My youth age for christ GOSPEL MINISTRY! ወጣትነቴን ለክርስቶስ!!🇪🇹🇪🇹
Открыть в Telegram
ወጣትነቴን ለክርስቶስ የታዳጊዎችና የወጣቶች የወንጌል አገልግሎት 👉ወጣቶችንና ታዳጊ ወጣቶችን ስለወንጌል እውነት ያስተምራል!! እንዲሁም ለታዳጊ ወጣቶች ሁለንተናዊ የሆነ ስልጠና ይሰጣል!! 👉ከተማሪዎች ጋር በመሆን በትምህርት ቤቶች ወንጌልን እንሰራለን።
Больше645
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
-130 день
Архив постов
"እኔ ክርስቲያን ነኝ ሞት ወደ ምወደው ወደ ጌታዬ የሚወስደኝ የተወደደ መንገድ ነው ዘላለሜ ምን እንደሆነ ጠንቅቄ አውቃለሁ የምጠብቀው ንጉስ በቅርቡ ይመጣል ወደ እውነተኛ መኖሪያዬ ይወስደኛል ለምድር ኑሮዬ እንግዳ ነኝና ዜግነቴ በሰማይ መኖሪዬ በሰማይ ነው አዎ እኔ ክርስቲያን ነኝ ክርስቶስን ተከታይ!!!"
Servant abela🎙
+1
ሰላም ውድ የጌታ ቤተሰቦች 🥰
እንደምን ቆያችሁ?
👉"ጥያቄ ለOJዎች" በሚል ርዕስ ወንድም ሳሙኤል ያዘጋጀውን ተከታታይ ትምህርት የምንለቅላችሁ ይሆናል🙏
💪ጊዜው የእኛ ነው💪 ግራ የገባውን የኑፋቄ አስተምህሯቸውን በጌታ ቃል እንመክታለን።
🖌📒 ታዲያ ሁሌ እንደምንላችሁ ብዕርና ማስታወሻ ይዘጋጅ👍
🥹OJዎች ጉድ ፈላባቸው😁
👉ይሄው ሊንኩ https://t.me/Romansbiblestud
ጨለማየን_ጌታ_እያበራ፦_ቃልኪዳን_ጥላሁን_ሊሊ_Kalkidan_Tilahun_Lily_Chelemayen_Geta.mp35.04 MB
Purity is often the hidden foundation behind spiritual strength. Many of our faith fathers were anointed not only because of what they did outwardly, but because they guarded their hearts and lived in purity before God.
God is not impressed by noise, appearance, or even public acts of worship alone. He looks deeper at the heart. A pure heart is what attracts His presence, because purity reflects humility, sincerity, and total dependence🙌🙌
🍞 *Daily Bread*
*'Surely he shall deliver thee from the snare of the fowler, and from the noisome pestilence.' Psalms 91:3*
God protects us from the traps of the enemy, releasing us from evil and destruction with His sovereign power. He is our constant shield. Today, we can trust the Lord as our liberator, knowing that He protects us from all bonds and preserves us to live safely under His protection.
Prayer: Lord, I thank you for releasing me from the hunt of the hunter. keep me from destruction and guide me into your shelter. let me live safe in you, in the name of Jesus our Savior, Amen.
Repost from Yirgalem Apologetics Team 🧱🛡
⭕️ ጥያቄ ለ "only jesus" ተከታዮች
♨️ ዋናውን መሠረት የሚንድ ጥያቄ
♨️ "አንድ" የሚለው ቃል ትርጉም
♨️ "እኛም አንድ እንደሆንን" 🤔
♨️ "እንደ እኛ አንድ እንዲሆኑ" 🤔
♨️ "እኔና አብ አንድ ነን" 😳😳
🔰 ይሄንን ትምህርት የሰማ የትኛውም የሥላሴ
አማኝ ከ Ojዎች ቄስ ጋር ፊትለፊት
ለመነጋገር አይፈራም
🔰 ጠያቂ ከሆናችሁ አሸናፊ ናችሁ
♨️ ይሄንን audio #download አድርጋችሁ (አውርዳችሁ) ለጓደኞቻችሁ ቀጥታ ላኩላቸው ፣ ይሄ audio በሁሉም አቅጣጫ መሰራጨት አለበት ‼️
🧱 ትምህርቱ ለሁሉም የሥላሴ አማኝ
እንዲደርስ share አድርጉ 🙏🙏
Repost from Zemere Addisu
ሚስዮናዊት ጺዮን ደምሴ ትባላለች።ተወልዳ ያደገችው በወላይታ ሶዶ ነው።ዩንቨረስቲ ትምህርቷን እንደጨረሰች ገና በለጋነት እድሜዋ በ22 ዓመቷ ለወንጌል ተልዕኮ ራሷን ሰጠች። የወንጌል ተልዕኮ ሸክም በውስጧ ስላየለ ወደ ደቡብ ኦሞ ሐመር ማህበረሰብ በመሄድ እዚያው በመኖር ወንጌልን በጨለማ ላሉት ማብሰር ጀመረች።
የወንጌል ሥራዋን የጀመረችው ሕጻናትን በማስተማር ሲሆን እርሷና ጓደኞቿ ምቾትና የከተማን ኑሮ ጥለው በዘር በቋንቋ ለማይመሳሰለው ህዝብ #የክርስቶስ #ፍቅር አስገድዶአቸው የሚያደርጉት ሥራ የብሔረሰቡን ጎሳ መሪ ልብ ስለነካው ጌታን ለመቀበል ወሰነ።ከዚያም ምቾትን አስጥሎ ለማታውቁት ሰው እንደዚህ እንድትሆኑ ለሚያደርጋችሁን አምላክ እዝሁ ቤተክርስትያን ሥሩ በማለት አዳራሽ መስሪያ ቦታ ሰጣቸው።
በአሁኑ ሰዓት ይች ወጣት በሐመር ማህበረሰብ ውስጥ የብዙዎች የመዳን ምክንያት እየሆነች ነው።
አንተስ ወጣትነትህን ለምን አላማ እያዋልክበት ነው? አንቺስ?
ይህ ዘመን ሰዎች የሶሻል ሚድያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎችን የሚያመልኩበት እንጂ እንደ እርሷ አይነት የሚደነቅበት አይደለም ።የሰው ማንነት በሚድያ ፎሎወር ብዟት በሚገመትበት ፣ሁሉም ወደተሻለ ከተማ ለመግባት በሚራወጥበት ራስን ለተልዕኮ አሳልፎ በመስጠት ገጠራማ ሥፍራዎች በመሄድ ለወንጌል ዋጋ መክፈል ምነኛ መታደል ነው።
የእኔ #ሞዴሎች እንደ እርሷ አይነት ሚስዮናዊያን ናቸው? የአንተስ? የአንቺስ?
ይህችን እህት በጸሎታችሁ አስቧት፣በገንዘባችሁም ደግፏት ።ለእኔ የመነቃቃት ምክንያት ሆናለች ለእናንተስ?
#ዘመረ #አዲሱ
#ሼር አድርጉት ምናልባት እንደ እኔ አንድ ሰው ለወንጌል ተልዕኮ ያነቃቃ ይሆናል
👆ይሄ የወንድማችን ሳሙኤል ተሰማ You Tube channel ነው።
✍ሳሚ ድንቅ ራዕይ ያለው ግሩም ወጣት ነው። ለብዙ ወጣቶች የሚሆንን ስራ እየሰራ ነው። እዩለት
👉አዳዲስ ነገሮችን ነው ይዞ የመጣው እና subscribe,like,share ይደረግ 👍
“በእርሱም ከጠላቶቻችን እጅ ድነን በዘመናችን ሁሉ ያለ ፍርሃት በቅድስናና በጽድቅ በፊቱ እንድናገለግለው ሰጠን።”
— ሉቃስ 1፥74-75
+1
ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን ቅዱሳን🙌
👩🦱እህቶች ለእናንተ ድንቅ ትምህርት ተዘጋጅቷል።
👉ከዚህ በቀደም በገላቲያ እና በሮሜ መልዕክት ትምህርቱ የተባረክንበት ወንድማችን ዮሴፍ ዘሪሁን መልዕክተ-እግዚአብሔርን "ልባም ሴት" በሚል ርዕስ አሰናድቶልናል።
🖌📚 🎧 ትምህርቱን እያዳመጣችሁ ማስታወሻ በመያዝ ለመባረክ ዝግጁ??
"ልባም ሴት" ተከታታይ ትምህርት
👉ሊንኩን እየነካችሁ join አድርጉ👉 https://t.me/Romansbiblestud
ከተስማማችሁ ❤️
ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን ቅዱሳን🙌
👩🦱እህቶች ለእናንተ ድንቅ ትምህርት ተዘጋጅቷል።
👉ከዚህ በቀደም በገላቲያ እና በሮሜ መልዕክት ትምህርቱ የተባረክንበት ወንድማችን ዮሴፍ ዘሪሁን መልዕክተ-እግዚአብሔርን "ልባም ሴት" በሚል ርዕስ አሰናድቶልናል።
🖌📚 🎧 ትምህርቱን እያዳመጣችሁ ማስታወሻ በመያዝ ለመባረክ ዝግጁ??
"ልባም ሴት" ተከታታይ ትምህርት
👉ሊንኩን እየነካችሁ join አድርጉ👉 https://t.me/Romansbiblestud
ከተስማማችሁ ❤️
👆observe the statics👆
እንጸልይ🙌
"በሰማይ የምትኖር አባታችን ሆይ በልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በአማራ ክልል ስምህ ይቀደስ።"
👉ወንጌል የሚናገሩ እግሮች ወደ አማራ ይፍጠኑ🙏
👉በክልሉ ሰላምና ጸጥታ ከጌታ ዘንድ ይሁን፣ መሪዎቻቸውም በእግዚአብሔር ይጠበቁ፣ ሰማያዊ ጥበብም ይብዛላቸው🙏
👉በአማራ ክልል ያለች የእግዚአብሔር ቤት ክርስቲያን በኢየሱስ ስም ከክፉ ሁሉ የተጠበቀች ትሁን🙏 መስፋትና መውረስም ይሁንላት🙏
🙌ዛሬ ይህንን ጸሎት ለአማራ የሕዝብ ክፍል አጥብቀን እንጸልይ🙏
ብሩካን ናችሁ✝
MYAFC
ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን የMYAFC ቤተሰቦች🙏
👉ለምን ዛሬ በሕይወት ቀጠልክ/ሽ❓
👉ለምን ኢየሱስ ክርስቶስ ተመልሶ አልመጣም❓
🙏መልሱ አንድ ነው! እርሱም ወንጌልን ሰምቶ በማመን የሚድን ነፍስ ስላለ🙏
📖“ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል።”
2ኛ ጴጥሮስ 3፥9
👉ለዚህ በሕይወት ለቀጠልንለት ለወንጌሉ ጉዳይ ማድረግ ያለብንን፦
1.ወንጌልን ላልሰሙት የሕዝብ ክፍሎች መጸለይ (1ኛ ጢሞ 2፥1-6፤ ማቴ 9፥37-38)
2. ወንጌል ወዳልደረሰባቸው አካባቢዎች በመሄድ መመስከር፤ ይሄ አጠገባችን ያሉትን ላላመኑ ሰዎችን መመስከርንም ያጠቃልላል። ለምሳሌ፦ ጎረቤት እና ጓደኛ
(ማቴ 28፥18-20)
3. ሦስተኛው የወንጌልን መልዕክት ይዘው ወንጌል ወዳልሰሙት የሕዝብ ክፍል የሚሄዱትን ሚሲዮኖችን መላክ ነው።
👉በዚህ ቤታችንም ከዚህ ቀደም ስናደርግ እንደ ነበረው የመጀመሪያውን ቅዱስ ሥራ እንሰራለን🙏
👉ወንጌል ላልደረሰባቸው የሕዝብ ክፍሎች አጥብቀን እንጸልያለን።
👍የሚስማማ ብቻ love emoji❤️
MY YOUTH AGE FOR CHRIST✝
#_በራሁ_Berahu_ፓስተር_እንዳለ_ወ_ጊዮርጊስ_Pastor_Endale_W_Giorgis256k.mp38.86 MB
"እልፍ ብዙ ብዙ ምህረት ማግኘቴ
አንዴ ገብቶ ጨርሶት ነው ዘላለሜን
ስለ ኃጢአቴ ይማልዳል ሊቀ-ካህኔ
ስራው አይደክምም በአብ ፊት ሊሆነኝ መታያዬ"
ዘማሪ ቢንያም ፀጋዬ
"አለመድከሙ"
ከጸጋ_መውደቅ_ማለት_ምን_ማለት_ነው❓
👉አብዛኛው ሰው "ከጸጋ መውደቅ" ማለት ከባድ ኃጢአት መሥራት ይመስለዋል።
ምናልባት ዋሽተህ ይሆናል፣ ወይም ደግሞ ወደ ቀድሞ ሱሱስ ተመልሰህ ሊሆን ይችላል፣ ወይም ደግሞ ለስድስት ወራት ያህል ቤተክርስቲያን ቀርተህ ይሆናል፤ በዚህ ጊዜ አንድ ሰው መጥቶ "ከጸጋ ወድቀሃል" ይልሃል። ጳውሎስ ግን ያለው ይህንን አይደለም።
📖ገላትያ 5፥4 እንዲህ ይላል፦ "በሕግ ልትጸድቁ የምትፈልጉ ከክርስቶስ ተለይታችሁ ከጸጋው ወድቃችኋል።"
👆ይህንን ቃል ቀስ ብላችሁ ደግማችሁ አንብቡት። ጳውሎስ ከጸጋ የወደቃችሁት ኃጢአት ስለሠራችሁ ነው አላለም። ከጸጋ የወደቃችሁት በእግዚአብሔር ፊት ለመቆም ወደ ሕግ ሥርዓት ስለተመለሳችሁ ነው እንጂ።
✍️ የገላትያ ሰዎች የሚታገሉት ከሥነ-ምግባር ብልሹነት ጋር አልነበረም፤ የሚታገሉት ከሃይማኖታዊ ሥርዓት ጋር ነበር። ጳውሎስ በሄደ ማግስት "ወግ አጥባቂዎች" የሆኑ መምህራን መጡና ለአዲሶቹ አማኞች እንዲህ አሏቸው፦ "በክርስቶስ ማመን ጥሩ ነው፣ ግን ብቻውን በቂ አይደለም፤ መገረዝ አለባችሁ፤ ሙሴን መከተል አለባችሁ፤ በጸጋ ላይ ሕግን መጨመር አለባችሁ።"
ጳውሎስ በዚህ ተቆጣ። ይህንን አመለካከት "ሌላ ወንጌል" ብሎ ጠራው። ይህንን የሚሰብክ ማንኛውም ሰው፣ መልአክ እንኳ ቢሆን "የተረገመ ይሁን" አለ። ስህተቱ ምን ያህል ከባድ እንደነበር ከዚህ መረዳት ይቻላል።
✍️ ጸጋ ለውድቀታችሁ መሸፈኛ ብቻ አይደለም፤ ጸጋ ሙሉ በሙሉ የተለየ ሥርዓት ነው።
👉ጸጋ ማለት እግዚአብሔር አንተ ስላደረግኸው ነገር ሳይሆን ክርስቶስ ስላደረገው ነገር አንተን "ጻድቅ" ብሎ የሚያውጅበት መንገድ ነው። ሮሜ 4፥5
እንዲህ በማለት በግልጽ ያስቀምጠዋል፦ "ነገር ግን ለማይሠራ፥ ኃጢአተኛውንም በሚያጸድቅ ለሚያምን ሰው እምነቱ ጽድቅ ሆኖ ይቆጠርለታል።"
✍️በጸጋ ላይ ሕግን ስትጨምር የበለጠ ቅዱስ እየሆንክ አይደለም። ይልቁንም ያለቀለትን የክርስቶስን ሥራ እየናቅህ ነው። ደሙ በቂ አይደለም እያልክ ነው። መስቀሉ የእኔን እርዳታ ይፈልጋል እያልክ ነው። ከጸጋ መውደቅ ማለት ይህ ነው።
✍️የገላትያ መልእክት የተጻፈው በመጀመሪያው ክፍለ ዘመን ለነበሩ አማኞች ነው። በወቅቱ የብሉይ ኪዳን ሥርዓት በአካል ገና አልፈረሰም ነበር፣ ቤተ መቅደሱም ነበረ። ወደ ሙሴ ሕግ ለመመለስ የሚደረገው ተጽዕኖ በጣም ከባድ ነበር። ጳውሎስ ገላቲያን የጻፈው በ2018 ወይም በ2026 ዓ.ም ሆነን በሐሳብ ደረጃ ለምንከራከር ሰዎች አይደለም፤ ያንኑ ዕለት ወደ ምኩራብ ሄደው መገረዝ ለሚችሉ ሰዎች እንጂ።
✍️ኢየሱስ በ ማቴዎስ 5፥18 ላይ "ሁሉ እስኪፈጸም ድረስ ከሕግ አንዲት የውጣ ወይም አንዲት ነጥብ አታልፍም" ሲል፣ ያንን ፍጻሜ ስለሚያየው ትውልድ እየተናገረ ነበር። ቤተ መቅደሱ ሲፈርስ ያ የብሉይ ኪዳን ዘመን ሙሉ በሙሉ አበቃ። ወደ እግዚአብሔር ለመቅረብ እንደ ሥርዓት የሚያገለግለው ሕግ አበቃ። ዕብራውያን 8፥13 ብሉይ ኪዳን አርጅቶ ሊጠፋ እንደቀረበ ይናገራል። እናም አብቅቷል።
👉ስለዚህ በዚያን ጊዜ ከጸጋ መውደቅ በጣም አደገኛ ነበር፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር ራሱ ሊያፈርሰው ወዳለው ሥርዓት መመለስ ማለት ነበር።
✍️ ዛሬም መሠረታዊው አተገባበር ያው ነው። በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት ለማግኘት የሃይማኖታዊ አፈጻጸም ዝርዝር ስታዘጋጅ:- አሥራት ማውጣት፣ ዘወትር ቤተክርስቲያን መገኘት፣ ለተወሰኑ ቀናት መጾም፣ የተወሰኑ ምግቦችን አለመብላት፣ ልዩ ቀናትን መጠበቅ፣ ወይም ከውድቀት በኋላ ወደ እግዚአብሔር ለመመለስ በራስህ ጥረት ዋጋ ለመክፈል ስትሞክር ከጸጋ ሥርዓት ወደ ሕግ ሥርዓት ተመልሰሃል ማለት ነው። ራስህን ባለዕዳ አድርገሃል።
ገላትያ 5፥3 ከቁጥር 4 ቀደም ብሎ እንዲህ ይላል፦ “ሕግንም ሁሉ እንዲፈጽም ግድ አለበት ብዬ ለሚገረዙት ሁሉ ለእያንዳንዶች ደግሜ እመሰክራለሁ።"
👆አንዴ ለመጽደቅ ወደ ሕግ መሰላል ላይ ከወጣህ፣ ሁሉንም ሕጎች የመጠበቅ ግዴታ አለብህ። መርጦ መጠበቅ አይቻልም። አንዱን መርጠህ ሌላውን መተው አትችልም።
ሮሜ 3፥20 ደግሞ ይህ የት እንደሚያደርስ በግልጽ ይነግረናል፦ "የሕግን ሥራ በመሥራት ሥጋ የለበሰ ሁሉ በእርሱ ፊት ስለማይጸድቅ።"
👉መጸለይ ስላቃተህ ከጸጋ አልወደቅህም።
👉በመውደቅህ ከጸጋ አልወደቅህም።
👉በመጠራጠርህ ከጸጋ አልወደቅህም።
👉መባና አስራት መስጠት ስላቆምክ ከጸጋ አልወደቅህም።
👉 ፆም ፀሎት ስላቆምክ ከጸጋ አልወደቅህም።
👉ከጸጋ የምትወድቀው የጸጋን ሥርዓት ትተህ ወደ ሕግ ሥርዓት ስትመለስ ብቻ ነው።
📌 እኔ ተቀባይነት ያገኘሁት በክርስቶስና በክርስቶስ ብቻ ነው" ወደሚለው ሐሳብ በተመለስክበት ቅጽበት፣ ድጋሚ በጸጋ ላይ ትቆማለህ።
#ጸጋ_በክርስቶስ_የተፈጸመ_ሥራ_ነው!
ፓስተር ጸጋዬ ግርማ🎙
“ዓይኖቼን ክፈት፥ ከሕግህም ተኣምራትህን አያለሁ።”
— መዝሙር 119፥18
📖 MYAFC✝
ነፍሴ_ተርባሃለች_by_Gosquala_sew_ጎስቋላ_ሰው_Nefse_Teribahalech_new_Amharic.mp36.24 MB
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
