es
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Ir al canal en Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Mostrar más
2 604
Suscriptores
+324 horas
+87 días
+2430 días
Archivo de publicaciones
በሰንበት ት/ቤታችን በነበረው ጠቅላላ ጉባኤ የምርጫ መርሐግብር የማስታወሻ ፎቶዎች ከብዙ በጥቂቱ

ደብረ ምጥማቅ ግንቦት ሃያ አንድ በዚች ዕለት አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ ፊቷ በግልጥ ስለመታየቱ የክርስቲያን ወገኖች ሁሉም ታላቅ በዓልን ያደርጋሉ። እርሷም በልጅዋ የመለኮት ብርሃን የተጐናጸፈች ናት በዙሪያዋም የመላእክት ሠራዊት የመላእክት አለቆችም በየማዕረጋቸው ክንፋቸውን ዘርግተው ይቆሙ ነበር ይጋርዷታልም። ሱራፌልም ማዕጠንታቸውን ይዘው ለንግሥዋ ገናናነት ይሰግዳሉ በየስግደታቸውም እንዲህ እያሉ ያመሰግኗታል። አብ በሰማይ ሁኖ ተመለከተ እንደ አንቺ ያለ አላገኘም አንድ ልጁንም ልኮ ከአንቺ ሰው ሆነ። ሁለተኛ ሰማዕታትም በየማዕርጋቸው ረቂቃን በሆኑ ፈረሶቻቸው ተቀምጠው እየመጡ መጀመሪያ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከአምባላይ ፈረሱ ወርዶ ይሰግድላታል እንዲሁም ባልንጀሮቹ ሰማዕታት መጥተው ይሰግዱላታል ። ከእርሱ በኋላ የሚመጣው በዱሪ ፈረስ የሚቀመጥ ይህ መርቆሬዎስ ነው። ከዚህም በኋላ ሰማዕታት ሁሉ በመከታተል መጥተው ይሰግዱላታል ምስጋናም ያቀርቡላታል። ሁለተኛም ደግሞ የጻድቃን አንድነታቸው መጥተው በፊቷ ሰግደው ይመላለሳሉ። ሄሮድስ የገደላቸው ሕፃናትም መጥተው ይሰግዱላታል በፊቷም እየዘለሉ አንዱ በአንዱ ላይ እየዘለለ በመተቃቀፍም ይጫወታሉ የተሰበሰቡትም በአዩ ጊዜ ደስታ ይመላባቸዋል በሰማይም ያሉ ይመስላቸው ነበር። እናትና አባቱም የሞቱበት ቢኖር ወይም ከዘመዶቹ ወይም ባልንጀራዉ ቅድስት ድንግል እመቤቴ ሆይ ዕገሌን አሳዪኝ ብሎ በሚለምናት ጊዜ ቀድሞ በነበረበት መልኩ ያን ጊዜ ታመጣዋለች። ደግሞ መሀረባቸውን ወደላይ ይወረውሩላታል የወደደችውንም በእጇ ተቀብላ መልሳ ትጥልላቸዋለች ለበረከትም በየጥቂቱ ይካፈሉታል። እንዲህም አምስት ቀን ሁሉ ክርስቲያንም እስላሞችም አረማውያንም ያይዋታል። ወደ ቤታቸውም ለመሔድ ሲሹ በፊቷ ሰግደው ይሰናበቷታል እርሷም ትባርካቸውና ይመለሳሉ።   እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ሰንበት ትምህርት ቤታችን ፍኖተ ብርሃንን ለሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት  የሚመሩ አመራሮች የተከናወነ የምርጫ ሂደት ሪፖርት      ያለፈው መጋቢት 20/2018 ዓ.ም  አስመራጭ ኮሚቴዎች በጠቅላላ ጉባኤ የተመረጡ ሲሆን  የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት በአዘጋጃቸዉ ሁሉም ስልጠናዎች ላይ በመገኘት ስልጠና ወስደዋል በዚህም መሰረት  የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት  መዋቅር በሚያዘዉ መሰረት በጎግል ፎርም / Google Form / እና በተለያዩ መንገዶች የአባላት ጥቆማ በመቀበል ከተጠቆሙት አባላት ዉስጥ 20 / ሃያ / አባላት ለስራ አመራር ( 40% ወይም 8/ ስምንት /ከመደበኛ አባላት 60% ወይም 12 / አሥራ ሁለት / ከልዩ መደበኛ አባላት ) እንዲሁም 8 /ስምንት / አባላትን ለኦዲትና ኢንስፔክሽን በመስፈርቱ መሰረት በመለየት በደብሩ ለሰባት ቀን ፀሎተ እጣን በማስደረግ  በምርጫው እለት የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ያሬድ ለገሰ ፣ ከክ/ከተማ መ/ር ሚኪያስ ደስታ እና ተሾመ አምዲሳ በታዛቢነት በተገኙበት በጠቅላላ ጉባኤዉ የእጣ ማዉጣት መርሐ ግብር አከናውነናል ።     በዚህም መሰረት ከመደበኛ አባላት 4 /አራት/ አባላት  ለስራ አመራር ሲመረጡ 4 /አራት/ አባላት በተጠባባቂነት ተይዟል ። ከልዩ መደበኛ አባላት 7/ሰባት/ አባላት ለስራ አመራር ሲመረጡ 4/አራት/አባላት በተጠባባቂነት  ተይዟል ። 5 /አምስት/ አባላት ለኦዲትና ኢንስፔክሽን ሲመረጡ 3 /ሦሥት/ አባላት በተጠባባቂነት ተይዟል ።     በዚህም መሰረት የአስመራጭ ኮሚቴ ያስመረጣቸዉ አባላት ዝርዝር :-   => ለኦዲትና ኢንስፔክሽን በዕጣ የተመረጡ 1, አቶ ሰለሞን ለገሰ 2, አቶ ሚኪያስ ፍቅሩ 3, ዲ/ን በኃይሉ ተፈራ 4, ዲ/ን ሸዋንግዘዉ ሀብቴ 5, አቶ ፀጋዘአብ ገ/መስቀል   => ተጠባባቂ ዕጣ       የወጣላቸዉ ኦዲትና ኢንስፔክሽን 1, መ/ር አንዱአምላክ በፍቃዱ 2, ወጣት ጌታቸዉ ከበደ 3, ኢ/ር አሸናፊ ጥበቡ  ሲሆኑ => 40% ከመደበኛ አባላት በዕጣ          የተመረጡ የስራ አመራር 1, ወጣት አብርሃም አስራት 2, ወጣት ዮናታን ብርሃኑ 3, አቶ በረከት ፍቅሩ 4, ዲ/ን አሌክሳንደር ወ/ገብርኤል => በተጠባባቂ ዕጣ የወጣላቸዉ የስራ አመራር 1, ዲ/ን አብርሃም ታደሰ 2, ወጣት ተመስገን ገ/እግዚአብሔር 3, ወጣት የአብሥራ አክሊሉ 4, ወጣት ምትኩ አሰፋ => 60% ከልዪ መደበኛ አባል       በዕጣ የተመረጡ 1, መጋቤ ሠናያት መ/ር ወንድወሰን መኮንን 2, ኢ/ር ዳዊት አበበ 3, ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖአምላክ 4, ወጣት አበራ መላኩ 5, ወ/ት ሩት ሞገስ 6, አቶ ላቀዉ ይርጋ 7, ዲ/ን ዳንኤል ተክሌ => ለአዲስ አበበ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት      በጠቅላላ ጉባኤ 12 ተኛ ሆኖ የተመረጠ 8, ዲ/ን ደረጄ ኤቢሳ => በተጠባባቂ ዕጣ የወጣላቸዉ 1, አቶ ሙሉጌታ ሰማን 2, ወ/ሮ ዮርዳኖስ ገ/እግዚአብሔር 3, መ/ር ስለሺ ይርጋ 4, ዲ/ን ዮናታን አርአያ ሆነው ሰንበት ትምህርት ቤታችንን በአመራርነት ያገለግሉ ዘንድ ተመርጠዋል ቅዱስ እግዚአብሔር አምላካችን አገልግሎታችንን ይቀበልልን!!

የሐዘን መግለጫ የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነው የወንድማችን ምትኩ አስፋው ወላጅ አባት አርፈዋል። ሥርዓተ ቀብራቸው ዛሬ  ግንቦት 20/2018 ዓ.ም በቀጨኔ መድኃኔዓለም ቤ/ክ ከቀኑ 8:00  የሚፈጸም በመሆኑ በቀብሩ ላይ መገኘት  የምትችሉ ተገኝተን እንዲሁም መኖሪያ ቤታቸው  ከረዩ ቀበሌ 30 ክበብ አካባቢ በመገኘት እንድናጽናናቸው ይሁን።  የአባታችንን ነፍስ  ይማርልን ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ማሕበራዊ ሚዲያ ለምትጠቀሙ የሰ/ት/ቤት አባላት በሙሉ። የፊታችን እሑድ ግንቦት23/2018ዓ.ም የደብራችን ዋና መጠሪያ የሆነው (ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት) የተባለበትን የጰራቅሊጦስን በዓል በታላቅ ድምቀት እንደምናከብር ይታወቃል። በመሆኑም ደብራችን በዋናነት የመንፈስ ቅዱስ እና የሐዋርያት በዓል የሚከበርበት መሆኑን ለመላው ምዕመናን ለመላው ምዕመን ለማሳወቅ ይረዳን ዘንድ ሁላችሁም የሰንበት ት/ቤታችን አባላትና ወዳጆቻችን በግል በምታንቀሳቅሷቸው ማሕበራዊ ሚዲያዎች በሙሉ በዓሉ በደመቀ ሁኔታ በደብራችን የሚከበር መሆኑን በየራሳችሁ መንገድ እንድታስተዋውቁ ይህንን መመሪያ እናስተላልፋለን ። ስለዚህ 1. የደብራችንን ስዕል በገጾቻችን ፊት ላይ (profile) በማድረግ 2. በሰንበት ት/ቤታችን የሚለጠፈውን ማስታወቂያ ለብዙዎች ማጋራት 3.የእኛን ደብር እና በዓሉን የሚያስተዋውቁ ሰዎችን እና ተቋማት ሀሳባቸውን ለብዙዎች እንዲዳረስ ማጋራት (share) አድርጉ ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን!!

ማሕበራዊ ሚዲያ ለምትጠቀሙ የሰ/ት/ቤት አባላት በሙሉ። የፊታችን እሑድ ግንቦት23/2018ዓ.ም የደብራችን ዋና መጠሪያ የሆነው (ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት) የተባለበትን የጰራቅሊጦስን በዓል በታላቅ ድምቀት እንደምናከብር ይታወቃል። በመሆኑም ደብራችን በዋናነት የመንፈስ ቅዱስ እና የሐዋርያት በዓል የሚከበርበት መሆኑን ለመላው ምዕመናን ለመላው ምዕመን ለማሳወቅ ይረዳን ዘንድ ሁላችሁም የሰንበት ት/ቤታችን አባላትና ወዳጆቻችን በግል በምታንቀሳቅሷቸው ማሕበራዊ ሚዲያዎች በሙሉ በዓሉ በደመቀ ሁኔታ በደብራችን የሚከበር መሆኑን በየራሳችሁ መንገድ እንድታስተዋውቁ ይህንን መመሪያ እናስተላልፋለን ። ስለዚህ 1. የደብራችንን ስዕል በገጾቻችን ፊት ላይ (profile) በማድረግ 2. በሰንበት ት/ቤታችን የሚለጠፈውን ማስታወቂያ ለብዙዎች ማጋራት 4. የእኛን ደብር እና በዓሉን የሚያስተዋውቁ ሰዎችን እና ተቋማት ሀሳባቸውን ለብዙዎች እንዲዳረስ ማጋራት (share) አድርጉ ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን!!

ማሕበራዊ ሚዲያ ለምትጠቀሙ የሰ/ት/ቤት አባላት በሙሉ። የፊታችን እሑድ የደብራችን ዋና መጠሪያ የሆነው (ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት) የተባለበትን የጰራቅሊጦስን በዓል በታላቅ ድምቀት እንደምናከብር ይታወቃል። በመሆኑም ደብራችን በዋናነት የመንፈስ ቅዱስ እና የሐዋርያት በዓል የሚከበርበት መሆኑን ለመላው ምዕመናን ለመላው ምዕመን ለማሳወቅ ይረዳን ዘንድ ሁላችሁም የሰንበት ት/ቤታችን አባላትና ወዳጆቻችን በግል በምታንቀሳቅሷቸው ማሕበራዊ ሚዲያዎች በሙሉ በዓሉ በደመቀ ሁኔታ በደብራችን የሚከበር መሆኑን በየራሳችሁ መንገድ እንድታስተዋውቁ ይህንን መመሪያ እናስተላልፋለን ። ስለዚህ 1. የደብራችንን ስዕል በገጾቻችን ፊት ላይ (profile) በማድረግ 2. በሰንበት ት/ቤታችን የሚለጠፈውን ማስታወቂያ ለብዙዎች ማጋራት 4. የእኛን ደብር እና በዓሉን የሚያስተዋውቁ ሰዎችን እና ተቋማት ሀሳባቸውን ለብዙዎች እንዲዳረስ ማጋራት (share) አድርጉ ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን!!

የሐዘን መግለጫ የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነው የወንድማችን አምሐ ክፍሉ ወላጅ አባት አርፈዋል። ሥርዓተ ቀብራቸው ዛሬ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም በቀጨኔ መድኃኔዓለም ቤ/ክ ከቀኑ 6:00  የሚፈጸም በመሆኑ በቀብሩ ላይ መገኘት  የምትችሉ ተገኝተን እንዲሁም መኖሪያ ቤታቸው ቴዎድሮስ አደባባይ ወረድ ብሎ ከቸርችል ሆቴል  ወደ ውስጥ አካባቢ በመገኘት እንድናጽናናቸው ይሁን።  የአባታችንን ነፍስ  ይማርልን ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ዛሬ በሰንበት ትምህርትን ቤታችን ግንቦት 16/2018 ዓ.ም በሚደረገው ምርጫ ላይ የደብራችን አስተዳደር ፣የስብከተ ወንጌል ተወካዮች ፣ የክፍለ ከተማ ሰ/ት/ቤት ተወካዮች፣ እንዲሁም ከአዲስ አበባ ሰ/ት/ቤቶች ተወካዮች ስለሚመገኙና የሰንበት ት/ቤታችን ደረጃም የሚለካበት በመሆኑ የአባላት ቁጥር መስፈርት አንዱ ስለሆነም በዕለቱ እንድትገኙ ይሁን።     ማሳሰቢያ :- ጸሎተ ኪዳን የሚደርስ በመሆኑ በጊዜ በሰዓቱ እንድትገኙ እናሳስባለን!!

ዛሬ በሰንበት ትምህርትን ቤታችን ግንቦት 16/2018 ዓ.ም በሚደረገው ምርጫ ላይ የደብራችን አስተዳደር ፣የስብከተ ወንጌል ተወካዮች ፣ የክፍለ ከተማ ሰ/ት/ቤት ተወካዮች፣ እንዲሁም ከአዲስ አበባ ሰ/ት/ቤቶች ተወካዮች ስለሚመገኙና የሰንበት ት/ቤታችን ደረጃም የሚለካበት በመሆኑ የአባላት ቁጥር መስፈርት አንዱ ስለሆነም በዕለቱ እንድትገኙ ይሁን።     ማሳሰቢያ :- ጸሎተ ኪዳን የሚደርስ በመሆኑ በጊዜ በሰዓቱ እንድትገኙ እናሳስባለን!!

ዛሬ በሰንበት ትምህርትን ቤታችን ግንቦት 16/2018 ዓ.ም በሚደረገው ምርጫ ላይ የደብራችን አስተዳደር ፣የስብከተ ወንጌል ተወካዮች ፣ የክፍለ ከተማ ሰ/ት/ቤት ተወካዮች፣ እንዲሁም ከአዲስ አበባ ሰ/ት/ቤቶች ተወካዮች ስለሚመገኙና የሰንበት ት/ቤታችን ደረጃም የሚለካበት በመሆኑ የአባላት ቁጥር መስፈርት አንዱ ስለሆነም በዕለቱ እንድትገኙ ይሁን።     ማሳሰቢያ :- ጸሎተ ኪዳን የሚደርስ በመሆኑ በጊዜ በሰዓቱ እንድትገኙ እናሳስባለን!!

ጰራቅሊጦስ ‹‹እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ ›› ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በእለተ ሰንበት በዓለ ጰራቅሊጦስ መ
ጰራቅሊጦስ  ‹‹እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ  ግን  ከላይ ኃይል እስክትለብሱ  ድረስ  በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ ›› ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በእለተ ሰንበት በዓለ ጰራቅሊጦስ መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት የወረደበት ቀን በአዲስ አበባ የመንፈስ ቅዱስ በሆነው ደብራችን በታላቅ ድምቀት ይከበራል!!   አድራሻ:- ከኢሚግሬሽን ወደ ላይ ከፍ ብሎ - ከቴዎድሮስ አደባባይ ሲመጡ ኤክስትሪም ሆቴል ገባ ብሎ