es
Feedback
ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

Ir al canal en Telegram

"ስለመጻሕፍት ከመጻሕፍት መንደር እንዘምራለን!"

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

El canal ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖 (@bookshelf13) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 18 610 suscriptores, ocupando la posición 1 875 en la categoría Libros y el puesto 1 808 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 18 610 suscriptores.

Según los últimos datos del 10 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -185, y en las últimas 24 horas de -3, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 12.38%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 4.41% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 2 303 visualizaciones. En el primer día suele acumular 820 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 15.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
"ስለመጻሕፍት ከመጻሕፍት መንደር እንዘምራለን!"

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 11 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Libros.

18 610
Suscriptores
-324 horas
-407 días
-18530 días
Archivo de publicaciones
«ታስፈሩኛላችሁ!! » [ አስኮ ጌታሁን እና A Madman's Diary] ➊ "A Madman's Diary" በታዋቂው ቻይናዊ ጸሐፊ Lu Xun የተጻፈው "A Madman's Diary" የተሰኘውን Short Story አንድ ወዳጄ ጋብዞኝ አነበብኩ። እውነትም ዩኒክ ነገር አለው። ፅሁፏ ስትታይ ቀድረ ቀላል ብትመስልም የምትጥለው ጥላ ግን ግዙፍ ነው። በዙሪያው ያሉ ሰዎች... ጎረቤቶቹ፣ አልፎ ተርፎም የገዛ ወንድሙ ጭምር ሰው በላዎች እንደሆኑና እሱን ለመብላት እንደሚያሴሩ የሚያምን የአንድ ሰው ማስታወሻ ነው። ሐኪም ሊያየው እጁንና እና የልብ ትርታውን ሲዳስስ ምን ያህል እንደሰባና ሥጋው ለምግብነት እንደሚሆን እየፈተሸ የሚመስለው አይነት። የዚህ የእብድ ማስታወሻ የአእምሮ ሕመምተኛ ቅዠት ቢመስልም ከጀርባው ግን philosophical የሆነ ማኅበራዊ ሂስን ያዘለ ነው። በታሪኩ መቅድም ላይ የዲያሪው አመጣጥ ይተረክበታል። አንድ ሰው፤ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እያለ በጣም የቅርብ ጓደኞቹ ወደነበሩ ሁለት ወንድማማቾች ዘንድ ይሄዳል። በቅርቡ አንደኛው በጣም ታሞ እንደነበር ወሬ ሰምቷል። እና ሊያያቸው ወደ ቤታቸው አቀና። ነገር ግን ያገኘው ታናሽ ወንድሙን ብቻ ነበር። እሱም ወንድሙ ከታመመ ቆይቶ አሁን ግን ሙሉ በሙሉ ድኖ ሥራ ፍለጋ ወደ ሌላ ከተማ እንደሄደ ይነግረውና ​"ወንድሜ አእምሮው በታመመበት ወቅት የጻፈውን ማስታወሻ ላንተ ለድሮ ጓደኛው ብሰጥህ ምንም አይደለም" ብሎ ያቀብለዋል። ​ማስታወሻውን ሲያነበው የተዘበራረቁ፣ ትርጉም የሌላቸውና የተቆራረጡ ፅሁፎች ነበሩ። ብዙ የቅዠትና የጭንቀት ንግግሮች ታጭቆበታል። የማስታወሻወቹ ዋና ነጥብ ግን ሰዎች ሊበሉት እንደሚፈልጉ ማመኑ ነበር። ሂዶ ሂዶ ማስታወሻው ድንገት ሲቋረጥ ሰውዬው መጨረሻ ላይ ምን እንደደረሰበት ግልጽ ሳያደርግ ጥርጣሬ ላይ ይተወናል። የመፅሐፉ መቅድም ላይ እብድ የተባለው ሰውዬ ድኖ ሥራ ፍለጋ ወደ ሌላ ከተማ መሄዱ ይነገረናል። ​ነገር ግን ሰውዬው የዳነው እንዴት ነው? የሚል ጥያቄ ደሞ ማንሳታችን አይቀርም። ​ ዳነ ማለት ወደ ፈራው ማኅበረሰብ ተመለሰ? እሱም እንደ ሌሎቹ ሰው በላ ሆነ ማለት ነው? ወይንስ ማኅበረሰቡ አስገዳጅ በሆነ መንገድ ዝም አሰኘው? ይህ ደራሲው ለአንባቢው የተወው ጥያቄ ይመስለኛል። መፅሐፉን በደንብ ከመረመርነው እብድ የተባለው ሰውዬ ብቻ ነው በዚያ በበሰበሰና በተበላሸ ሥርዓት ውስጥ ብቸኛው ጤነኛ እና ሀቁን የተረዳ ሰው ሆኖ የሚገኘው። ማኅበረሰቡ ሰውዬውን ጨልሏል ይለዋል። እሱ ግን በዙሪያው ያሉ ሰዎች ሁሉ ሰብአዊነት የጎደለውና አንዱ ሌላውን የሚበላበት ሥርዓት ውስጥ መኖሩን የተረዳ ብቸኛው ሰው ነበር። የማስታወሻው ማብቂያ ላይ «ይህንን ሥርዓት መቀየር አለብን። ሰውን መብላት ማቆም አለብን! ሰውን የማይበላ አዲስ ማኅበረሰብ መፍጠር ይቻላል። ልጆቹን አድኑ...» ይላል እብዱ ሰው። ይህች የመጨረሻዋ ተማጽኖ የተቀላቀለባት ዓረፍተ ነገር ማስታወሻው ብቻ ሳይሆን ሙሉው አጭር ልብ-ወለድ የሚደመደምበት መስመር ናት። ❷ «አስኮ ጌታሁን» ይህንን Lu Xun ታሪክ ሳነብ ትዝ ያለኝ የጃርሶ ሞትባይኖር ኪሩቤል "አስኮ ጌታሁን" አጭር ልብወለድ ነው። ሀሳባቸው ከሞላ ጎደል ተመሳሳይ ነው። ◉ ጌታሁን ፍቅረየሱስ (አስኮ ጌታሁን) ጎበዝ መምህር ነበር። ግን ደፍረው ሀቅ ሀቋን የሚናገሩ መምህር ስለሆኑ ከብዙ ሰው ጋር መቀያየማቸው አልቀረም። የመምህርነት ሙያ ምግባረ ቀና እና የተማሩና የተገነዘቡ ሰዎችን ማፍራት እንጂ ለደመወዝ ማግኛ ብቻ የሚፈፀም የግብር ይውጣ መሆን እንደሌለበት የሚያምን ነበር። እንዲህ ማሰባቸው ባላንጣ ከማፍራት አልከለላቸውም። ትምህርት ቤት አይፈርስም ስላለ በሹመኞች ቂም ተቋጥሮበታል። በራስ አነሳሽነት የጀመሩት በየገጠሩ በመሄድ ተማሪዎችን ፊደል ማስቆጠራቸው ከሀገሬው ምስጋና አትርፎላቸው፤ ከሹማምንት ወታደር የመሳሪያ ሰደፍ አሸልሟቸዋል። ሚስቱን የዘመድ ባላንጣዎች መርዝ አብልተው የገደሉበት ሰው ነው። በሴራ 18 ዓመት ታስሮ ወጥቷል። በደረሰበት መከራና ጭንቅላቱ ላይ በደረሰ ጉዳት ያ አስፈሪው "አስኮ ጌታሁን" ይወለዳል። አስኮ እየጮኸ ሁሌ የሚናገራት አንዲት ቃል አለች.. «ታስፈሩኛላችሁ!! » ◉ ይህች "ታስፈሩኛላችሁ" የምትለው ቃል የሁለቱንም ታሪኮች ማዕከላዊ ስሜት ትገልጻለች። ንጹሕና ሀቀኛ ሰው በክፉዎች፣ በሴረኞችና በሰው በላዎች በተከበበ ማኅበረሰብ ውስጥ ሲኖር የሚሰማው የመጨረሻው የስሜት ጥግ ፍርሃት ነው። «ታስፈሩኛላችሁ!» ወይም «ሊበሉኝ ነው!» የሚለው ፍርሃት የአእምሮ ሕመም ሳይሆን የአንድን ማኅበረሰብ መበስበስ የተረዳ ንቁ ሕሊና ያለው ሰው የሚያሰማው ዋስትና የማጣት ጩኸት ነው። ​ ​የዛሬዋ ዓለም በካፒታሊዝም፣ በፖለቲካዊ ሽኩቻና በራስ ወዳድነት የምትመራ ናት። ጠንካራው ደካማውን የሚበላበት፣ ባለሥልጣኑ ተራውን ሕዝብ የሚጨቁንበት፣ ትልልቅ አገራት ትናንሾቹን የሚያጠፉበት ሥርዓት ነው። Lu Xun እና ጃርሶ ሞትባይኖር ሊነግሩን የፈለጉት ዓለማችን በሕግ ትገዛለች ቢባልም፤ በሥልጣኔ ብትስፈነጠርም፣ በቴክኖሎጂ ብትራቀቅም፤ በሞራልና በሰብአዊነት ግን ወደ አውሬነት እየወረደች መሆኑን ነው። ​በሁለቱም ታሪኮች ውስጥ እብደት የተባለው ነገር ከግለሰቦቹ የአእምሮ መታወክ የመጣ ሳይሆን፣ ማኅበረሰቡና ሥርዓቱ እውነቱን የተናገሩትንና ከጭፍን ልማድ የወጡትን ንጹሐን ሰዎች የሚቀጡበትና ስም የሚሰጡበት መንገድ መሆኑን ነው። ​ ◉ "A Madman's Diary" ውስጥ ታሪኩ የሚደመደመው "ልጆቹን አድኑ..." በሚል የልመና ጥሪ ነው። ተስፋው ገና ባልተበከሉ ሕፃናት ላይ ነው። ​በ"አስኮ ጌታሁን" ውስጥም መምህር ጌታሁን ሕይወታቸውን ሙሉ የደከሙት ለታዳጊ ትውልድ ነበር። ​ ሁለቱም ገጸ-ባህሪያት ለአዲሱ ትውልድ ትልቅ ስፍራ አላቸው። ለዛ ነው ልጆቻችሁን አድኑ ብለው የሚለፍፉት። እና እኔ ምን እያልኳችሁ ነው? "ታስፈሩኛላችሁ!" ▭▭ © Mes Oud

ሰለሞን ደሬሳ ይሄን ሲያይ ነው “በአያትህ በር ማን እንዳለፈ አታውቅም” ያለው። እንዲህ አይነት ደስ የሚያሰኝ ታሪክ ነበረን። ይሄን ሁነት ደራሲው እንዲህ ይገልጸዋል። “በዚህ አይነት ከተለያዩ አካባቢዎች ተጉዘው በበጌምድር በሰፈሩት የኢትዮጵያ ልዩ ልዩ ብሄረሰብ አባላት ሳቢያ፣ የጎንደርና የምዕራብ ወሎ ሕዝብ ምን ያህል እንደተቀላቀለና በልጅ ልጆቹም እንደተዋለደ መረዳት ይቻላል። ሰፈራው በአገራችን ታሪክ ከጥንት ጀምሮ ከተከናወኑ ማህበራዊ ሰፈራዎች አንዱና በልማት ሳቢያ ‘በወዶ ፈቃድ’ እንደተከናወኑ ከሚነገርላቸው አንዱ ነው። ዛሬ ‘ጎንደር ቤቴ፣ ርስቴና ጉልቴ’ እያለ በጎንደሬነቱ የሚኮራው ብዙ የአካባቢው ህዝብ ደሙ ከምዕራብ፣ ከደቡብ፣ ከምስራቅና ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ልዩ ልዩ አካባቢ ነዋሪዎች የተቀዳመሆኑን ያስገነዝበናል”። ይላል። እና ሰው ሀረግ ነው። እኛ አሁን ከምናስበውና ከምናውቀው በተለየ መልኩ እንዲህ እርስ በእርስ የተዳቀልን ህዝቦች ነን። ምናልባት ይሄን አይነቱን ታሪካችንን ስለማናውቀው ነው ወይስ ሆነ ብለን ስለምንክደው እንዲህ እርስ በእርስ የምንናከሰው እያልሁ መብሰልሰሌን ተያያዝሁት። ንጉሱ ባቡር እየገነቡ፣ የተጎዳ አካባቢንም እንዲህ እያለሙ፣ በዓለም ፊትም ግርማቸውን እንደለበሱ ሞት አይቀሬው ወሰዳቸው። ይሄው እኛም አለን። ባቡሩ አዲስ አበባ ከደረሰ በኋላ እስከ ጅማ የማድረስ ሃሳብ ነበራቸው። ከቪክቶሪያ ሃይቅ ጋር አገናኝተው በመርከብ ንግድ ላይም የመሳተፍ ትልቅ ህልም ነበራቸው። ግን ይሄው መቶ ዓመታት አለፉ። ባቡሩ ጅማ ደረሰን? ሁሌም ትውልድን የሚያናጋ ጥያቄ ነው። የታሪክ ሰዎቻችንም ሆኑ ፖለቲከኞቻችን ምናለ እንዲህ አይነቱን ቢነግሩን? ይሄ መጽሐፍ ሌሎች እልፍ ቁም ነገሮች አሉት። አንዷን ጉዳይ ብቻ እየመዘዙ ካልተወያዩበት ጠቅልሎ እንዲህ ለማለት ያስቸግራል። የታጨቁ ሁነቶችና ታሪኮች የሞሉት ነውና። ታነብቡት ዘንድ ግን በደስታ እጋብዛችኋለሁ። ደራሲ ንጉሴ አየለ ተካ ሆይ እጅግ እናመሰግናለን። ለብርታትህም ኮፍያችንን አውልቀን ክብርችንን እንገልጻለን። ቀሪዎቹንም ታደርስልናለህ ብለን ተስፋ እንደርጋለን። ሰናይ ንባብ። Reviewer : © ውብአረገ አድምጥ © Think Ethiopia

ጎንደር ቤቴ፣ ርስቴና ጉልቴ - ከኦዛና ምኒልክ ታላቁ ክብር ኢትዮ አትላንቲክ ዘዳግማዊ ምኒልክ ወ ልጅ እያሱ! (ተጻፈ ከንጉሴ አየለ ተካ!) ይሄንን መጽሐፍ እንደወጣ ተስገብግቤ ነው የገዛሁት። ምክንያቱም ደራሲው ንጉሴ አየለ ከዚህ በፊት ‘ታላቁ ጥቁር’ በሚለው መጽሐፉ ያስነበበን ታሪክ አጃይብ የሚያስብል ነበርና ነው። እናም ቶሎ ገዛሁት። አነበብሁትም። ተደነቅሁም። ታሪኩ የሚያጠነጥነው የእኛ ታሪክ በተለይ የአድዋን ድል ተከትሎ በአሜሪካና በካረቢያን ምን ይመስል ነበር? ንጉሶቻችን ምን አይነት ቦታ ነበራቸው? የአሜሪካ ጋዜጦች ስለእኛ ምን ይሉ ነበር? እኛስ እንደ ሀገር ምን አይነት ቦታ ነበረን የሚሉና ተመሳሳይ ታሪኮችን የሚያነሳ ነው። በአስራ አምስት ምዕራፎች የተከፋፈለው መጽሐፍ ስለ አስራ አምስት የተለያዩ ጉዳዮች በጥልቀት የሚያስስ ነው። ጸሐፊው ስለ አንድ ጉዳይ ያነሳና ጭብጡን እየተከተለ ሰምተነው የማናውቀውን ታሪክ ከባህር ማዶ መዛግብቶችና ከዘመኑ የጋዜጣ እትሞች ላይ እያጣቀሰ አጃይብ ያስብለናል። ጽሑፎቹ ከእነ ማስረጃቸው ባይሆኑ ኖሮ በተለይ በዚህ ዘመን ለመካድ የሚያስመኙ የሚመስሉ ብዙ ታሪኮች ተካተውበታል። አሁን በሞቴ አንድ ወቅት ወደ ኢትዮጵያ ለሰርግ ሽርሽር (ሃኒሙን) ታላላቅ ሰዎች ይጎርፉ ነበር ቢባል ማን ያምናል? አጤ ምኒልክ በሜዳ አህያ ብቻ አጠቃላይ የዲፕሎማሲ ስራቸውን ይሰሩ ነበር ቢባል ማን ያምናል? እንዲያው በሞቴ አቢሲኒያ የሚሰኝ ቴአትር ይታይ ነበር። የእነ ሳባ ታሪክ ሰርክ መማሪያ፣ የእነ ጣይቱ ስም ለሴቶች መታገያ ነበር ቢባልስ ማን ያምናል? ሀጂ አብደላሂ አሊ ሳዲቅ የተባሉ የምኒልክ መልዕክተኛ በአሜሪካ ያገኙት አቀባበልና በኋይት ሃውስ የተደረገላቸውን ግብዣ ቢሰማ ማን በጄ ይላል? ስለ ኢትዮጵያ ኮከብና ስለ ባንዲራችን። ስለ ጥቁሮች ትግልማ ምኑ ይወራል። እንዲያው ደራሲው በታላቁ ጥቁር እንደነገረን አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር የንግድ ውል ስትዋዋል የስምምነቱ አይነት እጅግ ከተወደዱና ከተመረጡ ሀገራት ጋር የሚደረግ “with great favored nation” እንደነበር ብናውቅ እውን ቁጭት ያድርብን ይሆን? ብቻ አሁን ካለንበት ምስቅልቅል ጋር አገናኝታችሁ በፍፁም አይደረግም እንዳትሉ። ሆኗል። ነበርም። ብዙ ብዙ ማለት ያስችል ነበር። ግና አንብባችሁ ፍረዱኝ ብዬ ወደ ጉዳዬ ልግባ እንደሚታወቀው በሀገራችን ባቡር ያስገቡት ዳግማዊ ምኒልክ ናቸው። ይሄን ባቡር ወደ ሀገራችን ለማስገባት በሞከሩት ወቅት ታላላቅ የአውሮፓ ሀገራት በተለይ እነ እንግሊዝ ጣሊያን የከፋ ጫና እያደረጉብን ነበር። የባቡሩን ግንባታም ለማሰናከል እየጣሩ ነበር። ዳግማዊ ምኒልክ ከእያንዳንዱ ግለሰብ በጭራ ገንዘብ ሰብስበው፣ የዓለምን ዲፕሎማሲም በደንብ ተጫውተው ባቡሩን አስቀጠሉት። ከመናገሻቸው ደርሶ የደከሙለትን ባቡር ፍጻሜውን ሳያዩት ቢያልፉም ህልማቸው ግን እውን ሆኗል። ለካ እያንዳንዱ ህዝብ አዋጥቶ የገነባው አባይን ብቻ አይደለም። ለመጀመሪያ ጊዜ ባቡሩንም በዚያ መልኩ ነው የገነባነው። አስራ አምስት ከብት ያለው አንዱን ለሀገሩ እያዋጣ ነው ባቡር የገነባው። እንዲያውም አንዳንዶቹ የከብት ቁጥራቸውን እየቀነሱ አስቸገሩ። ከሁሉም ግን ዘመቻውን ተቃውመው ወደ ጎረቤት ሀገር ማለትም ወደ እንግሊዝና ፈረንሳይ ቅኝ ግዛት እንዳይሄዱ መኖሪያቸውን ቋሚ አድርገው ሃብት እስኪያፈሩ ድረስ የሁለት ዓመት የግብር እፎይታ እንዲሰጣቸው አጼ ምኒልክ የጻፉት ደብዳቤ እንዲህ ይላል። (ደብዳቤ 1243 ይድረስ ከሼህ ሆጀሌ የዘመቻው ጊዜ እየሸሸ ወደ እንግሊዝ አገር የገባው ሰው ሁሉ የሁለት ቀን መጥቶ ተቀበለኝ ብለህ የላክኸውን ደብዳቤ አይቼ ደስ አለኝ። አሁንም የቀረውን ያንተን ሰው ሁሉ በዝግታ እንዲገባ ማድረግ ነው። ደግሞም አገሩ እንዲለማ ለአንድ ዓመትና ሁለት ዓመት ግብሩን አንነካውም። የመጋቢት 3 ቀን 1900 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ተጻፈ (ምንጭ፣ አጤ ምኒልክ በሀገር ውስጥ የተጻጻፏቸው ደብዳቤዎች። በጳውሎስ ኞኞ ገጽ 322)) በዚህ መልኩ በሀገሬው ብርታት በንጉሱም አስተዳደር ባቡሩ እውን ሆነ። ቀልቤን የሳበው ግን ሌላም ነገር አለ። ከዚህ በፊት ታሪክ ላይ ማንበቤን አላስታውስም። ይሄን ክስተት ጸሐፊው ንጉሴ አየለ ተካ በዚህ መጽሐፉ እኝዲህ ይገልጸዋል። “በዚህ ወቅት ያጋጠመ አንድ አስገራሚ ክስተትም ነበር። በወቅቱ በጌምድር ተብሎ በሚጠራው የጎንደር አካባቢና የሰሜን አውራጃዎች ከብቶች በድርቅና በበሽታ አልቀው ስለነበር ንጉሱ ከዚያ አካባቢ የተሰደደው ህዝብ እንዲመለስና እንዲቋቋም በማረሻ ከብቶች እጥረት ሳይታረስ ጦም ያደረው መሬት እንዲለማ ተጨማሪ ዘመቻ ያስፈጽሙ ነበር።” ይላል። (ኦዛና ምኒልክ ገጽ 164) ይሄም ከሌላ አካባቢ ሰዎችን እየወሰዱ በጌምድር ማስፈር ነው። ለዚህም አስረጂ ይሆኑ ዘንድ በወቅቱ ንጉሱ የጻፏቸውን ደብዳቤዎች እንጠቅሳለን። (ደብዳቤ 1186 ይድረስ ከሼህ ሆጀሌ አሊ ሐሰን በጌምድር የሚባለው አገር ከብድ ካለቀ ወዲህ ሳይታረስ ቀርቶ ጠፍ ሆኗል። አሁንም ከብትም ገበሬም ሰድጄ በጌምድርን አቀናለሁ ብያለሁና አንተም ገበሬ የሚሆኑ (የቤንሻንጉል) ሰዎች ከነሚስቶቻቸው ከዘመድህም ከወዳጅህም ፈልገህ እንድትሰድልኝ ይሁን። ቁጥሩን ግን እኔ ይህን ያህል አልልህም። የተገኘልህን ያህል ስደድልኝ። የካቲት 22 ቀን 1900 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ተጻፈ ። (ምንጭ፣ አጤ ምኒልክ በሀገር ውስጥ የተጻጻፏቸው ደብዳቤዎች። በጳውሎስ ኞኞ ገጽ 322)) ሌላ አንድ እንጨምር. . . (ደብዳቤ 1187 ይድረስ ከራስ ወልደ ጊዮርጊስ በጌምድርስ ከብት ካለቀ ወዲህ ሳይታረስ ቀርቶ ጠፍ ሆኗል። አሁንም ከብትም ገበሬም ሰድጄ በጌምድርን አቀናለሁ ብያለሁና አንተም ገበሬ የሚሆኑ መቶ ወንድ (የኦሮሞ ሰዎችህን) ከነሚስቶቻቸው ከዘመድህም ከወዳጅህም ፈልገህ እንድትሰድልኝ ይሁን። ይህንንም መቶ እስቲሞላ አትጠብቅ። የተገኘ የተገኘልህን ቶሎ ቶሎ ስደድልኝ። የካቲት 22 ቀን 1900 ዓ.ም አዲስ አበባ ተጻፈ ። *በዚሁ ቃል ለራስ ተሰማ፣ ለደጃዝማች ጆቴ፣ ለደጃዝማች ገብረ እግዚአብሔር፣ ለደጃዝማች ደምሰው፣ ለአባ ጅፋር፣ ለደጃዝማች ለማ፣ ለደጃዝማች ገብሩ፣ ለአዛዥ ባደግ ተጽፏል። (ምንጭ፣ አጤ ምኒልክ በሀገር ውስጥ የተጻጻፏቸው ደብዳቤዎች። በጳውሎስ ኞኞ ገጽ 323)) እነዚህ ፈቃዳቸውን የሰጡ ሰዎች ቋሚ ህይወት መስርተው እንዲኖሩ ባልና ሚስት መሆን ይገባቸው ነበር። እንዲያውም ከድሃው ህዝብ የሚሄድ ቢጠፋ የሹማምንቱ ዘመዶች እምቢ እንደማይሉ ንጉሱ የተረዱ ይመስላሉ። ከደቡብ፣ ከምዕራብ፣ ከምስራቅና ከመካከለኛው የሀገራችን ክፍል እየተመለመሉ ወደ ንጉሱ ይቀርባሉ። ንጉሱም ጥማድ በሬና ቀለብ ሰጥተው፣ ግብር አብልተው ወደ በጌምድር ይልኳቸዋል። እነዚህ ሰዎች በንጉሱ ትዕዛዝ ሰፍረው፣ ህይወታቸውን መስርተው የልጅ ልጆቻቸውን ተክተው አልፈዋል። ይህ ከመቶ ዓመት በፊት የሆነ ታሪክ ነው። ዛሬ እነ ጥርት ያልሁ ጎንደሬ ነኝ! እኔ ጽድት ያልሁ ጎጃሜ ነኝ።! እኔ ሽቅርቅር ወሎዬ፣ እኔ ምርጥ ትግራዋይ! እኔ ጥርት ያልሁ ኦሮሞ ነኝ! እኔ የበቃሁ የነቃሁ እንዲህ ነኝ እያልን ስንፎክር እገረማለሁ። እንኳን የጥንቶቹን ይቅርና ይሄን በመቶ ዓመት ውስጥ እንዲህ ያለ ታሪክ አለን።

◉ አትፍረድ ! ➊ ይህ «Aattam» (The Play) የተሰኘው የMalayalam ፊልም በተለየ መልኩ እወደዋለሁ። ከራሴ ጋር እንዳወራ አድርጎኛል። ታሪኩ የሚያተኩረው Arangu በተሰኘ የአንድ የቲያትር ቡድን አባላት ዙሪያ ነው። በዚሁ የቲያትር ቡድን ውስጥ ብቸኛ ሴት ተዋናይ አለች። እና ይቺ ሴት ከአንድ ትርኢት በኋላ በተዘጋጀ የምሽት ግብዣ ላይ በቡድኑ ውስጥ ካሉ ወንዶች በአንዱ የጾታ ትንኮሳ ጥቃት ይደርስባታል። ​ድርጊቱ ይፋ ከወጣ በኋላ በቡድኑ ውስጥ ያሉትን 11 ወንዶች ያካተተ አስቸኳይ ስብሰባ ይጠራል። ታሪኩ ሙሉ በሙሉ የሚያተኩረው እነዚህ ወንዶች ጥቃቱን በሰሙበት ወቅት በሚያሳዩት የተለያየ ባህሪና በሚያደርጉት ሙግት ዙሪያ ነው። ወንዶቹ መጀመሪያ ላይ ለሴቷ ሙሉ ድጋፍና አጋርነት ያሳዩ ቢመስሉም፣ ቀስ በቀስ የራሳቸው የግል ጥቅም፣ ዝና እና የሚያገኟቸው የገንዘብ እድሎች ጥያቄ ውስጥ ሲገቡ አቋማቸውን መለዋወጥ እና ጥቃቱን ማሳነስ ይጀምራሉ። ❷ ይህን ፊልም ካየሁ በኋላ በቀጥታ ታዋቂው የሆሊውድ ክላሲክ ፊልም "12 Angry Men" ነው ትዝ ያለኝ። በቅርፅም ሆነ በይዘት እጅግ በጣም የሚቀራረቡ ናቸው። በ12 Angry Men ውስጥ 12 የዳኞች ማህበር አባላት የአንድን ልጅ እጣ ፈንታ ለመወሰን እንደሚከራከሩት ሁሉ፣ በAattam ውስጥም 11 የቡድኑ ወንዶች በአንዲት ሴት ላይ በደረሰው ጥቃት ዙሪያ ይከራከራሉ። በሁለቱም ፊልሞች መጀመሪያ ላይ ሁሉም ሰው በአንድ ወገን የተሰለፈ ቢመስልም፣ ውይይቱና ክርክሩ እየጠነከረ ሲሄድ ግን የሰዎች አቋም እንደ ፍላጎታቸውና ጥቅማቸው ሲዋዥቅና ሲቀያየር ይታያል። ❸ ​Aattam የ12 Angry Menን መዋቅር ቢወስድም የስነ-ልቦና ብርበራውን ከፍ ወዳለ ደረጃ ያሳድገዋል። ወንዶቹ ለሴቷ የቆሙ መስለው፣ በመጨረሻ ግን የራሳቸውን ጥቅም ለማስከበር ሲሉ ተጎጂዋን ዳግመኛ እንዴት እንደሚበድሏት እናያለን። ፊልሙ ሲያልቅ ፍርዱን በቀጥታ ለተመልካች በመተው ነው። ፊልሙ መጨረሻ ላይ "ተጠርጣሪው ጥቃቱን በእርግጥ ፈጽሟል ወይስ አልፈጸመም? ወንዶቹስ ምን ሆኑ?" የሚለውን ፍርድ ቤት ወይም ፖሊስ ዘንድ አድርሶ በቁጥጥር ስር ሲውሉ አያሳየንም። ዳይሬክተሩ ይህንን ያደረገበት ምክንያት ፊልሙ ትኩረት እንዲሰጠው የፈለገው በአንድ ወንጀለኛ ላይ ብቻ ሳይሆን ጠቅላላው ማህበረሰቡ ራሱን እንዲፈትሽና እንዲመለከት ስለፈለገ ይመስለኛል ። ● ፊልሙ ለእኛ የተወልን ጥያቄ ሲመስለኝ ይሄ ነው... ​"አንድ በደል ሲፈጸም፣ ለተበዳዩ የምንቆመው እውነትንና ፍትህን ፈልገን ነው ወይስ የራሳቸውን ጥቅም እስካልነካ ድረስ ብቻ?" የፊልሙ ደራሲ ወይንም አዘጋጅ በታሪኩም ጭምር መፍረድ የፈሩት ክብደቱን ስለተረዱ ይሆናል። ❹ ያው የሰው ልጅ ፍፁም ነፃ (እንደ ነጭ ወረቀት) ሆኖ አይፈርድም። እያንዳንዱ የሚያሳልፈው ውሳኔ፣ ፍረጃ ወይም አቋም ከውስጣችን ማንነት፣ ከኖርንበት ህይወት፣ ካለን ፍርሃትና ከግል ጥቅማችን የሚቀዳ ነው። ለዚህ ነው በህግና በፍትህ ሥርዓት ውስጥ Objective Truth ላይ መድረስ እጅግ ከባድ የሚሆነው። አንድ ዳኛ ፍፁም ፍትሃዊ ለመሆን መጀመሪያ የራሱን ውስጣዊ ጭፍን ጥላቻ፣ ፍላጎትና ስሜት ድል ማድረግ አለበት። ይሄ ደሞ ሲሲፈስ ከዛ አለት ጋር እንደሚታገለው ትግል ሆነ ማለት ነው። ከሰው ልጅ ተፈጥሮ ጋር መታገል ማለት ስለሆነ አስቸጋሪ ነው። ● ከ 12 Angry Men ምሳሌ እንስረቅ ◉ ፊልሙ መገባደጃ ላይ 11ዱም ዳኞች ማስረጃዎቹን አንድ በአንድ እየመረመሩ ሲመጡ "ልጁ ጥፋተኛ አይደለም " ወደሚለው አቋም ይሻገራሉ። መጨረሻ ላይ የቀረው ብቸኛው ሰው ዳኛ ቁጥር 3 ይሆናል። "Not Guilty" ለማለት ያንቀዋል። ልጁ እንዲሰቀል ነበር የፈለገው። እስከመጨረሻው ሰከንድ ድረስ በንዴትና በእልህ ልጁ ጥፋተኛ ነው እያለ ይሞግታል። ነገር ግን መጨረሻ ላይ በንዴት ውስጥ ሆኖ የራሱን ልጅ ፎቶግራፍ ከኪሱ አውጥቶ ሲቀደው ሽሽግ ምስጢሩ ይገለጣል። ዳኛው ልጁን ሊቀጣ የፈለገው ከራሱ ልጅ ጋር ባለው የግል ጠብና ቂም ምክንያት እንደነበረ ይረዳል። በራሱ ስሜት ተሸንፎ ስቅስቅ ብሎ ካለቀሰ በኋላ "ጥፋተኛ አይደለም!" ብሎ ድምፁን ይሰጣል። በዚህም 12ቱም ዳኞች በአንድ ድምፅ ልጁን ነፃ ያደርጉታል። ❺ ​ “አትፍረድ ይፈረድብሃል!” የሚለው አባባል በትክክልም የሰው ልጅን ጉድለትና የስነ-ልቦና ሀቅ የሚፈትሽ መርህ ነው። በአንድ ሰው ላይ የምንሰነዝራት ፍርድ ወይም የምንወረውራት ትችት ስለ ተከሳሹ ሳይሆን ስለ እኛ ውስጣዊ ማንነት የሚናገረው ነገር ይበልጣል። በ12 Angry Men ላይ ያለው ዳኛ በተከሳሹ ልጅ ላይ በጭካኔ ሲፈርድ የነበረው በራሱ ህይወት ውስጥ ካለው ቁስልና ቂም የተነሳ እንደነበረው። መፍረድ ከባድ ነገር ነው። ምክንያቱም እውነተኛ ፈራጅ ለመሆን መጀመሪያ ከራስ ጥቅም፣ ከራስ ስሜት፣ ከራስ ታሪክና ጥላቻ ነፃ መሆንን ይጠይቃል። አለዚያ አንዷን ጣት ስትቀስር አራቱ ወደ ራስ ያመለክታል እንደሚባለው ይሆናል። ባጭሩ ሁለቱም ፊልሞች የሚያሳዩን በሸንጎ ስለሚቆሙት ተከሳሾች ሳይሆን፣ በፈራጆቹ ወንበር ላይ ተቀምጠን ስለምንፈርደው ስለ እኛ ማንነት ነው። ▭▭ © Mes Oud

የሆነው ሁሉ ሁኖ መጨረሻ ላይ ሕሊና አዕምሮን ፈልጋ ስትሔድ በሩን ዘግተው ሊያስቆሟት የሚሞክሩት እኒያው ደባል ሱሶቹ ነበሩ። የዚያኔ ግን ድክመቷን ብቻ ሳይሆን ድክመቶቹንም ጠንቅቃ ስለተረዳች ማናቸውም ሊያስቆሟት አልቻሉም። የወይን አበባዬ 📯 የወይን 🎶 © Mickael Azmeraw

የወንዶች ጉዳይን ከሳቅ በዘለለ መረዳት የሚፈልግ አንድም ጤነኛ ሰው ያለ አይመስለኝም። እኔ ግን ጤና ስለሚጎለኝ የወደድኩትን ነገር እስክጠላው ድረስ መጎርጎሬን አላቆምም። የመጀመሪያው ጥያቄዬ "ደራሲው የዋና ገፀባሕሪዎቹን ስም አዕምሮ እና ሕሊና ያለው ባጋጣሚ ነው?" የሚለው ነበር። በርግጥ ይሕ ጥያቄ ብቻውን ወደ ሌላ አለም ይወስደኛል ብዬ አላሰብኩትም። ምክኒያቱም ሌሎች ደራሲዎች እንዲህ አይነት ነገር የሚያደርጉት ከላይ ሲታይ ደስ ስላላቸው ብቻ ነው የሚሆነው። አድማሱ ግን የደበቀውን ታሪክ እንድናገኝበት ያስቀመጠልን ካርታ ነበር። ፊትለፊታችን ሁኖ የተሰወረው ስቶሪ ባጭሩ ይሕ ነው። አዕምሮ ውስጣዊ ሰላም ለማግኘት ሲል ሕሊናውን እየዋሻት ነው። እንዲዋሻት የሚተባበሩት ደግሞ ስድስት ደባል ሱሶች አሉበት😃 ላይሆን ይችላል...ይሕ ቲዎሪ ብቻ ነው። እስከሚያስኬደን ድረስ እንሒድበት🙂 ወዳጆቹ...እስከጥግ የሚገዙለት አንድ ነገር አላቸው። አንደኛው ያገኘውን የሚያገበሰብስ ሆዳም ነው። አንደኛው አላፊ አግዳሚውን የሚያስረግዝ ዘማዊ ነው። አንደኛው ሰርግ ቤት ሳይቀር ከመለኮስ የማይመለስ አጫሽ ነው። አንደኛው ከሰከንድ በፊት ያገኛትን ሴት ቂጧን ካልጨበጥኩ የሚል ሴሰኛ ነው። አንደኛው እቁብ ሲወጣለት ልብስ ልግዛ ሶፋ ልቀይር ሳይሆን "ዛሬ ይጠጣል!" የሚል ጠጃም ነው። አንዳቸውም በሰውነታቸው ላይ ሀይል የላቸውም። ህይወታቸው በሱሳቸው ዙሪያ ነው የሚያጠነጥነው። ሱሰኛ ብቻ ሳይሆን ሱስ ራሱ ናቸው። ግን አትጠሏቸውም። በጣም ነው የሚያዝናኑት። ሲጫወቱ ለምናያቸው ለኛ "ጓደኞቼ በሆኑ!" የሚያስብሉ ናቸው። ያው ሱስ ሱስን ይወዳልና አንድ ላይ ሰብሰብ ብለው የመሰረቱት ማሕበርም አላቸው። የዚህ ማሕበር አስተባባሪ እና ዋና ፀሀፊ ቀጮ ነች። ቀጮ እንደሌሎቹ ሱስን አትወክልም። "ታዲያ ሱስ ካልሆነች ሱሶችን የምትሰበስባቸው እሷ ማነች?" ልትሉ ትችላላችሁ። ቀጮ ማለት ሴት ሁና ሳለ ራሷን እንደ ሴት የማታይ ሰው ነች። "ሴቶች" እየተባለ ሲወራ እንኳን እኔን ይመለከተኛል ብላ አትሰማም። ለዛም ነው ወንዶች ሴቶች ላይ ለሚፈፅሙት ተንኮል ተባባሪ ሁና የምትገኘው። ያ ማለት ግን ሴቶችን ትንቃለች ማለት አይደለም። የምትንቀው ራሷን ነው። አዕምሮን ስትመርቅ እንኳን "ቀጠን ያለችዋን፤ እንደ እንዝርት ተሽከርካሪዋን፤ እንደ ዳር ተወርዋሪዋን ያጋጥምህ!" ነው የምትለው። የሷ ምርጥ ሴት...እሷን የማትመስል ነች። ስለዚህ የነዚህ ሱሶች ሰብሳቢ የወረደ በራስ መተማመን ያላት እና ከተቃራኒ ወገን ተሰልፋ የምትዋጋ ፍጡር መሆኗ ስሜት ይሰጣል። ሱሶችን የሚጠራቸው ይሔ አይነቱ ራስ ጠልነት ነው'ና! (ቀጮ Insecurity ነች እያልኩ ነው ምዕመናን😭) አዕምሮም ወደነሱ የተሳበው በዚችው ጎኑ ነው። ማሕበራቸውን እንዲቀላቀል ያላደርጉት ጥረት አልነበረም። አንዱም አልሰራም። የሚወዳት ፍቅረኛው ከውጭ ለመጣ ሰው ጥላው መሔዷም ለሽንፈት አላበቃውም። ከዛ በፊትም ብዙ ሴት ጋ ተለያይቷል። ብርቁ አይደለም ፍቅሩን ማጣት። ለሽንፈት ያጋለጠው ከመሔዷ በፊት የጣለችበት ንግግር ነው። "አንተን ብዬ መቼም ከምመኛት አሜሪካ መቅረት አልችልም!!!" 😃 ይሕ ንግግር ጥላቻም የለውም። ርሕራሔም የለውም። ምርር ያለ እውነት ብቻ ነው። ይሔንን እውነት ለመዋጥ አዕምሮን Pride ያንቀዋል። ያጥወለውለዋል። ስራ ትቶ መኝታ ላይ ይውላል። የዚያኔ ማሕበርተኞቹ ደም እንዳሸተተ ሻርክ ተቀላቀለንና ከሀዘንህ እናድንህ እያሉ ይዞሩታል። የደረሰበትን ሽንፈት እምደሚያስረሱት ደጋግመው ቃል ይገቡለታል። መፍትሔው ያለው በነሱ እጅ እንደሆነ ጨቅጭቀው ያሳምኑታል ልክ ሁነውም ይገኛሉ። በአጭር ጊዜ ውስጥ ከወደቀበት ተነስቶ መሳቅ መጫወት ይጀምራል። ሕሊናውን ከመዋሸት ቢሆንም ደስታው የተገኘው ከነበረበት መጥፎ ስሜት አንፃር ይሔ አስር እጥፍ የሚሻል መንገድ ይሆንለታል። "አሁንማ እንከባከብሀለን ቅድም እኮ ቅጥል ነው ስታደርገን የነበረው!" እያሉ የበለጠ ሰምጦ እንዲገባ ያበረታቱታል። ውሸቱ እንዲሰራ መንገዱን ያሳልጡለታል። ፅዋ ያነሱለታል። እጃቸውን ጭነው ይመርቁታል። ሁሉም ነገር አልጋ ባልጋ ይሆናል። ችግሩ ይሔንን ስሜት ለማስቀጠል ሁሌም ጧት ተነስቶ አንድ አዲስ ውሸት መዋሸት አለበት። ዛሬ አለቃውን አታልሎ ከስራ የቀረ እንደሆነ ነገ ደግሞ የእህቱን ሽቶ ሰርቆ ቤቱን መበጥበጥ ይኖርበታል። ደባል ሱሶቹ ለሚሰጡት ደስታ በምላሹ ከሱ የሚጠይቁት ሕሊናን እንዲተኛት፤ በውሸት አለም ውስጥ እንዲያባክናት...ባጭሩ Corrupt እንዲያደርጋት ነው። እንደመጀመሪያዎቹ ጊዜያትም ቶሎ ቶሎ አይስቁለትም። በሆነ ባልሆነው ነው የሚነጫነጩበት። "ታዲያ አዕምሮ ይሔ ሁሉ ውሸት ውስጥ ሲዋኝ ሕሊና እንዴት መጠርጠር ይሳናታል?" የሚለው ሁለተኛው ጥያቄዬ ነበር። እንግዲህ አዕምሮ የምናዬው የምንዳስሰው የማሰቢያ ማሽን ነው። ይሕን ማሽን የሚጠልፉትም የምናያቸው የምንዳስሳቸው አደንዛዥ ዕፆች ናቸው። ሕሊና ግን የማናያት፤ 'ማንዳስሳት...አዕምሯችንን እየወቀሰች በትክክለኛው መንገድ እንዲሔድ የምታስገድደው ስውር አለቃችን ነች። ህሊናን ሱስ አያሸንፋትም። እሷን ሚጠልፋት እንደሷ ለማዬት ለመዳሰስ የሚከብደው ዲያቢሎስ አልያም እርኩስ መንፈስ ነው። ሸዊት የምትጫወታት ገፀባህርይ (ማርታ) የምትወክለው ይቺን ከሕሊናችን ጆሮ ላይ የማትጠፋውን አንሾካሿኪ ድምፅ ነው🙂 ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ለአዕምሮ ውሸቶች የምትማልለው እሷ ነች እንጂ ሕሊና አልነበረችም። በፍቅሩ ተይዛለች። "ሶፋ ብናስቀይረው፤ ወርቅ ብናስገዛው" እያለቻት ነው ጆሮዋ ላይ ቁማ። ሐሳቧን ውድቅ እንዳታደርግባት ደግሞ ለቤተሰባችን ስንል ነው እያለች ታግባባታለች። ቤት የጋበዘችው ቀን ሶፋቸው መበላሸቱን ነግራ ልታስገዛው ስትሞክር አዕምሮ "እሰራዋለሁ!" ብሎ መዶሻ ነገር ፍለጋ ይገባል። ማርቲ አመዷ ቡን ብሎ "ምንም ነገር የለንም...ጎረቤትም የላቸውም!" ስትለው ሕሊና ተነስታ ከጠረንጴዛው ስር የተቀመጠውን ዘነዘና ትሰጠዋለች። የአዕምሮ እውነተኛ ማንነነቶች ፈንቅለውት በሚወጡበት ቅፅበቶች ሁሉ ሕሊናን ይማርካታል። በተቃራኒው ማርታን ያቅለሸልሻታል። ሁለቱ ያለ ሶስተኛ ወገን ብቻቸውን ሲገናኙ የሆነ ደስ የሚል ነገር አላቸው። አንዳቸው ላንዳቸው ነው የተፈጠሩት ያስብላሉ። መዋደዳቸውም ያስቀናል። ነገር ግን መሰረቱ ወሸት ላይ ነው'ና ሒሳቡ ሳይወራረድ ግኑኝነቱ ሊፀና አይችልም። አዕምሮ መቼም መቼም መቼም ቢሆን ከገባበት ክብ መውጣት አይችልም። ከገባበት ክብ ልታወጣው የምትችለው ሕሊናው ብቻ ነች። እሷ ደግሞ እሱን ማውጣት እንድትችል በቅድሚያ ጆሮዋ ላይ ያለችውን መንፈስ ጠንቅቃ መረዳት ይኖርባታል። መረዳት ብቻ ሳይሆን ንቃ መተው መቻልም አለባት። ያን ማድረግ እንድትችል መንፈሳዊ እገዛ ትፈልጋለች። ለዛ ነው የቤተክርስቲያኑ ትዕይንት ትክክለኛ ቦታ ላይ ገብቷል የምለው። አዕምሮ እንደልማዱ "ጌታዬ ውሸቴን የማስቀጥልበት ገንዘብ ስጠኝ!" አይነት ፀሎት ይፀልያል። እሷ ግን እውነቱን መኖር እንዲጀምሩ ነው የምትማፀነው። ጌታም የሕሊናን ልመና ሰምቶ የጠዬቀችውን ብርታት ይሰጣታል። ማርታ ያስጀመረቻትን ድራማ ትታ ሀቁን በማፍረጥረጥ አዕምሮን ከገባበት ስካር ታባንነዋለች። ነፍሱ ስትያዝ ይናዘዛል። መክፈል ያለበትን የንስሀ ዋጋ ይከፍላል። እውነቱን ማውራት ሲጀምር እሷም እንዳዲስ እየወደደችው ትመጣለች።

መብለጥ አያኩራራም፤ መበለጥ አያሳምምም! (The Mind Under Comparison) (እ,ብ,ይ.) ሰው ሁሉ እኩል አይደለም፡፡ ሰው ከሰው የሚለያይበት ብዙ ነገር አለው፡፡ ተፈጥሮ አንድዓይነት ቢሆን ያሰለቻል፡፡ የስምንት ቢሊየን ህዝብ ፊት የተደጋገመ ቢሆን ኖሮ ሰውን ከሰው መለየት አዳጋች ይሆን ነበር፡፡ ፈጣሪ ይህቺን ዓለም የሰራት በልዩነት ጥበብ ነው፡፡ ልዩነት ለዘላለም ይኑርና መንታዎች እንኳን ከአንድ እንቁላል ተፈጥረው በሁሉም ነገር አንድ አይሆኑም፡፡ አምላክ የእናትን ሆድ ዥጉርጉር ያደረገው ልዩነት ጥበብ ብቻ ሳይሆን ውበትም ጭምር ስለሆነ ነው፡፡ ሰው በመልኩ፣ በቁመቱ፣ በአስተሳሰቡ፣ በፀጋው፣ በዝንባሌው፣ በፍላጎቱ፣ በብርታቱ፣ በምኞቱ፣ በግቡ፣ በዕቅዱ፣ በዓላማው፣ በአፈፃፀሙ፣ በምግባሩ፣ ወዘተ በብዙ ነገሩ አንድ ዓይነት ስላልሆነ ሊበላለጥ ይችላል፡፡ አንዱ ካንዱ የሚያንስበትና የሚበልጥበት ብዙ ነገር አለው፡፡ እሱ ያለው፤ ሌላው የሌለው፤ ሌላው ያለው እሱ የሌለው የትየለሌ ነው፡፡ አንድ ከሚያደርገን ይልቅ የምንለያይበት ነገር እልፍ ነው፡፡ አካላችን ቢመሳሰልም አስተሳሰባችን ለየቅል ነው፡፡ ማፍቅርና መፈቀር መፈለጋችን፣ ከምንወደው ስንለይ ማዘናችን፣ መራብ መጠማታችን፤ መጥገብ መፈንጠዛችን፣ ማጣት ማግኘታችን፣ የመሳሰሉት ተፈጥሯዊ ስሜቶቻችን ሁሉ የጋራ ፀጋዎቻችን ቢሆኑም እነሱን የምንተረጉምበት መንገድ ግን እንደአኗኗራችን፣ እንደአስተዳደጋችን፣ እንደአስተሳሰባችንና እንደልምዳችን የተለያየ ነው፡፡ ከሁሉም እበልጣለሁ ወይም ክሁሉም አንሳለሁ ብሎ ማሰብ ሁለቱም ስህተት ነው፡፡ የምናንስበትና የምንበልጥበት ጉዳይ መኖሩን መረዳት ነው ባነስንበት ጉዳይ እንድንሻሻልና በበለጥንበት ደግሞ እንድንበረታ የሚያደርገን፡፡ የትኛውም ሰው በሁሉም ነገር አንደኛ አይሆንም፤ በሁሉም ነገርም መጨረሻ አይወጣም፡፡ ማንም ማነፃፀሪያውን ሌሎች ሰዎችን ካደረገ በሰው መስፈርት ነው ራሱን የሚለካው፡፡ ከሰዎች ተሞክሮን መውሰድ፣ አዲስ ሃሳብ መማር ብልህነት ነው፤ ቁጭ እነሱን ለመሆን መሞከር ግን ድንቁርና ነው፡፡ ሰው ራሱን እንጂ ሌላውን ልሁን ቢል አይችልም፡፡ ሌላውን ለመምሰል መታገል ራስን መጥላት ነው፡፡ ራሱን የሚወድ ሰው ራሱን ነው የሚሆነው፡፡ ለዚህ ነው ኦስካር ዋይልድ “ በፍቅር ውስጥ መሆን ማለት ራስን ማሽነፍ ማለት ነው (To be in love is to surpass one’s self) ” የሚለን፡፡ ሌሎችን ለመብለጥ ደፋ ቀና የሚል ሰው የራሱ መለኪያና መስመር የለውም፡፡ የሌሎች መስፈርት ጥገኛ ነው፡፡ በራሱ ላይ ትክክለኛ ለውጥና እድገት የሚፈልግ ሰው ግን ከሌሎች መስመር ነጻ ነው፡፡ ዓላማችን ሌሎችን መብለጥ፤ ግባችን ሌሎች ላይ የበላይ ለመሆን ከሆነ እውነተኛ ደስታ አናገኝም፡፡ ሌሎችን በመብለጥ የምናገኘው ደስታ እኛም በሌሎች ስንበለጥ ደስታችን ወደሀዘን ይለወጣል፣ ዓይናችን ደም ይለብሳል፤ የሌሎች ማግኘት የእኛ መውደቅ ይመስለናል፡፡ አርስጣጢሊስ “ድላችን ሌሎች ላይ የበላይ ለመሆን ከሆነ መቼም ቢሆን አሸናፊ መሆን አንችልም፡፡ እውነተኛ ስኬት ሌላ ሰውን መብለጥ ሳይሆን ራስን መብለጥ ነው፡፡” ይላል፡፡ ኤፔኪቲተስ ደግሞ “ሌሎችን ለመብለጥ እና በሌሎች ዘንድ ተቀባይነት ለማግኘት ስንል የምናደርገው ነገር መጨረሻው ህመም ነው የሚያመጣብን፡፡” ሲል ጤናማ ውድድር ከራስ ጋር የሚደረግ ስለመሆኑ ይናገራል፡፡ ለዚህ ነው አለማየሁ ገላጋይም በ”ፈሪሳ” መጽሐፉ ገጽ 44 ላይ “መበለጥ የሚያሳምመውን ያህል ታመምኩ፡፡” በማለት በመበለጥ የሚሰቃዩ እንዳሉ የሚነግረን፡፡ በመበለጡ የሚታመም ሰው በቀላሉ ተስፋ ይቆርጣል፤ “አይሆንልኝም፣ ከሌሎች አንሳለሁ፣ አልችልም” እያለ ራሱን ወደኋላ ይጎትታል፡፡ የተሰጠውን ፀጋ ፈልጎ አያገኝም፡፡ የራሱን ትቶ የሌላውን ይመኛል፡፡ በርግጥ መበለጥ ሁሉ አሉታዊ ስሜት አለው ማለት አንችልም፡፡ በአግባቡ መበለጡን የሚተረጉም ሰው ከሌሎች ተሞክሮ በመውሰድ ለመሻሻልና ራሱን መስመር ለማስያዝ ይጠቀምበታል፡፡ ፍሬደሪክ ኒቼ “መበለጥ ከፉ ቅናትን ወይ ደግሞ ለማደግ የሚሆን ቆስቋሽ ስሜትን ይፈጥራል” የሚለው አተያያችን አጥፊም ሆነ አልሚ ስሜትን እንደሚያዋልድ አፅንኦት ለመስጠት ነው፡፡ መበለጡን በመልካም ቅናት ለተመለከተው ሰው ከበለጠው ሰው ትምህርት በመቅሰም ራሱን ለመለወጥ አቅጣጫ ያገኝበታል፡፡ ግለሰቡ መበለጡን እንደመስታወት ራሱን የሚመለከትበት ከሆነ ክፍተቱን በማወቅ፣ የጎደለውን በመረዳት መበለጡን ለበጎ ዓላማ ይጠቀምበታል፡፡ በተገቢው መንገድ ከመነዘርነው መልካም ቅናት ቁጭትን በማዋለድ አዲስ መንገድ ያስገኛል፡፡ ወዳጄ ሆይ..... ሁለት ሰዎች ስለአንድ ነገር ያላቸው አመለካከት አንድ አይሆንም፡፡ አንዱ ከእሱ የሚበልጠውን ነገር ሲያይ “ይሄን ነገር እኔ ላደርገው አልችልም፤ ብቁ አይደለሁም” ብሎ በተሸናፊነት ስሜት እያሰበ ራሱን ዝቅ ያደርጋል፤ ሌላኛው ደግሞ “የሌሎች ስኬት እኔም ከጣርኩ ላሳካው የምችለው ነገር ነው”” ብሎ በጎ በጎውን አስቦ ጥረት ይጀምራል፡፡ ጨዋታው ያለው የእያንዳንዳችን አሰተሳሰብ ላይ ነው፡፡ መበለጥን በቅን ዓይን ከተመለከትነው አዎንታዊ ለውጥ ያመጣል፡፡ በተቃራኒው ካየነውም ሁሌ በሰው ስኬት አንጀታችን ሲቆስልና ዓይናችን ደም ሲለብስ ይኖራል፡፡ መብለጥ አያኩራራም፤ መበለጥ አያሳምምም! መቀደም አያናድድም፤ መቅደምም አያስኮፍስም፡፡ ሌሎች በሁሉም ነገር ከአእኔ ያንሳሉ ብለህ በአንዲቷ ስኬትህ አትመካ፤ አንተም ከሌሎች የምታንስበት ብዙ ነገር መኖሩን አትዘንጋ፡፡ ተበልጫለውም ብለህ አትታመም፡፡ መበለጥህን ራስህን እንደማንቂያ ደወል ተጠቀምበት፡፡ ከፍ ያለ ስኬት በትናንሽ ስኬቶች እውን መሆን እንደሚጀምር ተረዳ፡፡ ቸር መበለጥ! ደግ መብለጥ! ------------------------------------ © እሸቱ ብሩ ይትባረክ (እ.ብ.ይ.) ሠኞ ሠኔ ፳፪ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም.

◉ Death in Tehran ➊ አጭሯ ተረት በአጭሩ ​«በአንዱ ቀን አንድ ታላቅ የፋርስ ንጉስ በቅንጦት መናፈሻው ውስጥ እየተዘዋወረ ሳለ፣ በድንገት አንድ ትልቅ የጩኸት ድምፅ ይሰማል፤ ወዲያውኑም በፍርሃት የራደ አገልጋዩ እየሮጠ ይመጣል። ​አገልጋዩም “ንጉስ ሆይ! እርዳታዎትን እሻለሁ! እዚህ መናፈሻ ውስጥ እየሰራሁ ሳለ «ሞትን» አገኘሁትና ሩሄ እስክትወጣ አስፈራራኝ። አምልጬ መምጣት የቻልኩ ቢሆንም፣ ለአንዲት ነፍሴ እጅጉን ፈርቻለሁ። እባክዎ ከፈረሶችዎ መካከል ፈጣኑን ይስጡኝ፤ እስከ ምሽት ድረስ ወደ ቴህራን ከተማ ገስግሼ መድረስ አያቅተኝም። ከዚያ በኋላማ ምን አለ? አመለጥኩ ማለት አይደለም? እዛ ሂጄ እደበቀዋለሁ” አለው። ​ንጉሱም ለጥቂት ጊዜ አሰበበት። ንጉሱ ካሳ ቢሆን አገልጋዩ ገብርዬ ነበር ለሱ። የታማኝ አገልጋዩን የብዙ ዓመታት መልካም ግብሩን መዘነና ፈቀደለት። ፈረሱንና ጥቂት ፈረንካም አከለለት። አገልጋዩ ፈረሱን እየጋለበ ሲሄድ የሚሰማውን የኮቴ ድምፅ እያደመጠ ንጉሱ በመናፈሻው ውስጥ መጓዙን ቀጠለ። በመሀል ንጉሱ ራሱ ያንን «ሞት» የተባለውን ጉድ አገኘው። ​ንጉሱም “አገልጋዮቼን ለምን አስፈራራሃቸው?” ሲል ጠየቀው። ​ሞትም እራሱን እየነቀነቀ (ወይም እንደ ዱርዬ ራሱን እያከከ) “አፉ ይበሉኝ ጌታዬ፣ ከሀቅ እኔ ያንን ሰው አላስፈራራሁትም። ዛሬ እዚህ የእርስዎ መናፈሻ ውስጥ ሳገኘው የተሰማኝን ግርምት ብቻ ነበር የገለፅኩት” ሲል መለሰ። ​ንጉሱም ቀጠል አድርጎ “ የኔ አገልጋይ እዚህ መገኘቱ እንዴት አስደነቀህ?” ብሎ ጠየቀ። ​ሞትም ፈገግ ብሎ መለሰ፤ “ ንጉስ ሆይ፣ እዚህ እሱን በማግኘቴ የተገረምኩት እኮ... ዛሬ ምሽት ቴህራን ውስጥ አብረን እንድንገናኝ ቀጠሮ እንዳለን ስለማውቅ ነው!” ❷ በተለያዩ እረኞች የተራባው ተረት ይሄ Death in Tehran" የተሰኘው ተረት በአለም አቀፍ ደረጃ በተለያዩ ስሪቶች የሚታወቅ ተረት ነው። ታሪኩ በተለያዩ እረኞች ተራብቷል። ሀሳቡ በአጭሩ «ከእጣ ፈንታ ወይም ከሞት ማምለጥ አይቻልም» የሚል ፍልስፍና አለው። አገልጋዩ ከሞት ለመሸሽ ወደ ቴህራን ሲጋልብ፣ ሳያውቀው ለካ ራሱ ወደ ቀጠሮው ቦታ እየሄደ ነበር። ​ምንም እንኳን የፅሁፉ ባለቤት Anonymous ተብሎ ቢቀመጥም ይህ ታሪክ ሲበዛ እድሜ ጠገብ ነው። መጀመሪያ አካባቢ በሱፊ ፍልስፍና ውስጥ በሰፊው የሚነገር ነበር ይላሉ። ታዋቂው ፋርስ ባለቅኔ Rumi ተመሳሳይ ይዘት ያለው ታሪክ "The Man Who Fled from Azrael" በሚል በግጥሞቹ አካቶታል። ይህ ታሪክ በምዕራቡ ዓለም በብዛት የሚታወቀው ደግሞ በደራሲ Somerset Maugham አማካኝነት ይመስለኛል። "The Appointment in Samarra" በሚል ርዕስ ባካተተው ስራው። ይህን ታሪክ ወዳጄ አገኘሁ አርባ «ሳማራ ላይ አለኝ ቀጠሮ» በሚል ርዕስ "አጫጭር ልቦለዶች ትርጉም" በሚለው የቴሌግራም ገፁ ላይ ለጥፎት አንብቤዋለሁ። ይህንኑ ተረት ትንሽ ለየት አድርገው መዝግበው ያስተላለፉ ሌሎች ሰዎችም ሊኖሩ ይችላሉ ልክ እንደ "Death in Tehran" ። ይህ ታሪክ በጥንታዊው የአይሁድ መጽሐፍ የባቢሎን ታልሙድ ላይም መቼቱን በጠቢቡ ሰሎሞን ቤተ መንግሥት አድርጎ ተከትቧል። ብቻ ይህ ታሪክ በተለይ በስነ-ፅሁፍ፣ በፊልሞች እና በፍልስፍና ውይይቶች ላይ የሰው ልጅ ስለ ህይወት፣ ስለ ጊዜ እና ስለማይቀረው ሞት ያለውን ግንዛቤ ለማሳየት በተደጋጋሚ ጥቅም ላይ ይውላል። ❸ እጣ ፈንታና ነፃ ፍቃድ ይህ ታሪክ እጅግ በጣም አሳማኝ የሆነ ምሳሌያዊ አተራረክ ስላለው፣ ታሪኩን ካነበብኩ በኋላ በእጣ ፈንታ ላይ እምነት ሳሳድር ራሴን አገኘዋለሁ። እኔ በ Free Will የተጠመቅኩ መስሎኝ። ​ምክንያቱም አገልጋዩ ከሞት ለማምለጥ ያደረገው ጥረት ሳያውቀው ወደ ሞት ደጃፍ የሚያደርሰው መሆኑን ሳይ በውስጤ «የአደም ልጅ የቱንም ያህል ቢጥር የተከተበለትን ነገር መለወጥ አይችልም" የሚል ሀሳብ ወደ አእምሮዬ ይሰርጋል። ​የምርም በህይወታችን ውስጥ የቱንም ያህል ብናቅድ፣ ብንጠነቀቅ እና በነጻ ፈቃዳችን ለመወሰን ብንሞክር፣ ሙሉ በሙሉ ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ነገሮች አሉ። የምንወለድበት ቦታ፣ ድንገተኛ አደጋዎች፣ አጋጣሚዎች ህይወታችንን በቅፅበት ሲቀይሩት እናያለን። ይህ ሲሆን ደግሞ ታሪኩ ይበልጥ ሀቀኛ መስሎ ይሰማኛል። ❹ የቪክቶር ፍራንክል ምሳሌ ይቺን ቁራጭ ታሪክ ፎቶ አንስቶ የላከልኝ ጓደኛዬ ሚሊየን ነው። ያገኘውም ከViktor Frankl መፅሐፍ "Man's Search for Meaning" ላይ ተካቶ ነው። ፍራንክል በናዚ ማጎሪያ ካምፖች ውስጥ በነበረበት ወቅት የደረሰበትን መከራና የታዘበውን የሰው ልጅ ስነ-ልቦና ሲተነትን፣ የምርም ይህንን ታሪክ ማካተቱ የግድ ነበር ብያለሁ። ​ምክንያቱም በካምፑ ውስጥ የነበሩ እስረኞች በየቀኑ የህይወትና የሞት ውሳኔዎችን መጋፈጥ ነበረባቸው። እስረኞቹ እጣፈንታቸውን በራሳቸው እጅ ለመለወጥ በሚያደርጉት ድንገቴ ምርጫ፣ ሳያውቁት ራሳቸውን ወደ ሞት አፍ ውስጥ ሊከቱ እንደሚችሉ ለማሳየት ፍራንክል ይህንን ታሪክ ተጠቅሞበታል። ​ፍራንክል በታመመበት ካምፕ ውስጥ እያለ ከአንድ ጓደኛው ጋር ሆኖ የማምለጥ እድል አግኝቶ ነበር። ነገር ግን በካምፑ ውስጥ ያሉትን የቆሰሉና በታይፈስ በሽታ የሚሰቃዩ ህመምተኞችን ጥሎ መሄድ ህሊናው ስላልፈቀደለት፣ ላለማምለጥና ከእነሱ ጋር ለመቆየት ወሰነ። ​በኋላ ላይ ምን ሆነ? እሱ ያመለጠ መስሎት በዝውውሩ የሄደውና ለማምለጥ የሞከረው ጓደኛው በጥፋት ካምፕ ውስጥ ህይወቱ አለፈ። ፍራንክል የቆየበት ካምፕ ግን ከጥቂት ቀናት በኋላ በዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ድርጅት ነፃ ወጣ። ፍራንክል ይህንን ታሪክ በመጽሐፉ ውስጥ የጠቀሰው በእጣ ፈንታ ላይ ሙሉ በሙሉ ተስፋ ቆርጠን እጃችንን እንድንሰጥ አይመስለኝም። በህይወታችን ውስጥ የምናደርጋቸው የድንጋጤ እና የፍርሃት ውሳኔዎች አንዳንድ ጊዜ ዋጋ እንደሚያስከፍሉን ለማሳየት ይመስለኛል። "ተይው መልሱን መጀመሪያ ጥያቄው ይግባሽ!" እንዳለው ያ እያዩ ፈንገስ እኔ አሁን Free will እና Destiny ነቅፌና ደግፌ ልከራከር አይደለም። ​ብቻ ይቺ ሚጢጢ ታሪክ የሰው ልጅ ሁልጊዜም በነጻ ፈቃድ እና በማይቀረው እጣ ፈንታ መካከል ያለውን ሚዛን ለመረዳት የሚያደርገውን ዘላለማዊ ትግል ታሳየኛለች። ▭▭ © Mes Oud

Wiesel ይህንን አስደንጋጭ ትዝታ ለዓመታት በልቡ ይዞት ቆይቷል። ታሪኩን በረጅም ልብወለድ፣ በተራ ተውኔት፣ በግጥም መልክ ሊጽፈው ቢሞክርም አልሰካለትም። በመጨረሻም ክስተቱን ከነበረበት የቅርብ ጊዜ ዘመን አውጥቶ፣ በታሪክ ወደኋላ በመመለስ በ1648-49 በዩክሬን ከተካሄደው አስከፊ የአይሁድ ጭፍጨፋ በኋላ እንዳጋጠመ አድርጎ በ tragic farce መልክ ጻፈው። Wiesel ይህን የልጅነት ገጠመኙን ከማስታወስም ባለፈ፤ ፈጣሪን መሞገት ከጥንትም የነበረ እንደሆነ በገፀባህሪዎቹ በኩል ሲያስረዳን እናገኛለን። አገልጋይቱ ማርያ ከተዋንያኖቹ ጋር የምታወራው ወግ ይህንን ያጠናክራል። ◦ ​MARIA- He wants to hold a trial. A real trial, with judges, a prosecutor, and a defense attorney. And the defendant will be God. ◦ ​AVRÉMEL- He is crazy. ◦ MENDEL- No, he is not crazy. It is an old Jewish tradition. From the time of Abraham, from the time of Job. We have always argued with God. ❹ ክህደት ሳይሆን የጠበቀ እምነት... መጽሐፉ ፈጣሪን ቢከስም፤ ዓላማው ግን "ጌትዬው የለም!" ማለቱ አይደለም። የ Atheism ስብከት አይደለም። ፕሮፌሰር ሮበርት ማካፊ ብራውን በመጨረሻው ገጽ ላይ እንደሚያብራሩት "ከፈጣሪ ጋር መጣላትና መከራከር ይቻላል፤ ዋናው ነገር ግን እሱን አለመካድና በዝምታ ቸል ብሎ አለማለፍ ነው" ይላሉ። እውነተኛ እምነት ጌትዬውን በግልጽ መጋፈጥና መጠየቅ መሆኑን ያሳያል ቴአትሩ ይላሉ። አዝኖ፣ ተከፍቶና የመጣውን በዝምታ አሜን ብሎ መቀበል ሳይሆን፣ በፍትሕ እጦት ላይ ድምፅን ማሰማት ሃይማኖታዊ ግዴታ ነው። እንደ Wiesel እይታ እውነተኛው ክፋት፤ መከራን እያዩ ዝም ማለትና ግድየለሽ መሆን ነው። ልክ ዛሬ ዝም እንዳልነው። Wiesel በመጽሐፉ ታላቅ የሞራል ኃላፊነትን ጥሎ ነው የሚያልፈው። «ሰዎች Divine injusticeን ወደ ሰውኛ ፍትሕ፣ ወደ ርህራሄ የመቀየር ኃላፊነት አለባቸው» ነው የሚለው። መከራ ሲመጣ ዝም ብሎ ሰማይን ከማየት፣ በምድር ላይ ፍትሕን በተግባር ማስፈን የሰው ልጅ የዕድሜ ልክ የቤት ሥራ መሆኑን ያስገነዝባል። ​ "The Trial of God" የሰው ልጅ ሥነ-ልቦናን፣ በስቃይ ውስጥ የሚፈተን እምነትንና በፍትሕ ላይ ያለንን አመለካከት የሚመረምር፣ ካነበቡት በኋላ ጠረኑ ለረጅም ጊዜ ከአእምሮ የማይጠፋ ፀዴ ስራ ነው። ▭▭ © Mes Oud

◉ «ጌትዬው በሸንጎ» ➀ [ የዚህ ፅሁፍ ሁለተኛው ክፍል ምናልባት አዲስ ነገር ይዞ ይመጣል፤ ይሄ የዛኛው መግቢያ ነው!] "The Trial of God" የኖቤል ሰላም ተሸላሚው አይሁዳዊ Elie Wiesel የጻፈው philosophical ተውኔት ነው። Elie Wiesel ​በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት በናዚዎች ከደረሰው አይሁዶችን የማጥፋት ዘመቻ በሕይወት የተረፈ ሰው ነው። «በታላቅ መከራ ውስጥ ጌትዬው አስችሎት እንዴት ዝምታን መረጠ? ዝም አይነቅዝም ነው? ዝምታ ወርቅ ነው እያለን ነው? ምን ማቱ ይሆን?» ሲል ደጋግሞ ይጠይቅ የነበረ ደራሲ ነው። ይሄ ጥያቄው ደግሞ "The Trial of God" ን አምጦ ወለደ። ➊ አለህ ወይ? የቴአትሩ መቼት በፈረንጆቹ (1649) "Shamgorod" በምትባል በዩክሬን የምትገኝ ትንሽ መንደር ውስጥ ነው። ይህ ዘመን በአይሁዶች ላይ አሰቃቂ ጭፍጨፋ የተካሄደበት ወቅት ነበር። ​በመንደሯ ውስጥ ከደረሰው አስከፊ ጭፍጨፋ የተረፉት ሶስት ሰዎች ብቻ ናቸው። ከእነዚህም አንዱ "Berish" የተባለው ገፀ ባህሪ ሲሆን፤ በደረሰው መከራ ምክንያት ከፍተኛ የህሊና ቁስል ያለበት የመጠጥ ቤት ባለቤት ነው። በታላቅ በዓል ምሽት ( Purim በተሰኘ) ሦስት ተቅበዝባዥ ቴአትረኞች ወደ መጠጥ ቤቱ ይመጣሉ። ይህንግዜ ቤሪሽ እነዚህን ተዋናዮች በመጠቀም አንድ ያልተለመደና አስደንጋጭ ድርጊት ለመፈጸም ይወስናል። ምን አደረገ? ...በሰዎች ላይ ለደረሰው ስቃይና ግፍ ፈጣሪን በሸንጎ ለማቆም ወሰነ። ​ጌትዬውን፤ ዓለምን በመፍጠሩ፣ ፍጥረታቱ (በተለይ ንጹሐን ሰዎች) በግፍ ሲታረዱና ሲሰቃዩ ዝም ብሎ በመመልከቱ፣ አልፎ ተርፎም ጭካኔን በመፍቀዱ ወንጀለኛ ነው ብሎ ይከሰዋል። የቤሪሽ ኃይለኛ ቁጣ ከክፋት ወይም ካለማወቅ የመጣ አይደለም። ንጹሕ የሆነችው ልጁ ሐና በግፍ ስትደፈር ምንም ማድረግ ባለመቻሉ በውስጡ ከተቀመጠው ብሶትና ቁጭት የመነጨ ነው። ይህ የንጹሃን ስቃይ ነው በኋላ ላይ ጌትዬውን በችሎት እንዲጠየቅ ምክንያት የሚሆነው። "ይህንን የፍርድ ቤት ችሎት አቁም። ከዋቃ ጋር ታረቅ" ቢሉት "ሰላምን የሚፈልግ ከሆነ ታች ወርዶ እኔኑ ይቅርታ ይጠይቀኝ" የሚል ቁጡ ሰው የሆነውም በዚህ ነው። ​BERISH- Reconcile? With Him? Never. If He wants peace, let Him come down and ask for my forgiveness. [ 49] የሚል ደፋር ወጥቶታል። ቴአትሩ የክርክርና የሙግት ጎተራ ነው። በርካታ ጥያቄዎች የሚነሱ ቢሆንም የጥያቄዎቹ ቁንጮ ግን "አለህ ወይ?" የሚል ነው። Master of the Universe... how can You look at this and remain silent? እንዲል YANKEL. ጥያቄዎቹ ሲሸከፉ እኒህን ይመስላሉ። Ⓠ ፈጣሪ ሩህሩህና ሁሉን ቻይ ከሆነ ለምን ንጹሐን ሕፃናትና ደጋግ ሰዎች በግፍ ይሰቃያሉ? የሰው ልጅ ነብስ ለምን እንደቅጠል ይረግፋል? Ⓠ ​በታላቅ መከራ ውስጥ ሆኖ እግዚአብሔርን ማመስገን እምነት ነው ወይስ ሞኝነት? ❷ ጌትዬው ተከላካይ ጠበቃ ያስፈልገዋል? ​ ቤሪሽ የተባለው ቁጡ ሰው ራሱ ከሳሽ (Prosecutor) ይሆናል። ሦስቱ ተዋናዮቹ ደግሞ ዳኞች ይሆናሉ። ነገር ግን ትልቁ ፈተና ለጌትዬው ተከላክሎ የሚከራከር ጠበቃ ማግኘት ላይ ነበር። ማንም ፈጣሪን ለመከላከል ፈቃደኛ ባልሆነበት ሰዓት፣ Sam የተባለ ምስጢራዊ ሰው ይመጣና ጌትዬውን ለመከላከል ጠበቃ ሆኖ ይቆማል። እዚህ ጋር ፈጣሪን ስለመከላከል፣ ለፈጣሪ ጥብቅና ስለመቆም የሚያወጉት ወግ ምፀታዊ ነው። ◦ MENDEL- And who will be the prosecutor? ◦ ​BERISH- I will. ◦ ​MENDEL- Good. Yankel and Avrémel will be the judges with me. We have a court, we have a prosecutor. But we need a defense attorney. Who will defend God? ◦ ​BERISH- No one. He has no defense. ◦ ​MENDEL- A trial without a defense is not a trial, it's an execution. Even God has the right to a lawyer. ◦ BERISH- Then find someone in the street. Go out and look. You won't find anyone. No one in this town will defend Him. [16 -17] እዚህ ጋር ቤሪሽ "ውጡና ፈልጉ። በዚህች ከተማ ውስጥ ማንም ለእሱ አይሟገትም።" የሚለው ንግግሩ ለፈጣሪ ጠበቃ ከመፈለግ በላይ ብዙ ያሳስባል። እንደክር የሚተረተር ሚስጥር ይዟል። ወደራስ እንድናጨነቁር፤ ያለንበትን የቸልታ ዘመን እንድናጤን ይመራል። Sam የተባለው ሚስጥራዊ ሰው ጌትዬውን ተከላክሎ ይከራከራል። ክርክሩ ታክቲካል ነው። ህግ የተማረ የሀይማኖት አባት ነው የሚመስለው። «ዱንያ ላይ ያሉ ውጥንቅጦች የጌትዬውን ጥፋተኝነት አያረጋግጡም። የጥፋት እሳቶችን የለኮሰው፣ ሰይፎቹን የሞረደው ፈጣሪ ሳይሆን ሰዎች ናቸው። እያንዳንዱን ክፉ ድርጊት ለማስቆም እሱ ኃይሉን የሚጠቀም ከሆነ፣ ታዲያ የሰው ልጅ ነፃነት የት አለ? ሰው ክፉን ለመምረጥ ነፃ ካልሆነ፣ መልካሙንም ለመምረጥ ነፃ አይሆንም።» ብሎ ይከራከራል። ◦ SAM- Evidence, Prosecutor? What evidence? History is full of ruins, but ruins do not prove the guilt of God. They only prove the nature of man. God did not light the torches. God did not wield the swords. Men did. ◦ ​BERISH- But He could have stopped them! He has the power! ◦ ​SAM- Ah, the power. If He uses His power to stop every evil deed, then where is human freedom? If man is not free to choose evil, he is not free to choose good. He becomes a puppet. Is that what you want? A world of puppets? ​[25] የሚያስደንቀው ነገር ግን ወዲህ ነው። በታሪኩ ማለቂያ አከባቢ፤ ለጌትዬው ጥብቅና ቆሞ ሲከላከል የነበረው ሳም የተባለው ሰው ማንነት ሲገለጥ ታሪኩን እጅግ ምፀታዊ ያደርገዋል። መልዕክቱን ደግሞ ጠጣር። ሳም የተባለው ገጸ-ባህሪ ሰይጣን እንደሆነ ፍንጭ ስናገኝ ግዜ ተገርመን ማቆም የለብንም። ምክንያቱም ይህ ተምሳሌት የሚያሳዬው የዓለምን ግፍ ያለምንም ጥያቄ ልክ ነው ብሎ የሚቀበል አካል የጭካኔና የክፋት ተባባሪ መሆኑን ነው። ❸ ይሄ መጽሐፍ ለምን ልዩ ሆነ? ​ፀሀፊው Elie Wiesel ገና በ15 ዓመቱ በናዚ የሞት ካምፕ (Auschwitz) በነበረበት ወቅት፣ አንድ ምሽት ሦስት ታላላቅ የአይሁድ ሊቃውንት ምስክሮችን ሰብስበው፣ ማስረጃ አሰባስበውና ተሟግተው ጌትዬውን በችሎት እንደከሰሱትና በፍጥረታት ላይ ለሚደርሰው ግፍ «ጥፋተኛ ነው!» የሚል ፍርድ በአንድ ድምፅ እንዳሳለፉ Wiesel ራሱ በዓይን ምስክርነት ያየውን ታሪክ ያካትታል። የሚገርመው፣ ፍርዱ እንደተጠናቀቀ የጸሎት ሰዓት ደርሷል ተብሎ ሁሉም ሊቃውንት ወደ ጸሎታቸው ተመልሰዋል።😂

ፍልስፍናን ከተዋወኳት ጊዜ ጀምሮ ካነበብኳቸው መጽሃፍት ውስጥ ማንኛውም ጥልቅ ሃሳብ ያለው ሰው ሊያነባቸው ይገባል ብዬ የማስባቸውን ምርጥ እስር መጽሃፍት ልጋብዛችሁ። እንግዲህ በሁሉም ትውልድ ውስጥ፣ ከመዝናኛነት ባለፈ ትልቅ ትርጉም ያላቸው መጽሐፍት አሉ። እነዚህ መጽሐፍት የለመድናቸውን አስተሳሰቦች ይሞግታሉ፣ ቅዠቶችን ያፈርሳሉ፣ የማይመቹ ጥያቄዎችን ያነሳሉ፣ እንዲሁም እራሳችንን እና ዓለምን የምንረዳበትን መንገድ ይለውጣሉ። እነዚህ የምጋብዛችሁ አስር መጽሃፍት ዝም ብለው የሚነበቡ መጽሐፍት ብቻ አይደሉም፤ የሰውን ልጅ የአስተሳሰብ አቅጣጫ ሊቀይሩ የሚችሉ የእውቀት ማዕበሎች ናቸው። ፈላስፋ፣ ተማሪ፣ ጸሐፊ፣ ወይም ዝም ብሎ ጥልቅ አስተሳሰብን የሚወድ ሰው ከሆናችሁ እነዚህ መጽሐፍት በመደርደሪያችሁ ላይም በአእምሯችሁ ውስጥም ቦታ ሊኖራቸው ይገባል። 1. The Republic— ፕላቶ ይህ መጽሃፍ ምናልባትም በፍልስፍና ታሪክ ውስጥ ከፍተኛ ተጽዕኖ ያሳደረው ስራ ሊሆን ይችላል። በሶቅራጥስ አንደበት፣ ፕላቶ ስለ ፍትህ፣ እውነት፣ ፖለቲካ፣ ትምህርት እና ስለ እውነታ (reality) ምንነት የሚመረምርበት ስራ ነው። እስካሁን ድረስ የሰው ልጅ ስለ አላውቂነትና እና እውቀት ካሰፈራቸው ታላላቅ ምልከታዎች አንዱ የሆነው ታዊቂው 'የዋሻው ምሳሌ' (Allegory of the Cave) የሚገኘውም በዚህ ድንቅ መጽሃፍ ውስጥ ነው ለምንድን ነው ይሄን መጽሃፍ ማንበብ ያለብን ካላችሁኝ ምክንያቱም እያንዳንዱ አሳቢ ሰው ውሎ አድሮ ፍትህ ምንድን ነው? እውነትስ ምንድን ነው? እንዲሁም እውነተኛውን ነገር ከቅዠት እንዴት እንለያለን? የሚሉ ጥያቄዎችን ማንሳቱ አይቀርምና እላቸሃለው። 2. Meditations — ማርከስ ኦሪሊየስ በሮማዊው ንጉሠ ነገሥት እንደ ግል ማስታወሻ የተጻፈው ይህ ዘመን አይሽሬ ስራ፣ ስለ ራስ-ስርዓት (self-discipline)፣ ስቃይ፣ ሟችነት እና ውስጣዊ ነፃነት ጥልቅ ግንዛቤዎችን የሚሰጥ መጽሃፍ ነው። ለምን እናንባብበው ካላችሁኝ ምክንያቱም ህይወት እኛን ከችግር ጋር ማጋፈጧ አይቀርም፤ ከዚህ መጽሃፍ በተሻለ ስለ ጽናት እና ክብር የሚያስተምሩ መጽሃፍት ጥቂት ናቸውና እላቹሃለው። 3. Critique of Pure Reason—ኢማኑኤል ካንት እስካሁን ካነበብኳቸው መጽሐፍት ውስጥ እጅግ ጠቃሚ እና ለመረዳት ከባድ ከሆኑት መካከል አንዱ ይህ መጽሃፍ ነው። በዚህ ስራ ውስጥ ካንት የሰውን ልጅ የእውቀት ገደብ ይመረምራል፤ እንዲሁም ስለ እውነታ በእውነት ምን ማወቅ እንደምንችል ይጠይቃል። ለምንድን ነው መነበብ አለበት ካላችሁን ምክንያቱም ዓለምን ከመረዳታችን በፊት፣ ዓለምን ለመመልከት (perceive ለማድረግ) እና ለመተርጎም የምንጠቀምባቸውን መሳሪያዎች መረዳት ስላለብን ነው እላቹሃለው። 4. Thus Spoke Zarathustra — ፍሪድሪክ ኒቼ ይሄ ከፊል ፍልስፍና፣ ከፊል ግጥም፣ እና ከፊል ትንቢት የሆነ የጀርመናዊው ፍሬድሪክ ዊልሄልም ኒቼ (My favorite philosopher of all time) ስራ ነው። በዚህ ስራው ውስጥ ኒቼ ባህላዊ የሞራል እሴቶችን፣ የሃይማኖት ዶግማዎችን እና የአስተሳሰብ ተገዥነትን ይሞግታል፤ ጎን ለጎን ደግሞ አዳዲስ እሴቶች እንዲፈጠሩ ጥሪ ያቀርባል። ለምን እናንብበው ካላችሁኝ ምክንያቱም የድሮ እርግጠኛነቶች (እምነቶች) ከፈረሱ በኋላ "እንዴት መኖር አለብን?" የሚለውን ጥያቄ እንድንጋፈጥ ስለሚያስገድደን እላቹሃለው። 5. The World as Will and Representation — አርተር ሾፐንሃወር ይሄ ስለ ፍላጎት፣ ስቃይ እና ስለ ህልውና እረፍት አልባ ተፈጥሮ የተደረገ ጥልቅ ፍለጋ ነው። ሾፐንሃወር በዘመናዊ ፍልስፍና፣ ሳይኮሎጂ እና ስነ-ጽሑፍ ውስጥ ተጽዕኖ ያሳደረ ድንቅ ፈላስፋ ነው። ለምን እናንብበው ካላችሁኝ የሰው ልጆች ለምን እንደሚሰቃዩ ከተጻፉት እጅግ ጥልቀት ያላቸው ትንታኔዎች አንዱ ስለሆነ እላቹሃለው። 6. Beyond Good and Evil— ፍሬድሪክ ኒቼ በዚህኛው መጽሐፉ ኒቼ በተለመደው የሞራል እይታ ላይ ቀጥተኛ ጥቃት ይሰነዝራል፤ እንዲሁም አንባቢዎች ተቀባይነት ካገኙ እውነታዎች በስተጀርባ የተደበቁትን ውስጣዊ ግፊቶች እንዲመረምሩ ይጋብዛል። ለምን እናንብበው ካላችሁኝ እውነተኛ አስተሳሰብ የሚጀምረው ሌሎች ሰዎች ሁሉ ያለምንም ጥያቄ የሚቀበሏቸውን ሃሳቦች መጠየቅ ስንጀምር ስለሆነ እላቹሃለው። 7. On the Genealogy of Morality— ፍሬድሪክ ኒቼ ይሄ ስለ ሞራል እሴቶች አመጣጥ የተደረገ ፍልስፍናዊ ምርመራ ነው። ኒቼ ሞራል እውነት ነው ወይስ አይደለም ብሎ ከመጠየቅ ይልቅ ከየት መጣ እና የማንን ፍላጎት ያገለግላል የሚለውን የመረመረበት ድንቅ ስራ ነው። ለምን እናንብበው ካላችሁኝ የእሴቶችን ታሪክ መረዳት እራሳችንን እንድንረዳ ስለሚያግዘን እላቹሃለው። 8. Fear and Trembling— ሶረን ኪርኬጋርድ ይህኛው ኬርኬጋርድ ስለ እምነት፣ ጭንቀት፣ ግለሰብነት፣ እና የሰውን ልጅ ህይወት ስለሚተረጉሙ ከባድ ምርጫዎች የጻፈው ድንቅ ስራ ነው። ለምን እናንብበው ካላችሁኝ በህይወት ውስጥ አንዳንድ እጅግ አስፈላጊ የሆኑ ውሳኔዎች በሎጂክ (በምክንያታዊነት) ብቻ ሊወሰኑ ስለማይችሉ በቀጥታ ወደ ሕልውና እንድናይ ስለሚረዳን እላቹሃለው። 9. Civilization and Its Discontent— ሲግመንድ ፍሮይድ ፍሮይድ በሰው ልጅ ደመነፍስ (instincts) እና ስልጣኔ በሚጠይቃቸው ነገሮች መካከል ያለውን ውጥረት የመረመረበት ስራ ነው። በዚህ መጽሃፍ ውስጥ ያሰፈራቸው ምልከታዎቹ ዛሬም ስለ ባህል እና ሳይኮሎጂ በሚደረጉ ክርክሮች ላይ ተጽዕኖ ማሳደራቸውን ቀጥለዋል። ለምን እናንብበው ካላችሁኝ በግለሰብ ፍላጎቶች እና በማህበራዊ ስርዓት መካከል ያሉትን የተደበቁ ግጭቶች ስለሚመረምር ጠቃሚ ነው እላቹሃለው። 10. The Structure of Scientific Revolutions — ቶማስ ኩን ይሄ ሳይንሳዊ እውቀት እንዴት እንደሚለወጥ የሚያሳይ አብዮታዊ ጥናት ነው። ኩን የአእምሯዊ እድገት አብዛኛውን ጊዜ እውነታዎችን በማከማቸት ብቻ ሳይሆን፣ በመሰረታዊ የአመለካከት ለውጦች (paradigm shifts) የሚመራ መሆኑን ያሳየበት ትልቅ ስራ ነው። ለምን እናንብበው ካላችሁኝ በጣም የምናምናቸው የእውቀት ስርዓቶቻችን እንኳን በታሪክ የተቃኙ እና ለለውጥ የተጋለጡ መሆናቸውን ስለሚያስተምረን እላቹሃለው። -------------------------------------------------------- እነዚህ አስር መጽሐፍት አንድ ወጥ የሆነ ፍልስፍና የላቸውም። እንዲያውም፣ አብዛኛዎቹ እርስ በርሳቸው በጥልቀት የሚጋጩ ናቸው። ሆኖም ግን አንድ ላይ ሲጣመሩ፣ ስለ እውነታ፣ እውቀት፣ ሞራል፣ ስቃይ፣ ነፃነት፣ ማህበረሰብ እና ስለ ህይወት ትርጉም አስደናቂ የሆነ ውይይት ይፈጥራሉ። እነዚህ መጽሃፍቶች ያላነበባችሁ ስታነቧቸው የመጨረሻ መልሶችን ለማግኘት ሳይሆን የተሻሉ ጥያቄዎችን እንዴት መጠየቅ እንደሚቻል ለመማር አንብቧቸው። ምክንያቱም ፍልስፍና የሚጀምረው እርግጠኛነትን ስናገኝ አይደለም። የሚጀምረው ለመጠራጠር፣ ለመመርመር፣ እና በራሳችን ለማሰብ የሚያስችል ድፍረት ስናዳብር ነው። ያነበባቹሃቸው ደግሞ ከነዚህ ውስጥ የትኞቹን መጽሃፍት አንብባቹሃል? እንዴትስ አገኛችሗቸው? ሃሳባችሁን አጋሩን እንወያይበት!! ይመቻቹ✌️ © Yonatan Abyss

ድንጋዩ፣ ከግዙፍ አለት ወደ ብይ እያነሰ መጥቶ፣ ከዛም የተሰወረ ቢመስለውም፣ ነገር ግን፣ በሆነ የማይታይ ቅርፅ ማንነቱን ቀይሮ በህልውና መኖር መቀጠሉን ጠረጠረ። ከዚህ መነሻ ነው ወደ "Theory of the small" ትኩረቱን ያዞረው። 'በዐይን የማይታይን ነገር እምን ላይ ላንከባለው?'ብሎ አንድ የእውቀት ተራራ ፈጠረ። ተራራውም አሁን "Particle phys-ics" ተብሎ የሚጠራው መሆኑ ነው። ይህ የሌሊሳ ግርማ ትርጓሜ ሲሲፈስን ከጥንታዊው አፈታሪክ አውጥቶ ወደ ዘመናዊው የሳይንስ እና የፍልስፍና አድማስ ያሸጋገረበት መንገድ እጅግ ረቂቅ ነው። ሲሲፈስን ከጉልበት ሰራተኛነት ወደ "Theoretical Physicist" የቀየረበት ጥበብ አዝናንቶ ያስደምመኛል። ​ ​ድንጋዩ ሟምቶ ሲያልቅ ሲሲፈስ የደረሰበት መደምደሚያ "Theory of the Small" መሆኑ ደሞ ሌላ አጃኢብ ነው። ይህም ቁስ (Matter) አይጠፋም፣ ቅርፁን ይለውጣል እንጂ የሚለውን የሳይንስ ህግ ያስታውሰናል። ሲሲፈስ ግዙፍ ድንጋይ መግፋት አቁሞ የማይታይ "Particle" ላይ ትኩረቱን ማድረጉ፣ ከሥጋዊ ድካም ወደ አእምሯዊ ሽግግር ማድረጉ ቢሆንስ። ​በጥንቱ ታሪክ ተራራው የዙስ ቅጣት ነበር፤ በዚህኛው ትርጓሜ ግን ተራራው የእውቀት ተራራ ሆኗል እያለን ቢሆንስ? ሲሲፈስ አሁንም ይገፋል፣ ነገር ግን አሁን የሚገፋው ድንጋይ ሳይሆን ጥያቄዎችን ወይም ሀሳቦችን ነው። ◉በአሁኑ ዘመን የሰው ልጅ እንደ ጥንቱ ድንጋይ በመሸከም ብቻ ሳይሆን፣ የማይታዩ ረቂቅ ነገሮችን በመመርመር ላይ ተጠምዷል ነው ሌሊሳ እያለን ያለው። ሌሊሳ ሲሲፈስን ድንጋዩ ሟምቶ ካለቀ በኋላ ወደ "Theory of the Small" እና "Particle Physics" ትኩረቱን እንዳዞረ አድርጎ መሳሉ፣ የዘመናችንን ሳይንሳዊ ግስጋሴ አይወክልም ነው የምትሉት? የሌሊሳ ትርጓሜ ሲሲፈስን ከግሪክ ተራራ አውጥቶ በዘመናዊው የሳይንስ ላብራቶሪ ያስቀምጠዋል። የአሁኑ ዘመን የሰው ልጅ መከራን ወደ ልምድ፣ ችግርን ደግሞ ወደ ብቃት የመቀየር አቅሙን የሚያጎላ ነው። ስራው "ገድለ ሲሲፈስ" መባሉ ራሱ ይህንን በጽናት የመታገልና የመለወጥ ሂደትን የሚያንፀባርቅ ነው። ▭▭ © Mes Oud