en
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Open in Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Show more
2 931
Subscribers
-124 hours
+1487 days
+38530 days
Posts Archive
አለቃ ከነ ልጁ 👥 ጀግና እና ደግ መሪ አለን:: እንደ እሱ ያለ መሪ ማግኘት መታደል ነው:: እድለኞች ነን:: ትዕግስቱ፣ አስተውሎቱ፣ ጥበቡ፣ ድፍረቱ፣ ደግነቱ እና ለሞት ያለው ንቀት እሱን ለየት
+1
አለቃ ከነ ልጁ 👥 ጀግና እና ደግ መሪ አለን:: እንደ እሱ ያለ መሪ ማግኘት መታደል ነው:: እድለኞች ነን:: ትዕግስቱ፣ አስተውሎቱ፣ ጥበቡ፣ ድፍረቱ፣ ደግነቱ እና ለሞት ያለው ንቀት እሱን ለየት ያደርገዋል:: ልጁ ንጉሥ ምሬም ልክ እንደ አባቱ ነው:: ለወራት የስፔሻል ኮማንዶ ስልጠና ወስዶ ተመርቋል:: በዚያ ጀግንነት ላይ ወታደራዊ እውቀትና ጥበብ ሲጨመርበት አስቡት:)

#በመጨረሻም አንዷን ቀለሃ ወደ ራሱ ተኩሶ የአፄ ቴዎድሮስን ክብር ተቀናጀ፦ "አርበኛ ቅዱሴ ዘውዱ ከአርበኛ ቀኝአዝማች ጨለፍ ተስፋው ጋር ለሁለት ወራቶች ብቻ በእድሜ ተበላልጠወ ተጠራርተው ወደቁ። ከሁለት ወር በኋላ የቀኝአዝማች ጨለፍ ተስፋውን ናፍቆት አልቻለው አለና ቅዱሴም ወደ ጨለፍ ገሰገሰ! "አርበኛ ቅዱሴ ከኔ በላይ ጀግና ነው። የቅዱሴ ጀግንነት ወደር አልባ ነው።" ብሎ ቀኝአዝማች ጨለፍ የመሰከረለት ሰልካካ ውብና ወንዳ ወንዱ አርበኛ ቅዱሴ ዘውዱ መቄት ምድር ካፈራቻቸው ጉምቱ ጀግና መካከል አንዱና ኮከቡ እርሱ ነው። "ሰኔ 20/2018 ዓ/ም በመቄት ወረዳ ቁርአምበሳ ከተባለ ቦታ ላይ ጠላት በመድፍና ፔምፒ ታግዞ ሙሉ መካናይዝድ ሆኖ 22ኛ ክፍለጦርን ለመክበብ በተቀሳቀሰበት ቅስፈት አርበኛ ቅዱሴ ዘውዱ የጠላትን ሰራዊትን እያራገበ ከበባ ውስጥ የገባን ሰራዊቱን ከጠላት ቀጠና ሙሉ በሙሉ ማውጣት ቻለ።ቅዱሴ በቀኝና ግራ ደረት ትጥቁ አራት ካዝና አምስተኛ ከነፍጡ የተገጠመ ካዝናውን በጥላት ሰራዊት ቅንድብና ግንባር ላይ ከተኮሰ በኋላ በመጨረሻም ሰላሳ አንደኛዋን ቀለሃ ወደ ራሱ ተኮሳት። "አርበኛው እጁን ለጠላት ሊሰጥ ፈፅሞ አልፈቀደም! እርሱ የአፄ ቴወድሮስ፣የንጉስ ሚካኤል፣ የእምዬ ምኒልክ፣ የራስ አበበ አረጋዊና የጀነራል አሳምነው ፅጌ የአብራክ ልጅ ነውና፣ በደም አጥንቱ፣ በእስትንፋስ በሞራሉ የአማራዊ የሞራል ልህቀት ባለቤት ነውና አንዷን ጥይት ወደ ራሱ ተኮሳታ! እሳት እጁን የሚጨብጣት የለምና የጨለፍ ተስፋው ወንድም በፀጋውና ክብሩ ታላቅ ጀብድን በጥላት ላይ በመፈፀም ለአማራ ህዝብ በክብር ተሰዋ!!! "በደረቱ ያነገባቸውን አራት ካዝናዎችና አንድ ከነፍጡ የተገጠመ ካዝናውን ከጥላት ሰራዊት ላይ አርከፈከፈው። ከአገዛዙ ሰራዊት መሀል ዘሎ ገብቶ በቀኝ እጁ ክላሹን ከጥላት ደረት ላይ ተኮሰው፤ በግራ እጁ ቦምቡን እየመነጨ የጥላትን ምሽግና ከለላ እያፈራረሰ ወደ ፊት እሳት ለብሶ እሳት ጎርሶ ተጓዘ። የጥላት ሰራዊትም በርካቶች ወደ ምድር እየተዝለፈለፉ ወደቁ። አርበኛ ቅዱሴ ዘውዱ በቀኝአዝማች ጨለፍ ተስፉ እየማለ ወራሪውን ሀይል ዶግ አመድ አደረገው። በፂም የተከለለ ስንጥቅ መልኩን በጥላቶች ፊት ላይ እያበራ ለልዕልና የሚመኙትን ሸበላነቱን እያፀባረቀ ወንድነቱን እያስመሰከረ የጥላትን የጥፋት ሰንሰለት እየቆራረጠ በመቄት ምድር ከመድፍና ፔምፒ ላቃ ጋር ተናነቀ። "አርበኛው ለሀገር ዋርካ ለቀልብ እፎይታን የተቸረው ወንዳወንድ ሲሆን ከቀኝአዝማች ጨለፍ ተስፋው ጋር የትግል ጅማሮውን የጀመረ ሲሆን ከዛ ማዶ ወዶ ገቦች ጭንቅና ፈተናን ሸሽተው ኮምቦልቻ በተወሸቁበትና አማራነታቸውን ክደው ለኦህዴድ ባጎበደዱበት ዕለት እርሱ ግን ህቅታውን ለአማራ ትውልድ ያለ ስስት ከጠላት ጋር በመተናነቅ ታላቅና ህያው ታሪክን ሰርቶ የነ በላይ ዘለቀን ስምና ዝናን ተቀናጅቷል። ጀግኖችን ፀንሶ የመውለድ ችግር የማይነካካት የመቄት ምድር ያፈራችው አርበኛ ቅዱሴ ዘውዱ ሰኔ 20/2018 ዓ/ም በክብር ለአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተሰዋ። "ጀግና የነፃነት አለምን ፈጥሮ ያልፋል! ትውልድ ሁሉ ለዘላለም ይዘክረዋል!!! ©አርበኛ ፋኖ Eshetu Abate

የፋሽሽቱ ብልፅግና ስራት ፕሮፖጋንዲስቶች ሚሊኤንስ ጊዜ ሲጮሁ የነበረውን ፕሮፖጋንዳ ይቺ የአርበኛው ሶስት መስመር ጽሁፍ እንዳልነበር አድርጋ ደምስሳባቸው አልፋለች። እሄው ነው!!
የፋሽሽቱ ብልፅግና ስራት ፕሮፖጋንዲስቶች ሚሊኤንስ ጊዜ ሲጮሁ የነበረውን ፕሮፖጋንዳ ይቺ የአርበኛው ሶስት መስመር ጽሁፍ እንዳልነበር አድርጋ ደምስሳባቸው አልፋለች። እሄው ነው!!

የስነልቦና ውድቀት ውስጥ የገባው አገዛዝ የፋኖ ቤተሰቦችን በማገት ተሸናፊነቱን አረጋገጠ !! ​ ቀን 21/10/2018 ዓ.ም በቤተ ዐምሐራ ወሎ ምድር በወረኢሉ ከተማና በዙሪያዋ የሚገኙ የፋኖ ቤተሰቦች «ልጆቻችሁ ፋኖ ናቸው» በሚል ሰበብ ብቻ ለአምስት ቀናት ያህል ያለምንም ጥያቄና ክስ በከተማዋ መስተዳድር ፖሊስ ጣቢያ ታስረው እንደሚገኙ ተረጋግጧል። ታሳሪዎቹ ከመደበኛ የቤተሰብ ጥያቄ የተከለከሉ ሲሆን፣ ለመጠየቅ ወደ ጣቢያው የሚመጡ የቅርብ ዘመዶቻቸውም «ለምን መጣችሁ?» በሚል በፀጥታ ኃይሎች ድብደባና እንግልት እየተፈጸመባቸው ይገኛል። የታሳሪዎች እስርና እንግልት የተፈጸመባቸው ወላጆችና ቤተሰቦች በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በአሳምነው ዕዝ በዓፄ ዘርዓያዕቆብ አንደኛ(1ኛ) ኮር ስር የሚገኘው የብሩኬ ደምሴ ክፍለጦር አመራሮችና አባላት ቤተሰቦች ሲሆኑ፣ ስማቸውም እንደሚከተለው ቀርቧል፦ 1. የአርበኛ ታደሰ ተስፋዬ እናት — ወ/ሮ ሰርኬ 2. የአርበኛ ከበደ ወርቁ እናት — ወ/ሮ አበበች ዳኜ 3. የአርበኛ አቡሺ ትዛዙ እናት — ወ/ሮ አምሳለ 4. የአርበኛ ደሳለኝ ከበደ እናት — ወ/ሮ ማሺላ 5. የአርበኛ አበበ ጥላሁን ወንድም — አበባዉ ጥላሁን 6. የፋኖ ገረመዉ ተሾመ እናት — ወ/ሮ ሰርኬ ምንጉዴ 7. የፋኖ ሞገስኪዳኔ አያት — ወ/ሮ ደመቁ አሰጨናቂ 8. የፋኖ ዋሴ ዑመር እናት — ወ/ሮ ፋንታየ ሰይድ 9. የፋኖ ቆራጥ ሻለሙ አባት — አቶ ሻለሙ አንዳርጌ 10. የፋኖ ጌቶ አዘነ አባት — አቶ አዘነ 11. የፋኖ ሃብቴ ወላጅ እናት እና ሌሎች በርካታ የታጋይ ቤተሰቦች ናቸው። ሆኖም አረመኒያዊ የብልፅግና ስርዓት በቀጥታ ትዕዛዙ ኃላፊነት የሚወስዱ አካላት ለእነዚህ ንጹሃን ወላጆች መታሰርና መገላታት ቀጥተኛ ትዕዛዝ የሰጡና በድርጊቱ ተጠያቂ የሚሆኑ የከተማዋና የወረዳው አመራሮች ስም ዝርዝር፦ 1. አቡሺ ይመር — የወረኢሉ ከተማ ከንቲባ 2. ደረስ እረሺድ — የወረኢሉ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ 3. በዛብህ ተሾመ — የወረኢሉ ከተማ ብልፅግና ቅ/ጽ/ቤት ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ 4. ሰይድ ሙሄ — የወረኢሉ ከተማ ብልፅግና ጽ/ቤት ኃላፊ 5. ብርሃን ይማም — የወረኢሉ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ 6. ደለለኝ ቸርነት — የወረኢሉ ወረዳ አስተዳዳሪ 7. አቶ ሞገስ ባህሩ — የወረኢሉ ወረዳ ብልፅግና ጽ/ቤት ኃላፊ ሲሆኑ፡ ​ ይሕንን እኩይ ድርጊት የፈፀመው አካል አስቸኳይ መፍትሔ የማይሠጡ ከሆነ የታሳሪ ልጆች የሆኑት የፋኖ አባላት ከላይ የተጠቀሱት የአስተዳደርና የፀጥታ ኃላፊዎች በቤተሰቦቻቸው ላይ ለደረሰው እስርና እንግልት ሙሉ ኃላፊነቱን እንደሚወስዱ ገልጸዋል። አናብስቶቹም አክለውም፦ «ቤተሰቦቻችን በአስቸኳይ የማይለቀቁ ከሆነ እኛም የአጸፋዊ ምላሹን በቅርብ ቀን ወስደን የምናሳይ ይሆናል» ሲሉ ከጥብቅ ማስጠንቀቂያ ጋር መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። "ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ወዲህ ስዞር ምሬ ወዲያ ስዞር ድርሳን ቀና ስል መከታ ጎንበስ ስል ዘመነን በቀኜ ደሱና ኢሳያስ በግራ ደረጀን ወጣ ስል ሀብቴ ገባ ስል ዝናቡን ደሞ ብዙ ሺ ፋኖዎች ከፊት ተሰልፈው እልፍ አእላፍ ጀግና ከኋላዬ ቁመው በዚህ ሁሉ መሀል በኩራት ስራመድ አሳምነው ፅጌ በሰራልኝ መንገድ ማን ይስተካከለኝ ማን ደፍሮ ይጠጋኝ ሁሌ ትግሌን ሳስብ ይህ ነው የሚሰማኝ #Dawit #Amhara

ወዲህ ስዞር ምሬ ወዲያ ስዞር ድርሳን ቀና ስል መከታ ጎንበስ ስል ዘመነን በቀኜ ደሳለኝ በግራ ደረጀን ወጣ ስል ሀብቴ ገባ ስል ዝናቡን ደሞ ብዙ ሺ ፋኖዎች ከፊት ተሰልፈው እልፍ አእላፍ ጀግና ከኋላ
ወዲህ ስዞር ምሬ ወዲያ ስዞር ድርሳን ቀና ስል መከታ ጎንበስ ስል ዘመነን በቀኜ ደሳለኝ በግራ ደረጀን ወጣ ስል ሀብቴ ገባ ስል ዝናቡን ደሞ ብዙ ሺ ፋኖዎች ከፊት ተሰልፈው እልፍ አእላፍ ጀግና ከኋላዬ ቁመው በዚህ ሁሉ መሀል በኩራት ስራመድ አሳምነው ፅጌ በሰራልኝ መንገድ ማን ይስተካከለኝ ማን ደፍሮ ይጠጋኝ ሁሌ ትግሌን ሳስብ ይህ ነው የሚሰማኝ #Dawit #Amhara

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ  ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር የሞርተር 120 እና ሞርተር 82 ሚሊ ሜትር ሰልጣኞችን በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ! ግንቦት 21/2018ዓ/ም ጀብደኛው የ102ኛ ኮር 12ኛ ክፍለጦር 7ኛ ሜካናይዝድ ሻለቃ ለሶስት (3) ተከታታይ ወር ልዩና ተጨማሪ አድስ የሞርተር 120 እና የሞርተር 82 ሚሊ ሜትር ተኳሽ ባለሙያዎችን በብቃት አስመረቀ። ጀብደኛው የ102ኛ ኮር ከዚህ በፊት በሁሉም ክፍለጦሮች ብቁ የሆኑ የሞርተር ተኳሾችንና የተዋጊ መሃንዲሶችን በማሰልጠን ለሌሎች የምኒልክ ዕዝ ኮሮች ጥሩ ተሞክሮ መተግበሪያ ማዕከል እንደሚሆን ተስፋ የተጣለበት መሆኑ ይታወቃል። በምረቃት ፕሮግራሙ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የ12ኛ ክፍለጦር ዋና ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ሀብተማሪያም መንበሩ ለሰልጣኞች የእንኳን ደስ አላችሁ መልካም ምኞታቸውን መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ ወታደራዊ አዛዡ አያይዘው እንደተናገሩት ከሆነ የአብይ አህመድን ጨፍጫፊ አገዛዝ በአጭር ጊዜ ለማስወገድ የተለያዩ ስልጠናዎች ወደፊት  እንደሚቀጥሉ ጠንከር  ያለ ሀሳብ አስተላልፈዋል። አርበኛው አያይዘውም የክፍለጦሩ  ወትሮ ዝግጁነትና  ሰራዊታችን በላቀ ወታደራዊ ስነ-ልቦና ላይ ይገኛል ሲሉ ገልፀዋል። በመቀጠል በምረቃት ፕሮግራሙ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የ102ኛ ኮር ዋና ወታደራዊ አስተዳደር አርበኛ ፈለቀ ደጉ ለሰልጣኞች የእንኳን ደስ ያላችሁ መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል። ወታደራዊ አስተዳደሩ አያይዘው እንደተናገሩት ከሆነ የአምባገነኑንና የብልፅግና መራሹን አገዛዝ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ለማስወገድ በተግባርና በንድፈ ሀሳብ የተደገፈ ዘመኑን የዋጀ ስልጠና በመስጠታችን ሰራዊታችንና አመራሮቻችን ለግዳጅ ዝግጁ ናቸው በማለት ገልፀዋል። በተጨሪም የአማራ ህዝብ ትግል የፖለቲካ፣ የህገ መንግስት፣የዴሞክራሲ፣ የእኩልነትና ነፃነት ግልፅ የሆነ ጥያቄ የያዘና ጦርነቱ ህዝባዊ ድጋፍ ያለው በመሆኑ ጭቁን ኢትዮጵያዊያን በሙሉ ለሚደረገው ተጋድሎ ከጎናችን እንድትቆሙ በማለት ጥሪ አስተላልፈዋል። እንዲሁም የ102ኛ ኮር የስልጠና መምሪያ ሀላፊ መቶ አለቃ ሲሳይ መንግስቴና የኮሩ ምክትል የስልጠና መምሪያ ሃላፊ ሻለቃ ቢሆን አከለ እንደተናገሩት ከሆነ የአማራ ህዝብ ትግል ከነፍስ ወከፍ መሳሪያ ወደ ቴክኖሎጅ መሳሪያዎች በመጠቀም የሽግግር ጊዜ ላይ በመሆኑ በከፍተኛ ደረጃ አዳዲስ የተግባርና የንድፈ ሀሳብ ስልጠናዎችን በመስጠት ላይ እንገኛለን ሲሉ ገልፀዋል። አሰልጣኛ አርበኛ ሻለቃ ቢሆን አከለ እንደተናገሩት ከስልጠና በኋላ ሁሉም ሰልጣኝ ባለሙያዎች በጠላት ወታደራዊ ቤዝ ላይ ኢላማውን የጠበቀ የሞርተር ድብደባ በማድረግ ብቃታቸውን በተግባር አሳይተዋል ሲሉ ስለ ስልጠናው ማብራሪያ ሰጥተውናል። በዚህ ሰልጠና ተሳታፊ የነበረችዉ እና ከፍተኛ ውጤት በማምጣት ኮከብ ሰልጣኝና  ተሸላሚ ለመሆን  የበቃችው ፋኒት ሳምራዊት  አለማየሁ  ትገኝበታለች። ሰልጣኟ እንደተናገረችው የ12ኛ ክፍለጦር የሜካናይዝድ አባል ሆኘ በመመረቄ በታማኝነትና በቁርጠኝነት የአማራን ህዝብ ለማገልገልና መሰዋትነት ለመክፈል  ደስተኛ  ነኝ ስትል ገልፃለች። በመጨረሻ የ102ኛ ኮር ምክትል የስልጠና መምሪያ ሀላፊ አርበኛ ሻለቃ ቢሆን አከለ የሞርተር 120 እና የሞርተር 82 ሚሊ ሜትር ኮከብ አሰልጣኝ በመሆን የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀት በሽልማት  ተሰጥቷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሰኔ 22/2018 ዓ.ም

የሁለቱ ብርጌድ አባት አርበኞችና አመራሮች በህልውና ትግሉ ላይ ውይይት አካሄዱ። ​ሰኔ 22/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ጽዮን ኮር ራስ አበበ አረጋይ ክፍለጦር ስር የተደራጁት የፋሲለደስ ክላስተር "አማራ አንባ" ብርጌድ እና የገነት ክላስተር "ሸዋ ታጠቅ" ብርጌድ አባት አርበኛ አባላት ጋር ትናንት በ21/2018 ዓ.ም ጥልቅ ወሳኝ ውይይት ተካሄደ። በዚህ ወሳኝ መድረክ ላይ የአፋብን ዘመቻ መምሪያ ሀላፊ ፊትአውራሪ ባዩ አለባቸው እና የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች ፋኖ ዳዊት ቀፀላ እና ፋኖ አለማዬሁ ውሮ በተገኙበት የሰራዊቱን የውስጥ አደረጃጀት፣ ስነ-ልቦና እና የወደፊት የትግል አቅጣጫዎች ላይ ሰፊ እና ጥልቅ ውይይት በማድረግ አቅጣጫዎች አስቀምጠዋል። ​በተለይም በአማራ ሕዝብ ላይ በአገዛዙ ቅጥረኞች አማካኝነት ዛሬም ድረስ እየደረሰ ያለውን ዘርፈ-ብዙ ጥፋትና ጥቃት ለመቀልበስ ሰፊ ግምገማ ተደርጓል። ውይይቱ ጥቃቶችን በመመከትና ራስን በመከላከል ላይ ብቻ መወሰን እንደሌለበት አጽንኦት የሰጠ ሲሆን፣ አደጋውን ከመነሻው ፈልቅቆ ለማጥፋት ቆርጦ መታገል ብቸኛውና የመጨረሻው አማራጭ መሆኑን በመስማማት የወደፊት የትግል አቅጣጫዎችን አስቀምጧል። ​📌 ከፍተኛ አመራሮቹ ለሰራዊቱ ባደረጉት ንግግርና በሰጡት ማብራሪያ ፦ ▸ በተለያዩ አካባቢዎች የሚፈጸሙ ግፎች፣ መፈናቀሎችና ጥቃቶች የአገዛዙ ስልታዊ እቅዶች አካል በመሆናቸው፣ ትግሉ ጥቃትን ከመከላከል ባለፈ የጥቃቱን ምንጭ ከመነሻው ሙሉ በሙሉ ማክሸፍ የሚያስችል ጠንካራ ስራዎች ላይ ማተኮር አለበት። ▸ አገዛዙ ሃይማኖት፣ ፆታ እና ዕድሜ ሳይለይ አማራነት እንደ አንድ መጥፊያ ቀይ ካርድ ሆኖ በሕዝቡ ላይ ጥቃት እያደረሰ ባለበት በአሁኑ ወቅት መዘናጋትና መተኛት በፍጹም ሊኖር እንደማይገባ ተገልጿል። ▸በአሁኑ ሰዓት ያለው አገዛዝ ሕዝባዊ ቅቡልነትን ሙሉ በሙሉ ያጣ መሆኑንና "እንደቆሰለ ጅብ" በውስጣዊ የመበላላት ሂደት ውስጥ እንደሚገኝ በመረዳት ከትናንቱ ይልቅ ዛሬ በሁሉም መንገድ መተባበር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። ▸ በትግሉ ሂደት ውስጥ የጠላትን አጀንዳ ተሸክመው የውስጥ አንድነትን የሚያናጉና የሚያደፈርሱ "ከፉፉይ" አካላት ካሉ ለይቶ የማጥራት ሥራ በተደራጀ መልኩ በአስቸኳይ መሥራት ይገባል። ▸ በአሁኑ ዘመን በአማራ ሕዝብ ላይ ከፊት ለፊትም ሆነ በስውር በርካታ ዘመቻዎች ቢከፈቱም ሕዝቡ በፈተናዎች መካከል ነጥሮ የወጣ ጠንካራና ወጥ የሆነ አታጋይ መሪ ድርጅት ስላለው ያሸንፋል፣ ለዚህም በሁሉም መስክ መታገል ነገ በነፃነት የምንኖርባትን ሀገርና መንግስ መፍጠሪያ መንገድ በመሆኑ ህዝባችን በሚችለው ሁሉ ሊታገል ይገባል።ያሉ ሲሆን:- ​💬የሁለቱ ብርጌድ አባላት በበኩላቸው በትግሉ መዋቅር ውስጥ የታየውን መሻሻልና የወደፊት ዝግጁነታቸውን በታላቅ ቁጭትና ወታደራዊ ወኔ ሲገልጹ፦ትናንት የነበረብን የልጆቻችን የአንድነት ስጋት ዛሬ ሙሉ በሙሉ በመሪዎቻችን ብልሀት ተወግዷል። አሁን ላይ በበቂ ሁኔታ ወኔም ትጥቅም ታጥቀናል፣ ተደራጅተናል፣ እንዲሁም ሰልጥነናል። ድርጅታችን የሚያዘንን ማንኛውንም ትዕዛዝ በመቀበል እራሳችንን ከሞት፣ ታሪካችንን ደግሞ ከጥፋት ለመታደግ ዝግጁ ነን ብለዋል። ​አባላቱ አክለውም ያለፉትን መዋቅራዊ በደሎችና ግፎች የሚያስታውስ እና ከትናንት እስከዛሬ በአሩሲ፣ በደራና አካባቢው (በመላው አማራ ምድር) የተፈፀመውን እና አሁንም እየተፈፀመ ያለውን ጭፍጨፋ የሚገነዘብ ማንኛውም አማራ ትግሉን ከመደገፍ ውጭ አማራጭ እንደሌለውና ይህንን ታሪካዊ እውነታ የሚረሳ ካለ እርሱ ከወገን ሊቆጠር እንደማይገባው በቁርጠኝነት አስታውቀዋል። ክብር ለትግሉ ሰማዕታት ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

እንደፈለጉ የምትረዱት ይመስለኛል! ቆሞስ አባ ጳውሊ ከግንባር

ይድረስ ለእውነተኛ ኢትዮጵያውያን:- የኢትዮጵያ ትንሣኤ እስኪረጋገጥ ድረስ እንደ ቅዱስ ገብርኤል "ንቁም በበህላዌነ" ብላችሁ ጽኑ! አይቀርም! በየመድረኩ የምናያቸው አንዳንድ የሁሉም የሃይማኖት አባቶች፣ እንዲሁም ሳያውቁ ያወቁ የሚመስላቸው ሁሉም የታሪክ ተመራማሪዎች፣ ጸሐፊዎች ምሁራን ነን የሚሉ የፖለቲካ አክቲቪስቶች የሚሰሩት ሥራ በእውነት ወዴት እየወሰደን ይሆን? ታሪክ ለምን ይጻፋል? ለማን ይጻፋል? እውነትስ የት አለች? ኢትዮጵያዊነትንስ እስከምን ድረስ ነው የምትረዱት? ሃይማኖትን ከሃገር ሃገርን ከሃይማኖት የምታጣርሱትስ እስከመቼ ድረስ ነው? በህዝብ ደም የምትነግዱት እስከየትኛው የሃብት ማማ ድረስ ነው? ለስልጣን ሴራ የምትቀምሩት እስከየትኛው የዙፋን መዘርጋት እርካታ ድረስ ነው? ስለ ዘር የምታቀነቅኑት ከአዳምና ከሄዋን አልፎ የት እስኪደርስ ነው? ስለቋንቋስ ከአሁን እስከ ባቢላናዊያን ዘመን የት እስኪያልፍ ነው የምትረዱት? ....... ዓለምን፣ ሰውንና ፍጥረታትን በፈጠረ ፈጣሪ የምናምን እንዲሁም ለሀገርና ለወገን የምንጨነቅ ከሆነ ታሪክን ከምንጩ እና እውነትን ከመሠረቱ መረዳት ይገባናል። ነገር ግን ዛሬ የምናነበው ታሪክ፣ በየቦታው የምንሰማው ትርክት፣ ስለ ፈጣሪ፣ ስለ ሀገር አመጣጥ፣ ስለ ሕዝብ፣ ስለ ቋንቋና ስለ ማንነት የሚነገረው ሁሉ እውነትን ያራቀ ነው:: ለፖለቲካ ጥቅም፣ ለሥልጣንና ለግዛት ለክፍፍል የተገነባ ትርክት ሆኗል:: የታሪክ መዛባት ብዙ ጊዜ ከብዕር ይጀምራል፤ ነገር ግን መጨረሻው ከባድ የሰው ልጅ ዋጋ የሚያስከፍል ነው:: አንድ ትውልድ የተሳሳተ ትርክት ሲማር ጎረቤቱን እንደ ጠላት ሊያይ ይችላል፤ ሰውን በቋንቋው፣ በብሔሩ ወይም በሃይማኖቱና በማንነቱ ለመመደብ ይጀምራል። ይህም ክቡር የሆነውን የሰውን ልጅ የመከራ ቀንበሩን የሚያከብድና በሰቆቃ እንድንኖር የሚያደርገን ነው:: ኢትዮጵያውያን አሁን ያለንበት ሁኔታ እጅግ አስከፊ ደረጃ ላይ ነን:: አንድ አምባገነን መንግሥት ህዝብን በተገቢው መንገድ ማስተዳደር ካልቻለ ስልጣኑን ለማራዘም ሲል ህዝብን የማያስማማ እና አንድነትን የሚንድ የመከፋፈል መንገድ በሁሉም አቅጣጫ ይፈጥራል:: በዚህም ጊዜ የታሪክ ስርን በመነካካት ሀሳዊ ህሳቤን በማጉላት የህዝብን ስስ ብልቶችን በመንካት ሁሉም ለአንድነትና ለነጻነት እንዳይቆሙ ለማድረግ ይሰራል:: በዚህ ጊዜ አገዛዙ አንዱን አወድሶ አንዱን ይሰድባል ለአንዱ ጥቅም ለአንዱ ጉዳት ይጀምራል! ትርክት ፍሬውን ማፍራት የሚጀምረው ከዚህ ነው:: ብልጽግና እንደመጣ ኦሮማራ በሚል የትግራይ ህዝብ መገለል እንዲሰማው በእልህም ጦርነቱ እንዲቀጥል ተደረገ! ወዲያውኑ ደግሞ ሁላችሁም የምታስታውሱት አማራና ኦሮሞ እንዲጣሉ ደግሞ በአንድ ወገን መንጋ የሚል በሌላ ወገን ደግሞ የቀድሞ ስርዓት ናፋቂ የሚል ትርክት ተስፋፋ:: መንግሥትና ኢትዮጵያ ጠል ምሁራን ነን ባዮች ሀገራችንን ለማጥፋት ከበፊቱ በበለጠ መልኩ አመች ሁኔታ ተፈጠረላቸው:: በመሰረቱ ትርክት ጥቅምንና ሥልጣንን የሚፈልግ አካሄድ ነው። በህዝብ ደም የሚበለጽጉና ስልጣን ለመጨበጥ የሚፈልጉ ሰዎች መንገዳቸው እርሷ ናት:: ህዝብ ልብ ለልብ ከተገናኘ ካልተለያየማ የፖለቲካ ነጋዴዎች እንዴት ይሳካላቸዋል? በታሪክ ውስጥ “ከፋፍለህ ግዛ” የሚለው ስልት የታወቀ ነው። ይህ አካሄድ ለህዝብ ሰላም፣ ፍቅርና ጥቅም የማያስገኝ በጦርነት በመታመስ እንድንኖር የሚያደርግ ሴራ ነው:: ሰዎች እንደ ሰውና እንደ ዜጋ ሳይሆን በቋንቋ፣ በብሔር ወይም በሃይማኖት ብቻ እንዲተያዩ ሲደረግ ተጠቃሚው ሕዝብ ሳይሆን ሥልጣንና ጥቅም የሚፈልጉ ኃይሎች ናቸው። ኢትዮጵያ ላይ ይህ እየተደረገ ያለው ሴራ ከበርካታ ጊዜ ጀምሮ እስከ ዛሬ በዓለም የሚካሄዱ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የኃይል ፉክክሮች፣ እንዲሁም ስለ “አዲስ የዓለም ሥርዓት” ጋር ለማስኬድ የታለሙ እንደሆኑ ማወቅ ይገባናል:: የዚህ ዓላማው ደግሞ አንድነት ቢመስልም ህዝብን ሊወጣው የማይችለው መከራ ውስጥ በመክተት ከእግዚአብሔር ህግ ውጭ እንዲጓዝና እንዲጠፋ ለማድረግ ነው:: ግን ስልት እየቀያየረ ብዙ መልክ ይይዛል:: ኢትዮጵያ ትልቋ ኢላማ ለምን እንደሆነች ብትነገሩ ተረት ተረት ስለሚመስላችሁ ዝም ብሎ ማለፍ ይሻላል:: ማንኛውም ሐሳብ ሰውን ከሰው፣ ወገንን ከወገን እየለየ ከሆነ ጥያቄ ማንሳት የግድ ነው። እውነተኛ ፖለቲካ ሕዝብን ያገለግላል፤ የጥቅም ፖለቲካ ግን ሕዝብን ይከፋፍላል። እውነተኛ ታሪክ ሕዝብን ያቀራርባል፤ የተዛባ ትርክት ግን ለትውልድ የማይጠፋ ቁስል ይተዋል። በእውነት ምሁር ማለት ማነው? የታሪክ ጸሐፊ ማለት ማነው? የተጻፈውን ሁሉ ሳይመረምር መቀበል እውቀት አይደለም። የጻፈ ሁሉ ምሁር አይሆንም፤ ያነበበ ሁሉም የተማረ አይሆንም፤ የተናገረ ሁሉ አንደበቱ የቀና አይደለም! ታሪክን ማዛባት፣ ሃይማኖትንና ሰዎችን ለፖለቲካ ጥቅም መጠቀም ሕዝብን በጥላቻ መከፋፈል በህሊና ፊት የሚያስጠይቅ ነገር ነው።እውነተኛ ምሁር የሕዝብን ቁስል የሚፈውስ ነው፤ እውነተኛ ጸሐፊ ሰዎችን የሚያቀራርብ ነው። እውነተኛ የሃይማኖት አባትም ለእውነት የሚኖር ነው! ስለዚህ ዛሬ መጠየቅ ያለብን ሰዎችን ብቻ ሳይሆን ሐሳቦችንም ነው። የምናነበውን ሁሉ በእውነት፣ በማስረጃና በህሊና እንመዝን። ዛሬ የምናየው ግጭት፣ መከፋፈል፣ መተማመን መጥፋት፣ ስደትና ህመም ከየት መጣ? ለዚህ ጥያቄ ሁላችንም መልስ መፈለግ አለብን። መልሱም አንድ ሆነን ለጋራ የሚበጀንን ስርዓት መስራት ብቻና ብቻ ነው! ፖለቲከኞችን እንርሳቸው! ህዝብ ሆይ እንንቃ ኢትዮጵያውያን ጠፍተናል! ታሪክን በሚገባ እንወቅ እውነትን ከምንጩ እንፈልግ:: ህሊናችንን ከጥላቻና ከሐሰት ትርክት እናጽዳ። ሀገርን በፍቅር፣ በእውነትና በፍትሕ እንታደግ። ወደድንም ጠላንም ማወቅ ያለብን አይቀርም ኢትዮጵያ ጠላቶቿ እያዩ ትነሳለች! የህዝብን መከራ ያከበዱ የፖለቲካ ቁማርተኞች ሁሉ ታሪክ ይሆናሉ! ትንሳኤያችንን ለማፍጠን የህዝብ ንቃተ ኅሊና ያስፈልጋልና ንቁ አታንቀላፉ! አንድ ነገር ማሳሰብ የምፈልገው እኔ ብሄርተኛ አይደለሁም! የቆምኩት ለእውነትና ለፍትህ ነው:: እግዚአብሔር የበጎች እረኛ ስላደረገኝ በጎቼን ከነጣቂ ተኩላ ለመጠበቅ ነው ጫካ የገባሁት:: ምንም ብትሉ ለእውነትና እግዚአብሔርን በመታዘዝ ስለወጣሁ ምንም አይመስለኝም! ለይሉኝታ ሰውን ሳይሆን እግዚአብሔር ብቻ እንስማ! እግዚአብሔር የቀባችሁ የበጎች እረኞች ሆይ ውጡ የመከራው ቀንበር የከበደውን ህዝብ አድኑ! እኛ በቻልንና እግዚአብሔር በረዳን መጠን ህዝብን ለማዳን ከመሰል አባቶቼ ጋር ከወጣን ቆይተናል:: ሰው የተባለ ሁሉ ዘር የምትሉት ምድራዊ እንዲሁም ሃይማኖት አይገድበንም! ሰው ለተባለ ሁሉ ነጻነት መቆም ግድ ይለናል:: የሰው ልጅ በምድር ሰላም ካገኘ ፈጣሪውን ለማወቅ መንፈሳዊ አገልግሎት ለማግኘት እድል ይኖረዋል:: ወንጌልም የሚስፋፋው ያኔ ነው:: አንዳንድ አስመ*ሳይ የነጠላ ክርስቲያኖች ሐዋርያት ወንጌልን በመከራ ነው ያሰራጩት ብሎ ስንፍናውን በስህተት ለመሸፈን ይሞክራል! በሐዋርያት ዘመን እንደ ነበሩ አባት እናቶቻችን አይነት ትዕግስትና ቀና ልቦና ካለህ በል በጽድቅ ጎዳና ተመላለሳ! ኢትዮጵያ እንዴት ተጠብቃ ማንስ ጠብቋት እንደኖረች በውል ስለማታውቁ አንፈርድባችሁም! ለማንኛውም ሰው የተባልክ በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠርክ ክቡር ፍጥረት ሆይ አስተውል! ያለንበትን ዘመን እንመርምረው! እያንቀላፋን ለስጋችንም ለነፍሳችንም አልሆንም! ንቁ ንቁ ንቁ....! ንቁ ስላችሁ ምን ለማለት

የሰዴ ወረዳ የሽሜ ቀበሌ አባት አርበኞች በተጠንቀቅ ላይ ይገኛሉ‼️ ➾➾➾➾➾➾➾➾➾➾➾➾➾➾➾➾➾ ሰኔ 22/2018 ዓ.ም ሰዴ ወረዳ ሽሜ ቀበሌ አባት አርበኞች ጦር ለግዳጅ ዝግጁ መሆናቸዉን የሰዴ ወረዳ ጊዚያዊ መንግስት ፀጥታ ዘርፍ ሀላፊዉ አርበኛ ይርጋ ዘውዴ እና ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴዎች በተገኙበት ገለፁ። የአማራ ህዝብ የጀርባ ደጀን የሆነዉ የሰዴ ወረዳ አባት አርበኞች ጦር የትግሉን መነሻ በማሳሰብ የድርጅታችን እና የትግሉ ቁመና በቂ ግንዛቤ ከተሰጠ በኋላ ወደፊት ለዚህ የህልዉና ትግል ከአባት አርበኞች የሚጠበቅባቸዉን የስራ ድርሻ በመገንዘብ ከዚህ ትግል ጎን በመሆን የሰኔ ዘመቻ በማለት ከየቦታዉ የተሰባሰበዉን ግብስብስ አረመኒያዊ የአብይ አህመድን ስልጣን አስጠባቂ ሰራዊት እና የአረመኔ ስብስብ ቡድን እስከ መጨረሻዉ ድረስ እንታገላለን ሲሉ ገልፀዋል። "የሰኔ ዘመቻን ወደ ልቅሶ ዘመቻ እንቀይረዋለን፣ "አማራ ወደ ፊት ብቻ!" ትግላችን እስከ ነፃነታችን! አዲስ ትውልድ፣አዲሰ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 2ዐ1ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር ሰዴ ወረዳ ጊዚያዊ መንግስት ሚዲያና ግንኙነት

የአብይ አህመድ በወረኢሉ ከተማና አካባቢዋ በፋኖ ቤተሰቦች ላይ እየተፈጸመ ያለው እስርና እንግልት እየተደርገ ይገኛል!! ​«የታጋይን ቤተሰብ በማሰር የሚቆም ትግል የለም!» በዚህም ​በወረኢሉ ከተማና በዙሪያዋ የሚገኙ የፋኖ ቤተሰቦች «ልጆቻችሁ ፋኖ ናቸው» በሚል ሰበብ ብቻ ለአምስት ቀናት ያህል ያለምንም ጥያቄና ክስ በከተማዋ መስተዳድር ፖሊስ ጣቢያ ታስረው እንደሚገኙ ተረጋግጧል። ​ታሳሪዎቹ ከመደበኛ የቤተሰብ ጥያቄ የተከለከሉ ሲሆን፣ ለመጠየቅ ወደ ጣቢያው የሚመጡ የቅርብ ዘመዶቻቸውም «ለምን መጣችሁ?» በሚል በፀጥታ ኃይሎች ድብደባና እንግልት እየተፈጸመባቸው ይገኛል። ​የታሳሪዎችና የፋኖ አባላት ዝርዝር ​እስርና እንግልት የተፈጸመባቸው ወላጆችና ቤተሰቦች በሸዋ ጠቅላይ ግዛት፣ በአሳምነው ዕዝ፣ በአፄ ዘርዓያዕቆብ አንደኛ ኮር ስር የሚገኘው የብሩኬ ደምሴ ክፍለጦር አመራሮችና አባላት ቤተሰቦች ሲሆኑ፣ ስማቸውም እንደሚከተለው ቀርቧል፦ 1. ​የአርበኛ ተደሰ ተስፋዬ እናት — ወ/ሮ ሰርኬ 2. ​የአርበኛ ከበደ ወርቁ እናት — ወ/ሮ አበበች ዳኜ 3. ​የአርበኛ አቡሺ ትዛዙ እናት — ወ/ሮ አምሳለ 4. ​የአርበኛ ደሳለኝ ከበደ እናት — ወ/ሮ ማሺላ 5. ​የአርበኛ አበበ ጥላሁን ወንድም — አበባዉ ጥላሁን 6. ​የፋኖ ገረመዉ ተሾመ እናት — ወ/ሮ ሰርኬ ምንጉዴ 7. ​የፋኖ ሞገስኪዳኔ አያት — ወ/ሮ ደመቁ አሰጨናቂ 8. ​የፋኖ ዋሴ ዑመር እናት — ወ/ሮ ፋንታየ ሰይድ 9. ​የፋኖ ቆራጥ ሻለሙ አባት — አቶ ሻለሙ አንዳርጌ 10. ​የፋኖ ጌቶ አዘነ አባት — አቶ አዘነ 11. ​የፋኖ ሃብቴ ወላጅ እናት እና ሌሎች በርካታ የታጋይ ቤተሰቦች። ሆኖም ​አረመኒያዊ የብልፅግና ስርዓት በቀጥታ ትዕዛዙ ኃላፊነት የሚወስዱ አካላት ​ለእነዚህ ንጹሃን ወላጆች መታሰርና መገላታት ቀጥተኛ ትዕዛዝ የሰጡና በድርጊቱ ተጠያቂ የሚሆኑ የከተማዋና የወረዳው አመራሮች ስም ዝርዝር፦ 1. ​አቡሺ ይመር — የወረኢሉ ከተማ ከንቲባ 2. ​ደረስ እረሺድ — የወረኢሉ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ 3. ​በዛብህ ተሾመ — የወረኢሉ ከተማ ብልፅግና ቅ/ጽ/ቤት ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ 4. ​ሰይድ ሙሄ — የወረኢሉ ከተማ ብልፅግና ጽ/ቤት ኃላፊ 5. ​ብርሃን ይማም — የወረኢሉ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ 6. ​ደለለኝ ቸርነት — የወረኢሉ ወረዳ አስተዳዳሪ 7. ​አቶ ሞገስ ባህሩ — የወረኢሉ ወረዳ ብልፅግና ጽ/ቤት ኃላፊ ​ ሆኖም ​የታሳሪ ቤተሰቦች የሆኑት የፋኖ አባላት ከላይ የተጠቀሱት የአስተዳደርና የፀጥታ ኃላፊዎች በቤተሰቦቻቸው ላይ ለደረሰው እስርና እንግልት ሙሉ ኃላፊነቱን እንደሚወስዱ ገልጸዋል። ​አናብስቶቹም አክለውም፦ «ቤተሰቦቻችን በአስቸኳይ የማይለቀቁ ከሆነ፣ እኛም የአጸፋዊ ምላሹን በቅርብ ቀን ወስደን የምናሳይ ይሆናል» ሲሉ ከጥብቅ ማስጠንቀቂያ ጋር መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

አንዳንድ ነገሮች‼️ አለም ፊቱን ዞሮበት፥ ወይንም እንደፍጥርጥሩ ለእጣፋንታው ትቶት "ረስቶት" እያለ "መተን ቀብረነዋል" የተባለው የአማራ ህዝብ "መቃብር" ፈንቅሎ ብድግ አለ። ያለ አንዳች መካሪና ተቆርቋሪ፥ ያለ አንድ ሰው ሃሳብ አበዳሪ ከመከራው ተምሮ፥ ከራሱ መክሮ አማራ የራሱን አቢዮት ራሱ ፈጠረ።ሲነሳ በደነገጡት ጠላቶቹ ፊት ራሱን በፍጥነት አደራጅቶ የህልውና ትግሉን ጀመረ።እፍኝ የማትሞላ ተተኳሽ በመቶ ሽዎች ብር እየገዛ፥ ታጣቂም አስታጣቂም ራሱ ሆኖ ወደ ራሱ ግብ መገስገስ ቀጠለ። እነሆ ሶስት አመት አለፈው። ትልቁ ብሄራዊ ሃብት ሰው ነው። የሁሉም ነገር... የፖለቲካውም፥ የታንኩም፥የዲፕሎማሲውም ፥ የርእዮተ አለሙም ግርግር ማእከሉ፥ መቋጫው ሰው ነው። ለሰው ልጆች የተሻለ ነገር ለማምጣት የሚደረግ ነው። የራሱን ህዝብ በሰማይም በምድርም እሳት አሰማርቶ የሚያነድ ዘረፈጅ ሥርዐት ስለ ብሄራዊ ክብርና ሉአላዊነት የት ያውቃል? ስለ ሃገር ለማውራት ሞራሉስ ከየት ይገኛል?አንገቷ ላይ ቆሞ እያነደዳት ያለችን ሃገር እወዳታለሁ ሊለን ይሞክራል። የጥፋት ተልእኮ ይዞ ሃገር እያቃጠለ ሳያፍር ሌላውን ሃይል በተላላኪነት ሊከስ ይዳዳዋል። ለግብፅ መላላክን፥ ለፕሬዝዝዳንት ኢሳያስ መሽቆጥቆጥን፥ ለህወሃት መንበርከክን አብይና ቡድኑ እንጅ ፋኖ አያውቀውም። በኛ በኩል የአለም ጥቅሞች ሁሉ ተሰልፈው ቢመጡ፥ መዳፋችን ላይ ቢቀመጡ አንዲት ግራም የአማራን ህዝብ ጥቅም አሳልፈን አንሰጥም። የአማራ ህዝብ ህልውና፥ ጥቅሙና ምኞቱ ለድርድር አይቀርቡም፥ "ቅዱስ" ናቸው። ቅዱሱን የሚነካም የሚያስነካም ማንም የለም።ነገር ግን ካለፉት ረጅም አመታትም ፥ከራሱ ከብልፅግና ስህተትና ውደቅትም ተምረን ከቀጠናዊና አለምአቀፋዊ ልውጥውጡ የማንም ወኪል ሳይሆኑ መጠቀምን እናውቅበታለን።በሊማሊሞ ገደል አናት በተወጠረ ገመድ ላይ አይናችን ታስረን እንኳን አመጣጥነን መራመድ እና ወደ ነገ መሻገር እንችላለን። ይህ መከራ ከእድሜው በላይ ያስተማረው ትግል ነው። ስለሆነም በፍፁም አንሳሳትም። ከኢትዮጲያውያን ሃይሎች ጋር በጋራ መርፌ የመግዛት ተልእኮ እንኳን ቢኖረን የአማራ ህዝብ በይፋ ሳያውቀው የምንጓዘው አንድም እንኳን ስውር እርምጃ የለም። ጠላት ግን ይጮሃል። "ይህን ውሃ ምን ያስጮኸዋል ቢሉት፥ በውስጡ ያለው ድንጋይ" ብሎ መለሰለት አሉ። በዚህ ወቅት ብልፅግና የተባለ የኩሬ ቦይን የሚያስጮሁት "ድንጋዮች" ሁለት ናቸው፦ 1)ፍርሃት። አብይ የቀጠናውና የሃገር ውስጥ ሃይሎች ከተባበሩ እድሜዬ በአንድ እጄ እጣቶች ልክ የተቆጠሩ ናቼው ብሎ ስለሚያምን ደንግጧል። እናም ድንገት ጥቂቶችን አደናግሬ የማምሻ እድሜ ባገኝ ብሎ ሌት ተቀን ይጮሃል።ከሞት የማያድን ጩኸት። 2)ጦርነት። በአብይ አህመድ ስሌት የአማራ፥ የትግራይ፥ የአፋርና ሌሎች ህዝቦች ገና በበቂ አልደቀቁም። ስለዚህ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ መድቀቅና መጥፋት አለባቼው። ይህ ይሆን ዘንድ ግን "ሰበብ " ያስፈልጋል። ስለሆነም አቅም አግኝቶ ነገ ወደ አንድ ተረኛ ህዝብ ቢተኩስ ለአለሙ የሚነግረው  ሰበብ "ተባብረው ሊያጠፉኝ ሲሉ ራሴን ለመከላከል ጦርነት ከፈትሁ" ይሆናል ማለት ነው። ይኸው ነው። ይህ ትግል የአማራንና የሃገራችን ህልውናን የማረጋገጥ ትንቅንቅ ብቻ አይደለም፥ ቢያንስ ለሚቀጥሉት አምስት መቶ አመታት የጥይት ድምፅ የማይሰማ ትውልድ የመፍጠር ተልእኮም ነው። ብልፅግና ይወገዳል፥የአማራ ህልውና ይረጋገጣል። ኢትዮጲያ ለኢትዮጲያውያን የፍቅርና የደስታ ምድር ትሆናለች፥ ሰላም ትሆናለች። ክፋት ለማንም፥ በጎነት ለሁሉም! አዲስ ትውልድ ፥አዲስ አስተሳሰብ፥አዲስ ተስፋ! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ሰኔ-21/2018 ዓ. ም! አርበኛ ዘመነ ካሴ!