ru
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Открыть в Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Больше
2 926
Подписчики
+3224 часа
+3727 дней
+36630 дней
Архив постов
ቤተሰብ ይህችን አሻራችሁ አስቀምጡ ክብር ይስጥልኝ፦ Can you add your signature? ✍️ https://c.org/yXvJgv2F5p

የመጨረሻውን የነፃነት ሳቅ የምንስቀው እኛ ነን! ✊​የአሳምነውነት ፅናት ያላቸው ጀግኖቹ ወንድሞቼ... መልካም ሰንበት ተመቸሁላችሁ! #Dave #Amhara
የመጨረሻውን የነፃነት ሳቅ የምንስቀው እኛ ነን! ✊​የአሳምነውነት ፅናት ያላቸው ጀግኖቹ ወንድሞቼ... መልካም ሰንበት ተመቸሁላችሁ! #Dave #Amhara

ሰበር ዜና! ዛሬም አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ 303ኛ አሳምነዉ ኮር ድልን ተጎናጽፏል። በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጀነራል በሆነው ኃይሉ ከበደ የተሰየመችው ነበልባሏ 14ኛ ኃይሉ ከበደ ክፍለጦር እና በአማራ የሕልውና ተጋድሎ ህያው ታሪክ እየፃፈ በሚገኘው ጀኔራል ተፈራ ማሞ ስም የተሰየመችው 19ኛ ተፈራ ማሞ ክፍለጦር እና ዋግሹም ብርጌድ በጋራ ዉጊያ የአገዛዙን ዘረ-ፈጅ ሰራዊት ዛሬም ድባቅ ተመትቷል! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ምኒልክ 1ኛ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር አካል በሆኑት 14ኛ ሐይሉ ከበደ ክፍለ ጦርና 19ኛ ተፈራ ማሞ ክፍለ ጦር እንዲሁም የዋግሹም ብርጌድ ቃኝዎች በጋራ በመሆን በቡግና ወረዳ 07 ቀበሌ ብርኮ ከተማ ላይ ገዥ ቦታ ላይ ደፈጣ በመጣል የብልፅግና 65ኛ ክፍለ ጦር  ሰራዊትን አይቀጡ ቅጣት ቀጥተውታል። ነሃሴ 30/ 2018 ዓ/ም በተደረገው ትንቅንቅ የጠላት ሐይል ከመድፍ ጀምሮ የአየር መቃወሚያ ዙ-23ን ጨምሮ በሜካናይዝድ የታገዘ ውጊያ ቢያደርግም አይበገሬዎቹ ፋኖዎች ጠላትን ስቦ በማስገባትና በቆረጣ ሲያራግፉት ያመሹ ሲሆን የፋኖዎችን ምት መቋቋም ያቃተው የአገዛዙ ሰራዊት አግሬ አውጭኝ ብሎ ወደ ነበረበት አይና ከተማ፣ ጭላና ላልኪው ፈርጥጦ ተመልሷል። ጠላት ከሦስት ቀን በፊት ነሐሴ 29/ 2018 ዓ/ም ድሐና ወረዳ አዚላ ከተማ ላይ ሐይሉ ሙሉ በሙሉ የተደመሰሰበት ሲሆን ያንን በሚዲያ ሰራዊቱ ማስተባበያ ለመስጠትና ሐሰት ነው ለማስባል አስቦ ሐይሉን በሦስት አቅጣጫ ማለትም ከጭላ በአዚላ፣ ከላልኪው ሰላምሬ እና ከአይና ብርኮ አቅጣጫ ያንቀሳቀሰ ቢሆንም በፋኖዎቹ ብርቱ ክንድ አከርካሪውን መትተውታል። በዚህ አውደ ውጊያ ሃያ ስድስት (26) የጠላት ሐይል ሲደመሰስ፣ አንድ (01) ብሬን፣ አንድ (01) ስናይፐር፣ 15 ጥቁር ክላሽ፣ 1500 የክላሽ ተተኳሽ፣ 39 ወታደራዊ ሻንጣ፣ በርካታ የሰው ኃይል ተማርኳል ሲል የ303ኛ አሳምነው ኮር ቃል አቀባይ መረጃውን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን መምሪያ ጷግሜ:-01/ 2018 ዓ/ም

_*አስቸኳይ የጥንቃቄ መልዕክት ለሁሉም የሰራዊት አመራርና የሰራዊት አባሎቶች መድረስ አለበት* :-_ ጠላት በዓልን ምክንያት በማድረግ የፋኖን ሰራዊትና አመራር አናጠቃለን ብለው ካቀዷቸው ዕቅዶች ውስጥ የሚከተሉት ናቸው። 1ኛ/ በዓልን ምክንያት በማድረግ ወደገጠሩና ፋኖ ወደያዛቸው ቀጠናዎች በሲቪል አስርጎ በማስገባት አመራሩን መምታት 2ኛ/ የፋኖ ሰራዊት ለበዓል ወደቤተሰብ ሊሄድ ሲለሚችል በየሰፈሩ የሰፈር ሚኒሻዎችን ለመረጃነት በመጠቀም ማፈንና መያዝ። 3ኛ/ ለበዓል ሰራዊቱ ሊዘናጋና መጠጥ ሊጠጣ ስለሚችል መረጃን ዘርግቶ ሰርጎ በመግባት ማጥቃት 4ኛ/ ሰራዊቱ ሰብሰብ ብሎ በዓል ሲያከብር መረጃዎችን አስርጎ በማስገባት በድሮን መምታት እና የመሳሰሉትን ዕቅዶች በማቀድ በዓልን እየጠበቀ መሆኑን መረጃዎች የደረሱን መሆኑን እየገለፅን የጠላትን እቅድ ማክሸፊያ ጥንቃቄዎች 1ኛ የሰራዊትም ሆነ የአመራር የፍቃድ እንደሌለ አስጠንቅቆ መንገር 2ኛ ወደኛ ቀጠና የሚመጡ ፀጉረ ልውጥ ሰዎችን በአግባቡ መከታተልና ከተገኙም በአግባቡ ይዞ ምርመራ ማድረግ 3ኛ ለበዓል ስንሰባሰብ ከሲቪሉ ማህበረሰብ ራቅ ያሉ ጫካማ ቦታዎችን መጠቀም 4ኛ/ ቋሚ ቦታዎችን አለመጠቀም እና በተቻለ መጠን ስብስቦችን ማስወገድ 5ኛ/ ጠላት ይመጣባቸዋል ተብሎ በሚጠረጠሩ ቦታዎች ላይ የቀንና የማታ ደፈጣዎችን ማድረግ 6ኛ/ ለረጅም ጊዜ ጫዋታና ጭፈራዎችን አለማድረግ እና ጫዋታ ካስፈለገም በከፍታ ቦታዎች ላይ የድሮንን እንቅስቃሴ የሚከታተል ተመልካች ማስቀመጥ ሰራዊቱን ደህንነት መጠበቅ። በመጨረሻም ሁሉም አመራር ለሁሉም አመራር እንዲደርስ አድርጉ እስከ ሻለቃ አመራሮች እንዲደርስ ይደረግ።

#ሰበር በላስታ ግንባር ብርኮ አከባቢ የጠላት ጦር 360° በፋኖ ተከብቦ ዳሽቆ ቀርቷል ብሬንና ስናይፐርን ጨምሮ በርካታ የጦር መሣሪያና የጠላት አባል በፋኖ ተማርኳል፤ ቀሪው ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል። ምስሉ ከተደመሰሰውን የአብይ አህመድ ሰራዊት በከፊል! ጳጉሜ 01/2018 ዓ.ም #Dave #Amhara

የአርበኞች ጦር በተሬ ክላስተር ወደ ዘመናዊ የክፍለ ጦር አደረጃጀት እየተሸጋገረ ነው ​   ጳጉሜ 01/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ የይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ተሬ ክላስተር የአርበኞች ጦር ሠራዊቱን ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር በጠንካራና ዘመናዊ አደረጃጀት እየሠራ እንደሚገኝ የዕዙ የስምሪት አመራሮች ገለጹ። የአማራ ሕዝብ ሕልውናውን ለማስከበርና የትውልዱን ነፃነት ለማረጋገጥ አደረጃጀቱን ማዘመን፣ ጠንካራ ተቋም መፍጠርና ቆራጥ አመራር መሰየም ወሳኝ መሆኑን በመገንዘብ የአባት አርበኞች ጦር አደረጃጀቱን በማጠናከር ላይ ይገኛል። ቀደም ሲል በብርጌድ ደረጃ ተደራጅቶ ሲንቀሳቀስ የቆየው የተሬ ሕዝብ ድሉን ለማፋጠንና ቀጠናውን ለማስተሳሰር ብርጌዶችን ወደ አርበኞች ክፍለ ጦር በማዋሃድ ለመዋቀር ተዘጋጅቷል። በቀጠናው ታላላቅ ወታደራዊ ጀብዶችን ሲያስመዘግቡ የቆዩት ብርጌዶች ጥልቅ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ግምገማ በማድረግ ውስጣዊ አንድነታቸውን በመፈተሽና ክፍተቶችን በመሙላት አወቃቀራቸውን በማዘመን ላይ ናቸው። በዚህ የግንባታ መርሃ ግብር ላይ ከፍተኛ የድርጅት አመራሮች፣የቀጣናው ስምሪት አካል የዕዝ ከፍተኛ አመራሮች እና የኮር አመራሮች የተገኙ ሲሆን፤ የአፋብን ተቀዳሚ ም/ል ሊቀመንበር አርበኛ መከታው ማሞ ድርጅቱ ወጥ አሰራሮችን በመተግበር ለማይቀረው የነፃነት ጉዞ መዋቅሮቹን እያጠናከረ መሆኑን ገልጸዋል።በዚህም ሁሉም በየደረጃው ለትግሉ የሚጠበቅበትን አበርክቶ በማድረግ ሁልጊዜም ንቁና ቆራጥ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል። በዚህም መሐመድ ስንዴው ብርጌድ እና ታደለ ወርቁ ብርጌድ አመራሮቻቸውን በማዋሃድ አንድ ታላቅ ክፍለ ጦር እንዲመሰርቱ አቅጣጫ ተቀምጧል። ለአዲሱ አርበኞች ክፍለ ጦር በውጊያ ሜዳ ብቃታቸው የተመሰከረላቸው ቆራጥ መሪዎች የተሰየሙ ሲሆን፣ በተደራጀ ሁኔታ ወደ ሥራ በመግባት የሕዝቡን ሰቆቃ ለመታደግ መዘጋጀታቸው ተገልጿል። ​"ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!"     "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!" የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ፋሽስቱ የአብይ አህመድ ስርዓት ያሰማራት የስለላ መረጃ በቁጥጥር ዋለች!! የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ(አፋብን) ምንልክ 1ኛ ዕዝ  101ኛ ኮር 15ኛ ክፍለጦር ባደረገው ጥብቅ ክትትል አገዛዙ በስለላ ስራ አሰልጥኖ ያሰማራትን መረጃ በቁጥጥር ስር ማዋል ችሏል። በደቡብ ወሎ ዞን ኩታ በር ወረዳ 014 ቀበሌ ነዋሪ የሆነችው ወ/ሪት ከድጃ መሀመድ ካሴ የተባለችው ግለሰብ ከፋሽስቱ የብልፅግና ስርዓት በተሰጣት ስምሪት የስለላ ስራ ለመስራት በእንቅስቃሴ ላይ እያለች በ101ኛ ኮር 15ኛ ክፍለ ጦር ቃኞች ተለያየን በተባለ ቦታ በቁጥጥር መዋል ችሏልች። ጉልበቱን ምላሱ ላይ ብቻ ያደረገው የፋሽሽቱ ስርዓት ሽንፈቱን ላለመቀበል ሲል በተለያየ መንገድ እየተጋጋጠ ቢገኝም ከክንደ ነበልባሎቹ የ101ኛ አናብስቶች ማምለጥ አልቻለም። ግለሰቧ ከ45ኛ ክፍለ ጦር ጋር ግሸን ተቀምጣ የተለያዩ ስራዎችንም ትሰራ እንደነበር ማረጋገጥ ችለናል ሲል 101ኛ ኮር ሚድያና ኮሙኒኬሽን ክፍል መረጃዉን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!   ጳጉሜ 1 /2018 ዓ.ም

6 የአገዛዙ ቅጥረኛ የሚኒሻ አባላት በ64ኛ ክ/ጦር በቁጥጥር ስር ሲውሉ 2 የሚኒሻ አባላት ክ/ጦሩን ተቀላቅሏል። 64ኛ ክ/ጦር ጶጉሜ 01/2018 ዓ.ም ~~~~~~ በሸበል በረንታ ወረዳ የሚገኘው አገዛዝ ወደ ትግራይ ክልል ለግዳጅ ዝግጁ እንዲሆኑ ትዛዝ ማስተላለፉን ተከትሎ የሚሊሻ አባላቱ እየተተራመሰ እና እየፈራርሰ ይገኛል። የአማራ ህዝብን ለአብይ አህመድ አገዛዝ አሳልፈው የሰጡት የሚኒሻ ተቋም አባል የነበሩ ከአገዛዙ ኃይሎች ጋር ከፍተኛ ውዝግብ ላይ የነበሩ ሆድአደር የሚኒሻ አባላት ወደ ትግራይ ክልል አንዘምትም የትግራይ ህዝብ ወንድማችን ነው የአገዛዙን ትዛዝ አንቀበልም በማለት በሸበል በረንታ መርገጭ ንዑስ ወረዳ ሌዲ እና አካባቢው ቀበሌ እያሱ ጎጥ ተደብቀው የነበሩ ቢሆንም በአካባቢው ማህበረሰብ ጥቆማ መሰረት ነሀሴ 30/2018 ዓ.ም በአፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር በቁጥጥር ስር ውለዋል። በቁጥጥስ ስር ከዋሉት የሚኒሻ አባላት ውስጥ:- 1ኛ.መኳንት ወረቅነህ ሚኒሻ 2ኛ.አባይ እሸቱ ሚኒሻ 3ኛ.ባንታምላክ አያሌው ሚኒሻ 4ኛ.ገበየሁ ድረስ ሚኒሻ 5ኛ.አብዩ እያሱ ሚኒሻ 6ኛ.ቢረስ ውዱ ሚኒሻ በቁጥጥር ስር ሲውሉ ቢወጣ ወርቁ ሚኒሻ የዕድውኃ ወረዳ እነቦርኪት ቀበሌ እና አዳርጋቸው ቦራ እነማይ ወረዳ አንስላል ቀበሌ ተወላጅ የሆኑ አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር ተቀላቅለዋል። አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!                 ጶጉሜ 01/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት

የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦርና የካራ ምሽግ አርበኞች ጦር በመርሀቤቴ አውራጃ በቅንጅት በነበረ ውጊያ ድል መቀዳጀታቸው ተገለፀ!! ጳጉሜ 01/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ በተደረገ የጨበጣ ውጊያ በ101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር ላይ ከፍተኛ ድል መቀዳጀቱን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ፣ አፄ ዓምደ ጽዮን ኮር አፄ ዳዊት ክፍለጦርና ካራ ምሽግ አርበኞች ጦር ድል መቀዳጀታቸውን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አስታወቀ። ቅዳሜ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም ከንጋቱ 11፡30 ጀምሮ የ101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር ከሚዳ ሬማ ወረዳ በመነሳት በሶስት አቅጣጫዎች ማለትም በሰንቀሌ ቆፌ፣ በቃራመጅት ሸንኮራ እና በሬማ ከተማ ቢራባ መስመሮች ወደ ፋኖ ቀጠና በማንቀሳቀስ ከበባ ለመፈፀም ሙከራ አድርጎ በነበረ ጠላት ላይ መሆኑን ገልጿል። ነገር ግን በአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር አሃዶች እና በካራ ምሽግ አርበኞች ጦር በተደረገ የተቀናጀ የጨበጣ አፀፋዊ ውጊያ ''ወደይላ'' በተባለው ልዩ ቦታ የመልሶ ማጥቃት እርምጃ በመውሰድ ታላቅ ድል መቀዳጀት እደቻሉ አብራርቷል። እስከ ቀኑ 8:00 ድረስ በቆየው በዚህ አውደ ውጊያ፡ አንድ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዥን ጨምሮ ከስምንት(8) የአገዛዙ ሰራዊት አባላት ጋር የተደመሰሱ ሲሆን፣ በርካቶች ደግሞ መቁሰላቸውን አክሏል። የቆሰሉት የጠላት አባላት በሬማ ከተማ ጤና ጣቢያ፣ በሬማ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ካምፕ እና በአለም ከተማ አናት ሆስፒታል ህክምና እየተከታተሉ እንደሚገኙ አረጋግጦ ተጠቅሶ፡ የሟችና የቁስለኛ ትክክለኛ ማንነት በመረጃ አጣርተን የምንመለስ ይሆናል ሲል ገልጿል። በዚሕ የአፀፋ ውጊያ ሽንፈት የተበሳጨው ጠላት የቃራ መጅት ነዋሪ የሆኑትን አርሶ አደር አቶ አቡሽ ሰጠኸኝን በጥይት ደብድቦ መግደሉ ሲረጋገጥ፤ ከ13 በላይ የሚሆኑ ወጣቶችን በአስገዳጅ ሁኔታ አፍኖ በመውሰድ "የተማረኩ ፋኖዎች ናቸው" በሚል ሀሰተኛ ፕሮፓጋንዳ ለመስራት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተረጋግጧል ብሏል። በተጨማሪም የአርሶ አደሮችን የሶላር ንብረቶች ጨምሮ ሌሎች ቁሳቁሶች በመዝረፍ ሙትና ቁስለኞቹን በሸራ ሸፍነው ወደ ሬማ ከተማ ከነ ሽንፈቱ መመለሱን ጠቅሷል። 👉 በመጨረሻም፣ በአካባቢው የሚገኙ ወጣቶች ከግዳጅ ወታደራዊ አፈሳ እራሳቸውን እንዲጠብቁ እያሳሰበ፣ አቅምና ፍላጎት ያላቸው ወጣቶች ትግሉን በመቀላቀል ራሳቸውንና ህዝባቸውን እንዲታደጉ ጥሪ አስተላልፏል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

‎አዲስ አመትን ከቤተሰቦቻቸው ጋር ለማክበር #የወሰኑ የአምባገነኑ ስርዓት ጠባቂ ሰራዊቶች አፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝን ተቀላቀሉ። ‎===================== ‎ነሐሴ : 30/2018 ዓ/ም ‎ ‎ከሞት ተርፈው ደጋ ዳሞት ከገቡት የአገዛዙ ሃይል በእየቀኑ እየከዳ ይገኛል። ‎ከነዚህም መካከል :- ‎1ኛ. አብዲ ምስጋናው --ጥቁር ክላሸንኮቭ ‎2ኛ ሳሊሞ ምሀመድ-- ጥቁር ክላሽንኮቭ ‎3ኛ. አብዱ ሰይድ-- ጥቁር ክላሽንኮቭ ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው አፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 109ኛ ኮር 99ኛ ክ/ጦር ደጋዳሞት ሻለቃን የተቀላቀሉ ሲሆን፤ በሻለቃ አመራሮች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ‎ ‎አዲስ ትውልድ አዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ ‎ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ‎ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም ‎ አፋብን|ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ

💢ሁለት ቲም መሪወችን ጨምሮ 3 የመከላከያ አባላት ፋኖን ተቀላቀሉ❗️ የስርዓቱን መውደቅ 11ኛው ሰዓት ላይ መሆኑን ቀድመው ያወቁ የአገዛዙ ጦር ሰራዊት አባላት በየቀኑ እየፈረሱ ወደ ፋኖ መቀላቀላቸውን በቀጠሉበት በዚህ ሰዓት የሰራዊቱ የተዋረድ አመራሮችና አባላት ከስምሪት ቀጠናቸው ከነሙሉ ትጥቃቸው በቡድን እና በተናጥል በመውጣት አንድያ ህይወታቸው እያተረፉ ይገኛል። በሰከላ ከተማ ግሽ ተራራ ላይ ከሰፈረው የምስራቅ ዕዝ 73ተኛ ክፍለ ጦር 3ኛ ሬጂመንት ፣ 2ኛ ሻምበል ፣ 1ኛ ጋንታ ውስጥ የቆዩት የቲም መሪ ፣ ምክትል ቲም መሪ እና አንድ አባል በመሆን ዛሬ ነሃሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም  2(ሁለት) ጥቁር ክላሽ እና አንድ(1) ባለሁለት እግር ክላሽ ፣ ከ600 መቶ ተተኳሽ ጋር በመያዝ ከነሙሉ ትጥቃቸው በመውጣት የፋኖ ሰራዊትን ተቀላቅለዋል። ዛሬ ነሃሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ከሰከላ ግሽ ተራራ ላይ ከሰፈረው የአገዛዙ ጦር መካከል ወደ ህዝባችን አንተኩስም በማለት ፋኖን በመቀላቀል ህይወታቸውን ያተረፋት የመከላከያ አባላት 1, ኢሳያስ - ቲም መሪ 2, ገዲሳ -  ም/ቲም መሪ 3, ሸጋው - አባል ሲሆኑ በአፋብን የቴወድሮስ 2ኛ ዕዝን ተቀላቅለዋል።   (ነሃሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም)