል።

ውድቀት መነሻው ራስን ካለመግዛት ነው።

ጥበቡ ወርቅዬ say's
ካንቺ ባላገኝ የልጅ ፍሬ አልቀይርሽም በሠው እኔ ሚዛን ደፋቶአል ፍቅሬ አሂሂ ካንቺ ባላገኝ የልጅ ፍሬ አልቀይርሽም በሠው እኔ ሚዛን ደፋቶአል ፍቅሬ አሂሂ......🥹❤️‍🔥
 የምር ግን እንደዚህ አይነት ወንድ አለ?🥺 ቆይ አንችስ ፍቅረኛሽ መውለድ ባይችል አብረሽው ለመኖር ምን ያህል ዝግጁ ነሽ? ፍቅር ማለት እስከዚህ ድረስ ነው እድሜ ልክሽን የተመኘሽውን እናትነትሽን እንኳን ልትተይለት የምትችይው ትልቁ መስዋትነት የሚጠይቅ ነገር ነው ። ብዙ sacrifice ለመክፈል ዝግጁ ካልሆናቹ በቃ አትፈቃቀሩ መጨረሻው ቁስል ነው 🥺💔

ደስታዋ እኮ የልጇ ደስታና ስኬት ነው።        እናቶች በምድርም በሰማይም ክፉ አይንካቸው!

መብራት ሐይል ጊቢ ውስጥ ጀነሬተር አየሁ እንዴት ነው ነገሩ?🤔

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ዒድ ሙባረክ!

ከሌለህ የሚፈልጉህ ባንክ ቤት ብቻ ናቸው እሱንም አካውንት ከሌለህ እንድታወጣላቸው!        #ለፈገግታ

፡ "ማፍቀር ማለት በጨለማ ሰማይ ላይ ከፈሰሱት ኅልቆመሳፍርት ከዋክብት፤ አንዷን መርጦ እንደ ጨረቃ ማግዘፍ ነው፡፡" (ከዕለታት ግማሽ ቀን) ፡

የዘመኑ አስር ብሮች እንደ ሰዉ ሆድ የባሳቸው ናቸው።