የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
前往频道在 Telegram
2 752
订阅者
-224 小时
+197 天
+5130 天
帖子存档
+2
እንኳን ለቅዱሳን ሐዋርያት አባቶቻችን ጴጥሮስ ወጳውሎስ ዓመታዊ በዓል አደረሳችሁ። ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ እና ቅዱስ ጳውሎስ የሰማዕትነትን አክሊል የተቀበሉበትን ዓመታዊ በዓል ሐምሌ ፭ ቅድስት ቤተክርስቲያን በታላቅ ክብር ታከብረዋለች።
"ውስተ ኩሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ
ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ
ወውስተ ጸሐይ ሤመ ጽላሎቶ" መዝ ፲፰፥፬
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ዕለታዊ የሰንበት ት/ቤታችን መረጃ!
በዛሬው ዕለት ለሦስት ቀናት ከተያዘው የጸሎት መርሐግብር የሦስተኛው ቀን የጸሎት መርሐግብር የደብራችን አስተዳዳሪ ክቡር መልአከ ብርሃናት አእምሮ ምስጋናው በተገኙበት ተከናውኗል። በዕለቱም ላለፉት አራት ዓመታት ሰንበት ት/ቤታችንን በአመራርነት ያገለገሉ ወንድሞችና እሕቶችን የምስጋና የማስታወሻ ስጦታ በክቡር አባታችን የተሰጠ ሲሆን፤ አዲስ ለተመረጡ አመራሮችና አስፈጻሚዎች አባታዊ ምክርና መመሪያ ሰጥተው በጉባኤው ፊት ቀርበው ጸሎተ ማርያም አድርሰውላቸዋል። ካሳለፋችሁት ጉዞ ይልቅ ወደ ፊት የሚጠብቃችሁ አገልግሎት ሰፊ በመሆኑ ራሳችሁን አዘጋጁ ብለው ማሳሰቢያ ሰጥተው ጉባኤውን በጸሎት አሳርገውልናል።
እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
+9
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ዕለታዊ የሰንበት ት/ቤታችን መረጃ!
በዛሬው ዕለት ለሦስት ቀናት ከተያዘው የጸሎት መርሐግብር የሦስተኛው ቀን የጸሎት መርሐግብር የደብራችን አስተዳዳሪ ክቡር መልአከ ብርሃናት አእምሮ ምስጋናው በተገኙበት ተከናውኗል። በዕለቱም ላለፉት አራት ዓመታት ሰንበት ት/ቤታችንን በአመራርነት ያገለገሉ ወንድሞችና እሕቶችን የምስጋና የማስታወሻ ስጦታ በክቡር አባታችን የተሰጠ ሲሆን፤ አዲስ ለተመረጡ አመራሮችና አስፈጻሚዎች አባታዊ ምክርና መመሪያ ሰጥተው በጉባኤው ፊት ቀርበው ጸሎተ ማርያም አድርሰውላቸዋል። ካሳለፋችሁት ጉዞ ይልቅ ወደ ፊት የሚጠብቃችሁ አገልግሎት ሰፊ በመሆኑ ራሳችሁን አዘጋጁ ብለው ማሳሰቢያ ሰጥተው ጉባኤውን በጸሎት አሳርገውልናል።
እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
+9
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
የዕለቱ የአገልግሎት ዜና
በዛሬው ዕለት ለሦስት ቀናት ከተያዘው የጸሎት መርሐግብር የሁለተኛው ቀን የጸሎት መርሐግብር በቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖአምላክ እየተመራ ተከናውኗል። ከትላንትናው የተሻለ የጸሎት ተሳታፊ የነበረ ሲሆን፤ በነገው ዕለት በሚደረገው የሦስተኛው ቀን ጸሎት ሁሉም አባል ተገኝተው እንዲሳተፉ መልእክት ተላልፏል። በተጨማሪም ላለፉት አራት አመታት ሰንበት ት/ቤታችንን በአመራርነት ሲያገለግሉ ለነበሩ አባላት የምስጋና መርሐግብር የተዘጋጀ ሲሆን፤ በአመራርነት እና አስፈጻሚነት ለተመረጡት አዲሶቹ አመራሮች የደብራችን አስተዳዳሪ በተገኙበት አባታዊ መልእክትና መመሪያ እንደሚሰጥ ተጠቅሷል። ጸሎቱ 11:30 ስለሚጀምር አባላት ቀድማችሁ እንድትገኙ በአምላከ ቅዱስ ሚካኤል ስም ጥሪ ተላልፏል።
እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
+4
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
የዕለቱ የአገልግሎት ዜና
በዛሬው ዕለት ለሦስት ቀናት ለተያዘው የጸሎት መርሐግብር የመጀመሪያው ዕለት ጸሎት ተከናወነ። በዝናብ ምክንያት የአባላት ቁጥር በቂ የነበረ ባይሆንም በተገኙት ጥቂት አባላት ጸሎቱ የተደረገ ሲሆን፤ በዕለቱም የደብራችን የመጻሕፍት መምህር የሆኑት ሊቀ ጠበብት አያልቅበት ጸሎቱን መርተውልናል። በነገውም ዕለቱ የጸሎቱ መርሐግብር የሚቀጥል ሲሆን የምትችሉ አባላት ተገኝታችሁ በጸሎቱ እንድትሳታፉ ጥሪ ተላልፏል።
እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ
“ወአኀሥሥ እምኔሆሙ ብእሴ…ዘየሐንፅ ዐረፍተ ወይቀውም ኀበ ዘተነሥተ በቅድሜየ ፡፡ ”
በፈረሰበት በኩል በፊቴ የሚቆምላትን ሰው እፈልጋለሁ ፡፡
ሕዝ = 22፥30 " ፡፡
ለተወደዳችሁ የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት በሙሉ !!
ከኹሉ አስቀድመን በየአላችሁበት ስፍራ ሁሉ በኀያሉ ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት ሰላመ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋራ ይሆን ዘንድ እየተመኘን መንፈሳዊ ሰላምታችንን እናቀርባለን ፡፡
እንደምታውቁት እናታችን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በእየዘመኑ በውስጥም ኾነ በውጭ እንደሚገጥማት ፈተና ሁሉ ዛሬም ከገጠማት የዐረፍተ ግብር አገልግሎት ክፍተት የተነሣ ኹላችን ልጆቿ የቅጥሯ አገልግሎት በሳሳበት በኩል በፊቷ ቆመን ቅጥሯን እንድናጸናላትና ከቅፅሯም እንዳንለይ ዛሬም ሁላችንን እየተጣራች ትገኛለች ፡፡
ምክንያቱም አገልግሎቷ የሁላቸንን አንድነትን ይሻል ፡፡ አንድነታችንም ለአገልግሎቷ ብቻ በሚውል ቀናዒነት ይገለጻል ፡፡ ደግመን እንላለን ፡፡ ለሁላችን የሁላችን አንድነት ያስፈልገናል ፡፡ አባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት በአንድ መንፈስ ከሚመራው ጉባኤ ሊወጡ የወደዱ ሐናና ሰጲራን በበትረ ሞት ቀጥተው አንድነትን አጽንተዋል፡፡ በአንድ ልብና በአንድ ሐሳብ በጸሎት ይተጉ በነበሩበት ወቅትም መንፈስ ቅዱስን ተቀብለዋል ፡፡ ሐዋ. 2፥4, 5፥1 ፡፡
ነገር ግን ክፉዎች ሰዎች ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ክብር ይልቅ ለግላዊ ክብርና ፍላጎት ሲሉ የሚፈጥሩትን ረቂቅ ክፍተት የአልተረዱ አንድ አንድ የዋሃን “ በተለያየ ጎራ ተሰልፈን እናገልግል ” ሊሉን ይችላሉ ፡፡ ይህም በአንዲት እናት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጥላ ሥር ያለቸውን የአንዲት ሰንበት ትምህርት ቤታችንን ዐይነተኛ የአንድነት መንገድ ከአለመረዳት የመጣ ነው ፡፡ ይልቁንም ከእንግዲህ የተጣላን ብንኖር ታርቀን ፤ የተበደልን ይቅር ብለን ፤ የበደልን ይቅርታ ጠይቀን ፤ በፍቅር በአንድነት እንድናገለግል እየጠየቅን ፤ እነሆ ከሐምሌ 2-4 2018 ዓመተ ምሕረት ድረስ የሚካኼድ የሦስት ቀናት ልዩ የጸሎት መርሐ ግብር ተዘጋጅቷል ፡፡
ስለዚኽ በአካል መገኘት የምችችሉ፤ በመገኘት ፤ በአካል መገኘት የማትችሉም በየአላችሁበት ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤታችንን እያሰባችሁ “ ሰላም ለኪ…” እንድታደርሱልን እጅግ ፍቅርን በተመላ ቤተሰባዊ ትሕትና እንጠይቃለን ፡፡
" ናሁ ሠናይ ወናሁ አዳም ሶበ ይሄልዉ አኃው ኅቡረ"
+9
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
325 የተልዕኮ ትምህርት ተማሪዎች ተመረቁ።
በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት የተልዕኮ ትምህርት ማስተባበሪያ ለአንድ ዓመት እና ለሶስት ዓመታት መንፈሳዊ ተከታታይ ትምህርት ሲያስተምራቸው የቆዩ 325 ተማሪዎችን ትላንት ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አስመርቋል።
በዕለቱ ትምህርተ ወንጌል በመ/ር ኢዩኤል የተሰጠ ሲሆን የዝማሬ አገልግሎት በዘማሪት ሲ/ር ሕይወት ተፈሪ እና በተመራቂ ተማሪዎች ቀርቧል። በዕለቱ የደብራችን ዋና አስተዳዳሪ መልአከ ብርሃናት አዕምሮ ምስጋናው መምህራነ ቤተ ክርስቲያን ፣ ተመራቂ ተማሪዎች ፣የተመራቂ ቤተሰቦች እንዲሁም ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።
የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
