ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Open in Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Show more2 937
Subscribers
-324 hours
+3667 days
+38130 days
Posts Archive
"ጥቆማ"
የህዝብን በደል የፋሽስቱን ደግሞ ገመና ስለ ማጋለጥ
ጨፍጫፊውና ፋሽስቱ የአማራን ህዝብ ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት አዋጅ ካስነገረ ድፍን 3 ዓመታት ተቆጥሯል።ይህ በሁሉም ዘርፍ የማጥፋት ዕቅድ ከጡት ነካሽ ብአዲኖች አስፈፃሚነት እየተከወነ ይገኛል።ጅምላ ጭፍጨፋው ያላረካው ይህ ፋሽስት ስልቱን እየቀያየረ ማጥቃቱን ቀጥሎበታል።በኑሮ ውድነትና በዝናብ እጦት የሚንገበገበውን የወረዳው መከረኛ ህዝብ፦
1.የሸበል በረንታ ወረዳን ህዝብ በማዳበሪያ አታወጡም ሰበብ የጤና መድህን ካስወጣ በኋላ የዕድውሃ ከተማ ላይ መድሀኒት ቤት በመክፈት ህዝቡ በነፃ መታከም ሲገባው ከከፈተው መድሀኒት ቤት እያስገዛ ነው።
2.በወረዳው በጣም ነጭ ጤፍ አስር ሺ ብር እየተሸጠ ሰርገኛ ጤፍ ለዘር በግድ ወሰዱ ተብሎ ኩንታል ሃያ ስድስት ሺ ብር እየሸጠ ነው።
ቆንጣጭ ያስፈልጋል
አርበኞች የት ናችሁ?
በደሉን ሰምታችሁ ይሆን?
ሌላው መከራማ ጊዜ ይቁጠረው
ቀኘው ነኝ።
+2
የብልፅግና መዋቅር ከዕለት ወደዕለት እየፈረሰ በመሆኑ የአገዛዙ አገልጋይ የነበሩ ሚሊሾች የነጎድጓድ ክ/ጦርን ተቀላቀሉ
ሐምሌ 09 ቀን 2018 ዓ.ም
ከአንጨቆረር ከተማ የመጡና ቀደም ሲል ከብልፅግና አስተዳደር ጎን ተሰልፈው የነበሩ ሁለት የሚሊሻ አባላት፣ ሙሉ ትጥቃቸውን ይዘው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር ነጎድጓድ ክፍለ ጦርን ተቀላቅለዋል። ሚሊሾቹ ይህ ክስተት የመንግሥት የፀጥታ መዋቅር ከውስጥ እየፈራረሰ መሆኑንና መደበኛው ጦር የፋኖን ኃይል ለመጋፈጥ የሚያስችል ወታደራዊ ሥነ-ልቦና ላይ አለመሆኑን ያሳያል ብለዋል።
አስተዳደሩ ከ40,000 በላይ የሚሊሻና የአድማ ብተና አባላትን ያለ ምንም መመዘኛ ወደ መከላከያ በመቀየር "አማራን በአማራ" የማጋጨት እቅድ ነበረው። ሆኖም ይህ ዕቅድ በፋኖ ጥንካሬ ምክንያት ሳይሳካ ቀርቷል።
ሁለቱ የሚሊሻ አባላት የታሪክ ተጠያቂ ላለመሆን የሕዝብ ጋሻ የሆነውን የፋኖ ሰራዊት ለመቀላቀል ወስነዋል።
ይህ እርምጃ የጠላትን ሰራዊት በማፈራረስ ትግሉን በድል ለመደምደም መቃረቡን የሚያሳይ በመሆኑ አሁንም መላው የሚሊሻ አባላት የፋኖን ሀይል በመቀላቀል ራሱን በህይወት ቤተሰቡን በነፃነት እንድመራ የተሰጠውን ዕድል መጠቀም ይኖርበታል ።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!"
— የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
አስከሬኑን ደራርቦ ትጥቁን አስረክቦ ወደ መጣበት #ተመልሷል።
===================
ሃምሌ : 08/2018 ዓ/ም
===================
ማቻክል አማኑኤል ከተማ የመሸገቡ የአብይ አህመድ ስርዓት ጥምር ጦር በከባድ መሳሪያዎች በዙ-23 ፣ በመድፍና ብረት ለበስ ተሽከርካሪ በመታገዝ በቀን 07/11/2018 ዓ/ም ከሌሊቱ 10:00 ሰዓት የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 109ኛ ኮር 99ኛ ክ/ጦር ማቻክል በላይ ዘለቀ ሻለቆችን #ለማፈን #ሙከራ አድርጓል።
ከሌሊቱ 10:00 የጀመረው ወደ ማቻክል ደብረቀለሞ ከተሳካለት ማቻክል ደጋ ሰኝን ከተማ ጮቄ ተራሮች ድረስ #ለማሰስ የተንቀሳቀሰው ይሄ የአምባገነኑ ስርዓት የብል(ፅ)ግና ጦር የደፈጣና የሽምቅ ውጊያ ጠብቆታል።
ለተከታታይ 12 :00 ሰዓት የቀጠለው አውደ ውጊያው #በፋኖ የበላይነት #ተጠናቋል።
በዚህ አውደ ውጊያ የጠላት ሃይል ሙትና ቁስለኛ ማድረግ የተቻለ ሲሆን፤ የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎች እስከ ተተኳሻቸው መማረክ ተችሏል።
በዚህ አውደ ውጊያ መቶ አለቃ እሱባለው ዋለ፣ አምሳ አለቃ ታደሰ ልንገር፣ የቴዎድሮስ ዕዝ ኮማንዶ ዩኒት፣ የስናን አባጅሜ ሻለቃ እና የማቻክሉ በላይ ዘለቀ ሻለቆች #በጥምረት ተሳትፈውበታል።
NB, አስከሬኖች ፌስቡክ የማያስተናግድ በመሆኑ ከማስተላለፍ ተቆጥበናል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አዲስ ትውልድ አዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ፤
ሃምሌ 08/2018 ዓ/ም
+2
በእነማይ ወረዳ የረዝ ቀበሌ ጥቁር አስፖልት ላይ በተወሰደው የደፈጣ ጥቃት የአገዛዙ ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ ሆኗል!!
ሀምሌ 08/2018 ዓ.ም
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ሀምሌ 08/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር በእነማይ ወረዳ የርዝ ቀበሌ በወሰደው የደፈጣ ጥቃት 2 አድማ ብተና አባላት ወዲያውኑ ሲወገዱ 3ቱ የሚሊሻ አባላት ቁስለኛ መሆናቸው ተረጋግጦል። ከእነዚህም የሚሊሻ አባላት ውስጥ #አላምኔ_ከቤ ሀገረህይወት ቀበሌ ተወላጅ ቢቸና የመጀመርያ ደርጃ ሆሲፒታል መግባቱ ተረጋግጦል።
አዲስ ትውድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!
ሀምሌ 08/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 109 ኮር 99ኛ ክፍለ ጦር በርካታ የአገዛዙ ሀይል በመደምሰስ ክላሽንኮቭ ማርኳል‼️
በዛሬው ዕለት በቀን 8/11/2018 ዓ/ም መነሻውን #ከአማኑኤል ከተማ በማድረግ ዙ-23፣ሞርተር፣መድፍ እና BM በመጠቀም ወደ ደጋ ሰኝን የተንቀሳቀሰው የአብይ አህመድ አውዳሚ ሰራዊት በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 109ኛ ኮር 99ኛ ክ/ጦር #በላይ_ዘለቃ_ሻለቃ እና በቴዎድሮስ #ዕዝ_ኮማንዶ_ዩኒት ድንቅ ጥምረት በርካታ የጠላት ሀይል የተደመሰሰ ሲሆን ከሰባት በላይ ጥቁር ክላሽና በርካታ ተተኳሽ ገቢ ተደርጓል። የቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ተርቦቹ #ስናን_አባጅሜ ሻለቃ በቆረጣ የጠላትን ሀይል ደማቅ አቀባበል ያደረጉለት ሲሆን የደረሰበትን ምት መቋቋም ያቃተው የጠላት ሀይል ወደ አማኑኤል ከተማ ፈርጥጧል።
ይህ በዕንዲህ እንዳለ #ከደምበጫ ከተማ ወደ #ገሊላ የተንቀሳቀሰው የአብይ ወራሪ በኢንጅነር ክበር ተመስገን ልጆች አይቀጡ ቅጣት ተቀጦ ሙት እና ቁስለኛውን እያዝረከረክ ወደኋላ እንዲያፈገፍግ ተገዷል።
ይህ በቻ አደለም ከደምበጫ ወደ #አንጀኔ ቀጠና የተንቀሳቀሰው ይህ ግሬሳ ሰራዊት ሞርተር ዲሽቃ መድፍ እና BM እና የነፍስ ወከፍ መሳርያ ቢጠቀምም የኢንጅነር ልጆች ላይሸሹ ተማምለዋል እና ሲያንቀጠቅጡት ውለዋል ተጨማሪ ኃይል ከደምበጫ ቢጨምርም ወይ ፍንክች ወይ ንቅንቅ ብለዋል ፣ በአሁኑ ሰዓት ሰቀለማርያም ላይ አፈግፍገው መመሸጋቸው ንስር አማራ አረጋግጣለች‼️
08/11/2018 ዓ.ም
+2
" እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር የአመራር ሪፎርም አካሄደ"!!
ሐምሌ 08/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት የአሳምነው ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር የአመራር ሪፎርም ማካሄዱን አስታወቀ።
በተካሄደው የሪፎርም መድረክ ላይ የዕዙ እና የኮሩ ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆን፤ ይህ የአመራር ለውጥ የተደረገው ከክፍለ ጦር ወደ ኮር ደረጃ በተቀየሩ አመራሮች ምትክ አዳዲስ አመራሮችን ለመተካት ታስቦ መሆኑ ተገልጿል።
ይህ የተከናወነው የሪፎርም መርሃ ግብር ሙሉ በሙሉ ወታደራዊ መዋቅሩን ብቻ የሚመለከት ሲሆን፣ በወቅታዊና በቀጣይ ወታደራዊ ተግባራት ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል። በዚሕ መርሀ ግብር ያለፈውን የአሰራር ውስንነት ገምግሞ ሕዝብና ሠራዊትን ከልብ በማገናኘት ሕዝብን ባማከለ መልኩ የዕዛችንን ዓላማና ግብ ለማሳካት ጠንካራ አቋም ተወስዷል።
ሌላው ቀጣይ በሠራዊቱ በኩል ለሚነሱት የአሰራር ውስንነቶችና ለሚያጋጥሙ ችግሮች መካች ወይም ተጋፋጭ የሆነ ኃይል እዲሁም ብቁ አመራር ለማፍራት እደሚሰሩ ቃል ገብተዋል። ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር ለሚሰጣቸው ድርጅታዊ ግዳጆች ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀው የተያዘው መድረ በስኬት ተጠናቋል ሲል የኮሩ ህዝብ ግንኙነት ክፍል ገልጿል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት"!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
አሳዛኝ የእስር ዜና
የአርበኛ በለጠ አዱኛ ባለቤት የነበረችዉ ወ/ሮ ቡርሳ ይስማዉ ከሐምሌ 3/11/2018 ዓ.ም ጀምሮ ታሰረች
በምዕራብ ጎንደር ዞን ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ አብርሃጅራ ከተማ የዉሃ ልማት ሙያተኛ የሆነችዉ ወ/ሮ ቡርሳ ይስማዉ ከምሰራት መስሪያ ቤት ወደ ቤቷ ስትመለስ ለአገዛዙ ተላላኪ የሆኑት ፓሊስና ፀረ ሽምቅ አፍነዉ እንደወሰዷት በአካባቢዉ የነበሩ የአይን እማኞች ለአማራ ፋኖ ጥቆማ አድርሰዋል።
የመረጃ ምንጮቻችን እንደገለፁት ወ/ሮ ቡርሳ ይስማዉ እና አርበኛ በለጠ አዱኛ በ2013 ዓ.ም በሰላማዊ መንገድ በፍች የተለያዩ መሆኑን የገለፁ ሲሆን አሁን ባለዉ ሁኔታ ምንም አይነት ግንኙነት የለላቸዉ መሆኑን የስራ ባልደረባዎቿ እና ያካባቢዉ ማህበረሰብ ለተቋማችን መረጃዉን አድርሰዉናል ።
አርበኛ በለጠ አዱኛ አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ፋይናስ መምሪያ ኃላፈ ሁነዉ እያገለገሉ ያሉት እና የፋኖ የረጅም ጊዜ ታጋይና አታጋይ የሆኑት በበኩላቸዉ መታሰሯን እንደማንኛዉም ሰዉ ሰምቻለሁ ከኔ ጋር ከተለያየን እረጅም ጊዜ ቢሆንም ቅርቃር ዉስጥ የገባዉ የብልፅግና ተላላኪ የፋኖ ቤተሰብ ናችሁ እያሉ በማሰር የሚመጣ ለዉጥ የለም ህዝባችን ዘራፊ እና ወራሪ በግድ መንግስት ነኝ እያለ ህዝባችን የሚያሰቃየዉ መጨረሻዉ ነጥብ ላይ ስለደረሰ እንደ አማራጭ የሚጠቀመዉ ማሰር ማንገላታት መግደል ነዉ ከዚህ በፊትም የብዙ ፋኖ ቤተሰብ ናችሁ በማለት ሲያስር ሲያንገላታ ኑሯል በማሰር ከዓላማችን ፈቀቅ አያደርገነም እንዲያዉም እንድንበረታ ያደርገናል ህዝባችን በመሳቀቁ በገፍ ፋኖን እየተቀላቀለ ይገኛል ሲል ምላሽ ሰጥቷል።
ወ/ሮ ቡርሳ ይሰማዉ በአብርሃጅራ ከተማ ፓሊስ ጣቢያ ታስራ የምትገኝ ሲሆን በምሰራበት መስሪያ ቤት የስራ ባልደረባ የሆኑት ሲገልፁ ወደ መስሪያ ቤታችን አገልግሎት ፈልገዉ የሚመጡ ደንበኞ እየተንገላቱ መሆኑን አስረድተዋል ።
ገዥ ነኝ ለሚለዉ አካል ተላላኪ የሆናችሁ የእናት ጡት ነካሸ ካድሬዎች የፋኖ ቤተሰብ ናቹህ እየተባለ በአማራ ህዝብ እና በፍኖ ቤተሰብ ምታደርጉትን የሞራል ዉድቀት ለማምጣት ምታደርጉትን ጥረት ልታቆሙ ይገባል ይህን ማድረግ ካልቻላችሁ ኮራችን ምን ሊሰራ እንደሚችል ጠንቅቃችሁ ታዉቃላችሁ አኛ አንደ ተስፋ ቆረጡ የብልፅግና ተልካሻ የብልፅግና ቤተሰብ ናቹህ ብለን ንፁኋንን አናስርም ነገር ግኔጨ ከኛ ጋር እየዋሉ በናንተ መረጃ አቀባዮቻችሁ ላይ አስፈላጊዉን እርምጃ እንወስዳለን
በአጠቃላይ መሪያችሁ እንደገለፀዉ እና እንዳረጋገጠዉ ማሰር መሸነፍ ነዉ እንዳለዉ መሸነፋችሁን አምናችሁ ካድሬዎች ወንጀላችሁን ብትቀንሱ ይሻላል ካልሆነ ግን እስር ቤቷ በህይዎት ከተረፋችሁ ለማን እንደምትሆን እያሰባችሁ ተንቀሳቀሱ።
@ ድል ለጭቁኑ የአማራ ህዝብ
@ ድል ለአማራ ፋኖ
@ በተባበረ ክንዳችን ነፃነታችን እናረጋግጣለን አርበኛ ባንዴራዉ ግርማይ -- የ305ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ
ሐምሌ 8/2018 ዓ .ም
ከ305ኛ ኮር
የብልፅግና ሰራዊት አባላት እርስ በርስ መገዳደላቸው ተገለጸ!!
ሐምሌ 08 ቀን 2018 ዓ.ም.
ብልፅግና የሠበሰበውን አጋፋሪ ኃይል ወደ አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት፣ አሳምነው ዕዝ፣ ከሰም ፪ኛ ኮር ቀጠና ለዘረፋ በኦህዴድ መራሹ ጦር አማራ ሕዝብ ላይ የጥፋት ተልዕኮውን እያከናወነ እንደሚገኝ ታውቋል።
ለምዝበራ ዘመቻ ከሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በእነ መካሻ አለማየሁ እና አባይ ግዛው የልመና ጥሪ ተሰባስቦ ወደ ከሰም የገባው ሰራዊት፣ ከአካባቢው ሚሊሻዎች ጋር በመቀናጀት በ32 የገጠር ቀበሌዎች ላይ ወረራ አካሂዶ "ፋኖን የማጥፋት ዘመቻ" በሚል የዘመተ ቢሆንም፣ ዘማቹ ኃይል በፋኖ ክንድ በመመታቱ ከባድ መስዋዕትነትን ከፍሎ ባለፉት 24 ቀናት ውስጥ ምንም ዓይነት ወታደራዊ ለውጥ ማምጣት አልቻለም ነበረ።
ሆኖም ካፈርኩ አይመልሰኝ በሚል ስሜት የዘመተው የአገዛዝ ኃይል የማህበረሰቡን መኖሪያ ቤቶች፣ ንብረቶች፣ ትምህርት ቤቶችና ጤና ኬላዎችን ሲዘርፍ መቆየቱ ተዘግቧል። በዚሕ የዘረፋ ተግባር ተጋላጭ የሆነችው ኮቱ ከተማ የደረሰው አሰቃቂ ድርጊት አንዱ ነው። በቀን 07/11/2018 ዓ.ም በኮቱ ታዳጊ ከተማ ውስጥ ሰራዊቱ በሴቶችና አዛውንቶች ላይ አሰቃቂ የአስገድዶ መድፈር ጥቃቶችን ሲፈጽም ከርሞባታል።
ከዚህም አልፎ በሚሊሻ ሚስቶች ላይ ጥቃት ለማድረስ የሞከረ ሲሆን፣ የአንድ ሚሊሻ ሚስትን አስገድዶ ለመድፈር ሲጎትት ባለቤቷ ለማስጣል ቢሞክርም ሕይወቱ ሊያልፍ ችሏል። አቶ ኃይሉ ሚሊሻ፣ ባለቤቱን እና ሌላ አንድ ሚሊሻን ጓዱን በአሰቃቂ ሁኔታ መከላከያ ተረሽነዋል። በዚሁ ጥቃት ከባድ ቁስለኛ ሆስፒታል የሚገኝ አንድ ሌላ የሚሊሻ አባል ይህንን የእምነት ቃል እንደሰጠ የከሠም ፪ኛ ኮር ሪፖርተር በውስጥ መረጃዎቼ ደርሰውኛል ሲል ገልፆል።
የአመራሮች ተሳትፎ እና ማሳሰቢያ፦
ይህ ጦር የተሰጠውን ተልዕኮ ማሳካት ሲያቅተው፣ በብአዴን ከፍተኛ አመራሮች ይሁንታ ማህበረሰቡን የመዝረፍ፣ የመግደል፣ እንዲሁም ሴቶችና ህፃናትን በአሰቃቂ ሁኔታ የመድፈርና አማራን የማጥፋት ዘመቻ እንዲያካሂድ እንደተፈቀደለት አውቃችሁ። እናንተ የአማራ ሚሊሻዎች ይህንን ሴራ ተገንዝባችሁ ከአረመኔውና ከዘራፊው አገዛዝ ተላቃችሁ ወደ ወገን ኃይል እድትቀላቀሉ እነሆ ጥሪያችን ነው።
"ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!"
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!"
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
#ደምበጫ_ማቻክል‼️
በዛሬው ዕለት ከንጋት ጀምሮ በደምበጫና በማቻክል ቀጠና አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 109ኛ ኮር 99ኛ ክፍለ ጦር ኢንጅነር ክበር ተመስገን ሻለቃና በላይ ዘለቀ ሻለቃ ከብልፅግናው ጥምር ኃይል እየተዋጉ ሲሆን በውጊያውም መድፍና የተለያዩ ከባድ መሳሪያዎች ውጊያ ተከፍቷል።
ከጠዋት የጀመረው ትንቅንቅ በተለያዩ ግንባሮች እየተካሄዱ ይገኛል።በአሁኑ ሰዓት በደምበጫ ወረዳ #በአንጀኔ እና #በዳባ ቀጠና እንዲሁም በማቻክል ወረዳ #ደብረቀለሞ ቀጠና ከባድ ትንቅንቅ እየተደረገ ይገኛል። በተጋድሎው ደምበጫ ከተማ ከመሸገው የአገዛዙ ኃይል ዙሪያ ወረዳ ቀጠናዎች በዘፈቀደ የመድፍ ድብደባ እያካሄደ ይገኛል።
#ማሳሰቢያ:- ይህ ውጊያ በርካታ ሰራዊት የተሰለፈበት ሲሆን አላማውም በደምበጫና በማቻክል ያለውን የወገን ኃይል አሰላለፍ በማዛበት #ደጋዳሞት ወረዳ ለመያዝ የተለመ ስለሆነ 99ኛ ክፍለ ጦር #ደጋዳሞት ሻለቃ ከወዲሁ በተጠንቀቅ እንዲቆምና ቴዎድሮስ ዕዝ የውጊያ እቅድ ነድፎ እንዲጠብቅ ወታደራዊ ምንጮች ለንስር አማራ ገልፀዋል
08/11/2018 ዓ.ም
በሌባ ላይ ፋኖ እና ህዝቡ በጋራ ተደራጅቶ እርምጃ መዉሰድ ጀመረ
አፍብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 305ኛ ኮር በ3ቱ ቀጠና የሚገኙ ክፍለ ጦሮችን እና ልዩ ዘመቻ በሌባ ላይ አስፈላጊዉን እርምጃ ህዝብን በማደራጀትና በማስተባበር እንዲወሰድ ኮሩ አቅጣጫ አስቀምጧል ።
ከዚህ በፊት የፋኖን መብረቃዊ ምት መቋቋም ያቃተዉ ግስንግስ የብልፅግና ሰራዊት እና የፓለቲካ አመራር ሽንፈቱን ቢያምንም ጊዜ ይገዙልኛል ብሎ ያመናቸዉን የአካቢዉን ተወላጅ የሆኑትን ሆድ አደሮች እና አንዳንድ አድማ በትን በመመልመል አረንጓዴ ኢኒፎርም በማልበስ ህዝቡንና እና ባለሃብቱን እንዲዘርፉ እንዲያገላቱ እገታ እንዲፈፅሙ አስፈላጊ ሲሆን ከዉስጥ በተሰጣቸዉ መረጃ መሰረት እንዲገሉ በማድረግ ፍኖ ዘረፈ ፍኖ ገደለ ከህዝብ ለመነጠል ሰፊ ጥረት እና የፕሮፖጋንዳ ስራ ሲሰራ መቆየቱ ይታወቃል።
የአማራ ፋኖ እየታገለትን ያለዉን አላማ የተረዳዉ ህዝባችን የአማራን ህዝብ ከማንነቱ መገፋት መገደል መንገላታት እየታገለ መሆኑን በመረዳት እዉነተኛ ፋኖዎች ገዳይ አይደሉም ዘራፊ አደሉም ፍኖ አሳዶ እርምጃ ሊወስድባቸዉ ሲል በምረት ትቀበሏቸዋላችሁ ዘርፈዉናል ብለን ስንጠይቅ በምረት የገቡ ስለሆነ መክሰስ አትችሉም ትሉናላችሁ ስለዚህ እነዚህ ዘራፊዎች ከናንተ ጋር ነዉ ሚሰሩት በማለት ይሞግታሉ ነገር ግን አዳማጭ የለንም እንዲያዉም ነፃነታችን የሚረጋገጠዉ ፍኖ በአካባቢያችን ሲኖር ነዉ በማለት በየ ስብሰባዉ ህዝባችን አዳማጭ ባያገኝም ሞግቷል ።
የኮራችን ወታደራዊ ክንፉ እንደገመገመዉ ከግሪሳዉ የብልፅግና ሰራዊት ጋር ግንኙነት ያላቸዉ የዉስጥ የደሞዝ ተቀጣሪዎች እና የኮንትሮ ባንድ ጋር ግንኙነት ያላችሁ መሆኑን ተረድተናል ከማን ጋር ያገታችሁት ገንዘብ እንደምትካፈሉ ባለሃብቱን ፌክ ደረሰኝ በማዘጋጀት ግብር ክፈሉ በማለት እቅም በመጣል ሰብስባችሁ ለቤተ መንግስት ላለዉ ዘራፊ ቡድን የህዝባችን ደም መጣጭ ለሆነ አካል እየተካፈላችሁ መሆኑን በዉስጥ መረጃችን እና አንዳንድ በቁጥጥር ስር ባዋልናቸዉ ዘራፊዎች አረጋግጠናል።
ከወልቃይት ጠገዴ አርማጭሆ አዳኛገር ጫቆ እስከ መተማ በተለይ ጠረፉን አካባቢ የሌባ ማፅዳት ዘመቻ አድርገን ብዙ የህዝብ ደም መጣጮችን በቁጥጥር ስር አዉለን ከገታና ዝርፊያ በተጨማሪ ምርመራ ስናካሄድ እንዲዘርፉ ትዛዝ የሚሰጣቸዉ ከስርዓቱ መረጃና ደህንነት ለኦህዴድ ብልፅግና ተላላኪ የፓለቲካ አመራር ነኝ ከሚሉ ከወታደራዊ አዛዥች በፀጥታ መኪና እና በመከላከያ ኦራሎች ወደ ሱዳን ሃሽሽ እና ህገ ወጥ የሰዎች ዝዉዉር ይሰራሉ ይካፈላሉ ።
የህዝባችን እንባ የምናብሰዉ ህዝቡና ፋኖ ተደራጅቶ በጋራ እርምጃ መዉሰድ ሲጀምር እራሱን መከላከል ሲችል መሆኑን በመረዳት ህዝባዊ አደረጃጁት በመፍጠር እራሱን ከዘራፊዎች ከአጋቾች ከነብሰ በላዎች እንዲከላከል ሰፊ ጥረት እየተደረገ ይገኛል።
በተለይ እነዚህ አረንጓዴ ኢኒፎርም መንግስት ነኝ የሚለዉ አካል ያለበሳቸዉ ከፋኖ ጋር ለማመሳሰልና ፋኖን ዘራፊ ለማስባል በህዝብ ጥላቻ ለመፍጠር ጥረት እያደረገ ይገኛል አሁን ባለዉ ሁኔታ ማን ከዘራፊ ጋር እንደሚገናኝ ህዝባችን ተረድቷልም ጠንቅቆም አዉቋል ለፋኖም ህዝባዊ አደረጃጀቱ በየቀበሌዉ የተደራጀዉ እዉነታዉን ተረድተናል ህዝቡን በማደራጀት በየ አካባቢያችን ሶስት አራት እየሆኑ ሚመጡ ዘራፊዎች ላይ አርምጃ መዉሰድ ጀምረናል አሁንም አጠናክረን እንቀጥላለን በናንተ በኩል አስፈላጊዉን ድጋፍ አድርጉል መፍትሄችንም እናንተ ናችሁ በመለት ጠይቀዋል።
አርበኛ ኤሊያስ ድንቁም የ305ኛ ኮር ወታደራዊ አዛዥ በበኩሉ የኮሩን ስራ አስፈፃሚ በመሰብሰብ እኛ ጫካ የወጣነዉ ይህ ዘር መርጦ ገዳይ የብልፅግና መንግስት ነኝ ብሎ እራሱን የሚጠራዉ በአማራ ህዝብ ላይ የሚያደርሰዉን ግፋ በመረዳ በመሆኑ ከዚህ ገዳይ ጋር የተዋደደ የተቀናጀ ዘራፊ አጋች ሌባ ላይ ምህረት የለነም ህዝባዊ አደረጃጀቱ ህዝቡን አስተባብሮ አስፈላጊዉን እርምጃ እንዲዎስድ በኛ ሰራዊትም ለህዝባችን ድጋፍና ከለላ እንድታደርጉ ትዛዝ ሰጥቻለሁ።
አርበኛ ኤሊያስ ድንቁ ወታደራዊ አዛዡ አክሎም በተለይ እነዚህ ዘራፊዎች የሚንቀሳቀሱት ከአብርሃ ጅራ እስከ መተማ የኃኒስ ጫፋ ጠረፋን አካባቢ እና ኢንቨስትመት በሚለማባቸዉ በምዕራብ በርሃማ ቀጠናዎች ስለሆነ በዚህ አካባቢ ተንቀሳቅሰን እነዚህን የብልፅግና ተልኮ አስፈፃሚዎች ለማፅዳት ከፍተኛ የጠላት ኃይል ሰፍሮ የሚገኝበት አካባቢ ስለሆነ በቀላሉ ለማፅዳት ተቸግረናል ምክንያቱም ደፈጣ ጥለን ልናፀዳ ስንል ፈጥኖ ወደለነበት ይደርሳ ተናበዉ ይሰራሉ እነዚህ ዘራፊ እና አጋቾች ወደነሱ ይጠጋሉ ስለዚህ ህዝባችን ተደራጅቶ እራሱን ይከላከል ድርጅታችንና ኮሩ ኃላፊነት ይወስዳል።
በአጠቃላይ ከህዝባችን ጎን ቁመን ይህን ፋሽሽት የሌባ መደበቂያ ስርዓት አስወግደን በአጥንትና በደም በቆመችዉ አገራችን በየትኛዉ አቅጣጫ አንተ ማነህ ሳይባል ጥሮ ግሮ ሰርቶ ሚያድርባት ለህዝባችን እናስረክባለን።
@ ድል ለአማራ ህዝብ
@ ድል ለአማራ ፋኖ
@ በተባበረ ክንዳችን ነፃነታችን እናረጋግጣለን
አርበኛ ባንዴራዉ ግርማይ _ የ305ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ
ሐምሌ 8/2018 ዓ.ም
ከ305ኛ ኮር
በኤፍራታ ግድም ክላስተር "ሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር መብረቃዊ ጥቃት ፈፅማ ድል ተቀዳጀች!!
ሐምሌ 08/2018 ዓ.ም
በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት በአሳምነው ዕዝ ስር የሚንቀሳቀሰው 7ለ70 ክፍለ ጦር፣ ታሪክ የማይረሳውን ደማቅ ወታደራዊ ገድልና የድል ታሪክ መጻፉን ዛሬም በደመቀ ሁኔታ ቀጥሎበታል። ክፍለ ጦሩ በትናትናው ዕለት ማለትም በሐምሌ 07/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ኤፍራታና ግድም ክላስተር በተቆጣጠራቸው ቀጠናዎች ላይ የነበረውን ይዞታ በፅኑ መሠረት ላይ እያጠናከረ በጠላት ላይ አመርቂ ድል አስመዘገበ።
በአራት አቅጣጫዎች የተሰነዘረበትን ጥቃት ከካራ ለጎማ ቀበሌ እስከ አርሶ አባ ዘንቦ ድረስ በነበረው ውጊያ የክፍለ ጦሩ የደህንነትና የወታደራዊ መዋቅር እጅግ በተቀናጀና መብረቃዊ በሆነ ፍጥነት በአንድ ጊዜ በአራት አቅጣጫዎች የተቀናጀ እርምጃ ወስዷል ።
➡ በበርግቢ ቀበሌ ኦፕሬሽን፦ የክፍለ ጦሩ አባላት ከአርብ ገበያ በመነሳት፣ የጠላትን ወታደራዊ የደህንነት መረብ በመበጠስ በርግቢ ቀበሌ ውስጥ በስኬት ሰርገው መግባት ችለዋል ። በዚህም የህዝብን ደህንነት አደጋ ላይ ጥሎ የነበረውን የሚሊሻ አባል በቁጥጥር ስር በማዋል የጠላትን ዓይንና ጆሮ ሙሉ በሙሉ አሳውረዋል ።
➡ የሞሉ ባህር ፍልሚያ፦ በዚያው ተመሳሳይ ሰዓት ከአጣዬ ከተማ በ-2 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ልዩ ስሟ «ሞሉ ባህር» በተባለች ስፍራ ጀግኖቹ ባደረሱት ከባድ ጥቃት በርካታ የጠላት አባላት እስከመጨረሻው ሲሸኙ፣ ወታደራዊ አቅማቸውን የሚያዳክም ልዩ ልዩ ቁሳቁሶች ተማርከዋል ።
የተማረኩ የጦር መሣሪያዎች፦
1.ሁለት(2) ጥርጥር
2.አምስት (6) ካዝና
3.45 የክላሽ ጥይት
4.ሁለት የደረት ትጥቅ
ሲሆኑ በቁጥር በትክክል ያልታወቁ የጠላት ኃይሎች መደምሰሳቸውና መቁሰላቸው ተረጋግጧል ።
➡ በፈረዱሃ ቀበሌና
በተመሳሳይ ሰዓት ወደ ፈረዱሃ ቀበሌ የዘለቁት የነፃነት ታጋዮቹ፤ ከወገንና ከሀገር ደህንነት ይልቅ ሆዳቸውን ያስቀደሙ፣ ለጥቅም ያደሩ የባንዳ ሚሊሻዎችን አንገት የሚያስደፋና ዳግም እንዳያንሰራሩ የሚያደርግ ከባድ እርምጃ ወስደዋል ። በዚህም የቅጥረኛ ሚሊሻ ስብስብ ግማሹ ሲደመሰስ፣ የቀሩት ደግሞ በከባድ ቁስለኛ ሆነዋል።
1. ተኮላ ሰብስቤ (የተደመሰሰ)
2.ነጋሽ (የተደመሰሰ)
3.ኮማንደር መሀመድ ( ቁስለኛ )
4.ሰለሞን በከባድ ቆስሎ ሪፈር የተላከ ።
➡ በተጨማሪም በዚሁ ተመሳሳይ ሰዓት በሸዋሮቢት አካባቢ የአገዛዙን ወንበር ጠባቂዎች በማስከዳት፣ አንድ የሳይፐር (Sniper Rifle) የጦር መሣሪያ ከነሙሉ ተተኳሹ ለትግሉ ገቢ ማድረግ የተቻለበት ትልቅ ስኬታማ ሥራ ተሰርቷል ።
ክፍለ ጦሩ ላስመዘገበው ድል በማሕበረሰባችን የመረጃ ትብብር ነውና ሕዝባችንን ከዚሕ በላይ የሚያኮራ የነፃነት ገድል ለመስራት በሙሉ ዝግጅት ላይ ነን ሲል የክፍለ ጦሩ ሪፖርተር ገልፆል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!!
በብልፅግና ፈቃድ የሃገርን ሉአላዊነት ጥሰው ወደ ቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል በገቡ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ታጣቂዎች ላይ የጉምዝ ነፃ አውጭ ኃይሎች እርምጃ መውሰድ መጀመራቸው ታወቀ!
በሱዳን ብሉ ናይል ግዛት በኩል ወደ ኢትዮጵያ ድንበር የተሻገሩት በመሃመድ ሃምዳን ዳጋሎ የሚመራው የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች፡ በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል የጦር ካምፕ መገንባታቸውን ተከትሎ በክልሉ ነዋሪዎች ከፍተኛ ቁጣ ተቀስቅሷል።
ታጣቂዎቹ በብልፅግናው አገዛዝ ፈቃድ የሃገርን ሉአላዊነት ጥሰው ወደ በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል በመግባት በክልሉ ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ ግፍና በደል እየፈፀሙ ይገኛሉ።
እራሱን የጉምዝ ሕዝብ ነፃ አውጭ ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን፡ በክልሉ ሰፍረው በህዝብ ላይ ግፍ ሲፈፅሙ በነበሩት በእነዚህ የሄሜቲ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን የመረብ ሚዲያ ምንጮች አረጋግጠዋል።
የብልፅግና አገዛዝ እነዚህን የሄሜቲ ታጣቂዎች፡ ቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልልን ለጦር ካምፕነት እንዲጠቀሙ በይፋ መፍቀዱ ሳያንስ፡ ታጣቂዎቹ በሕዝቡ ላይ ለሚፈፅሙት ሰቅጣጭ ድርጊት ምንም አይነት መከላከያ ካለማደጉም በላይ ለታጣቂዎቹ ጋር ወግኖ "ጥቃት ተፈፀመብን" በሚል አቤቱታ በሚያቀርቡ የክልሉ ነዋሪዎች ላይ እርምጃ ሲወስድ መቆየቱን መረብ ሚዲያ ከዚህ ቀደም በሰራቸው ዘገባዎች ለሕዝብ ማድረሱ አይዘነጋም።
ጣቢያችን ያነጋገራቸው የክልሉ ነዋሪዎች እንደገሉፁት፡ ታጣቂዎቹ በክልሉ ሰፍረው ግድያ፣ ዝርፊያ እና አስገድዶ መድፈርን ጨምሮ ሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ሲፈፅሙ ቆይተዋል።
ታጣቂዎቹ በየሆቴሉ እና በየሱቁ እየገቡ ለሚመገቡት ምግብና ለሚገዙት ንብረት ክፍያ ሲጠየቁ "ብልፅግና ይክፈላችሁ" በማለት በባለቤቶቹ ላይ ሲሳለቁ እንደነበር ነው መረብ ሚዲያ ያነጋገራቸው የክልሉ ነዋሪዎች አክለው የገለፁት።
የብልፅግና አገዛዝ ካድሬዎች የዜጎችን ደህንነት ከማስጠበቅ ይልቅ፡ ግፉን የሚቃወሙ ነዋሪዎችን እያደኑ በማሰር ለውጭ ታጣቂዎች ከለላ እየሰጡ መሆናቸው ነው የታወቀው።
"ከሱዳን ተነስተው ወደ ኢትዮጵያ የገቡት የሄሜቲ ታጣቂዎች፡ የቤኒሻንጉልን የፀጥታ ሁኔታ አደጋ ላይ ጥለውታል። ይህ ድርጊት አገዛዙ ለሀገር ሉዓላዊነት ያለውን ንቀት የሚያሳይ ነው" ሲሉ ነዋሪዎቹ ቃል በቃል ገልፀዋል።
የሃገርን ሉአላዊነት ጥሰው በመግባት በሕዝብ ላይ ግፍና መከራ በሚያደርሱት በነዚህ የሄሜቲ ታጣቂዎች ላይ ነው እራሱን የጉምዝ ሕዝብ ነፃ አውጭ ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ኃይል እርምጃ መውሰድ የጀመረው።
ታጣቂ ቡድኑ የሄሜቲ ጦር የሰፈረበትን ካምፕ ከማውደም ጀምሮ እስከ ጨበጣ ውጊያ የዘለቀ እርምጃ በመውሰድ ወታደሮቹ ክልሉን ለቀው ወደ ሃገራቸው እስኪመለሱ ድረስ እርምጃውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው የታወቀው።
