es
Feedback
Gondar City Education Department

Gondar City Education Department

Ir al canal en Telegram

ይህ የጎንደር ከተማ አስ/ትምህርት መምሪያ የቴሌ ግራም ቻናል ነው። የፌስቡክ ገጻችንንም ይከተሉ፦ https://www.facebook.com/GondarEdu ወቅታዊና ጠቃሚ ትምህርት ነክ መረጃዎችን ያገኙበታል።

Mostrar más
3 612
Suscriptores
+424 horas
+247 días
+11130 días
Archivo de publicaciones
​🚀 የሳይንስ እና ፈጠራ አቅማችሁን ለዓለም የምታዩበት ወርቃማ ዕድል! 🔬💡 ​የጎንደር ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል በበጀት ዓመቱ በመንግስትና በግል ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ከ9ኛ - 12ኛ ክፍል
​🚀 የሳይንስ እና ፈጠራ አቅማችሁን ለዓለም የምታዩበት ወርቃማ ዕድል! 🔬💡 ​የጎንደር ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል በበጀት ዓመቱ በመንግስትና በግል ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ከ9ኛ - 12ኛ ክፍል ያሉ የፈጠራ አቅም ያላቸውን ተማሪዎች አወዳድሮ በሀገር አቀፍ የሳይንስ ፈጠራ ውድድር ላይ ለማሳተፍ የአካባቢያዊ የሳይንስ ፈጠራ (Local Science Fair) ውድድር አዘጋጅቷል። ​በመሆኑም በፈጠራ ሥራዎቻችሁ መወዳደር የምትፈልጉ ተማሪዎች እስከ መስከረም 15/2019 ዓ.ም ድረስ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። ​የውድድር ዘርፎች (Categories)፦ 1️⃣ የጤና፣ ግብርና እና አካባቢ ችግሮች መፍትሔ (Health Tech, Agriculture & Environmental Solutions) 2️⃣ የማምረቻና ኢንዱስትሪ (Manufacturing & Industrial Solution) 3️⃣ ዲጂታል ቴክኖሎጂ እና የሶፍትዌር ልማት (Digital Technology & Software Dev't) 4️⃣ ሮቦቲክስ እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች (Robotics & Emerging Technology) ​📝 የአመዘጋገብ እና የፈጠራ ሥራ ማስረከቢያ መንገድ፡ ተወዳዳሪዎች ሙሉ ስም፣ ዕድሜ፣ ጾታ፣ የክፍል ደረጃ፣ የመጡበት ትምህርት ቤት እና የፈጠራ ሥራችሁን ዝርዝር መግለጫ (Proposal) በመያዝ፦ ​📧 በኢሜይል፡ ceil@uog.edu.et በመላክ ወይም ​🏢 በአካል፡ በዩኒቨርሲቲው ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ማዕከል አስተባባሪ ቢሮ በመገኘት መመዝገብ ትችላላችሁ። ​📅 ማስታወሻ፦ ​የምዝገባ ማብቂያ ቀን፡ እስከ መስከረም 15/2019 ዓ.ም ​ውድድሩ የሚካሄድበት ቀን፡ ጥቅምት 11 - 12/2019 ዓ.ም ​📍 ዒላማ የተደረጉት፡ በጎንደር ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ ሁሉም ትምህርት ቤቶች የሚገኙ የ9ኛ - 12ኛ ክፍል ተማሪዎች።

እንኳን ደስ አለን! እንኳን ደስ አላችሁ! 🎉 የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ያስፈተኗቸው ተማሪዎች 100% ሙሉ በ
እንኳን ደስ አለን! እንኳን ደስ አላችሁ! 🎉 የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ያስፈተኗቸው ተማሪዎች 100% ሙሉ በሙሉ 50% እና ከዚያ በላይ አስመዝግበዋል 📈📚 በአማራ ክልል ይህንን ድንቅ ውጤት ካስመዘገቡ 8 ትምህርት ቤቶች መካከል 2ቱ በከተማችን የሚገኙ በመሆናቸው ታላቅ ኩራት ይሰማናል 👏🏫

🚨 ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች እና ወላጆች በሙሉ! ​"የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከዛሬ ምሽት 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ" — የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ​የ2018 ትምህር
🚨 ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች እና ወላጆች በሙሉ! ​"የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከዛሬ ምሽት 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ" — የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ​የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸው አማራጭ አድራሻዎች ይፋ ሆነዋል። ​ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ከታች በተቀመጡት ሊንኮች (Links) በመግባት ውጤታችሁን ማየት ትችላላችሁ። ​📌 የቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜን በተመለከተ፦ ቅሬታ ያለው ማንኛውም ተፈታኝ በአካል መምጣት ሳያስፈልገው ከነሐሴ 19 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በተዘጋጀው ማስፈንጠሪያ ቅሬታውን ማቅረብ እና ምላሹንም በዚያው መከታተል የሚችል መሆኑን አገልግሎቱ አሳውቋል። ​👇 ውጤት ለማየት እና ቅሬታ ማቅረቢያ ሊንኮች:- ውጤት ለማየት፡- - በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et - ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram - አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms ቅሬታ ለማቅረብ፦ https://result.eaes.et/complaint

🚨 ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች እና ወላጆች በሙሉ! ​"የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከዛሬ ምሽት 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ" — የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ​የ2018 ትምህር
🚨 ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች እና ወላጆች በሙሉ! ​"የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከዛሬ ምሽት 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ" — የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ​የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸው አማራጭ አድራሻዎች ይፋ ሆነዋል። ​ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ከታች በተቀመጡት ሊንኮች (Links) በመግባት ውጤታችሁን ማየት ትችላላችሁ። ​📌 የቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜን በተመለከተ፦ ቅሬታ ያለው ማንኛውም ተፈታኝ በአካል መምጣት ሳያስፈልገው ከነሐሴ 19 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በተዘጋጀው ማስፈንጠሪያ ቅሬታውን ማቅረብ እና ምላሹንም በዚያው መከታተል የሚችል መሆኑን አገልግሎቱ አሳውቋል። ​👇 ውጤት ለማየት እና ቅሬታ ማቅረቢያ ሊንኮች:- ውጤት ለማየት፡- - በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et - ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram - አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms ቅሬታ ለማቅረብ፦ https://result.eaes.et/complaint

በአማራ ክልል በ2019 የትምህርት ዘመን ከ7.6 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ለመመዝገብ ታቅዷል፡፡ - የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በአማራ ክልል በ2019 የትምህርት ዘመን ከቅድመ 1ኛ-2ኛ ደረጃ የትምህ
በአማራ ክልል በ2019 የትምህርት ዘመን ከ7.6 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ለመመዝገብ ታቅዷል፡፡ - የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በአማራ ክልል በ2019 የትምህርት ዘመን ከቅድመ 1ኛ-2ኛ ደረጃ የትምህርት እርከኖች ከ7.6 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎችን ለመመዝገብ መታቀዱን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል፡፡ በ2018 ዓ.ም መላውን ማኅበረሰብ በማሳተፍ ከ4.1 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመጡ ማድረግ መቻሉን የቢሮው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጌታቸው ቢያዝን ተናግረዋል፡፡ በክልሉ የባለፈው ዓመት የትምህርት ዘርፍ አፈጻጸምን ያብራሩት ኃላፊው፤ ለ2019 ትምህርት ዘመን የሦስት አዳሪ ትምህርት ቤቶች እና አራት ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ግንባታ በማጠናቀቅ ወደ ሥራ ለማስገባት እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ከነሐሴ 18 እስከ ጳጉሜን 05/2018 ዓ.ም በሁሉም ትምህርት ቤቶች የአዲስ እና የነባር ተማሪዎች ምዝገባ እንደሚካሔድጨመገለፁ ይታወቃል፡፡ ባለፈው ዓመት ከትምህርት ገበታ ውጪ የነበሩ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል፡፡

📢 ለ9ኛ ክፍል ተማሪዎች ልዩ ዕድል! 🎓✨ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ትምህርት ቢሮ በ2019 ዓ.ም. በክልሉ በሚገኙት፦ 🏫 ይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት – ደሴ 🏫 ክቡ
📢 ለ9ኛ ክፍል ተማሪዎች ልዩ ዕድል! 🎓✨ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ትምህርት ቢሮ በ2019 ዓ.ም. በክልሉ በሚገኙት፦ 🏫 ይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት – ደሴ 🏫 ክቡር ዶ/ር ሐዲስ ዓለማየሁ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት – ደብረ ማርቆስ 🏫 ደብረ ታቦር ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት 🏫 ሰቆጣ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም. በክልሉ በመንግሥትም ሆነ በግል ትምህርት ተቋማት ተምረው የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና የወሰዱ እና የተቀመጡትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። 📌 1. የመመዝገቢያ መስፈርቶች 1.1 የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና አማካይ ውጤት 👧 ለሴቶች፦ 80% እና ከዚያ በላይ 👦 ለወንዶች፦ 82% እና ከዚያ በላይ 1.2 የ7ኛ እና 8ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት አማካይ ውጤት 👧 ለሴቶች፦ 83% እና ከዚያ በላይ 👦 ለወንዶች፦ 85% እና ከዚያ በላይ 📅 2. የምዝገባ ጊዜ እና ሂደት 🗓 የምዝገባ ቀን፦ ከነሐሴ 06–15/2018 ዓ.ም. 📍 የምዝገባ ቦታ፦ በአማራ ክልል በሚገኙ ሁሉም የወረዳ/ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤቶች። ➡️ ከነሐሴ 16–20/2018 ዓ.ም. በዞን ትምህርት መምሪያዎች የመረጃ ማጣራትና ማደራጀት ሥራ ይከናወናል። ➡️ ከነሐሴ 21–22/2018 ዓ.ም. የተደራጀው መረጃ ለክልል ት/ቢሮ ይላካል። 📝 3. የመግቢያ ፈተና 📍 የፈተና ቦታ፦ በዞን ዋና ከተሞች 📅 የፈተና ቀን፦ ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም. ⚠️ ማስታወሻ፦ ተማሪዎች ለፈተና ሲመጡ የፋይዳ መታወቂያ ይዘው መቅረብ አለባቸው። 📊 4. የመጨረሻ ውጤት አሰላለፍ ከ100% 📝 የጽሑፍ ፈተና – 80% 🇬🇧 እንግሊዝኛ 40% ➗ ሒሳብ 40% 📚 የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና 15% 📖 የ7ኛ እና 8ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት 5%

በአማራ ክልል የ2018 ትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል። በክልሉ 194,374 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን፤ 165,342 (85.06%) ተማሪዎች 50%
በአማራ ክልል የ2018 ትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል። በክልሉ 194,374 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን፤ 165,342 (85.06%) ተማሪዎች 50% እና በላይ ውጤት በማስመዝገብ ማለፋቸውን የክልሉ ትምህርሮ አሳውቋል። ውጤት ለማየት 👇 https://amhara6.ministry.et/#/result አድራሻውን ከተጫኑ በኋላ የተማሪውን መለያ ቁጥር እና ስም በአማርኛ በማስገባት 'Check your result' የሚለውን በመጫን ውጤትዎን ማየት ይችላሉ፡፡ በቴሌግራም ቦት ለማየት 👇 @emacs_ministry_result_qmt_bot የቴሌግራም ቦት ላይ ከገቡ በኋላ Start የሚለውን ይጫኑ፣ ክፍልዎን ይምረጡ፣ ከዚያም ክልልዎን ይምረጡ፣ የምዝገባ መለያ ቁጥር እና የመጀመሪያ ስምን በማስገባት ውጤትዎን ማየት ይችላሉ። ቅሬታ ለማቅረብ 👇 https://amhara6.ministry.et/#/complaint VPN የምትጠቀሙ ከሆነ በቅድሚያ ማጥፋት ይኖርባችኋል፡፡ በክልሉ የ8ኛ ክፍል ውጤት ትናንት መለቀቁ ይታወቃል።

የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ። በአማራ ክልል የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል። ከሰኔ 3-5/2018 ዓ.ም የተሰጠውን የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ
የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ። በአማራ ክልል የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል። ከሰኔ 3-5/2018 ዓ.ም የተሰጠውን የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና 173,699 ተማሪዎች ውስደው ነበር። ፈተናውን ከወሰዱት ተማሪዎች መካከልም 135,003 (77.72%) ተማሪዎች 50% እና በላይ ውጤት አስመዝግበዋል። ተማሪዎችም ውጤታቸውን https://amhara.ministry.et/#/result የሚለውን አድራሻ በመፃፍ ፤ በሚመጣው ቅጽ ላይ  የተማሪ መለያ ቁጥር (Registration Number) እና ስም በአማርኛ በማስገባት ፤ ዉጤት ይመልከቱ (Check your result) የሚለውን ቁልፍ በመጫን ማየት ይችላሉ፡፡ በተጨማሪም @emacs_ministry_result_qmt_bot  ላይ መመልከት ይችላሉ። ተማሪዎች ማንኛውም ከውጤት ጋር የተያያዘ ቅሬታ ካላቸው https://amhara.ministry.et/#/complaint ላይ በመግባት ቅሬታቸው ማቅረብ እንደሚችሉ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል። 2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይደረጋል ተብሏል።

photo content
+9

photo content
+9

photo content
+9

photo content
+9

የ2018/19 ዓ.ም የጎንደር ከተማ ትምህርት መምሪያ የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ዝውውርና ምደባ መረጃ
+9
የ2018/19 ዓ.ም የጎንደር ከተማ ትምህርት መምሪያ የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ዝውውርና ምደባ መረጃ

የ2018/19 ዓ.ም የጎንደር ከተማ ትምህርት መምሪያ መምህራንና የትምህርት አመራሮች ዝውውርና ምደባ በፌስቡክ ፔጃችን ተያይዟል፤ ገጹን https://www.facebook.com/GondarEdu በመከተል (follow) ወቅታዊ መረጃዎችን ማግኘት ትችላላችሁ👨‍🏫📚📢

Mock Exam schedule
Mock Exam schedule

ሰላም የተከበራችሁ ሱፐርቫይዘሮችና ር/መምህራን ጥሩ ቅድመዝግጅት አድረጋችሁ በተለይ የማጠቃለያ ፈተናችሁን ቴብል ኦፍ ስፔሲፊኬሽን በመጠቀም ጥራት ያለው ፈተና በማዘጋጀትና ኩረጃን/መቀሳሰምን የሚያስወግድ አሰራር በመዘርጋት የመንፈቀ አመቱን ማጠቃለያ ፈተና እያካሄዳችሁ እንደሆነ እናምናለን፡፡ ከማጠቃለያ ፈተናችሁ በኋላ ትኩረት የምትሰጡት አንድ አብይ ጉዳይ በተለይ የታሪክ ወይም በተዛማጅ የትምህርት መስክ የተመረቁና ተሰጥኦ ያላቸው መምህራንን በማስተባበር አመታዊ የት/ቤታችሁን ታሪክ መጻፍ ይሆናል፡፡ ቀደም ባሉ ዓመታት የት/ቤት የታሪክ መዝገብ ተዘጋጅቶ በየዓመቱ ወይም በየጊዜው በት/ቤቱ የተከናወኑ አበይት ጉዳዮች አመቱን ሙሉ እየተጻፉ ይቀመጡ ነበር፡፡ መዝገቡም የት/ቤት የታሪክ መዝገብ ተብሎ ለትውልድ የሚተላለፍ መረጃ ይሰነድ፣ ለአጥኚዎች እንደ ዋና መረጃ ያገለግል ወዘተ ነበር፡፡ ዛሬ ሰኔ 15/2018 ዓም ከሰዓት በኋላ አንዳንድ ት/ቤቶችም እንደታደማችሁት በጎንደር ዩኒቨርስቲ የዩኒቨርስቲው፣ የማህበረሰብ እና የአዳሪ ሞዴል ት/ቤቱን አመሰራረት ወዘተ የያዘ ታሪካዊ መጽሐፍ በሶስት የዩኒቨርስቲው መምህራን ተጽፎ በተመረቀበት ወቅት የኛ ት/ቤቶች ቀደምት የት/ቤት የታሪክ መዝገብ ትዝ ስላለንና በምረቃ ስነስርአቱ የወሰድነው ተሞክሮ በመሆኑ እንዲሁም በቀጣይ በዲጂታል ቴክኖሎጂ መረጃው እየተሰነደ ለትውልድ እንዲተላለፍ ስለሚደረግ ታሪካችሁን ጻፉ- በቃል ያለ ይረሳል በጽሁፍ ያለ ይወረሳል ነው ብሂሉና የቀጣይ ትኩረት ጉዳያችን እናድርገው፡፡ በመዝገብ ወዘተ የጻፍነውን የት/ቤታችንን ታሪክ ለብዙዎች እንዲደርስ ቢያንስ በመጽሄት መልክ እናሳትመው እናሰራጨው፡፡ የት/ቤት መሻሻል አንዱ ጉዳይ ትምህርትን ማስተዋወቅ ስለሆነ የት/ቤታችሁን ታሪክ መጻፍ፣ ማሳተምና ማሰራጨት የተለየና አዲስ ተግባር አይደለም፡፡ ማን ይሆን ፋናወጊ ት/ቤት? ወይም ታሪኩን ጽፎ የያዘ ት/ቤት? ወይም እጻፈ ያለ ት/ቤተ? ተሞክሯችሁን በቀጣይ መድረክ እናቀርበዋለን፡፡ እናመሰግናለን፡፡

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የጊዜ ሰሌዳ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የፈተና የሚሰጥበት የጊዜ ሰሌዳን ይፋ አድርጓል። በኦንላይን/
+1
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የጊዜ ሰሌዳ   የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የፈተና የሚሰጥበት የጊዜ ሰሌዳን ይፋ አድርጓል።   በኦንላይን/Computer-Based Testing (CBT) የሚፈተኑ ተፈታኞ በስድስት ዙር ፈተናቸውን እንደሚወስዱ አገልግሎቱ ገልጿል፡፡   በዚህም ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ፈተና የሚሰጥ ሲሆን፤ ከአራተኛ እስከ ስድስተኛ ዙር የማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ፈተናቸውን ይወስዳሉ፡፡   ፈተናውን በወረቀት የሚፈተኑ ተፈታኞች የተፈጥሮ ሳይንስ በሦስተኛ ዙር ላይ የሚፈተኑ ሲሆን፤ የማኅበራዊ ሳይንስ በአራተኛ ዙር በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚፈተኑ መሆናቸውን አገልግሎቱ አሳውቋል።   (የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ ያደረገው ዝርዝር የፈተና የጊዜ ሰሌዳ/Schedule ከላይ ተያይዟል።)

🤖 የክረምት እረፍትዎን በቴክኖሎጂ ያሳምሩ! ለተማሪዎች በሙሉ የቀረበ ታላቅ የሥልጠና ጥሪ! 🚀 የዘንድሮውን የክረምት እረፍት በዕውቀትና በክህሎት እያደጉ ለማሳለፍ ዝግጁ ናችሁ? የኢትዮጵያ አርቲፊ
🤖 የክረምት እረፍትዎን በቴክኖሎጂ ያሳምሩ! ለተማሪዎች በሙሉ የቀረበ ታላቅ የሥልጠና ጥሪ! 🚀 የዘንድሮውን የክረምት እረፍት በዕውቀትና በክህሎት እያደጉ ለማሳለፍ ዝግጁ ናችሁ? የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ለሆናችሁ ተማሪዎች በሙሉ በዘመኑ ምርጥ የቴክኖሎጂ መስኮች ራሳችሁን የምታንጹበት ልዩ የክረምት ሥልጠና አዘጋጅቶላችኋል። 💡 የሥልጠናው ዋና ዋና መስኮች፦ 🤖 ፈንዳሜንታል ኦፍ ኤ.አይ (Fundamentals of AI) 💻 ፕሮግራሚንግ (Programming) 🧠 ማሽን ለርኒንግ (Machine Learning) ⚙️ ሮቦቲክስ እና አይ.ኦ.ቲ (Robotics & IOT) 📊 ዳታ ሳይንስ (Data Science) እና ሌሎችም የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ትምህርቶች! 📅 የዘመኑን ቴክኖሎጂ ለመጨበጥ አሁኑኑ ይመዝገቡ! ⏳ የምዝገባ ማብቂያ ቀን፦ እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ 🔗 የምዝገባ ሊንክ (Google Form)፦ https://forms.gle/uDGPmQsiZcWWeNuRA ዕድሉ እንዳያመልጥዎ! ለወንድም እህቶችዎ፣ ለልጆችዎ እና ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት (Share በማድረግ) የመረጃው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያድርጉ። ✨ #AI #Ethiopia #ArtificialIntelligence #SummerTraining #TechForStudents #Coding #Robotics #DataScience #EthiopianTech የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት

የአብክመ ትቢሮ የዝውውር መመሪያ 2018.pdf9.75 MB