es
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Ir al canal en Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Mostrar más
2 757
Suscriptores
+124 horas
+17 días
+4230 días
Archivo de publicaciones
የተልዕኮ ተማሪዎች የምርቃት መርሐግብር የፊታችን እሑድ ሰኔ 28/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:30 ጀምሮ በደብራችን የስብከተ ወንጌል አዳራሽ
የተልዕኮ ተማሪዎች የምርቃት መርሐግብር የፊታችን እሑድ ሰኔ 28/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:30 ጀምሮ በደብራችን የስብከተ ወንጌል አዳራሽ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! የሰሞኑ የአገልግሎት መረጃ ባሳለፍነው ቅዳሜ በነበረው የሥራ አመራር ስብሰባ ላይ የአመራሩን የአገልግሎት ማስተባበሪያ ክፍል ድልድል እና የሥራ አስፈጻሚን እጩዎችን ከሦስት ቀን የጸሎተ እጣን እና የጸሎተ ማርያም ልመና በኃላ በእጣ የመለየት ተግባራት ተከናውኗል። በዚህም መሠረት የሥራ አመራር አጠቃላይ የአገልግሎት ማስተባበሪያ ክፍሎች ድልድል እንደሚከተለው ሲሆን 1. መ/ር ኢ/ር ዳዊት አበበ፦ የሥራ አመራር ሰብሳቢ 2. አቶ ላቀው ይርጋ ፦ የሥራ አመራር ም/ሰብሳቢ 3. ወ/ሮ ዮርዳኖስ ገ/ሚካኤል ፦ የሥራ አመራር ጸኃፊ 4. ወጣት አበራ መላኩ ፦ የሥራ አስፈጻሚ ሰብሳቢ (ዋና ሥራ አስፈጻሚ) 5. ወጣት በረከት ፍቅሩ ፦ እቅድ፣ ጥናትና ምርምር ማስተባበሪያ 6. ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖአምላክ ፦ ትምህርትና እቅበተ እምነት ማስተባበሪያ 7. ዲ/ን አሌክሳንደር ወ/ገብርኤል፦ አባላትና ተቋም አደረጃጀት ማስተባበሪያ 8. ዲ/ን ዳንኤል ተክሌ፦ ሚዲያና ሕዝብ ግንኙነት ማስተባበሪያ 9. መ/ሰ ዲ/ን ወንድወሰን መኮንን ፦ መረጃና ወቅታዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ 10. ወጣት አብርሃም አስራት ፦ ሒሳብና ንብረት አስተዳደር ማስተባበሪያ 11. አቶ ሙሉጌታ ሰማን ፦ ምጣኔ ሀብትና ማኅበራዊ አገልግሎት ማስተባበሪያ 12. ወጣት ዮናታን ብርሃኔ ፦ ቴክኖሎጂ ትስስር ማስተባበሪያ በተጨማሪም የሥራ አስፈጻሚ የአገልግሎት ክፍል ድልድል 1. ወ/ሮ ቤተልሔም ገነነው ፦ ም/ዋና ሥራ አስፈጻሚና ጸሐፊ 2. አቶ ዮናስ ይርዳው፦ ዕቅድ ትግበራ እና ክትትል ክፍል 3. ዲ/ን አብርሃም ታደሰ ፦ ትምህርትና ሥልጠና ክፍል 4. ዲ/ን ኪሩቤል መንገሻ ፦ መርሐግብር እና ጉባኤያት ክፍል 5. አቶ አለሙ ጉደታ ፦ መረጃ እና የውስጥ ግንኙነት ክፍል 6. አቶ እንግዳወርቅ አረፋይኔ ፦ መዝሙርና በዓላት ክፍል 7. አቶ ሔኖክ ኃይሉ ፦ ኪነ ጥበብና ሥነ ጥበብ ክፍል 8. አቶ ፍቃዱ ኪሮስ ፦ የሰው ሀብት አስተዳደር ክፍል 9. አቶ ተሾመ እንዳለ ፦ ልማትና በጎ አድራጎት ክፍል 10. ወ/ሮ አቻምየለሽ ደምሴ ፦ በጀትና ንብረት አስተዳደር ክፍል መሆናቸውን እያሳወቅን። በቀጣይ ጊዜ ሥራ አመራሩና ሥራ አስፈጻሚው በየንዑስ ክፍላት የሚያገለግሉ አባላትን በጋራ ተወያይተን እንደምናሳውቅ ለመግለጽ እንወዳለን። የሥራ አመራር ጽ/ቤት እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር

እግዚአብሔር አምላካችን ለኢትዮጵያ ሐዲስ ሐዋርያ አድርጎ ለመረጣቸው ጻድቁ አባታችን ተክለ ሃይማኖት ወርሐዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት ረድኤት በረከት አይለየን!
እግዚአብሔር አምላካችን ለኢትዮጵያ ሐዲስ ሐዋርያ አድርጎ ለመረጣቸው ጻድቁ አባታችን ተክለ ሃይማኖት ወርሐዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት ረድኤት በረከት አይለየን!!

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ማስታወቂያ ለፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት አባላት በሙሉ! ሰንበት ትምህርት ቤታችን በተለያዩ ክፍላት ለአገልግሎት ስንጠቀምባቸው የነበሩት ሁሉም የባንክ አካውንቶች በጊዜያዊነት ስለተዘጉ በቀጣይ ለአገልግሎት የምንጠቀምበትን አካውንት እስከምንገልጽላችሁ ድረስ ምንም ዓይነት ገንዘብ ወደ አካውንት ቁጥራችን ገቢ እንዳትፈጽሙ ለማሳሰብ እንወዳለን። እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር

ሰኔ ሃያ ሦስት በዚህች ቀን በእስራኤል ሁሉ ላይ የነገሠ  በእግዚአብሔር የተመረጠ ንጉሠ እስራኤልጠቢበ ጠቢባን ወልደ ዳዊት የሰሎሞን የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ማስታወቂያ ለፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት አባላት በሙሉ! በተለያዩ ጊዜያት በአገልግሎት አማካኝነት በእጃችሁ ላይ የሚገኝን ማንኛውንም የሰንበት ት/ቤታችንን ንብረት እስከ ሰኔ 24/2018 ዓ.ም ለሚመለከተው የአገልግሎት ክፍል በመመለስ እንድትተባበሩን በአምላከ ቅዱስ ሚካኤል ስም እናሳስባለን። በአካባቢያችሁ መራቅ ምክንያት እስከ ረቡዕ ድረስ መመለስ የማትችሉ አባላት ካላችሁ፤ ንብረቱ በእጃችሁ ላይ መኖሩን ለንብረትና ሒሳብ አስተዳደር ክፍል እንድታሳውቁ በአክብሮት እንጠይቃለን። እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር

እመቤታችን ሰኔ ሃያ አንድ በዚች ዕለት የአዳምና የዘሩ ድኅነት የተደረገባት አምላክን የወለደች የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የታላቁ በዓል መታሰቢያና በዓለም ሁሉ የቤተ ክርስቲያን መታነፅ መታሰቢያ ነው። ከሁሉ አስቀድሞ ያቺ ቤተ ክርስቲያን በሐዋርያት ዘመን ብቻዋን ታነፀች። ይኸውም ጳውሎስና በርናባስ በአሕዛብ ውስጥ በሰበኩ ጊዜ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ከሰዎች ቤቶች በቀር ቅዱስ ቊርባንን የሚቀበሉበት ቤተ ክርስቲያንም አልነበራቸውም ነበር። ስለዚህም ወደ ጴጥሮስና ወደ ሐዋርያት ሁሉ ስለ ቤተ ክርስቲያን መታነፅ ጉዳይ እየለመኑ መልእክትን ላኩ። ሐዋርያትም እንዲህ ብለው መለሱላቸው ክብር ይግባውና ያለ ጌታችን ፈቃድ እኛ ምንም ምን አንሠራም። ነገር ግን የምንሠራውን እስኪያስረዳን ድረስ ወደ እግዚአብሔር እየጸለዩና እየማለዱ አንድ ሱባኤ ይጾሙ ዘንድ ወደ ሃይማኖት የተመለሱ አሕዛብን እዘዙአቸው እንዲህም አዘዙአቸው። በሱባዔውም ፍጻሜ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጸላቸው ሐዋርያትንም ሁሉ ከየአገሮች ሁሉ እስከ ፊልጵስዮስ በደመና ሰበሰባቸው ከእርሳቸውም ጋር ጳውሎስና በርናባስ ነበሩ ጌታችንም ባረካቸው እንዲህም ብሎ ነገራቸው "ይቺ ዕለት በእናቴ በማርያም ስም በአራቱ ማእዘነ ዓለም አብያተ ክርስቲያናት እንድታንፁ የፈቀድኩባት ናት።" ይህንንም ብሎ ከከተማዋ በስተ ምሥራቅ በኲል አወጣቸው የቤተ ክርስቲያኒቱንም ቦታና መሠረቷን ወሰነላቸው ከእርሳቸውም ጋራ የእግዚአብሔር ኃይል ነበረ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕንፃዋ እስከ ተፈፀመ ድረስ ደንጊያዎች በሐዋርያት እጆች ውስጥ ይለመልሙ ነበረ ጌታችንም ነዋየ ቅድሳቷን አልባሳትዋንና መሠዊያዋን አዘጋጀ። ከዚህ በኋላ ጌታችን እጁን በጴጥሮስ ራስ ላይ ጭኖ በአራቱ ማእዘነ ዓለም ውስጥ "አርሳይሮስ" ብሎ ሾመው ይህም "ሊቀ ጳጳሳት" ማለት ነው። ለሐዋርያት አለቃ ጴጥሮስ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ የጳጳሳት አለቃ ይሆን ዘንድ ይገባዋል ይገባዋል ይገባዋል እያሉ ሰማያውያን መላእክትና ምድራውያን ሰዎች ሦስት ጊዜ አሰምተው ተናገሩ። ከዚህም በኋላ ጌታችን ሐዋርያትን የቊርባኑን ቅዳሴ ሥርዓት ያከናውኑ ዘንድ ለሕዝቡም ሥጋውን ደሙን ያቀብሏቸው ዘንድ አዘዛቸው እንዲህም የሚል አለ ራሱ መድኃኒታችን ቀድሶ ሥጋውንና ደሙን ለሐዋርያት አቀበላቸው። እንዲህም አላቸው በዚች ቀን የእጃቸውን ሥራ እንዳይሠሩ ሕዝቡን ሁሉ አዘዙአቸው ይኸውም በሰኔ ወር ሃያ አንድ ቀን ነው። ከዚህም በኋላ መድኃኒታችን ከእርሳቸው ዘንድ በታላቅ ክብር ወደ ሰማያት ዐረገ። ከዚያችም ቀን ጀምሮ አባቶቻችን ሐዋርያት በዓለሙ ሁሉ ውስጥ አምላክን በወለደች በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም ቤተ ክርስቲያን የሚያሳንፁ ሆኑ። የእመቤታችን በረከት በሁላችንም ላይ ይደር አሜን።

ደብራችን ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ሕንጻ ቤተክርስቲያን ከተመሰረተ 84 ዓመት ሞላው። መላው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምዕመናንና አገልጋዮች በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ!! የፍኖተ ብርሃን
ደብራችን ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ሕንጻ ቤተክርስቲያን ከተመሰረተ 84 ዓመት ሞላው። መላው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምዕመናንና አገልጋዮች በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ!! የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት

ሕንጸተ ቤተክርስቲያን ሰኔ ሃያ በዚች ቀን በኬልቄዶን አውራጃ በቂሣርያ አገር የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ያለ ዕንጨት ያለ ጭቃና ውኃ በሦስት ደንጊያዎች በተወደደ ልጅዋ እጅ የታነፀችበት ነው። ይኽም በዓል ከእመቤታችን 33ቱ በዓላት አንዱ ነው። ‹‹ሕንጸተ ቤተ ክርስቲያን›› ይባላል። የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን የታነጸችው በሰኔ 20 ቀን ነው። ያነጸውም እራሱ ባለቤቱ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ነው፤ ቦታው ፊልጲስዩስ ነው፤ ቤተክርስቲያኗ የተሰየመችው ደግሞ በእመቤታችን ስም ነው። እመቤታችን ካረገች በ4ኛ ዓመት ጳውሎስና በርናባስ በፊሊጲስዩስ ገብተው አስተምረው ሕዝቡን አሳምነው ካጠመቁ በኋላ ‹‹እንግዲህ ወደ ቤተ ጣዖት አትሂዱ›› አሏቸው። አሕዛብ የነበሩትና አምነው የተጠመቁትም ‹‹የለመድነውን ከከለከላችሁን መካነ ጸሎት ስጡን›› አሏቸው። የከበሩ ሐዋርያትም ወደ ጴጥሮስና ዮሐንስ መልእክት ላኩባቸው። ጴጥሮስና ዮሐንስም ‹‹ያለ ጌታችን ፈቃድ አንዳች ልታደርጉ አይገባምና ጸልዩ እኛም እንጸልያለን›› ብለው መለሱላቸው። ሁሉም ሱባኤ ይዘው በጸሎት ተጉ። ጸሎትና ሱባኤያቸውን ከጨረሱ በኋላ ጌታችን በሞት ያረፉትን አስነሥቶ በሕይወት ያሉትንም ደቀመዛሙርቱን በደመና ጠቅሶ ፊልጵስዩስ ሰበሰባቸው። ጌታችን በኪሩቤል ጀርባ ላይ ሆኖ እልፍ አእላፍ መላእክትን አስከትሎ ይወርዳል እመቤታችን በቀኙ ነበረች። ቅዱስ ዮሐንስም ‹‹ጌታዬ ለምን ሰበሰብከን?›› ብሎ ጠየቀ። ጌታችንም ‹‹በእናቴ ስም ከጽንፍ እስከ ጽንፍ አብያተ ክርስቲያናት እንዲታነጹ ፈቃዴ ነውና ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ላሳያችሁ ሥርዓት ላስተምራችሁ ነው›› አለው። ይህንን ብሎ ወደ ምሥራቅ ወሰዳቸው። በዚያም ተራርቀው የነበሩ 3 ደንጊያዎች ነበሩ። ጌታችንም ሦስቱን ድንጋዮችን በተአምራት አቀራርቦ አንሥቶ ጎተታቸው። ድንጋዮቹም እንደ ሰም ተለጠጡ፣ እንደ ግድግዳም ሆኑ። ቁመቱን ወርዱን መጥኖ ለሐዋርያቱ ሠጣቸው። እነርሱም እሳት እንዳየው ሰም ከእጃቸው እየለመለሙ (እየተሳቡ) ቁመቱን 24 ወርዱን 12 ክንድ አድርገው ሠርተውታል።  ዳግመኛም የብርሃን ምሰሶ ወረደ በሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም አምሳያ አድርጎ አነጻት ሁለንተናዋም ተጠናቀቀ። ከዚህም በኋላ ጌታችን ለሐዋርያቱ ‹‹እንግዲህ እናንተም እንዲህ አድርጋችሁ ሥሩ›› ብሏቸው ዐረገ። ሦስቱ ድንጋዮች የሥላሴን ሦስትነት ወደ አንድ ሆነው አንድ ሕንፃ መታጹ የሥላሴን አንድነት ያስረዳል። በአጠቃላይ የቤተ ክርስቲያን መታነጽ ለኛ ለክርስቲያኖች እጅግ ታላቅ በዓልና ደስታ ነው። ስለዚች ቤተ ክርስቲያን አባቶች ደማቸውን አፍስሰውላታል፣ አንገታቸውን ለሰይፍ ሰጥተውላታል፣ አጥንታቸውን ከስክሰውላታል፣ ቆዳቸው ተገፏል፣ በድንጋይ ተወግረዋል፣ በእሳት ተቃጥለዋል፣ በአውሬ ተበልተዋል። ቤተ ክርስቲያን ግድግዳዋ ውኃ መሠረቷ ደም ነው። የማትታደስ ነገር ግን ከኃጢአት ከበደል የሚታደሱባት ርትዕት ናት። ይህች ቤተ ክርስቲያን ‹‹የክርስቶስ አካሉና ሙላቱ ናት።›› እናም የዚህችን ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መጣስና ትምህርቷን መቆነጻጸል የክርስቶስን አካል ማድማት ነው።  ዳግመኛም በማግሥቱ ሰኔ 21 ቀን ጌታችን ድንግል እናቱን እመቤታችንንና ቅዱሳን መላእክትን አስከትሎ ወረደ። እመቤታችንን መንበር፣ ጴጥሮስን ተራዳኢ ካህን፣ እስጢፋኖስን ሠራዒ ዲያቆን አድርጎ ቀድሶ ለሐዋርያቱ አቁርቧቸዋልና ፍጹም ደስታም ሆነ።  ዳግመኛም ጴጥሮስን እጁን ጭኖ ፓትርያርክ አድርጎ ሾሞታል። በዚህም ጊዜ ሰማያውያን መላእክት ምድራውያን ሐዋርያት አንድ ሆነው አመስግነዋል። ከዚህ በኋላ ሐዋርያት ከጌታችን እንዳዩት በዓለም ዞረው ቤተ ክርስቲያን አንጸዋል። ከዚያ በፊት የነበረው የእነ ሰሎሞን ቤተ መቅደስ፣ የአይሁድ ምኲራብ፣ የአይሁድ ሥርዓተ አምልኮ መፈጸሚያ እንጂ የአዲስ ኪዳን የቁርባንም ሆነ የጥምቀት ሥርዓት መፈጸሚያ አልነበረም። እንኪያስ ‹‹ሐዋርያት የት ነበር ሕዝቡን የሚያጠምቁትና የሚያቆርቡት?›› ከተባለ እንደ ማርቆስ እናት ቤታቸውን ለሐዋርያት በሰጡ ‹‹በየአማኞቹ ቤት›› ይከናወን ነበር። ሰኔ 20 ቀን ሕንጸተ ቤተክርስቲያን (የቤተ ክርስቲያን መታነጽ) ታላቅ በዓል ነው። ቤተ ክርስቲያን እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ውኃ ፈሻሽ የመጣችና ሩቅ ብእሲ የመሠረታት ሳትሆን እራሱ ጌታችን አምላካችን በገዛ ደሙ የመሠረታት ናት። ሐዋ 20÷28 በዕለተ ዐርብ በዕፀ መስቀል ላይ ከጌታችን የፈሰሰው ቅዱስ ደም ቅዱሳን መላእክት በብርሃን ፅዋ ቀድተው በዓለም ሁሉ ረጭተውታል። ስለሆነም የጌታችን ወርቀ ደም በነጠበባቸው ቦታዎች ሁሉ ላይ ዛሬም ድረስ ቤተ ክርስቲያን ይሠራባቸዋል። ቅዱስ እግዚአብሔር አምላካችን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም እና ከቅድስት ቤተክርስቲያን በረከት ያሳትፈን አሜን!!

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! የሰሞኑ የአገልግሎት መረጃ አዲስ የተመረጡት የሥራ አመራር አባላት ለሥራ አስፈጻሚነት እንዲያገለግሉ ከተጠቆሙ 56 አባላት መካከል የማጣራት ሥራዎችን ሰርተው 28 አባላትን ከመረጡ በኃላ፤ ከእነርሱ ውስጥ ለሥራ አስፈጻሚነት የሚመረጡ 10 አባላትን በእጣ ለመለየት የሦስት ቀን ጸሎት እንዲደረግበት ወደ ቤተ መቅደስ የተላከ ሲሆን፣ ቅዳሜ በእጣ የሚመረጡትን አስፈጻሚዎች ለአባላት የምናሳውቅ ይሆናል። በመቀጠለም የንዑስ ክፍላት አገልጋዮችን ከሚመረጡት የሥራ አስፈጻሚ አባላት ጋር በመሆን ለይተን የምናሳውቃችሁ ይሆናል ብለው መረጃውን አድርሰውናል። በቀጣይም ሁላችንም በምንመደብበት የኃላፊነት ቦታ በትጋት በማገልገል ሰንበት ት/ቤታችንንና ቅድስት ቤተክርስቲያንን ወደ ተሻለ የአገልግሎት ከፍታ እንድናሳድግ እግዚአብሔር እንዲረዳን በጸሎት እንተሳሰብ በማለት መልእከቱን አድርሰውናል። መረጃው የሥራ አመራር /ቤት ነው እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ!

የሰኔ 12/2018 ዓ.ም ዓመታዊ ክብረ በዓል በፎቶ(3)