en
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Open in Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Show more
2 931
Subscribers
-124 hours
+1487 days
+38530 days
Posts Archive
አባትና ልጅ ለአንድ ዓላማ የተሰለፉበት የአማራ ፋኖ ቅዱስ ትግል! በዚህ በእኛ ዘመን አንድን ህዝብ ወደ ፍጹም የሆነ የጠመንጃ አቢዮት የሚገፋፉት ምክንያቶች ውስጥ ከህልውና አደጋ በላይ የሆነ አሳማኝ ምክንያት አይገኝም። ዛሬ በአማራ ምድር እየታየ ያለው የፋኖ ተጋድሎ፣ አንድን ታሪካዊ ሕዝብ ከምድረ ገጽ ለማጥፋት ከታቀደ መዋቅራዊ የዘር ማጥፋት ለመታደግ የሚደረግ የመጨረሻው የሞት ሽረት ትግል ነው። በዚህ ልክ ለምን አባትና ልጅ ወደ ግንባር ወጡ? ለምን? የሚለው ነው። ለምንድነው ብዙ አባቶች የሥጋ ልጆቻቸውን ይዘው ወደ እሳት የሚገቡት? መልሱ ያለው አማራው ባለፉት ዓመታት ውስጥ ካለፈበት ሰቆቃ ላይ ነው። አማራው በገዛ አገሩ ባይተዋር ሲደረግ፣ በዘሩ ምክንያት የማንነት ጥቃት ሲፈጸምበት፣ እርስቱ ሲነጠቅና ልጆቹ በፊቱ ሲታረዱ የታገሰው ትዕግስት በይስተካከል ይሆናል የሚል የጅል ተስፋ ጋር ተያይዞ ነበር። ሆኖም ግን፣ ጥቃቱ ከመገለል አልፎ ወደ አጠቃላይ የዘር ማጥፋት ሲቀየር፣ የአማራ ህዝብ አንድ መራራ ምርጫ ላይ ደረሰ፣ በየቤታችን ተራ በተራ ከመታረድ፣ በጋራ ተዋግተን ህልውናችን ማስጠበቅ የሚል ድምዳሜ ነው። አባትና ልጅን ለአንድ ዓላማ ያሰለፈው ይሄው የጋራ ሰቆቃ ነው። አባቶች ልጆቻቸውን ይዘው የወጡት፣ ለልጆቻቸው የሚያስረክቡት አገር ቀርቶ አማራ ህልውናው ጠፍቶ፣ በታሪክ አማራ የሚባል ታላቅ ህዝብ ነበር፣ ህልውናው የጠፋ እየተባለ የሚወራበት ዘመን እየመጣ መሆኑን ስለተረዱ ነው። የእነዚህ እንቁ የፋኖ መሪዎቻችን ትልቁ ድንቅ ተግባር፣ እኔ የምሞትለትን ዓላማ ልጄም ይሙትለት ብለው የሥጋ ልጆቻቸውን በታሪክ አደባባይ ለነፃነት መስዋዕትነት ይዘው መውጣታቸው ነው። ይህ ድርጊት አንድ ትልቅ መልዕክት ያስተላልፋል፤ ይኸውም ትግሉ የአማራ ሕዝብ የመጨረሻው የህልውና ምሽግ መሆኑን ነው። አንድ አባት ልጁን ይዞ ወደ ሞት ግንባር የሚሰለፈው፣ ከፊቱ ያለው አደጋ ከልጁ ሕይወት በላይ መሆኑን ሲረዳ ብቻ ነው። በዚህ ታሪካዊ አውድ ውስጥ እንደ አርበኛ ዘመነ ካሴና አርበኛ ምሬ ወዳጆ ያሉ መሪዎች መከሰታቸው ለትግሉ የሞራል ልዕልናን ሰጥቶታል። በዓለም ፖለቲካ ውስጥ መሪዎች ልጆቻቸውን ወደ ውጭ አገር ለድሎት ሲልኩ፣ የአማራ ፋኖ መሪዎች ግን ልጆቻቸውን ወደ ባሩድ ጭስ መርተዋል። አርበኛ ዘመነ ካሴና አርበኛ ምሬ ወዳጆ ልጆቻቸውን ከጎናቸው አሰልፈው ግንባር ላይ መገኘታቸው፣ የአመራር ጥበብን ወደ መስዋዕትነት ከፍታ አውጥቶታል። ይህ መሪነት ህልውናን መሠረት ያደረገ መሪነት ነው። አሁን ላይ የአማራ ሕዝብ ንቃተ-ህሊና ወደ አዲስ ምዕራፍ መሸጋገሩን ያሳያል። የፋኖ የኃይል ሚዛን በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና ወደር የለሽ የሆነው ለመሞት በቆረጠና በትግሉ የቆረበ ታጋይና አታጋይ ስላለው ነው። አባትና ልጅ በአንድ ምሽግ የሚዋደቁበት ትግል በታሪክ አጋጣሚ ተሸንፎ አያውቅም። ምክንያቱም መሸነፍ ማለት የአንድን ትውልድ ብቻ ሳይሆን፣ የዘር ግንዱን ቀጣይነት ማጣት ማለት መሆኑን የፋኖ ታጋይ ስለሚገነዘብ ነው። መሪዎቹ ልጆቻቸውን ይዘው ወደ ትግሉ አደባባይ መውጣታቸው፣ አማራው እንደ ሕዝብ የደረሰበትን የህልውና አደጋ መጠን ለዓለም የሚያሳይ ትልቅ መልዕክትና የጽናት ማሳያ ነው። ታሪክ ይህንን ዘመን ሲዘክረው፣ የፋኖ መሪዎች ለሕዝባቸው ነፃነት ሲሉ ቤተሰቦቻቸውን ወደትግል ሜዳ ይዘው የገቡበት የታሪክ ምዕራፍ ብሎ በወርቅ ቀለም ይጽፈዋል። Birhanu Chalie Demelash

ከሻለቃ ሶስት ተወርዋሪ አባት ፋኖ አባለት ጋር ውይይት ተደረገ።                 ሰኔ 23/10/2018 ዓ.ም ይህ መድረክ የተዘጋጀው ተወርዋሪ የአባት ፋኖ ሃይል በማደራጀትና፣በትግል ሂደት ላይ ወትደራዊ ስምሪቶችና የሲቪል አስተዳድሩን ይበልጥ በማቀናጀት፣የቀጣይ የነፃነት ጉዞውን ስትራቴጅካዊ በሆነ መንገድ ለመምራት ታስቦ እንደሆነ ተገልጿል። በመድረኩ ለይ የጊዜያዊ መንግስት እና የዕዝ አመራሮች በግንባር ቀደምትነት ተገኝተውበታል። በዕለቱ በተደረገ በዚህ መድረክ ላይ የትግሉን የወደ ፊት አቅጣጫ የሚያመላክቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች ቀርበው ጥልቅ ውይይት ተደርጎባቸዋል። በዕለቱ በተካሄደው በዚህ መድረክ ላይ ከተወርዋሪ አባት ፋኖ ተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎች፣አስተያይቶች የተነሱ ሲሆን፣ለተነሱ ጥያቄዎች፣በጊዜያዊ መንግስት አመራሮች ማብራሪያ ተሰጦባቸዋል። በመጨረሻም ተወርዋሪ የአባት ፋኖ አባላት የሚሰጣቸውን ማነኛውም አይነት ግዳጅ በግንባር ቀደምትነት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። አዲስ ትውልድ!! አዲስ አስተሳስብ!! አዲስ ተስፋ!! የደምበጫ ወረዳ ጊዜያዊ መንግስት ሚዲያ ግንኙነት ክፍል

የአብይ አህመድ ተላላኪዎች የአርበኛ ሳሙኤል ባለዕድል ባለቤቱ እና እህቱን  ከሰኔ 02 ቀን ጀምሮ ባህር ዳር ሰባታሚት አስረዋቸው ቆይተዋል። ሆኖም  በተጠረጠሩበት ወንጀል ጠበቆች ተከራክረው ከፍተኛው ፍርድ ቤት በ50ሺህ ብር ዋስ የፈቀደላቸው ቢሆንም ከፍርድ ቤቶች በላይ ጡንቻ ያለው ፓሊስ የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ ጥሶ ከሰባታሚት ማረሚያ ቤት አውጥቶ እዛው ባህር ዳር ከጋምቢ ሆስፒታል ጎን በሚገኘው 2ኛ ፖሊስ ጣቢያ  እንደገና አሰሯቸዋል። ብልጽግና አዲስ አበባም ጅማም ነቀምትም ባህር ዳርም ጎንደርም ስሪቱ አንድ አይነት ነው !! በእዚህ አጋጣሚ ለባሕር ዳር እና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች ሙያችሁን ተጠቅማችሁ ህጉ የሚፈቅደውን ውሳኔ ብቻ ያለምንም ጫና እና ፍርሀት በመወሰናችሁ ክብር ይገባችኋል 👏👏👏 ። እዚህ ግፍ ውስጥ እየተሳተፋችሁ የምትገኙ የፖሊስ አመራሮች እና ካድሬዎች ዋ ! ያች የጭንቋ ቀን ደርሳለች እና የአብይ አህመድ ኮማንዶ ያስጥላችሁ እንደሆነ እናያለን !!

የድል ዜና!!! አፋብን ወለጋ(ቢዛሞ) አንሻ ሰይድ ዕዝ ይበልጣል መኮነን አድስ አለም ክ/ጦር ዛሬ በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ አሙሩ ወረዳ አጋምሳ ቀበሌ እና ዋሊ ሉቁማ ቀበሌ ባደረገው በተጠና ኦፕሬሺን የአገዛዙ ሰራዊት እና የክልሉ ፀጥታ ሀይልአድማ፣ሚሊሻ፣ፖሊስ፣ሪፔሎላ እና ጋቸና ሲርናን ጧት በተደረገው ውጊያ ሁለቱንም ቀበሌዎቺ ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሯል።ይህ የብልፅግና ስረዓት መቀመጫውን አጋምሳ አድርጎ መዳረሻውን ጣቦ ሶንቶም ቡሬ ወረዳ አድርጎ ለዘመናት የአማራን ማህበረሰብ ሀብት ንብረት ሲዘርፍና ንፁኋንን ሲገል የነበረ ዛሬ በይበልጣል መኮነን አድስ አለም ክ/ጦር የህዝብ የቁርጥ ቀን ልጆቺ በሆኑት ጥላትን በማያዳግም እርምጃ ከሁለቱም ቀበሌ ሙትና ቁስለኛ ሁኖ ብትንትኑ ወጥቶ ቦታውን ለቆ ወደ አሙሩ ወረዳና እና ወደ ጣቦ ሶንቶም በሁለት አቅጣጫ እግሬ አውጪኚ ብሎ ሸሽቷል። ፨የተደመሰሰ የጥላት ሃይል 43 ፨የቆሰለ 29 ፨የየተማረከ ክላሺ እኮቭ 14 ፨የክላሺ ተተኳሺ 1287 እንድሁም የወገብና እና የደረት ትጥቆቺ 7  ሲማርክም ፋኖም የበላይነቱን አረጋግጧል።ጥላትም እደለመደው  ውርደቱን ተከናንቧል።የወለጋ ቢዛሞ አማራ ታሪክን በክንዱ ሃይልን በፈጣሪ ተማምኖ ተማምኖ መፃፍ ጀምሯል። አፋብን ወለጋ(ቢዛሞ)አንሻ ሰይድ ዕዝ ም/የህዝብ ግነኙነት መምሪያና የይበልጣል መኮነን አድስ አለም ክ/ጦር የህዝብ ግነኙነትመምሪያ ሀላፊ አበበ አብራሃም ሰኔ 23ቀን2018ዓም

ማርኮ የሚያክም በኢትዮጵያ ምድር የአማራ ፋኖ ይባላል ‎ የአብይ ሠራዊት ተሳክቶለት ሲማርክ የፍ--ጥኝ  አ-ስ-ሮ የሚያደርገውን ያደርጋል። የአማራ ሕዝብ ስነልቦና ይህ ነው። ፋኖ ስትሆን ነገ እንደምታሸንፍ እና ሃገር እንደምትረከብ ስለምታውቅ ኃላፊነት ይሰማሃል። ዛሬ በሞጣ ሰማይ ስር የታየው ልብ የሚነካ ሰብዋዊነትን የተላበሰ ትይንት ነው! ‎ ‎

ውድ አማራዊያን እንዲሁም ኢትዮጵያዊያን ይህ የፊስቡክ ቢጅ በእየግዚው እየተዘጋ ተቸግረናል አዲሱን የፊስ ቡክ ፒጅ ሸርና ጆይን በማድርግ ይወዳጁን!! https://www.facebook.com/share/1EM5UnWVjY/

መሃል አማራ ሳይንት ወረዳ ደንሳ ከተማ ሻለቃ መሪው ከነ አጃቢው ተደመሰሰ፤ የአጃቢው ስናይፕርም ተማረከ!! ተልዕኮ ተቀብለው ለልዩ ኦፕሬሽን ወደ ጠላት ሰርገው የገቡ  ትንታግ ታጋዮች ሻለቃ መሪውን በመቀንደሽና ስናይፐር በመማረክ አስደናቂ ጀብዱ ፈፀሙ! በመሃል አማራ ሳይንት ወረዳ (ዴንሳ) ከተማ ተወሽቆ ከሚገኘው የኦህዴድ/ብልፅና ወንጀለኛ ቡድን ስልጣን ጠባቂ ቅጥረኛ ኃይል መካከል የሆነውና በግንባር ቀደምትነት የግፍ ግፍ ሲፈፅም የነበረው  የሻንበል ማዕረግተኛ የሆነው ሻምበል ስንታየሁ የተባለ ሻለቃ መሪ ከአጃቢው መሠረታዊ ወታደር ብርሃኑ ጋር ደንሳ ከተማ ውስጥ በተለምዶ ጎጃም በር በሚባለው የከተማው ክፍል ሲንቀሳቀስ በጀግኖች እስከወድያኛው ተሸኝቷል። ሻለቃ መሪውን እስከ አጃቢው ባፍጢሙ የከነበሉትና  ስናይፐር ማርከው እየፎከሩ ወደ ሻለቃቸው የተመለሱት ጀግኖች በአፋብን ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 47 ክ/ጦር አትሮንስ ሻለቃ የክብር አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ይህን የተሳካ ኦፕሬሽን ያቀናበረው  የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር ም/ዘመቻ ኃላፊ አርበኛ ጎሹ ታረቀ ሲሆን ኦፕሬሽኑን በብቃት የፈፀሙት ደግሞ በዋናነት ፋኖ አበጀ እሚያምረውና ፋኖ ደመቀ ዋስዬ ናቸው። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ          ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ/ም

የደጃዝማች ተሰማ እርገጤ ክፍለ ጦር በልዩ ኦፕሬሽን ጠላትን ሲደመስስ ፤ ወታደራዊ ቁሳቁስም ተማረከ!! ቀን 23/10/2018 ዓ.ም [ሸዋ ጠቅላይ ግዛት] — በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት፣ በአሳምነው ዕዝ መሐመድ ቢሆነኝ ኮር ስር የሚንቀሳቀሰው የደጃዝማች ተሰማ እርገጤ ክፍለ ጦር፣ በጠላት ኃይል ላይ ስኬታማ የልዩ ኦፕሬሽን እርምጃ መውሰዱን የዕዙ ህዝብ ግንኙነት አስታወቀ። የክፍለ ጦሩ ሁለተኛ ሻለቃ አባል የሆነው ጀግናው ፋኖ ገዝሀኝ ዘነበ፣ ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ጣርማበር ወረዳ፣ አርማኒያ ቀበሌ ውስጥ በተንቀሳቀሰው የገዢው ሥርዓት ታጣቂ (ሚሊሻ) ላይ የተጠናና ጥንቃቄ የተሞላበት ድንገተኛ ጥቃት ሰንዝሯል። በተወሰደው ፈጣን ወታደራዊ እርምጃ የጠላት ታጣቂው የተደመሰሰ ሲሆን፣ የሚከተሉት የጦር መሣሪያዎችና ትጥቆች በቁጥጥር ስር ውለዋል፦ .ሁለት (2) የክላሽንኮቭ (AK-47) ጠመንጃዎች .ሰላሳ (30) የክላሽንኮቭ ጥይቶች የኦፕሬሽኑ ፈጻሚ የሆነው ፋኖ ገዝሀኝ ዘነበ የተጣለበትን ግዳጅ በብቃትና በጀግንነት ካጠናቀቀ በኋላ፣ የማረከውን ወታደራዊ ንብረት ይዞ ወደ ተመደበበት የደጃዝማች ተሰማ እርገጤ ሁለተኛ ሻለቃ አሃዱ በሰላም ተቀላቅሏል። የአሳምነው ዕዝ ወታደራዊ አመራር የፋኖ ገዝሀኝ ዘነበን ብቃትና ቁርጠኝነት ያደነቀ ሲሆን፣ ይህ ዓይነቱ ስልታዊ ጥቃት የሕዝባችንን የህልውና ትግል ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ገልጿል። ሕዝባዊ ኃይላችን የጋራ አንድነቱን በማጠናከር የጀመረውን የነፃነት ጉዞ አጠናክሮ ይቀጥላል። "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን ይረጋገጣል! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት ሸዋ፣ ኢትዮጵያ

🚨 ሰበር ዜና 🚨 ​ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ​በሁለት እጁ እነሴ ወረዳ ልዩ ስሙ "ሞጣ ሙገር ቻይና ካምፕ መሽጎ የነበረውና የብልፅግና መራሹን ዕድሜ ለማራዘም የሚንቀሳቀሰው የብርሃኑ ጁላ ሰራዊት ላይ የቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር በ54ኛ ክፍለ ጦር እና በ64ኛ ክፍለ ጦር (ሳተናው ሻለቃ) በመቀናጀት ባካሄዱት መብረቃዊ ኦፕሬሽን የአማራን ህዝብ በማሰቃየትና ሴት በመድፍር ተሰማርቶ የነበረውን የጠላት አንድ ሙሉ እሬጅመንት ኃይል ሙሉ በሙሉ በመደምሰስ ቀጠናውን ሙሉ በሙሉ ነፃ በማድርግ ድልኝ ተቀናጅተዋል!! ​በዚህ በታቀደና በተመራ ከፍተኛ ወታደራዊ ኦፕሬሽን ከሌሊቱ 10:00 ሰዓት እስከ 12:40 በዙ=23እና በመድፍ የታገዘ ውጊያ ቢያደርግም ጀግኖች በድል በማጠናቀቅ በጠላት ኃይል ላይ ከባድ ኪሳራ የደረሰ ሲሆን፣ ከፍተኛ መጠን ያለው የጦር መሣሪያ እና የተተኳሽ ጥይት በጀግናው የቴዎድሮስ ልጆች ፋኖ እጅ በግባት የተማረኩ የጦር መሣሪያዎች ​የቡድን እና የነፍስ ወከፍ መሣሪያዎች በየ3ወሩ ግብር መገበር የማይሰለቸው የአብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ የብርሃኑ ጁላ ሰራዊት ተደምስሷል በዚህም የ201ኛ ኮር የ54ኛና የ64ኛ ክ/ጦር ባቀዱትና በመሩት ኦፕሬሽን መሰረት ►2 ብሬን ►1ስናይፐር ►1 ዲሽቃ ►47 ክላሽ ►5 አብራራው ►4 ኤስኬስ ሲሆን ►7000ሺ የክላሽ ተተኳሽ ►1400 የዲሽቃ ተተኳሽ ►2500የብሬን ተተኳሽ ► 11ወተደራዊ ትጥቅ ተማርኳል የጠላት አንድ እሬጅመንት ሀይል ሙሉ በሙሉ ደምስሰን ቀጠናውን ነፃ አድርገናል። አዲስ ትውልድ፣አዲሰ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

የደጃዝማች ተሰማ እርገጤ ክፍለ ጦር በልዩ ኦፕሬሽን ጠላትን ሲደመስስ ፤ ወታደራዊ ቁሳቁስም ተማረከ!!                              ቀን 23/10/2018 ዓ.ም [ሸዋ ጠቅላይ ግዛት] — በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት፣ በአሳምነው ዕዝ መሐመድ ቢሆነኝ ኮር ስር የሚንቀሳቀሰው የደጃዝማች ተሰማ እርገጤ ክፍለ ጦር፣ በጠላት ኃይል ላይ ስኬታማ የልዩ ኦፕሬሽን እርምጃ መውሰዱን የዕዙ ህዝብ ግንኙነት አስታወቀ። የክፍለ ጦሩ ሁለተኛ ሻለቃ አባል የሆነው ጀግናው ፋኖ ገዝሀኝ ዘነበ፣ ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ጣርማበር ወረዳ፣ አርማኒያ ቀበሌ ውስጥ በተንቀሳቀሰው የገዢው ሥርዓት ታጣቂ (ሚሊሻ) ላይ የተጠናና ጥንቃቄ የተሞላበት ድንገተኛ ጥቃት ሰንዝሯል። በተወሰደው ፈጣን ወታደራዊ እርምጃ የጠላት ታጣቂው የተደመሰሰ ሲሆን፣ የሚከተሉት የጦር መሣሪያዎችና ትጥቆች በቁጥጥር ስር ውለዋል፦ .ሁለት (2) የክላሽንኮቭ (AK-47) ጠመንጃዎች .ሰላሳ (30) የክላሽንኮቭ ጥይቶች የኦፕሬሽኑ ፈጻሚ የሆነው ፋኖ ገዝሀኝ ዘነበ የተጣለበትን ግዳጅ በብቃትና በጀግንነት ካጠናቀቀ በኋላ፣ የማረከውን ወታደራዊ ንብረት ይዞ ወደ ተመደበበት የደጃዝማች ተሰማ እርገጤ ሁለተኛ ሻለቃ አሃዱ በሰላም ተቀላቅሏል። የአሳምነው ዕዝ ወታደራዊ አመራር የፋኖ ገዝሀኝ ዘነበን ብቃትና ቁርጠኝነት ያደነቀ ሲሆን፣ ይህ ዓይነቱ ስልታዊ ጥቃት የሕዝባችንን የህልውና ትግል ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ገልጿል። ሕዝባዊ ኃይላችን የጋራ አንድነቱን በማጠናከር የጀመረውን የነፃነት ጉዞ አጠናክሮ ይቀጥላል። "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን ይረጋገጣል! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት ሸዋ፣ ኢትዮጵያ

የቴዎድሮስ ዕዝ 201 ኮር 54 ክፍለ ጦር በሞጣ/ሙገር መብረቃዊ ጥቃት ፈጸመ፤ ዲሽቃና ልዩ ልዩ የጦር መሣሪያዎችንም ማረከ ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በአማራ ፋኖ የቴዎድሮስ ዕዝ አባላት በሞጣ/ሙገ
+1
የቴዎድሮስ ዕዝ 201 ኮር 54 ክፍለ ጦር በሞጣ/ሙገር መብረቃዊ ጥቃት ፈጸመ፤ ዲሽቃና ልዩ ልዩ የጦር መሣሪያዎችንም ማረከ ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በአማራ ፋኖ የቴዎድሮስ ዕዝ አባላት በሞጣ/ሙገር ግንባር ላይ በጠላት ኃይል ላይ አስደማሚ መብረቃዊ ጥቃት ፈጽመዋል። ትናንት በተከናወነው በዚህ የስኬት አውደ ውጊያ የጠላትን ኃይል መበታተን የተቻለ ሲሆን፣ በርካታ ወታደራዊ ንብረቶችና የጦር መሣሪያዎች በጀግኖቹ አርበኞች እጅ ሊማረኩ ችለዋል። በአሁኑ ሰዓት የተማረኩ ንብረቶች የመቁጠርና የማደራጀት ሥራ እየተሠራ ሲሆን፣ እስከ አሁን በተደረገው ማጣራት 1 ዲሽቃ፣ ብሬን፣ ስናይፐር፣ በርካታ ክላሽንኮቭ ጠመንጃዎች፣ ወታደራዊ ሻንጣዎች እና ልዩ ልዩ ወታደራዊ ቁሳቁሶች በፋኖ ቁጥጥር ሥር ውለው ገቢ መደረጋቸውን የዕዙ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አስታውቋል።