en
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Open in Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Show more
2 926
Subscribers
+3224 hours
+3727 days
+36630 days
Posts Archive
ሰበር ዜና በቅርቡ ያስመረቅናቸው የጮቄው ነብርርርር 201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር በጥዋት ዲሽቃ፣ብሬን፣ ስናይፐር፣ክላሽ በገፍ ተማርኳ በዝርዝር እንመለሳለን #Dave #Amhara
ሰበር ዜና በቅርቡ ያስመረቅናቸው የጮቄው ነብርርርር 201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር በጥዋት ዲሽቃ፣ብሬን፣ ስናይፐር፣ክላሽ በገፍ ተማርኳ በዝርዝር እንመለሳለን #Dave #Amhara

በአፋብን 1ኛ ምኒልክ ዕዝ እና 5ኛ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ለአምስት ወር በጋራ ሲስለጥኑ የነበሩ ምልምል የሰራዊት አባላት በዛሬዉ ዕለት ተመረቁ! ​በአፋብን 1ኛ ምኒልክ ዕዝ (15ኛ ኮር 45ኛ መብረቅ ክፍለጦር) እና በ5ኛ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ (1ኛ አፄ ዘርያቆብ ኮር በፍቃዱ በላይ ክፍለጦር) አዘጋጅነት ለተከታታይ አምስት ወራት የቆየውን ወታደራዊ ሥልጠና ሲከታተሉ የነበሩ ምልምል የፋኖ አባላት በዛሬው ዕለት ነሐሴ 10 ቀን 2018 ዓ.ም. በደማቅ ሥነ-ሥርዓት ተመርቀዋል። ​በዚሁ የምረቃ መርሐግብር ላይ የምኒልክ ዕዝ ከፍተኛ አመራር አርበኛ አማረ አያሌው፣ የዕዙ ማሕበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ሐጅ ኑረዲን አበበ ሐሰን፣ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ ዘርያቆብ ኮር ሎጀስቲክስ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ጌታሁን ቦጋለ፣ በፍቃዱ በላይ ክፍለጦር ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ በላቸው እሸቴ፣ የ45ኛ መብረቅ ክፍለጦር አዛዥ አርበኛ ሃጂ ንጉሴ ሃሚድ፣ የ45ኛ ክፍለጦር ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ በቃሉ አስማማው (ቼኩቬራ) ጨምሮ ሌሎች የኮርና የክፍለጦር አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ ተከናውኗል። ​በመርሐግብሩ ወቅት ንግግር ያደረጉት ተጋባዥ እንግዶች ተመራቂዎች የተሸከሙትን የትግል አደራ እና የተሰው ጓዶቻቸውን መስመር ጠብቀው፣ በቀጣይ ለሚገጥሟቸው ማንኛውም ዓይነት ተግዳሮቶች ሙሉ በሙሉ ዝግጁ እንዲሆኑ አሳስበዋል። ​ተመራቂዎቹ በበኩላቸው ላለፉት አምስት ወራት ከቀሰሙት ተግባራዊና ፅንሰ-ሀሳባዊ ወታደራዊ ትምህርት በመነሳት ለክብር እንግዶቹ የሚመጥን ወታደራዊ ትርኢት አቅርበዋል። በተጨማሪም የተሰው ጓዶቻቸውን አደራ በመጠበቅ፣ ለአማራ ሕዝብ ሕልውና መከበርና ከተጋረጠበት አደጋ ለመታደግ የተጣለባቸውን ማንኛውንም ግዳጅ በብቃት ለመወጣት ቃል-መሐላ በመፈጸም መርሐግብሩ በደማቅ ሁኔታ ተጠናቋል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ወሎ ቤተአማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ! ነሐሴ 10/2018 ዓ.ም

ለፈረንሳዩ ጋዜጣ፤ የአፋብን ሊቀመንበር አርበኛ ዘመነ ካሴ ካነሷቸው ነጥቦች መካከል፦ 1ኛ, የፋኖ የትጥቅ ትግል ዓላማን ሲያብራሩ፦ የአማራ ህዝብን ህልውናን ማስከበር፤ የኢትዮጵያን አንድነት መጠበቅና አገሪቱን ከውድቀትና ብተና መታደግ ነው። 2ኛ, ከዚህ ቀደም በየ ጠቅላይ ግዛቱ፣ ዕዝ መስርተው አገዛዙን ሲታገሉ የነበሩ የፋኖ ኃይላት፣ አሁን በአንድ በተዋሃደ ዕዝ እንድ ማዕከላዊ ድርጅት ስር መሰባሰባቸውን ገልፀዋል። 3ኛ, አገዛዙ በድሮን፣ በከባድና በቡድን መሳሪያዎች ንፁሃን አማራዎችን፣ የእምነት ተቋማትን፣ ትምህርት ቤቶችን፣ የጤና ተቋማትንና የአርሶ አደሩን መጠለያና ሀብት ንብረት እያወደመ እንደሚገኝ ገልፀዋል። 4ኛ, የተባበሩት ዓረብ ኢምሬትስን (UAE ) የመሳሰሉ የውጭ አገራት፤ ለአገዛዙ የድሮንና የተተኳሽ ድጋፎችን ከማድረግ ባሻገር የቴክኒክ ድጋፍ የሚሰጡ የሰው ኃይላትን ጭምር ለአገዛዙ ድጋፍ እያደረጉ እንደሆነ አጋልጠዋል። 5ኛ, በአገር ውስጥ ከሚገኙ ፀረ አገዛዙ የታጠቁ ኃይሎች ጋር አብሮ ለመስራት ንግግሮች መኖራቸውንና በሩ ክፍት መሆኑን አንስተዋል። 6ኛ, የትጥቅ ትግሉ የመጨረሻ ግብ፣ የአገዛዙን ቁንጮ ከስልጣን በማውረድ ስር ነቀል የአስተዳደር ስርዓት በመገንባት፣ ለሁሉም ኢትዮጵያዊያን ፍትህ፣ የሕግ የበላይነትና እኩልነትን የሚያሰፍን መንግስታዊ ስርዓት መትከል እንደሆነ ጠቁመዋል። ነሐሴ 10/2018 ዓ.ም

አርበኛ ዘመነ ካሴ ፋኖ የተባበረ ዕዝ መመስረቱን እና መንግስትን ለመጣል አዳዲስ ጥምረቶችን መፍጠሩን አስታወቁ:: በስዊዘርላንድ ለሚታተመው «ሌ ቴምፕስ» (Le Temps) ጋዜጣ ሰፊ ቃለ ምልልስ የሰጡት የፋኖ ንቅናቄ መሪ አርበኛ ዘመነ ካሴ፣ ቡድናቸው የተባበረ ማዕከላዊ ዕዝ መመስረቱን ይፋ አድርገዋል። «የምንታገለው ለነጻነት እና ለእኩልነት ነው» በሚል ርዕስ በወጣው የጋዜጣው ዘገባ መሠረት፣ የንቅናቄው ዋነኛ ዓላማ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን መንግስት ከስልጣን ማስወገድ፣ የአማራን ህዝብ ህልውና ማስጠበቅ እና የኢትዮጵያን መበታተን መከላከል መሆኑን አርበኛ ዘመነ አስታውቀዋል። አርበኛ ዘመነ ካሴ በማብራሪያቸው ከዚህ ቀደም በሸዋ፣ ወሎ፣ ጎንደር ፣ በጎጃም እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል በወለጋ አቅራቢያ በተናጠል ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የፋኖ ኃይሎች አሁን ላይ በአንድ ማዕከላዊ ዕዝ ሥር መሰባሰባቸውን ገልፀዋል። ከዚህም በተጨማሪ፣ ፌደራል መንግስቱን ለመጣል በማሰብ በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ወቅት ይዋጓቸው ከነበሩት የትግራይ ኃይሎች ጋር መወያየታቸውን እና ጥምረት መፍጠራቸውን ገልጸዋል። ይህ ትብብር ከትግራይ ኃይሎች ባሻገር ከጉሙዝ፣ ቤርታ፣ ሶማሌ እና ኦሮሞ ኃይሎች ጋርም መደረጉን መሪው በቃለ ምልልሳቸው አብራርተዋል። በጦር ሜዳው ስላለው የኃይል ሚዛን የተናገሩት አርበኛ ዘመነ ካሴ፣ የፋኖ ኃይሎች በአሁኑ ወቅት ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነውን የገጠር አካባቢ እና በርካታ ትናንሽ ከተሞችን መቆጣጠራቸውን ተናግረዋል። አያይዘውም መንግስት ወደ ክልሉ ካሰማራቸው 13 የጦር እዞች ውስጥ አሥሩን በውጊያ ገጥመዋቸው ማሸነፋቸውን ገልጸዋል። በሌላ በኩል፣ መንግስት በንፁሃን ዜጎች፣ ትምህርት ቤቶች፣ ገበያዎች እና የአባይ ጊዮርጊስ ቅድስት አርሴማን ጨምሮ በገዳማት ላይ ያለምንም ልዩነት የድሮን ጥቃት እየፈፀመ ነው ሲሉ ከሰዋል። ለዚህም የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች የቱርክ ሰራሽ ድሮኖችን ለመንግስት በማቅረብ እንዲሁም እስራኤላውያን የቴክኒክ ድጋፍ በማድረግ በኢትዮጵያ ጉዳይ ጣልቃ እየገቡ መሆኑን አርበኛ ዘመነ ካሴ በብርቱ ተችተዋል።

በአብይ አህመድ ስርዓት ላይ ጠጠር ከሚወረውሩ ሃይሎች ሁሉ አብረን እንቆማለን!! የአፋብንን ተጋድሎ በአምስተኛ ሰልፍ ተሳለፊ ግለሰቦች ለመጥለፍ መሞከር የማህበራዊ ክደት ፀያፍ ተግባር ነው። ➤.የምንዋጋው ዘረ ፈጁን ጠላት ነው። ➤.የምንዋጋው አረመኔውን የብልፅግና ሃይል ነው!! ➤.የምንዋጋው ጠቅላይ እና ስግብግብ የሆነውን የኦህደድ ሃይል ነው!! ➤.የምንዋጋው የጥንት ጠላቶቻችን ዋና ፍላጭ ነው!! ➤.የምንዋጋው አማራን በኢትዮጲያ ሰማይ ስር ሲገድል እና ሲጨፈጭፈው ከሚውለው ወራሪ ሃይል ነው!! ታዲያ አማራ እና ኢትዮጲያ ከብልፅግና በላይ ማን ክፉ ጠላት አላቸው ?? መልሱን ለእናንተው ትቼዋለሁ!! እኛ ግን እንላለን!! ✅የአማራን ህዝብ ከብሔራዊ ከበባ ለማውጣት በብልፅግናው ስርዓት የህልውና አደጋ ከገጠማቸው የትኞቹም ሃይሎች ጋር በትብብር እንሰራለን። ✅አላማችን ግልፅ ነው። እርሱም የአማራን ህዝብ ህልውና ማረጋገጥ ይሆናል። ✅መረረኸም ጣፈጠኸም ትብብሩ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ✅በአማራ ህዝብ እና በልጆቹ ትግል ዕጣ ፋንታ ወሳኞቹ እኛው ነን። አሉባልታን እንደ ግብአት ጥርጣሬን እንደ መሳሪያ በመጠቀም በህዝባችን ትግል ላይ ዳግም በቀል ለመፈፀም መሞከር ተቀባይነት የለውም። እኛ በቀለኞች አይደለንም እንጅ በአምስተኛው ሰልፍም ውስጥ የሚገኙ ግለሰቦች በአማራው ህዝብ መብት እና ጥቅም ላይ የዋለ ያደረ ክፉ ሃሳባችሁን ሳናውቅ ቀርተን አልነበረም!! ዘፋኙ "አለፈ ያ ዘመን" እንዳለው በህልውና ትግላችን ውስጥ ስርገትን እንደ መደላድል ተጠቅመው አዛዥ ናዛዥ ለመምሰል እዚህም እዛም ለሚሉ "በድርብ ማንነት እና የስነ ልቦና ማታለል" ውስጥ ለሚገኙ አካላት ጩኸት ቦታ አንሰጥም!! ዝንታለም አማራ ወይራው አማራ

የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አከበር ስመኘው🙏 * የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር ነጎድጓድ ክፍለ ጦር ወጣት
+5
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አከበር ስመኘው🙏                    * የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር ነጎድጓድ ክፍለ ጦር ወጣት መሪዎች፤ የታዛዢነት፣ የብስለትና የጀግንነት አርአያዎች! ​በየክፍለ ጦሩ የአማራውን ነገ የሚያሳምሩና የድርጅት ፍሬ የሆኑ በርካታ ኩራት የሆኑ ወጣት መሪዎች አሉን። ከነጎድጓድ ክፍለ ጦር ወንድሞቼ ጋር በነበረኝ የፖለቲካና ወታደራዊ ውይይት የተለየ ብስለት፣ ጥበብ እና መሪነትን ታዝቤያለሁ። ​   ከእነዚህ ወጣት መሪዎች የታዘብኩት  ፡     ----------------------------------------------- የህዝብን ጥያቄ በጥልቀት የመረዳትና ለወደፊት ራዕይ በሰከነ መንገድ የመስራት አቅም። የትግሉን ዋና መስመር በመለዬት በዛ ዙሪያ  በፅናት የመቆም ፣ የማስተባበር፣ የማነሳሳት አቅምና ወትሮም ዝግጁነት። እነዚህ ወጣቶች መሪዎች የዛሬ የአማራ ጠንካራ ክንድ የወደፊት የአማራ ተስፋ፣ የጽናታችንና የድላችን ምስክሮች ናቸው። የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምድ ፅዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ኃላፊ አርበኛ መምህር ይድነቃቸው ማሙዬ

የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አከበር ስመኘው🙏 * የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር ነጎድጓድ ክፍለ ጦር ወጣት
+5
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አከበር ስመኘው🙏                    * የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር ነጎድጓድ ክፍለ ጦር ወጣት መሪዎች፤ የታዛዢነት፣ የብስለትና የጀግንነት አርአያዎች! ​በየክፍለ ጦሩ የአማራውን ነገ የሚያሳምሩና የድርጅት ፍሬ የሆኑ በርካታ ኩራት የሆኑ ወጣት መሪዎች አሉን። ከነጎድጓድ ክፍለ ጦር ወንድሞቼ ጋር በነበረኝ የፖለቲካና ወታደራዊ ውይይት የተለየ ብስለት፣ ጥበብ እና መሪነትን ታዝቤያለሁ። ​   ከእነዚህ ወጣት መሪዎች የታዘብኩት  ፡     ----------------------------------------------- የህዝብን ጥያቄ በጥልቀት የመረዳትና ለወደፊት ራዕይ በሰከነ መንገድ የመስራት አቅም። የትግሉን ዋና መስመር በመለዬት በዛ ዙሪያ  በፅናት የመቆም ፣ የማስተባበር፣ የማነሳሳት አቅምና ወትሮም ዝግጁነት። እነዚህ ወጣቶች መሪዎች የዛሬ የአማራ ጠንካራ ክንድ የወደፊት የአማራ ተስፋ፣ የጽናታችንና የድላችን ምስክሮች ናቸው። የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምድ ፅዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ኃላፊ አርበኛ መምህር ይድነቃቸው ማሙዬ

የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አከበር ስመኘው🙏 ***** የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር ነጎድጓድ ክፍለ ጦር ወጣት መሪዎች፤ የታዛዢነት፣ የብስለትና የጀግንነት አርአያዎች! ​በየክፍለ ጦሩ የአማራውን ነገ የሚያሳምሩና የድርጅት ፍሬ የሆኑ በርካታ ኩራት የሆኑ ወጣት መሪዎች አሉን። ከነጎድጓድ ክፍለ ጦር ወንድሞቼ ጋር በነበረኝ የፖለቲካና ወታደራዊ ውይይት የተለየ ብስለት፣ ጥበብ እና መሪነትን ታዝቤያለሁ። ​ ከእነዚህ ወጣት መሪዎች የታዘብኩት ፡ ----------------------------------------------- የህዝብን ጥያቄ በጥልቀት የመረዳትና ለወደፊት ራዕይ በሰከነ መንገድ የመስራት አቅም። የትግሉን ዋና መስመር በመለዬት በዛ ዙሪያ በፅናት የመቆም ፣ የማስተባበር፣ የማነሳሳት አቅምና ወትሮም ዝግጁነት። እነዚህ ወጣቶች መሪዎች የዛሬ የአማራ ጠንካራ ክንድ የወደፊት የአማራ ተስፋ፣ የጽናታችንና የድላችን ምስክሮች ናቸው።🔥

ሰበር የድል ዜና!! አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር በወሰደው የደፈጣ ጥቃት አንድ አይሲዙ የአገዛዙ ሰራዊት አባላትን የውሃ እራት አድረጓል !! 64ኛ ክ/ጦር ሀምሌ 10/2018 ዓ.ም ~~~~~~~ በእነማይ ወረዳ ዲማ ጊዮርጊስ፣ ቅድስጌ ቀበሌና አካባቢው የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍል ላይ ከፍተኛ ጥፋት ለመፈፀም ከማህበረ ብርሃን ቀበሌ ወደ ቢቸና ከተማ በጉዞ ላይ የነበሩ የብልፅግና አገዛዝ ሰራዊት አባላት ላይ ነሀሴ 09/2018 ዓ.ም ከምሽቱ 8:00 ሰዓት አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር በወሰደው #ደፈጣ አንድ ኦባማ የአገዛዙ ሰራዊት አባላት ሙሉ በሙ በሱሃ ወንዝ ላይ ማስጠሙን አረጋግጦል። በሱሃ ወንዝ ላይ በተሰራው የደፈጣ ጥቃት ከሞት አፋፍ የተረፍት የአገዛዙ ሰራዊት አባላት በቢቸና የመጀመረያ ደረጃ ሆሲፒታል ከፍተኛ ቁስለኛ ሆነው መግባታቸው ተረጋግጦል። ከእነዚህም ውስጥ:- 1ኛ.መልካሙ ማሞ አዲሱ 2ኛ.ዘሩ ማሞ ወልዴ 3ኛ.አብነት ደምሌ ታምሩ የሚባሉ የአገዛዙ ሰራዊት አባላት ይገኙበታል። ነሀሴ10/2018 ዓ.ም ከተለያዩ ቦታዎች የተሰባሰበው አገዛዙ ሰራዊት በእነማይ ወረዳ የዲማ ገዳምን ለማውደም በዲማ ከተማ፣ በቅድስጌና ቦርቦር ቀበሌዎች ላይ ወረራ ለመፈፀም ቢሞክረም ጀግኖች የአባ ኮስትር በላይ ዘለቀ የመንፈስ ልጆች አይበገሬዎቹ 64ኛ ክ/ጦር ከባድ ተጋሃድሎ እያደረጉ ይገኛል። ጀግናው ሰራዊታችን በዲማ ከተማና አካባቢው እያካሄደ ያለውን ተጋሃድሎ ሙሉ መረጃ ይዘን የምንመለስ ይሆናል። ድል ለደጅ አዝማች በላይ ዘለቀ ልጆች🔥🔥🔥 ሽንፈት ሀገርን እያወደመ ለሚገኘው የአገዛዙ ሰራዊት🔥🔥🔥 አዲስ ትውልድ ፣አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!! ነሀሴ 10/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት

የእለተ ሰንበት ልዩ ዳሰሳ የትግል ሰንሰለት እና የዘመነ ካሴ የዕድገት ምዕራፍ ታሪክን ከትውልድ ትውልድ የሚያሻግሩ፣ የሕዝብን ውጣ ውረድና ስቃይ በቅንነት ተሸክመው የሚጓዙ መሪዎች የሚፈሉት ከሕዝብ ውስጥ ነው። ከእነዚህ የዘመኑ ታጋዮች መካከል የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ (አፋብን) መሪ የሆነው አርበኛ ዘመነ ካሴ የትግል ጉዞ ልዩ ትኩረት የሚሰጠው ነው። የአርበኛ ዘመነ የትግል ጉዞ የተጀመረው ገና በለጋ ዕድሜው፣ በወጣቶች ሊግ ሊቀመንበርነት ነበር። በወቅቱ የነበረው የኢህአዴግ ሥርዓት ለወጣቶች ፍትሃዊ ዕድል የማይሰጥ፣ አግላይና አባካኝ እንደነበር ይታወሳል። የሕዝብን ጥያቄዎች በሰላማዊ መንገድ ለመመለስ የሚደረጉ ጥረቶችን በሚገባ ያውቅ የነበረው ወጣቱ ዘመነ፤ ከዚያም ባሻገር በአማራ ሕዝብ ላይ እየደረሰ የነበረውን ስልታዊ መገለል፣ መፈናቀል እና ግፍ በመቃወም ከቀድሞው ግንቦት 7 የትጥቅ ትግል ጋር በመቀላቀል ለፍትህ ቆመ። በዚያ የትግል ምዕራፍም ለአማራ ሕዝብ መብትና ደህንነት የሚችለውን ሁሉ ሲያደርግ ቆይቷል፤ የቆመለትም ዓላማ ሁልጊዜም የሕዝብ ዕድገትና ነፃነት ነበር። ወደ አገር ቤት የተደረገው ተስፋ እና አዲስ ፈተና እኤአ በ2018 (በ2010 ዓ.ም. ግድም) በመጣው አጠቃላይ የፖለቲካ ለውጥ ምክንያት፣ አርበኛ ዘመነ ካሴ ከሌሎች የትግል አጋሮቹ ጋር በመሆን ወደ አገር ቤት በመግባት ሰላማዊ ትግልን ለመሞከር ሞክሯል። ለሕዝቡ ሰላም ሲባል የተደረገው ይህ ጉዞ ትልቅ ተስፋ የተጣለበት ቢሆንም፣ አገሪቱ ውስጥ የነበረው ሥርዓት ለአማራ ሕዝብ የሰጠው ቦታ ዝቅተኛ በመሆኑ ተስፋው አጭር ሊሆን ቻለ። ሕዝቡ ከዕለት ወደ ዕለት በሚባባስ ማንነት-ተኮር ጭፍጨፋ፣ ግድያ እና መፈናቀል ውስጥ መውደቁን ቀጠለ። መንግሥታዊ አወቃቀሩ ራሱ ለሕዝቡ ደህንነት ዋስትና መሆን ባለመቻሉ፣ ሕልውናውን የማዳን ጥያቄ የሁሉ ነገር ቀዳሚ አጀንዳ ሆነ። የሁለተኛው ምዕራፍ ትግል እና የጽናት ፈተናዎች ይህንን ሕልውናን የሚፈትን አደገኛ አዙሪት በዝምታ ማለፍ ያልቻለው አርበኛ ዘመነ፤ ከወንድሞቹና ከትግል አጋሮቹ ጋር በመሆን የሁለተኛውንና የላቀውን የትጥቅ ትግል መሠረት ጣለ። በዚህ አስቸጋሪ የትጥቅ ትግል ጉዞ ውስጥ አርበኛ ዘመነ ካሴ ብዙ እንግልቶችን፣ ውጣ ውረዶችን እና የከፋ እስርን ተጋፍጧል። መንገዱ አስቸጋሪና አውሎ ንፋስ የሞላበት ቢሆንም፣ ዓላማውን ከግብ ለማድረስ ያሳየው ጽናት ዛሬም ድረስ አርዓያ የሚሆን ነው። የታሰሩባቸው ጊዜያት፣ የተጋፈጣቸው የፖለቲካ ጫናዎች እና የዕለት ተዕለት ውጣ ውረዶች የዕድገቱንና የቁርጠኝነቱን ጥንካሬ እንጂ ድክመት አላሳዩም። ይባስ ብሎም ሕዝቡ በእሱ ላይ የነበረውን እምነትና አክብሮት ይበልጥ እንዲጨምር አድርጓል። የአንድነት ምዕራፍ እና የሰዓቱ አበይት ጥያቄ የተበታተነውን የአማራ ሕዝብ ትግል በአንድ ማዕቀፍ ሥር ለማሰባሰብ ባደረገው ከፍተኛ ጥረት አሁን ላይ ሕዝቡን በአንድ አስተሳሰብና ዓላማ ማስተሳሰር ተችሏል። በአራቱም የአማራ ክልል አካባቢዎች የሚገኙ የፋኖ አደረጃጀቶችና አርበኞች በአንድነት በመመከር፣ አርበኛ ዘመነ ካሴን የንቅናቄው ሊቀመንበር አድርገው መርጠውታል። ይህ ምርጫ የሰዎች ፍላጎት ብቻ ሳይሆን፣ በወቅቱ የትግሉ ሁኔታ ያስገደደው ታሪካዊ ኃላፊነት ነው። > ማጠቃለያ: ታሪክ በሰጠው አደራ እና ሕዝቡ ባሳየው የጸና እምነት መሠረት አርበኛ ዘመነ ካሴ ዛሬ ላይ የጠቅላላው የአማራ ሕዝብ የትግል መሪ ሆኖ ወጥቷል። ይህንን ታሪካዊ እውነት በመገንዘብ፣ ሕዝባዊ አላማውን ከግብ ለማድረስ ለተነሳው ኃይል አብሮ መቆም፣ መተጋገዝ እና የጀመረውን ትግል ማጠናከር የሰዓቱ አስገዳጅ ጥያቄ ነው። #Dave #Amhara

ነሐሴ 10/2018 ዓ.ም ​አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ በዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር ንስር በለሳ ኢንጂነር ቅጣው እጅጉ ክፍለ ጦር ተክለሃይማኖት እና ፊታውራሪ ባንቲሁን ዘለቀ ብርጌዶች እና ሻለቆች ከተውጣጡ አመራሮች ጋር የስልጠና እና የውይይት መድረክ አካሂዷል። ​የአመራሩን የመሪነት ሚና ከፍ ለማድግ ተከታታይ የሆኑ ስልጠናዎች እና ውይይቶች አስፈላጊ በመሆናቸው በክፍለ ጦሩ መተዳደሪያ ደንብ እና መመርያ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናና ውይይት ተደርጓል። ክፍለ ጦሩ በተከታታይ እያከናዎናቸው ካሉ ወቅታዊ ግዳጆች ባሻገር የማህበረሰብ አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማነት፣ ህዝባዊ አደረጃጀቶችን አጠናክሮ መጓዝ በሚያስችሉ ነጥቦች ላይ ውይይት በማድረግ የጋራ አመራር ተሰጥቶባቸዋል ሲል መረጃውን ያደረሰን የክፍለ ጦሩ የህዝብ ግንኙነት ነው። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ​አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!