ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Open in Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Show more2 921
Subscribers
-124 hours
+1487 days
+38530 days
Posts Archive
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሐቤቴ አውራጃ ለአባት አርበኞች ኃይል ስለ ፖለቲካዊ ትጥቅ ትግሉ የግንዛቤ ፈጠራ ሥልጠና ተሰጠ
ሰኔ 21 /2018 ዓ.ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት የመርሐቤቴ አውራጃ፣ የትግሉ የኋላ ሞተርና የሕዝብ ዘብ ለሆነው የአባት አርበኞች ኃይል ስለ ወቅታዊው የትግል ነባራዊ ሁኔታ የግንዛቤ መፍጠሪያና የማብቂያ ሥልጠና ተጠናክሮ ቀጥሏል።
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት የአሳምነው ዕዝ ሥር የሚንቀሳቀሰው የአባት አርበኞች ኃይል በሁሉም የጠቅላይ ግዛቱ አካባቢዎች አደረጃጀቱን እያሰፋ የሚገኝ ሲሆን፣ በዛሬው ዕለት በመርሐቤቴ አውራጃ በተካሄደው የንቅናቄ መድረክ ላይ በዋና ዋና በትግሉና አካባቢያዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
በዕለቱ በተሰጠው ሥልጠና እና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ የሚከተሉት አበይት ነጥቦች ትኩረት ተሰጥቶባቸዋል፦
▸በአገዛዙ እብሪት እየተጨፈጨፈ ያለው አማራ ህዝብ ነፃነቱን በክንዱ ለማረጋገጥ እየተዋጋንም የአካባቢው ሕዝብ ደህንነቱ እንዲጠበቅና መብቱ እንዲከበር የአባት አርበኛው የጀርባ አጥንት ሆኖ እንደሚቆም አቅጣጫ ተሰጥቷል።
▸እየተካሄደ ስላለው የህልውና ትግል አጠቃላይ መነሻና መድረሻ ለተሳታፊዎቹ ግልጽ ማብራሪያ በመስጠት የተሻለ ግንዛቤ ተፈጥሮበታል።
▸ አገዛዙ በሞራልም በሰው ሀይልም እየተንኮታኮተ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ የፋኖ ኃይል ሙሉ በሙሉ ሕዝባዊ መሠረት ያለውና በአባት አርበኞች ሰፊ ደጀንነት እየተደገፈ የሚገኝ መሆኑ ተረጋግጧል።
ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘረያዕቆብ ኮር ናደው ክፍለ ጦር በሁሉም መስክ ኩራት መሆኑን የጠቀሱት የዕለቱ አስተባባሪዎች፣ ክፍለ ጦሩ ጠንካራ አደረጃጀቶችን በመዘርጋት፣ የውስጥ ደንብና ሕግጋትን በማውረድ እንዲሁም ለተዋጊውና ለደጀኑ ኃይል ሥልጠና በመስጠት ረገድ ከፍተኛ አበርክቶ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ትግሉ ሙሉ በሙሉ ሕዝባዊ ባህሪ የተላበሰ በመሆኑ፣ በየአካባቢው ፍትሕ ያጣው ግን ፍትህን በክንዱ የሚሰራው የአማራ ህዝብ ለአሸናፊነቱ በግንባር ቀደምትነት እየተሳተፈበት ይገኛል ተብሏል።
በመጨረሻም፣ "ትናንት አፍርሻቸዋለሁ" በማለት ሲፎክር የነበረው ገዥ አካል፣ ዛሬ በሕዝባዊው ኃይል ጠንካራ ክንድ ምሽጉ እየፈረሰ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ ትግሉን በአስተማማኝ ሁኔታ ከግብ ለማድረስ የተጀመረው የተቀናጀ ንቅናቄ ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል መልዕክት ተላልፏል።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
በስቦ ማስከዳቱ ሁለት የመከላከያ ሰራዊት አባላት 101ኛ ኮር ውስጥ ባሉ ክፍለ ጦሮች ውስጥ 35ኛ ክፍለጦርን ተቀላቀሉ!
መነሻቸውን ከጃራ፣ ከሀብሩ ና ወረባቦ ወረዳ ከሚንቀሳቀሰው የብልፅግና ሰራዊት ከደቡብ ዕዝ 205ኛ ኮር አሀድ የሆኑ የመከላከያ አባላት ስርዓቱን በመፀየፍና በመጥላት በየአቅራቢያቸው ከሚገኙ ወንድሞቻቸው የፋኖ አደረጃጀት ተቀላቅለዋል።
ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ/ም የተቀላቀሉት ሁለት መሰረታዊ ወታደር ከ42ኛ ክፍለ ጦር አምስተኛ ሬጅመንት በመውጣት 35ኛ ክፍለ ጦርን፣ ሁለት ጥቁር ክላሸ በመያዝ ተቀላቅለዋል።
የመከላከያ አባላቱም ሁሉም ጥቁር ክላሽ በመያዝ የገቡ ሲሆን ፣6ካዝና ከነተተኳሹ፣ ሁለት የወገብ ትጥቅ፣ ስድስት የእጅ ቦምብ ይዘው ተቀላቅለዋል ::ይህ በእ ንድህ እንዳለ ከ 104ኛ ኮር በተውጣጡ መቺ ሀይሎች ሰኔ 20 /2018 ዓ.ም የሚግራን 015 ቀበሌ ሀይቅ ዳር አካባቢ የስርዐቱ ተላላኪ ና መንገድ እየመሩ ህዝብን የሚያስጨፈጭፉና አማራን ለዳግም ባርነት ለማድረግ የሚሰሩ ሀይሎች ላይ እርምጃ ወስደዋል።በዚህ አስደማሚ ኦፕሬሸን ሙሉ ተሾመ የተባለ ባንዳን እጂ ከፈንጂ መያዝ ሲቻል እጂ አልሰጥም ብሎ አሻፈረኝ ያለን ሰይድ ሁሴን እንድሪስ የተባለ ባንዳን የማያዳግም እርምጃ በመውሰድ የተሳካ ኦፕሬሸን ተሰርቷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!
አፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
ሰኔ:- 21/ 2018 ዓ/ም
ታሪክ በወርቅ ቀለም ይፃፈው፤ የታሪክ ድርሳናት ይመስክሩ! የሚኒልክ ቃልኪዳን ያስተጋባ፤ የአሳምነውም ታላቅ መንፈስ ዛሬ በሸዋ ተራራዎች ላይ አፍ አውጥቶ ይናገራል! የአማራን ሕዝብ ታሪካዊ ክብርና የመኖር ነፃነት ለማስከበር በሚደረገው እልህ አስጨራሽ ተጋድሎ ውስጥ፣ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የማይበገረው የነፃነት ጋሻ ሆኖ ቆሟል።
ይህንን ታላቅ የሕዝብ አደራ በትከሻቸው ከተሸከሙት የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች አንዶቹ የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዙ ዋና መሪ አርበኛ ኢንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሽዋ እና ምክትል ወታደራዊ አዛዡ አርበኛ ኢሳያስ ደመቀ በተግባር በተፈተነና በተመሰከረለት የመሪነት ጥበባቸው ትግሉን ወደ ላቀ የድል ምዕራፍ እየመሩት ይገኛሉ።
ምድርን የሚያንቀጠቅጡት ክንደ ነበልባሎች የሕዝባቸውን ህልውና ለመቅጠፍ የመጣውን አረመኔያዊ የአብይ አህመድ አየር ወለድ ሰራዊት፣ እነዚህ የአሳምነው ልጆች በገባበት ገብተው ምድር እያስገቡት፣ ታሪክዊ ቅጣት እየቀጡት ይገኛሉ።
በ24 ሰዓት የማይታክት ኃይል ደከመኝ፣ ሰለቸኝ" የሚሉ ቃላትን ከትግል መዝገባቸው የሰረዙት እነዚህ መሪዎች፣ ሌት ከቀን ለሕዝባቸው ጋሻና መከታ ሆነዋል።ተፈጥሮን ያንበረከከ ጽናት ቁጭጭ የሚያደርገውን የሸዋን ውርጭ፣ እልህ አስጨራሽ ሰንሰለታማ ተራራዎችንና ገደላማ አቀበቶቹን በጀግንነት በመቋቋም የድል ታሪክ እየፃፉ ነው።
የነፃነቱ ቀዳሚ ባለቤቶች በመሪነት ጥበባቸውና በቁርጠኝነታቸው እነዚህ ሁለቱ የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መሪዎች፣ ለሕዝባቸው የመኖር ነፃነት መረጋገጥ የመጀመሪያውንና አንበሳውን ድርሻ ይወስዳሉ!
የሸዋ ተራራዎች ያስተጋባሉ፤ ትግላችን የህልውና ነው፣ መዳረሻችንም ፍፁም ነፃነት!! #Dawit #Amhara
ብልፅግና የለዬለት የውንብድና ተግባር ውስጥ ገብቷል።
የአገዛዙ ሰራዊት በስውር እና በግልፅ ነጋዴወችን ሲዘርፍ መቆዬቱ ይታወቃል። ከሰሞኑ ዳንግላ ላይ በእስልምና አባቶች ላይ የተፈፀመው ተግባርም የዚሁ አካል ነው።
ካሳሁን አስማረ የዳግላ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ፤ ኮማንደር ደሴ ብርሃኑ አድማ ብተና አዛዥ፤ ብርሃኑ ገድፍ የዳንግላ ከተማ የሚኒሻ ጽ/ቤት ኃላፊ እንዲሁም ዋና ኢ/ር ጀጀው ሞላ የዳግላ ከተማ ፓሊስ ፅ/ቤት ኃላፊ (ቀደም ሲል አርማጭሆ አካባቢ ለረጅም ጊዜ ሽፍታ የነበረ) ያዋቀሩት የዘረፋ ቡድን ዳንግላ ላይ ተከታታይ ግድያወችን ፈፅሟል።
ይኸው ገዳይ ቡድን ታላቁ አባት ይሳ አልቂ በቀን ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 2:30-3:00 ስዓት በቀበሌ 02 በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በመግባት ገድሏቸዋል።
እንዲሁም ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ታላቁ አባት ሸህ ሶፊያ ሙሃመድ በዳንግላ ከተማ በ02 ቀበሌ በሚገኘው መስጊድ የፀሎት መርሃ ግብር ጨርሰው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲመለሱ ከምሽቱ 2:30 ሲሆን በዚሁ ገዳይ ቡድን በጥይት ተደብድበው ተገድለዋል።
ሁለቱም ሟቾች በዳንግላ ከተማ የታወቁ ነጋዴወች ሲሆኑ ለገዳዩ ቡድን ከአንድ ሚሊዬን ብር በላይ እንዲሰጡ ተጠይቀው ያንን ለመፈፀም ዳተኛ ናችሁ በሚል ምክንያት ነው።
የዳንግላ ከተማ እና አካባቢው ህዝብ ከብልፅግና አገዛዝ ፍትህ ቢጠይቅም ምላሹ ሌላ ግድያ ሆኗል። ይህንን የሽብር አገዛዝ በኃይል ከማስወገድ የተሻለ አማራጭ የለም።
በአያት 49 ኮንዶሚኒየም የጋራ መጠቀሚያ ቦታ ይዞታ ላይ የተነሳው ውዝግብ ወደ ግጭት እና እስራት ማምራቱ ተገለጸ
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3፣ አያት 49 ቁጥር-2 የጋራ መኖሪያ (ኮንዶሚኒየም) መንደር ውስጥ ለጋራ መጠቀሚያነት በተከለለ ቦታ ላይ የተነሳው የይዞታ ውዝግብ ቅዳሜ ሰኔ 163 ቀን 2018 ዓ.ም ወደ ግጭት እና ወደ ነዋሪዎች እስራት ማምራቱ ተሰማ።
የአዲስ አበባ ፖሊስ በአካባቢው በሚገኝ "የመንግስተ ሰማይ እንደራሴዎች ዓለም አቀፍ ቤተክርስቲያን" ላይ ዝርፊያና ውድመት ፈጽመዋል ያላቸውን 21 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ማዋሉን ቢገልጽም፣ የአካባቢው ነዋሪዎች ግን የችግሩ መነሻ የይዞታ ነጠቃ፣ የንግድ ፍላጎት እና የሕግ ጥሰት መሆኑን በመጥቀስ የተሰጠውን መግለጫ ያስተባብላሉ።
የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚያስረዱት ከሆነ፣ አወዛጋቢው መሬት ቀደም ሲል በአካባቢው የነበሩ ገበሬዎች መጥተው ያርሱበት የነበረ ቢሆንም፣ ነዋሪዎቹ የኮንዶሚኒየሙ ሕጋዊ ካርታ ውስጥ የተካተተ መሆኑን በማስረዳት በፍርድ ቤት ትእዛዝ እንዲከበር አድርገውት የነበረ የጋራ ይዞታ ነው። መሬቱ በፕላኑ መሠረት የነዋሪዎቹ መኪና ማቆሚያ፣ የልጆች ኳስ መጫወቻ እና አረንጓዴ ቦታ (Green Area) ሆኖ ሲያገለግል የቆየ ነው።
ይሁን እንጂ ቦታው "የመንግስተ ሰማይ እንደራሴዎች ዓለም አቀፍ ቤተክርስቲያን" መሪ ለሆኑት ነቢይ ገቢ ጉተማ ተላልፎ መሰጠቱ መነጋገሪያ ሆኗል። ማኅበረሰቡ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ወስዶ ክርክር እያደረገ ባለበት እና ቦታው ላይ እንዳይገነባ በፍርድ ቤት ታግዶ እያለ፣ የፓስተሩ ወገኖች ዕገዳውን በመጣስ በድንገት በቆርቆሮ ማጠር መጀመራቸው በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል። ይህ የሕግ መተላለፍ እና ድንገተኛ ግንባታ ነው ማኅበረሰቡን ወደ መቃወም እና የተሰራውን አጥር ወደማፍረስ የመራው።
ነዋሪዎች እንደሚገልጹት ነቢይ ገቢ ጉተማ በአያት 49 40/60ኮንዶሚኒየም አካባቢ ተመሳሳይ ድርጊት ሲፈጽሙ ይህ የመጀመሪያቸው አይደለም። ቀደም ሲልም በአካባቢው የነበረ ሌላ የልጆች መጫወቻ ቦታን በመንጠቅ ቤተክርስቲያን መገንባታቸውን፣ ከህንጻው ስር ደግሞ ሱቆችን በመሥራት ለግል ጥቅማቸው እያከራዩ እንደሚገኙ ነዋሪዎች በምሬት ይናገራሉ። አሁን የተያዘውም ሰፊ የጋራ ቦታ ለተመሳሳይ የንግድ እና የግል ጥቅም ዓላማ የተፈለገ በመሆኑ ማኅበረሰቡ መብቱን ለማስከበር እንደተገደደ ይገልጻል።
አጥር መፍረሱን ተከትሎ የጸጥታ ኃይሎች በአካባቢው በመሰማራት በነዋሪዎች ላይ ድብደባና የጅምላ እስራት መፈጸማቸውን የዓይን እማኞች ገልጸዋል። በቁጥጥር ስር የዋሉት ግለሰቦችም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ምርመራ እየተጣራባቸው ይገኛል።
ድርጊቱ የተፈጸመው በተለያዩ እምነቶች ተከታዮች በጋራ በሆነ ማኅበረሰባዊ ጥያቄ ቢሆንም እስራቱ ግን የማኅበረሰቡን መሪዎችና የተወሰኑ የእምነት ተከታዮችን ያነጣጠረ መሆኑን ነዋሪዎች ይገልጻሉ። ከታሰሩት 21 ነዋሪዎች መካከል የአካባቢው የማኅበረሰብ ተወካዮች እና የኮሚቴ አባላት የሆኑት አቶ ካሰውን፣ ፍንታውን እና አሌ የሚገኙበት ሲሆን፤ የታሳሪዎቹ የሃይማኖት ስብጥርም፦
6 የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች
5 የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች
3 የሙስሊም እምነት ተከታዮች እና
ቀሪዎቹ የሌሎች ልዩ ልዩ እምነቶች ተከታዮች መሆናቸውን የደረሰን መረጃ ያረጋግጣል።
በተጨማሪም አንዳንድ የጸጥታ አካላት በወቅቱ ጉዳዩን ከፖለቲካዊ እና ከከፍተኛ የመንግሥት የሥልጣን አካላት እምነት ጋር በማያያዝ ነዋሪዎችን ለማስፈራራትና "ሽብር ነው" በማለት ለመፈረጅ መሞከራቸውን ገልጸዋል።
ይህ በአያት 49 ኮንዶሚኒየም የተከሰተው ክስተት የቦታው የብቻ ክስተት አለመሆኑንና በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ በርካታ የጋራ መኖሪያ መንደሮች ውስጥ ያሉ የጋራ መጠቀሚያ ይዞታዎች፣ የመኪና ማቆሚያዎች እና አረንጓዴ ቦታዎች "በመንግሥት ድጋፍ" ለተለያዩ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች እና ነቢያት ተላልፈው እየተሰጡ መሆኑን የማኅበረሰብ ተሟጋቾች ይናገራሉ።
ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ የሕግ ባለሙያዎች እንደሚጠቁሙት፣ የከተማዋ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ይዞታዎች በሕግ የተወሰነ የጋራ መብት ያላቸው በመሆኑ፣ ፍርድ ቤት በጉዳዩ ላይ ውሳኔ ሳይሰጥ እና የነዋሪዎችን መብትና የሕግ አሰራርን ሳይከተል የሚደረግ ማንኛውም የመሬት ቅበላ ሕገ-ወጥ መሆኑን ያሳስባሉ።
በአያት 49 ኮንዶሚኒየም የተነሳው ግጭት፡ “የፈረሰው የቆርቆሮ አጥር እንጂ የተገነባ ቸርች የለም፤ የተዘረፈ ንብረትም ውሸት ነው”
የአዲስ አበባ ፖሊስ እና አንዳንድ የዜና አውታሮች በአያት 49 ቁጥር-2 ኮንዶሚኒየም ውስጥ “በተጠናቀቀ የሃይማኖት ተቋም ላይ የሚሊዮኖች ብር ዝርፊያና ውድመት ተፈጸመ” በማለት ያሰራጩት መረጃ ፍፁም ከእውነታው የራቀ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች እና የዓይን እማኞች ገለጹ።
፩. በስፍራው የነበረው እውነታ
የተገነባ ቸርች የለም፦ በቦታው ላይ የተገነባ የቤተክርስቲያን ሕንፃም ሆነ መዋቅር የለም። ያየነው ነገር ቢኖር ገና ግንባታ ለመጀመር በሕገ-ወጥ መንገድ የታጠረ የቆርቆሮ አጥር ብቻ ነው።
የተዘረፈ ንብረት የለም፦ ፖሊስ አስር ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት ተዘረፈ ማለቱ ማኅበረሰቡን ለመወንጀል የተፈበረከ የሐሰት ትረካ ነው። ክፍት በሆነ እና በቆርቆሮ ብቻ በታጠረ መሬት ላይ ሊዘረፍ የሚችል ምንም ዓይነት ንብረት አልነበረም።
የፈረሰው አጥሩ ብቻ ነው፦ የነዋሪዎቹ ቁጣ የሕግ ዕገዳን ጥሶ የተተከለውን የቆርቆሮ አጥር በማፍረስ ላይ ብቻ የተገደበ ነበር።
፪. የቦታው ባለቤትነት እና የሕግ ጥሰቱ
ይህ ቦታ በኮንዶሚኒየሙ ሕጋዊ ካርታ ውስጥ የተካተተ፣ ለነዋሪዎች መኪና ማቆሚያ እና ለልጆች መጫወቻነት የሚያገለግል የጋራ አረንጓዴ ስፍራ ነው። ጉዳዩ በፍርድ ቤት እየታየ ባለበት እና እንዳይገነባበት የፍርድ ቤት ዕገዳ ባለበት ሁኔታ፣ ፓስተር ገቢ ጉተማ ዕገዳውን በመጣስ በቆርቆሮ ማጠራቸው ነው ሕዝቡን ለቁጣ የዳረገው።
፫. የማኅበረሰቡ ፍላጎት
ይህ ክስተት የሃይማኖት ግጭት ሳይሆን፣ የጋራ መገልገያ ቦታን ከሕገ-ወጥ ወረራ ለመከላከል የተደረገ ሕዝባዊ ተቃውሞ ነው። በመሆኑም መንግሥት ሐሰተኛ የዝርፊያ ትረካዎችን ከማሰራጨት ተቆጥቦ፣ የታሰሩትን የኮሚቴ አባላት (አቶ ካሰውን፣ ፍንታውን እና አሌ) ጨምሮ 21ዱንም ነዋሪዎች በአስቸኳይ እንዲፈታ እና የፍርድ ቤቱን ዕገዳ እንዲያከብር ማኅበረሰቡ ይጠይቃል።
+3
በአፋብን ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር ቢቡኝ ወረዳ ደብረዘይት ኩችት ቀበሌና አዞሬ መድሀኒያለም አባት አርበኞች በተጠንቀቅ ላይ ይገኛሉ‼️
➾➾➾➾➾➾➾➾➾➾➾➾➾➾➾➾➾
ሰኔ 20/2018 ዓ.ም
በምስራቅ ጎጃም ዞን ቢቡኝ ወረዳ ደብረዘይት ኩችት ቀበሌና አዞሬ መድሀኒያለም አባት አርበኞች ጦር ለግዳጅ ዝግጁ መሆናቸዉን የቢቡኝ ወረዳ ጊዚያዊ መንግስት ፀጥታ ዘርፍ ሀላፊዉ እና አስፈፃሚ ኮሚቴዎች በተገኙበት ገለፁ።
የፋኖ የጀርባ ደጀን የሆነዉ የቢቡኝ ወረዳ አባት አርበኞች ጦር የትግሉን መነሻ በማሳሰብ የድርጅታችን እና የትግሉ ቁመና በቂ ግንዛቤ ከተሰጠ በኋላ ወደፊት ለዚህ የህልዉና ትግል ከአባት አርበኞች የሚጠበቅባቸዉን የስራ ድርሻ በመገንዘብ ከዚህ ትግል ጎን በመሆን የሰኔ ዘመቻ በማለት ከየቦታዉ የተሰባሰበዉን ግብስብስ አረመኒያዊ የአብይ አህመድን ስልጣን አስጠባቂ ሰራዊት እና የአረመኔ ስብስብ ቡድን እስከ መጨረሻዉ ድረስ እንታገላለን ሲሉ ገልፀዋል።
"የሰኔ ዘመቻን ወደ ልቅሶ ዘመቻ እንቀይረዋለን፣ቀይረነዋልም!"
"አማራ ወደ ፊት ብቻ!"
ትግላችን እስከ ነፃነታችን!
አዲስ ትውልድ፣አዲሰ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ
ሰኔ 20/2018 ዓ.ም(የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 2ዐ1ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር የቢቡኝ ወረዳ ጊዚያዊ መንግስት ሚዲያና ግንኙነት)
በ2እጅ እነሴ ወረዳ ሀገረ ሰላምቀበሌ ላይ በወቅታዊ ጉዳዮች በወረዳው ጊዜያዊ መንግስት አመራሮች በመገኘት ውይይት ተካሄደ።
=============================
....ሰኔ20/2018 ዓ.ም
የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር በ2እጁ እነሴ ወረዳ ሀገረሰላም ቀበሌ ህዝብ ጋር በቀን 19/2018 ዓ.ም የጋራ ውይይት ተደርጓል።
➺ በፍትህ አሰጣጥ እና የመልካም አስ/ር ➺በፀጥታ ዙሪያ ያሉ ችግሮችን በመለየት
➺የሐብት አሰባሰብን በተመለከተ
➺የወል መሬት አጠቃቀም በተመለከተ
➺የአፋብን ትግል ከየት ወደየት የደረሰበት
ሁኔታ እና ህዝባዊ አስተዳደርን ጨምሮ የተገመገመና የወደፊት አቅጣጫ ማስቀመጥ የተቻለ ሲሆን ትግላችን አሁን ላይ የደረሰበትን ሁኔታ አጭር ማብራሪያ በኮሩ እና በክፍለ ጦር አመራሮች የማስረዳት ስራ ተሰርቷል።
እናደራጃለን ! እንመክራለን! እንፈፅማለን!!
አዲስ ትውለድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ!!
አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
+9
#ደጋዳሞት_ጎጃም_ዐማራ‼️
ለተከታታይ ቀናት በደጋዳሞት ወረዳ የተደረገው ትንቅንቅ በሻለቃ ዝናቡ ልንገረው እና በመቶ አለቃ አበበ ሰውመሆን እየተመራ በትናንትናው ዕለት በቀን 19/10/2018 በደጋዳሞት አባት አርበኞች፣ በቋሪት አባት አርበኞች፣በ109ኛ ኮር 99ኛ ክ/ጦር ደጋዳሞት ሻለቃ እና በ206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ስናን አባጅሜ ሻለቃ ድንቅ ብቃት በድል ተጠናቋል።
በዚህ አውደ ውጊያ የተገኙ ድሎች ...
👉1 -ባለ 82 mm ሞርተር
👉2-ዲሽቃ
👉8-ብሬን
👉5-እስናይፐር
👉230- ክላሽ
👉2 ስታር ሽጉጥ
👉7 -icom መገናኛ
👉5 -የሞርተር ቅንቡላ
👉800 -የዲሽቃ ተተኳሽ
👉3250 -የክላሽ ተተኳሽ
👉30 -f1 ቦንብ
👉12-የጭስ ቦንብ
👉300- ካዘና
👉11 የደረት ትጥቅ እንዲሁም ሌሎች ወታደራዊ ቁሳቁሶች ተማርኳል ። የተደመሰሰ የጠላት ሀይል አንድ የ76ኛ ክ/ጦር አዛዥ ሙሉ ኮሎኔል እና አንድ ሌተናል ኮሎኔል፣ 2 የሻለቃ አመራሮች፣ ከ8 በላይ መስመራዊ የጦር መኮነኖች እና ከ150 በላይ እግረኛ ሰራዊት ተደምስሷል ።
ዐማራ በልጆቹ ታፍሮና ተከብሮ ይኖራል!!
#አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አሰተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!
©አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 109ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት!
ሰኔ 20/2018 ዓ.ም ሰለም እደሩ ቤተሰብ
+1
ከጦር መሪው እስከ እግረኛ ሰራዊቱ ግብዓተ መሬቱ የተፈፀመበት የብልፅግናው አገዛዝ በአሁኑ ሰዓት በደጋ ዳሞት ፣ በቋሪት፣ በጎንጅ፣ በአዴት እና አካባቢው 2 የጦር ጄትና 1 ድሮን በመላክ አንበሶቹን ለመደብደብ ሙከራ እያደረገ ይገኛል።
ጀግኖቹ ግን አሁንም በየጥሻው የተበታተነውን እግረኛ ሰራዊት እየተከተሉ እየለቀሙት ይገኛል።
የአማራ ህዝብ የአርበኝነት ዘረ-መል የፋኖ ትግልና የአዲሱ ትውልዱ ስነ-ልቦናዊ ሽግግር!
በዚህ የቪዲዮ ምስል ውስጥ የሚታዩት ህፃናት ከወዳደቁ እንጨትና መሰል ቁሳቁሶችን በመጠቀም ወደ ተምሳሌታዊ መሳሪያነት ሲለውጡ፣ የቁሳቁስ እጥረትን በሐሳብ ልዕልና የማሸነፍ ጥበብን ያሳያሉ። በፖለቲካ እይታ፣ የትጥቅ ትግል ስኬት የሚለካው በጦር ሜዳ ድል ብቻ ሳይሆን፣ በትግሉ ዙሪያ በሚገነባው የተረክ የበላይነት ነው። ይህ የቪዲዮ ምስል የፋኖ ትግል ከወታደራዊ እንቅስቃሴነት ተሻግሮ፣ ወደ ማህበራዊ ባህልና ወደ ትውልድ ስነ-ልቦናዊ መዋቅር ውስጥ በጥልቀት ሰርጾ መግባቱን የሚያረጋግጥ ህያው ምስክር ነው።በቪዲዮው ላይ የሚታየው የህፃናቱ ገፅታ የፍርሃት ሳይሆን የኩራት እና የድል ስሜት የሚንጸባረቅበት ነው። ይህም የፋኖ ትግል በአካባቢው ላይ የፈጠረው የስነ-ልቦና ነፃነት ውጤት ነው።
ለብዙ ዓመታት በአማራው ማንነት ላይ ሲሰነዘር የነበረው የስነ-ልቦና ጥቃት ዛሬ በፋኖ ትግል አማካኝነት ወደ ባለቤትነትና አሸናፊነት ተለውጧል። ህፃናቱ ፋኖን እንደ አርአያ መምረጣቸው፣ ትግሉ በህዝቡ ዘንድ ያለውን ከፍተኛ የሞራል ተቀባይነት ያሳያል። ይህ የሚያሳየው የፋኖን ትግል ግብና አላማ የህፃናቱ አእምሮ በፈቃደኝነት የተቀበለው መሆኑን ነው። አንድ ትግል በህፃናት ጨዋታ ውስጥ ጀግንነት ሆኖ ከተቀረጸ፣ ያ ትግል የማይሸነፍ ማህበራዊ መሰረት ጥሏል ማለት ነው። እዚህ ጋር ፋኖነት እንደ ተራ ታጣቂ ቡድን ሳይሆን፣ እንደ አንድ የሞራል ልዕልና እና የፍትህ መለኪያ ተደርጎ በለጋ አእምሮዎች ውስጥ መታተሙን ያሳያል። ይህ የስነ-ልቦና ሉዓላዊነት ተብሎ የሚጠራው ክስተት፣ አንድ ማህበረሰብ ራሱን ከጭቆና ቀንበር ነፃ ለማውጣት የሚያደርገው የመጀመሪያውና ትልቁ ድል ነው።
ህፃናቱ በእጃቸው የያዙት የእንጨት መሳሪያ፣ ፋኖ በጅምር ላይ እያለ ምንም ሳይኖረው ካለው ፅኑ እምነትና ከህዝቡ በሚያገኘው ድጋፍ ብቻ ተነስቶ የደረሰበትን የአሸናፊነት ደረጃ ይወክላል። የፋኖ አብዮት በአሁኑ ሰዓት በህፃናቱ ልብ ውስጥ የነፃነት ምልክት ሁኖ ሰርጿል። ህፃናት የትግል ምልክቶችን በጨዋታቸው ውስጥ ሲያካትቱ፣ ያ ትግል በረጅም ጊዜ ሂደት ውስጥ የማይሸነፍ እና ትውልድ ተሻጋሪ የመሆኑ ዋስትና ነው። ህፃናቱ ራሳቸውን እንደ ነገው ፋኖ መቁጠራቸው፣ የፋኖ እሴቶች ማለትም ጀግንነት፣ መስዋዕትነት እና ፍትህ የማህበረሰቡ ቀጣይ መመሪያዎች መሆናቸውን ያበስራል። ይህ ደግሞ በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ መልክዓ-ምድር ውስጥ አዲስና የማይቀለበስ የኃይል ሚዛን መፈጠሩን ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚያሳይ ግልፅ መልዕክት ነው።
ሃገራችን ኢትዮጵያ የውጭ ወራሪዎችን ድል ያደረገችው በዘመናዊ መሳሪያ ብዛት ሳይሆን፣ በውስጣዊ የአሸናፊነት መንፈስና በሀገር ፍቅር ስሜት ነበር። ይህ ቪዲዮ ያንን ጥንታዊ የጀግንነት ታሪክ ዛሬ ላይ በፋኖ ትግል አዲስ ህይወት ዘርቶበት እናየዋለን። ህፃናቱ የነገው የነፃነት አርበኞች ሆነው እየተቀረጹ ነው። ይህም የሚያሳየው፣ የፋኖ ትግል ወቅታዊ ወታደራዊ ግብን ማሳካት ብቻ ሳይሆን፣ ለአማራ ህዝብ የዘላቂ ደህንነትና የክብር ዋስትና የሚሆን ትውልድ እንዳለው የሚያሳይ መሆኑን ነው።
የአንድ ህዝብ የነፃነት ፍላጎት አንዴ በህፃናት ልብ ውስጥ ከሰረፀ፣ ያንን ህዝብ በምንም አይነት ወታደራዊ ኃይል ወይም የፖለቲካ ሴራ ማሸነፍ አይቻልም። የፋኖ ትግል በአንድ ወቅት ተጀምሮ የሚያበቃ ሳይሆን፣ አዲስ የማንነት እና የክብር ትርጉምን ለቀጣዩ ትውልድ እያወረሰ ያለ ታላቅ አቢዮት ነው። ህፃናቱ በእንጨት የሰሩት መሳሪያ የዛሬ ጨዋታ ቢሆንም፣ በውስጣቸው የሰረፀው የአሸናፊነት እና የጀግንነት መንፈስ የነገውን የአማራን ልዕልና እና የኢትዮጵያን የታሪክ አቅጣጫ የሚያሳይ የነፃነት መንገድ ነው።
የፋኖ አብዮት የትውልድ አብዮት ነው፤ ውጤቱም የማይቀለበስ የአሸናፊነት ታሪክ ነው!
የ106ኛ ኮር 22ኛ ክፍለጦር ሰኔ 20/2018 ዓ/ም በመቄት ወረዳ ከመድፍና ፔምፒ ጋር ጉሮሮ ለጉሮሮ በመተናነቅ ታላቅ ጀብድን ተፈፅሟል!
ከፍላቂት ተነስቶ ወደ ጋሸና ሲግተለተል በነበረ የጠላት ሰራዊት ላይ 22ኛ ክፍለጦር መብረቃዊ ጥቃት ተፈፅሟል። ከወደ ፋኖዎቹ ከባድ የከበባ ጥቃት የተፈፀመበት ከበባውን ለመስበር የድሽቃ፣ የፔምፒና የመድፍ ቅቡላን ለተከታታይ ሁለት ሰዓት ሲተኩስ የዋለ ሲሆን፤ በመቄት አናብስቶች የስርዓቱ ስልጣን ጠባቂ የአገዛዙ ሰራዊቶች ግን ወደ ሲዖል ከመሸኘታቸው የታደጋቸው ምንም አይነት ስርዓታዊ ሀይል አልነበረም።
መቄት ቁርአበሳ ከተባለ ቦታ ላይ የብልፅግናው አገዛዝ ተከፋይ ሰራዊት በአናብስቶቹ የ22ኛ ክፍለጦር ነፍጠኞች ነፍሱ ለሲዖል ስጋው ለጅብ ሲደረግ፤ በዚህ አውደ ውጊያ በጠላት ላይ የተወሰደ አካላዊ እና ቁሳዊ ኪሳራዎች፦
✔️42 የተደመሰሰ የጠላት ሰራዊት
✔️ 37 ቁስለኛ የተደረገ
✔️ 531 የክላሽ ተተኳሽ
✔️ 301 የብሬን ተተኳሽ እና
✔️ ከ17 በላይ ቦንብና
✔️ ዘጠኝ የወገብ ትጥቅ
ከዚህ በተጨማሪ ለወቅቱ ማዕረጋቸው ያልታወቁ ሁለት(2) ከፍተኛ የአገዛዙ የጦር መኮነኖች መደምሰሳቸውን ከስርፋው ማረጋገጥ ተችሏል።
መዳረሻውን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ይቀጥላል ሲል መረጃውን የ106ኛ ኮር ሚዲያና ኮሚኒኬሽን መምሪያ ሃላፊ አርበኛ እሸቱ አባተ መረጃውን አድርሷል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሰኔ 20/2018 ዓ/ም
