HOP Ministry
Ir al canal en Telegram
HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. A discipleship platform sharing devotionals, revival histories, spiritual biographies, testimonies, and Amharic Christian literature to build Christ-like lives. Based on Luke 11:28.
Mostrar másEl país no está especificadoLa categoría no está especificada
445
Suscriptores
+224 horas
+237 días
+6630 días
Archivo de publicaciones
446
#የእግዚአብሔር_አብሮነት_ከከነዓን_ይበልጣል።
የእግዚአብሔር አብሮነት ከከነዓን ይበልጣል።
ለእግዚአብሔር ሕዝብ፦ የእግዚአብሔር አብሮነት የሌለበት ከነዓን ሕይወት አይሆነውም፣ አይረባውም።
የእግዚአብሔር ሕዝብ ልዩነትና ሞገስ፦ ያለው ሀብት፣ በረከት፣ የሚወርሰው ከነዓን ሳይሆን፤ ሁሉን ሰጪው፣ የባርኮቱ ምንጭ የሆነው አምላኩ እግዚአብሔር ነው።
የእግዚአብሔር አብሮነት የሌለበት ከነዓን አይረባንም። አብሮነቱ በሌለበት ከሚሰጠን ከነዓን ይልቅ፤ ሁሉን አጥተን እግዚአብሔርን ማግኘት፣ በእርሱም መገኘት ይብዛልን!!
ከእግዚአብሔር ሀልዎት ውጪ እኛን ሕያው፣ ልዩ፣ ባለ ሞገስ የእግዚአብሔር ሕዝብ የሚያደርገን ምን አለ?
ዘጸአት 33 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁴ እግዚአብሔር (ያህዌ) “ሀልዎቴ ከአንተ ጋር ይሄዳል፤ ዕረፍትም እሰጥሃለሁ” ብሎ መለሰ።
¹⁵ ከዚያም ሙሴ እንዲህ አለው፤ “ሀልዎትህ ከእኛ ጋር ካልሄደ ከዚህ አትስደደን።
¹⁶ አንተ ከእኛ ጋር ካልሄድህ፣ አንተ በእኔና በሕዝብህ መደሰትህን ሌላው እንዴት ያውቃል? እኔንና ሕዝብህንስ በገጸ ምድር ከሚገኙት ከሌሎቹ ሕዝቦች ሁሉ ልዩ የሚያደርገን ሌላ ምን አለ?”
✍️ መክሊት አየለ
📆 July 21, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
446
So Will I (100 Billion X)
Song by Hillsong Worship and Taya ‧ 2018
"God of creation
There at the start
Before the beginning of time
With no point of reference
You spoke to the dark
And fleshed out the wonder of light
And as You speak
A hundred billion galaxies are born
In the vapour of Your breath the planets form
If the stars were made to worship so will I
I can see Your heart in everything You've made
Every burning star
A signal fire of grace
If creation sings Your praises so will I
God of Your promise
You don't speak in vain
No syllable empty or void
For once You have spoken
All nature and science
Follow the sound of Your voice
And as You speak
A hundred billion creatures catch Your breath
Evolving in pursuit of what You said
If it all reveals Your nature so will I
I can see Your heart in everything You say
Every painted sky
A canvas of Your grace
If creation still obeys You so will I
So will I
If the stars were made to worship so will I
If the mountains bow in reverence so will I
If the oceans roar Your greatness so will I
For if everything exists to lift You high so will I
If the wind goes where You send it so will I
If the rocks cry out in silence so will I
If the sum of all our praises still falls shy
Then we'll sing again a hundred billion times
God of salvation
You chased down my heart
Through all of my failure and pride
On a hill You created
The light of the world
Abandoned in darkness to die
And as You speak
A hundred billion failures diappear
Where You lost Your life so I could find it here
If You left the grave behind You so will I
I can see Your heart in everything You've done
Every part designed in a work of art called love
If You gladly chose surrender so will I
I can see Your heart
Eight billion different ways
Every precious one
A child You died to save
If You gave Your life to love them so will I
Like You would again a hundred billion times
But what measure could amount to Your desire
You're the One who never leaves the one behind"
446
"And as You speak
A hundred billion failures diappear
Where You lost Your life so I could find it here
If You left the grave behind You so will I
I can see Your heart in everything You've done
Every part designed in a work of art called love
If You gladly chose surrender so will I"
446
#ኢየሱስ_ማን_መሆኑን_በቅጡ_ማወቅ!
ብዙ ነገሮች አጥተን ኖረን አይተነዋል፤ ብዙ ነገሮች ጥለውን ሄደው ስንቀጥል ራሳችንን አግኝተናል። ጌታ ኢየሱስን ላየ፣ ቸርነቱን ለቀመሰ ሰው ግን ከኢየሱስ መለየት፣ ያለ እርሱም መኖር ሞት ነው። የኢየሱስ ሁሉ በሁሉነት ሲገባን የሚያስፈልገን እርሱ ብቻ እንደሆነ፤ ያለ እርሱ መኖር፣ ምንም ማድረግ እንደማንችል እንረዳለን።
ኢየሱስ ከያዕቆብ ጉድጓድ መብለጡ የእውነት ለገባው ሰው ኢየሱስ ጊዜያዊ ጥምን የሚያረካ ነገር ሳይሆን የዘላለም ውኃ ምንጭ፣ የሕይወት ውኃ ነው። ኢየሱስ ማን መሆኑን ማወቅ የዘላለም ሕይወትን ማትረፍ ነው። ያውም ትርፉ በምድር ስሌት የማይሰላ ዘላለማዊ ትርፍ ነው።
ሳምራዊቷ ሴት ኢየሱስ ማን መሆኑን በቅጡ ሳትረዳ በፊት የያዕቆብ ጉድጓድ የምታዜምለት፣ ታላቅነቱን የምትመሰክርለት፣ ከእርሱ ሌላ ምንጭ ያለ እንኳ እስካይመስላት ድረስ የምትመካበት ምንጯ ነበር።
የኢየሱስ የዘላለም ውኃ ምንጭነት ሲገባት ግን አይደለም ደግማ ስለ ያዕቆብ ጉድጓድ ልታወራ፣ "አንተ ይህን ጉድጓድ ከሰጠን ከአባታችን ከያዕቆብ ትበልጣለህን?" ብላ ኢየሱስን ከያዕቆብ ጋር ልታወዳድር ይቅርና ስለ ኢየሱስ የዘላለም ውኃ ምንጭነት መለስ ብላ ለማሰብና ለመጠራጠር እንኳ ጊዜ አላገኘችም። ለእርሷ የበራላት ብርሃን ለብዙዎች እንዲበራ፣ ያየችውን ብዙዎች እንዲያዩት፣ የገባትንና የቀመሰችውን እውነት፣ ሕይወት ብዙዎች እንዲቀምሱ፣ ብዙዎችን ወደ እርሱ ልታፈልስ ወደ ሕዝቡ ሮጠች፤ እርሱ ማን መሆኑን አውቃለችና።
ኢየሱስ ማን መሆኑን በቅጡ ማወቅ፦ ከብዙ ብክነት፣ በአላስፈላጊ፣ በሰው ሰራሽ፣ ጥምን በማይቆርጡ፣ በጥቃቅን ምንጮች ከመርካት ይጠብቃል፤ እርሱን ብቻ ለመጠማት፣ ከእርሱ ብቻ ለመጠጣት፣ በእርሱ ብቻ ለመርካት ይጠቅማል። ኢየሱስን በማንነቱ ማወቅ፣ እርሱ ማን መሆኑን በቅጡ መረዳት፣ ማስተዋል ይሁንልን!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 July 19, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
446
#የማያልቅ_ርዕሰ_ጉዳይ!
በምድር ስላሉት ጉዳዮቻችን፣ ስለምንፈልጋቸውና ስለሚያስፈልጉን ነገሮች የምንጸልየው ፀሎት በፀሎት መልስ ይሻራል። መልሳችንን ስንቀበል፣ የጠየቅነውን ነገር ስናገኝ ፀሎቱን እንተወዋለን፣ እንቀይረዋለን።
ስለ ራሱ ስለ እግዚአብሔር፣ ስለ መገኘቱ፣ ስለ ሕልውናው፣ ስለ መንፈሱ የሚደረግ ፀሎት ግን ጊዜ የማይሽረው፤ አሁንም፣ ዛሬም፣ ነገም፣ ከነገ በስቲያ፣ በምድር እስካለን ድረስ፣ ጌታን ፊት ለፊት እስከምናየው ድረስ የሚዘልቅ፣ መዝለቅ ያለበት ፀሎት ነው።
በጊዜያዊ ነገሮች ላይ የፀና ፀሎት እንደተቀያየረ፣ እንደዋዥቀ ይኖራል፤ ድካም አለበት፣ ጉልበትን ያዝላል። ዘላለማዊውን ነገር፣ ዘላለማዊውን አምላክ ለማግኘት የሚደረግ መቃተት ግን ሕይወት አለበት፤ ጸላዩን፣ ፈላጊውን ሕያው እያደረገ፣ እያለመለመ ይሄዳል፤ በቃኝም አይባልም ሌላ እልፍ ረሃብ ይወልዳል።
ጌታ በቸር እጆቹ ይንካን፤ ቸር መሆኑን ያቅምሰን፤ ያኔ እያየነው፣ እያገኘነው፣ በእርሱ እየተዳሰስንና እየተነካን፦ የያዝነው አይመስለንም፣ አብረነው ሆነን ይናፍቀናል፣ የእርሱ እልፍ ረሃብ ይበዛልናል፣ ጌታን ጌታን ብለን እየናፈቅነው፣ እያገኘነው ይርበናል፣ ይርበናል....፣ እርሱን መከተል፣ መከታተል ስራችን ይሆናል።
ከምንፈልገው፣ ከሚያስፈልጉንም ነገሮች በላይ እግዚአብሔር፣ መንፈስ ቅዱስ፣ ኢየሱስ ያስፈልገናል። እግዚአብሔርን እየፈለግን መፈለግ፣ እየናፈቅን መናፈቅ ይሁንልን!! የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር እንኳ ሳይቀር የምትመረምረው መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር በሆነው ነገር ሙላን!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 July 18, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
446
ከምንፈልገው፣ ከሚያስፈልጉንም ነገሮች በላይ እግዚአብሔር፣ መንፈስ ቅዱስ፣ ኢየሱስ ያስፈልገናል። እግዚአብሔርን እየፈለግን መፈለግ፣ እየናፈቅን መናፈቅ ይሁንልን!!
🌿 HOP Ministry — Hear. Obey. Practice.
https://t.me/hopministry10
446
ሌሎች ረሃቦቻችንን ሁሉ ተቀምተን #በአንድ_ረሃብ (በእግዚአብሔር ብቻ) ብንጠመድ፣ ሌላውን ለማየት፣ ለመስማት፣ ለመንካት፣ ለመብላት አቅም አጥተን ለሕይወት ቃል፣ ለሕይወት ውሃ፣ ለሕይወት ውሃ ምንጭ ረሃብ፣ ጥማት ብንበረታ፤ የጌታ የፍቅሩ ትኩሳት የልባችንን ጓዳ ቢያሞቀው፣ ለብታችን በፍቅሩ እሳት ግለት ቢሻር፣ ትናንት ባላየነው መንገድ ጌታ ቢያገኘን፣ መሰዊያችን ቢታደስ፣ ከማለዳ እስከ ምሽት የቃሉ አሰላስሎት አሳባችንን ቢቆጣጠረው፣ ማብቂያዋ መቼ እንደሆነ የማይታወቀው እንፋሎት ዘመናችን ለኢየሱስ እየነደደች የምታበራ መብራት ብትሆን.....ይሄ ሁሉ ልቤ የሚብሰለሰልበት፣ ጌታ በኃይሉ ችሎት ቢያደርግልን ብዬ የምናፍቀው ናፍቆቴ፣ ቁጭቴ ነው።
ናፍቆቴን እንደምትጋሩኝ እምነቴ ነው፤ ይህ ሁሉ በእኛ እውን እንዲሆን የመንፈስ ቅዱስ ጉብኝት ያግኘን!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 April 12, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
446
እግዚአብሔርን አምነን፣ ታምነን በመንገዱ ላይ እየሄድን ከሆነ፦ እርሱ አላዘገየንም፣ አላስቸኮለንም፤ እርሱ ሁሉን በፈቃዱ ምክር መሰረት እየሰራ ይገኛል።
ረፈደብኝ፣ ወደኋላ ቀረሁ፤ መፍጠን ከሚገባኝ በላይ ፈጥኜ በአላስፈላጊ መንገድ ተጓዝኹ አንበል። እግዚአብሔር ብቻውን መምራት፣ ከግብ ማድረስም ያውቅበታልና ሕይወታችንን በመሪያችን እጅ ላይ በእምነት እናኑር፤ እግዚአብሔርን አምነን፣ ሳናይ እንከተለው፣ እንከታተለው። በእግዚአብሔር መንገድ ፀንተን አንጸጸትም፤ እርሱ ያሳርፈናል!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 July 16, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
446
🌿 HOP Ministry — Hear. Obey. Practice.
በእግዚአብሔር መንገድ ፀንተን አንጸጸትም፤ እርሱ ያሳርፈናል!!
https://t.me/hopministry10
446
““እናንት ሸክም የከበዳችሁና የደከማችሁ ሁሉ ወደ እኔ ኑ፤ እኔም ዕረፍት እሰጣችኋለሁ።”
— ማቴዎስ 11፥28 (አዲሱ መ.ት)
“እርሱ ስለ እናንተ ስለሚያስብ የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት።”
— 1ኛ ጴጥሮስ 5፥7 (አዲሱ መ.ት)
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
446
Lay It All Down
Song by United Pursuit and Will Reagan ‧ 2017
" Bring your worry, grief, and pain
Every cause you have for shame
Lay it all down
Lay it all down
When your cares have buried you
And there's nothing left to do
Lay it all down
Lay it all down
At the feet of Jesus
At the feet of Jesus
Carried on but your heart was tired
Feared the worst and felt the fire
Lay it all down
Lay it all down
Filled with all those anxious thoughts
And your doubts became your god
Lay it all down
Lay it all down
At the feet of Jesus
At the feet of Jesus
Lay it all down, lay it all down
Lay it all down, lay it all down
Lay it all down, lay it all down
Lay it all down, lay it all down (won't you lay it down?)
Lay it all down, lay it all down
Lay it all down, lay it all down (lay it all down)
At the feet of Jesus
Down, at the feet of Jesus
When we've given up on better days
There are memories we can't erase
Lay it all down
Lay it all down
When we've come to fear what we can't explain
And there's nothing here that can ease the pain
Lay it all down
Lay it all down
At the feet of Jesus
At the feet of Jesus
Lay it all down, lay it all down
Lay it all down, lay it all down
Lay it all down, lay it all down
Lay it all down, lay it all down (won't you lay it all down?)
Lay it all down, lay it all down
Lay it all down, lay it all down
Down, at the feet of Jesus
At the feet of Jesus
Lay it all down, lay it all down
Lay it all down, lay it all down (won't you lay it all down?)
Lay it all down, lay it all down
Lay it all down, lay it all down (down at the feet)
Lay it all down, lay it all down
Lay it all down, lay it all down
At the feet of Jesus (lay it down at the feet)
At the feet of Jesus
Lay it all down, lay it all down (lay it all down)
Lay it all down, lay it all down (lay it down)
Lay it all down, lay it all down (down, down, down, down)
Lay it all down, lay it all down
Lay it all down, lay it all down
Lay it all down, lay it all down (lay it down)
At the feet of Jesus
At the feet of Jesus"
446
#የምስራች፦
#እግዚአብሔር_ለደካሞች_ኃይላቸው_ነው።
ደካሞች በእግዚአብሔር ይበረታሉ፣ ይታደሳሉ። ድካም በእግዚአብሔር ፊት ድካም ሆኖ አይቀጥልም፤ በብርታት ይቀየራል።
እግዚአብሔር ለደካማው ኃይል ይሆናል፤ ዝለት በእግዚአብሔር ፊት እንዳልነበር ይሆናል፤ እግዚአብሔር ኃይላቸው መሆኑን አምነው የተጠጉት፣ በመተማመን የሚጠባበቁት፦ ከድካም ተፋተው፣ ኃይላቸውን አድሰው፣ እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ፤ አይደክሙም፣ አይታክቱም፤ ምክንያቱም የኃይል ሁሉ ምንጭ የሆነው ኃያል አምላክ ኃይል ይሆናቸዋልና።
ድካም በእግዚአብሔር እንደሚረሳ፣ እንደሚቀየር፣ እንደሚነሳ፤ እግዚአብሔርም ለደካማ ኃይል እንደሚሆን እኔ ምስክር ነኝ።
የተሰበረው ልቤን አድምጦ፣ ደክሞኛል፣ አልቻልኩም ከሚለው ቃሌ ቀድሞ ሲያነሳኝ፣ ሲጠግነኝ፣ ኃይል ሲሆነኝ እግዚአብሔርን እልፍ ጊዜ አይቼዋለሁ። በድካሜ ያላሸማቀቀኝ፤ ይልቁንም ያበረታኝ፣ ኃይል የሆነኝ እግዚአብሔር ለደካሞች ኃይላቸው ነው ስል በድፍረት እመሰክራለሁ።
የምስራች:- እግዚአብሔር ለደካሞች ኃይላቸው ነው!!
ኢሳይያስ 40
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁷ ያዕቆብ ሆይ፥ እስራኤልም ሆይ፦ መንገዴ ከእግዚአብሔር ተሰውራለች ፍርዴም ከአምላኬ አልፋለች ለምን ትላለህ? ለምንስ እንዲህ ትናገራለህ?
²⁸ አላወቅህምን? አልሰማህምን? እግዚአብሔር የዘላለም አምላክ፥ የምድርም ዳርቻ ፈጣሪ ነው፤ አይደክምም፥ አይታክትም፥ ማስተዋሉም አይመረመርም።
²⁹ ለደካማ ኃይልን ይሰጣል፥ ጕልበት ለሌለውም ብርታትን ይጨምራል።
³⁰ ብላቴኖች ይደክማሉ ይታክቱማል፥ ጐበዛዝቱም ፈጽሞ ይወድቃሉ፤
³¹ እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን ያድሳሉ፤ እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ፤ ይሮጣሉ፥ አይታክቱም፤ ይሄዳሉ፥ አይደክሙም።
✍️ መክሊት አየለ
📆 July 15, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
