es
Feedback
My youth age for christ GOSPEL MINISTRY! ወጣትነቴን ለክርስቶስ!!🇪🇹🇪🇹

My youth age for christ GOSPEL MINISTRY! ወጣትነቴን ለክርስቶስ!!🇪🇹🇪🇹

Ir al canal en Telegram

ወጣትነቴን ለክርስቶስ የታዳጊዎችና የወጣቶች የወንጌል አገልግሎት 👉ወጣቶችንና ታዳጊ ወጣቶችን ስለወንጌል እውነት ያስተምራል!! እንዲሁም ለታዳጊ ወጣቶች ሁለንተናዊ የሆነ ስልጠና ይሰጣል!! 👉ከተማሪዎች ጋር በመሆን በትምህርት ቤቶች ወንጌልን እንሰራለን።

Mostrar más
651
Suscriptores
+124 horas
-67 días
+230 días
Archivo de publicaciones
ፀጋውን እንጂ ጽድቄን አልቆጥር ከሰጠኝ በላይ ምንም አልጨምር የማልጠቅም ባሪያ ታሪክ የሌለው አንድ ነገር ግን አውቃለው....... ኢየሱስ እንዳዳነኝ!!!😇

ፍቅርህ_ብዙ_ነው_የኔ_ጌታ_ዘማሪ_እዝራ_ንጉሴ_FIKREH_BIZU_NEW_YENE_GETA_EZRA_NIGUSSE256k.mp37.85 MB

ዝም በሉ! ሁለት ሰዎች መግባባት እንዲችሉ ሁለቱ እኩል አያወሩም አንዱ ዝም ብሎ ሌላውን ማዳመጥ አለበት። እኛም ዛሬ ለእግዚአብሔር ምናወራው በዝቶብን ምናልባት ከእግዚአብሔር መስማትን ትተን እንዳይሆን የኛን ነገር ብቻ ነግረነው የእርሱን ሳንሰማ እንዳንቀር አሁን ዝም እንበልና እርሱን እንስማ። በዝምታ ውስጥ እግዚአብሔርን መስማት አለ እግዚአብሔርን በመስማት ውስጥ ዕረፍት፣ሰላም፣ደስታ አለ።
ምሳሌ1:33የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል፥ ከመከራም ሥጋት ያርፋል።

አታምታቱ! 1. ይቅርታ እና አብሮነት አንድ ሰው ሆን ብሎ እና ደጋግሞ የሚያጠፋችሁ ከሆነና ይቅርታ የሚጠይቃችሁ ከሆነ፣ ይቅርታውን ተቀበሉና ይቅር በሉት፡፡ ነገር ግን ይቅርታን እና አብሮነትን አታምታቱ፡፡ ሰዎችን ይቅር ብላችሁ በአብሮነት ግን ያለመቀጠልን ጥበብ ማዳበር ትችላላችሁ፡፡ ሁለቱ የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡ ሰዎች ምንም ያህል ሆን ብለው ደጋግመው ቢያጠፉኝም ይቅር ብዬ አብሮነቴን መቀጠል እፈልጋለሁ ካላችሁ ደግሞ ደጋግማችሁ ለመጎዳት ራሳችሁን ማዘጋጀት የግድ ነው፡፡ 2. አጋርነት እና ወዳጅነት አጋርነትን እና ወዳጅነትን አታምታቱ፡፡  ከሰዎች ጋር በአጋርነት እየሰራችሁ የግድ ወዳጅ መሆን የለባችሁም፡፡ ሁለቱ የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡ ከአንድ ሰው የስራ አጋር ሆናችሁ ጓደኛ ላትሆኑ ትችላላችሁ፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ ከአንድ ሰው ጋር የቅርብ ጓደኛ ሆናችሁ በምንም አይነት የስራ ዘርፍ አጋር ያለመሆንን ነጻነት ልትጠብቁ ትችላላችሁ፡፡ ያንንም በማድረጋችሁ ምንም ጥፋተኝነት ሊሰማችሁ አገባም፡፡ ከወዳጆቼ ሁሉ ጋር የስራ አጋር መሆን እፈልጋለሁ ካላችሁ ደግሞ በስራ አጋርነት ምክንያት ወዳጅነታችሁን የመሰዋት ሁኔታ ሲከሰት ለዚያ ሁኔታ ራሳችሁን አዘጋጁ፡፡ 3. መግባባትን እና የቀይ መስመር መግባባትን እና ቀይ መስመርን አታምታቱ፡፡  ከአንድ ሰው ጋር በጣም ተግባባችሁ ማለት መከበር ያለበት የቀይ መስመር የላችሁም ማለት አይደለም፡፡ ሁለቱ የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡ ከሰዎች ጋር እጅግ ተግባብታችሁ ሳለ፣ እንዲከበርላችሁ የምትፈልጉት ወሰን ሊኖራችሁ ይችላል፡፡ መግባባት አንደኛችን ለሌላኛው ያለን አመለካከት ጉዳይ ነው፡፡ የቀይ መስመር ወሰን ግን የሚፈቀደውና የማይፈቀደው የሚለይበት ገደብ ነው። አንድ ሰው ከቀረበኝ ምንም አይነት የቀይ መስመር ማስመር አልፈልግም ካላችሁ ደግሞ፣ የስሜት፣ የጊዜ፣ የቁሳቁስና የመሳሰሉት ክስረቶችን ለማስተናግድ ተዘጋጁ፡፡ የመርህ ሰው መሆን ማለት ክፉ መሆን ማለት አይደለም! ይህንን እውነት ስትለማመዱ በማንም ሰው ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ሰላምና ውስጥ መረጋጋት ታገኛላችሁ፡፡ Dr. eyob Mamo

ትዝብት #3 (በዋናነት እህቶቻችንን ይመለከታል) __ ወንጌልን ለመስበክ የሚወጡ እህቶቻችንን አለባበስ አስተውላችሁ ታውቃላችሁ? ሁሉም ማለት በሚቻል ደረጃ በወንጌል ምስክርነት የተሰማሩ እህቶቻችንን
+6
ትዝብት #3 (በዋናነት እህቶቻችንን ይመለከታል) __ ወንጌልን ለመስበክ የሚወጡ እህቶቻችንን አለባበስ አስተውላችሁ ታውቃላችሁ? ሁሉም ማለት በሚቻል ደረጃ በወንጌል ምስክርነት የተሰማሩ እህቶቻችንን መደበኛ የሆነ አለባበስን(1) ነው የሚከተሉት። ወንጌል ምስክርነት ቡድንን መርቼ ስለማውቅ ይህ አይነቱ አለባበስ ለዚህ አገልግሎት ለምን እንደሚመረጥ መናገር እችላለሁ። ይኸውም 'አድማጮቻችን እህቶቻችን በሌሎች ቦታዎች የሚለብሷቸውን አይነት ኢ-መደበኛ አለባበሶች(1) ለብሰው ቢወጡ መልዕክታቸውን በአለባበሳቸው ብቻ በማቃለል በቀላሉ ላይቀበሉ ይችላል' ተብሎ ስለሚታመን ነው። ስለዚህም በብዛት ዘርፋፋ ቀሚስ(እንደ ድሪያ የመሰሉ)፣ ወይንም ከጉልበት በላይ ያላጠረ ቀሚስ እህቶቻችን እንዲለብሱ ይደረጋል። ከወገብ በላይም ጡትን ወይንም እምብርትን የማያሳይ ልብስ እንዲለብሱ ይመከራል። 👉. እንግዲህ ዋናው ሀሳብ ያለው እዚህ ጋር ነው። ወንጌል ስርጭት ላይ ከኢ-መደበኛው ይልቅ መደበኛው አለባበስ የሚመረጠው '#ሰዎችን_ያሰናክላል!' ተብሎ ከሆነ ስለምን እህቶቻችን ይህን አለባበስ በሌሎችም ቦታዎችም አያስቀጥሉትም? የሚል። ሰዎች(በተለይም ወንዶች) በማናቸውም ቦታዎች ልንሰናከል የምንችል ከሆነ በሌሎች ቦታዎች እህቶቻችን ኢ-መደበኛ አለባበስ እየለበሱ ስለምን መሰናከያ ሰበብ ይሆኑናል? የሚል(2)። እግዚአብሄር ጠንካራ አቋም ባላቸው እህቶች ይባርከን!

"ሰማይንና ምድርን የፈጠረውን ፣ነገር ሁሉ በፊቱ ራቁት ያለውን፣ ልብንና ኩላሊትን ሁሉ የሚመረምረውን እግዚአብሔርን ይቅርና እኔን እንኳ ማታለል አትችልም፤ የተከፈተው አፍህ ልብህን እና ከአመት አመት ያልተገራው ባሕሪህ የማንነትህን ልኬት ይነግረኛል፤ በቃሉም እመዝንሃለሁ።" 👉ወዳጆቼ እግዚአብሔር አይዘበትበትምና አናስመስል!🙏 MYAFC🎙

እግዚአብሔር አምላክ ክብሩን ለማንም አያጋራም!! 🙌

አንድ ሰው ምንም ሳይሆን ትልቅ የሆነ ቢመስለው ራሱን ያታልላል። እያንዳንዱ የራሱን ተግባር ይመርምር፤ ከዚያም በኋላ፣ ከሌላ ሰው ጋራ ራሱን ሳያወዳድር፣ ስለ ራሱ የሚመካበትን ያገኛል፤ ገላትያ 6፥3
አንድ ሰው ምንም ሳይሆን ትልቅ የሆነ ቢመስለው ራሱን ያታልላል። እያንዳንዱ የራሱን ተግባር ይመርምር፤ ከዚያም በኋላ፣ ከሌላ ሰው ጋራ ራሱን ሳያወዳድር፣ ስለ ራሱ የሚመካበትን ያገኛል፤ ገላትያ 6፥3-4

Wolaita Gospel Movement የተሳካ የወንጌል ጉዞ🗣 🏙በቦዲቲ ከተማ በተደረገው የወንጌል ስርጭት በአንድ ለአንድ እና ጀማ 👂 ወንጌልን የሰሙ 👉 1751 ሰዎች 🙏 ተስፋ የሰጡ 👉 2
Wolaita Gospel Movement የተሳካ የወንጌል ጉዞ🗣 🏙በቦዲቲ ከተማ በተደረገው የወንጌል ስርጭት በአንድ ለአንድ እና ጀማ 👂 ወንጌልን የሰሙ 👉 1751 ሰዎች 🙏 ተስፋ የሰጡ 👉 24 ሰዎች 🙌 በንስሐ የተመለሱ 👉 8 ሰዎች ✝ ጌታ ኢየሱስን የተቀበሉ 👉 23 ሰዎች 🙌 ክብር ሁሉ ለጌታ ይሁን🙏

03_Hamlet_Beljun___TEWLED_ALE___ትውልድ_አለ(256k).mp34.30 MB

"Pride is the only sin the enemy never makes you feel guilty about." 🎙derekprince #wisdom #pride

ከኀጢአት ጋር ውጊያውን እንዳታቆም፣ ዓይኖችህን ከመስቀሉ ላይ ዘወር እንዳታደርግ! ሰይጣን፣ ዐለም እና ስጋ ድል ነሳን ብለው ጮቤ የሚረግጡት ዓይኖችህ ከክርስቶስ ላይ ዘወር ያሉ ጊዜ ብቻ ነው። ሰይጣን አንተን አይፈራም፣ ድል እና ድባቅ የተመታበትን የቀራኒዮን ደም ግን አብዝቶ ይፈራል። ለኃጢአት ያለህ ጥላቻ ለክርስቶስ ከሚኖርህ ፍቅር ጋር እያደረግህ ለዚህ ለሞት ከተሰጠ ለኃጢአትም ባሪያ ከሚሆን ሥጋችን በትንሳኤ አካል እስኪያከብረን በመውደቅ በመነሳት የሚቤዤንና የቤዛነታችንን ቀን ተስፋ እያደረግን እንቀጥላለን፣ Stay fighting by his might brother 💪. 🎙Aman shalom

05_ጣፍጥልኝ-Taftilgn__Yosef_Aschalew_(0).mp37.19 MB

ክርስትናን_መኖር_Singer_kalkidan_Chikesa_Original_Song_by_Pastor_Agegnew.m4a7.81 MB

🤩ለ 50 ወጣቶች እና ታዳጊዎች ድንቅ የንባብ እድል በክረምት📔🌨 ⚡️ ከላይ የምትመለከቷቸውን እና ሌሎችንም የምትፈልጉትን መጻሕፍት በሚመጡት የክረምት ወራት ተቀብላችሁ ለማንበብ ዕድሉ የተዘጋጀው
+9
🤩ለ 50 ወጣቶች እና ታዳጊዎች ድንቅ የንባብ እድል በክረምት📔🌨 ⚡️ ከላይ የምትመለከቷቸውን እና ሌሎችንም የምትፈልጉትን መጻሕፍት በሚመጡት የክረምት ወራት ተቀብላችሁ ለማንበብ ዕድሉ የተዘጋጀው ለ50 ሰው ብቻ ስለሆነ እስከ ሰኔ 26 ድረስ በ0919709309 እየደወላችሁ ተመዝገቡ። FOOD FOR MIND PROJECT ETHIO🇪🇹

_በእምነት_እኖራለሁ_Bemnet_Enoralehu_አስናቀች_ተ_ደስታ_ቢ_ተስፋዬ_ጋ_አባይነህ_ሻ_አቤል_ተ.mp39.33 MB

+2
11_ስንፍናችንን-_Sinfnachinin__Yosef_Aschalew(0).mp34.58 MB