en
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Open in Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Show more
2 767
Subscribers
+3524 hours
+447 days
+5030 days
Posts Archive
ሰበር የድል ዜና ! የአፋብን|ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 105ኛ ኮር 66ኛ ክ/ጦር በረቀቀ ወታደራዊ ጥበብ በጠመደው ፀረ-ተሽከርካሪ ፈንጅ መተከል ፓዊ ወረዳ መንደር 24 ቀበሌ ልዩ ስሙ ሰኞ ገበያ ከተባለ ቦታ ላይ  የአረመ*ኔውን ብልፅግና አንድ ጋንታ ሙሉ ሠራዊት እና ሙሉ ሎጅስቲክስ የጫነ አንድ የኦራል ተሽከርካሪን ሙሉ በሙሉ አመድ አድርጓል። አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!

እነ ሞት አፈሪዎቹ የ7/ለ70 ክፍለ ጦር፤የጦር አበጋዞች በብርቂቶ ቀበሌ ጠላትን ድባቅ በመምታት ታላቅ ድል ተቀዳጁ!!     ጳጉሜ 02/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ 7/ለ70 ክፍለ ጦር በኤፌሶን አጣዬ አላላ ክላስተር ብርቂቶ ቀበሌ በተደረገ ከፍተኛ ተጋድሎ የጠላትን ኃይል አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ድል መቀዳጀታቸው ታወቀ።  ለዐቢይ አህመድ አገዛዝ ታማኝ እንደሆነ የሚነገርለት 102ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር ከአጣዬ እና ከሰንበቴ አቅጣጫዎች በመነሳት በፋኖ ላይ ድንገተኛ ከበባ ለማድረግ ብርቂቶ የተከሰተውን ጠላት፤ ቀድመው በመዘጋጀት ስልታዊ የማጥቃት ውጊያ ያደረጉት አናብስቶች ታላቅ ድል አስመዝግበዋል። በብርቂቶ ቀበሌ በተካሄደው ከባድ ውጊያ የጠላት ኃይል ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳቁሳዊ ውድመት ማስተናገዱን " ጫላ ስዩም" የተባለ አንድ የአገዛዙ አባል እጁን ለፋኖ ከሰጠ በኃላ እንዲሕ ሲል አብራርቷል፤ የአብይ አሕመድ ስርዓት በተሳሳተ ትርክት ከየስራ ቦታችን አፍሶ አምጥቶ፣ ከፋኖጋ በነበረው ውጊያ በጣም በርካታ አባሎቻችን ሙትና ቁስለኛ ሆነውብናል ሲል አረጋግጧል። ይሕንን ታላቅ ገድል የክፍለ ጦሩ አካል ደመላሽ ሻለቃ ያስመዘገበች ሲሆን፣ ከጠላት የሚከተሉትን ንብረቶች ለክፍለ ጦሩ ገቢ አድርጋለች፦ ✔ (2) ጥርጥር ክላሽንኮቭ መሳሪያ ✔ (120) የክላሽኮቭ ተተኳሽ ✔  (3) ወታደራዊ ቦርሳዎች ✔ (2) የውሃ ኮዳዎች ✔ (8) ካዝናዎች ✔ (4) F1 ቦንቦች በመጨረሻም በዚሕ አውደ ውጊያ ክፉኛ የቆሰሉት የጠላት አባላት ወደ አጣዬና ሰንበቴ ለህክምና በሪፈር እደተላኩና ሌሎች ቀላል ቁስለኞች በአላላ ጤና ጣቢያ እየታከሙ እንደሆነ በውስጥ መረጃዎቹ ማረጋገጡን ገልጿል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

የ7/ለ70 ክፍለ ጦር፤የጦር አበጋዞች በብርቂቶ ቀበሌ ጠላትን ድባቅ በመምታት ታላቅ ድል ተቀዳጁ!!     ጳጉሜ 02/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ 7/ለ70 ክፍለ ጦር በኤፌሶን አጣዬ አላላ ክላስተር ብርቂቶ ቀበሌ በተደረገ ከፍተኛ ተጋድሎ የጠላትን ኃይል አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ድል መቀዳጀታቸው ታወቀ።  ለዐቢይ አህመድ አገዛዝ ታማኝ እንደሆነ የሚነገርለት 102ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር ከአጣዬ እና ከሰንበቴ አቅጣጫዎች በመነሳት በፋኖ ላይ ድንገተኛ ከበባ ለማድረግ ብርቂቶ የተከሰተውን ጠላት፤ ቀድመው በመዘጋጀት ስልታዊ የማጥቃት ውጊያ ያደረጉት አናብስቶች ታላቅ ድል አስመዝግበዋል። በብርቂቶ ቀበሌ በተካሄደው ከባድ ውጊያ የጠላት ኃይል ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳቁሳዊ ውድመት ማስተናገዱን " ጫላ ስዩም" የተባለ አንድ የአገዛዙ አባል እጁን ለፋኖ ከሰጠ በኃላ እንዲሕ ሲል አብራርቷል፤ የአብይ አሕመድ ስርዓት በተሳሳተ ትርክት ከየስራ ቦታችን አፍሶ አምጥቶ፣ ከፋኖጋ በነበረው ውጊያ በጣም በርካታ አባሎቻችን ሙትና ቁስለኛ ሆነውብናል ሲል አረጋግጧል። ይሕንን ታላቅ ገድል የክፍለ ጦሩ አካል ደመላሽ ሻለቃ ያስመዘገበች ሲሆን፣ ከጠላት የሚከተሉትን ንብረቶች ለክፍለ ጦሩ ገቢ አድርጋለች፦ ✔ (2) ጥርጥር ክላሽንኮቭ መሳሪያ ✔ (120) የክላሽኮቭ ተተኳሽ ✔  (3) ወታደራዊ ቦርሳዎች ✔ (2) የውሃ ኮዳዎች ✔ (8) ካዝናዎች ✔ (4) F1 ቦንቦች በመጨረሻም በዚሕ አውደ ውጊያ ክፉኛ የቆሰሉት የጠላት አባላት ወደ አጣዬና ሰንበቴ ለህክምና በሪፈር እደተላኩና ሌሎች ቀላል ቁስለኞች በአላላ ጤና ጣቢያ እየታከሙ እንደሆነ በውስጥ መረጃዎቹ ማረጋገጡን ገልጿል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ከጠላት ነፃ ባወጣቸው ቀጠናዎች ሰፊ ሕዝባዊ መድረክ እና ጊዜያዊ የሲቨል አስተዳደር መዋቅር አዋቀረ! በደቡብ ወሎ ዞን መቅደላ ወረዳ 016 ደብረ ዘይት ታዳጊ ከተማ ከህዝብ ጋር ሠፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን አብዘሃኛው የቀበሌው ማህበረሰብ በመድረኩ ላይ ተገኝቷል። በዚህ ደማቅ ህዝባዊ መድረክ ላይ የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን ከነዚህም መካከል የአማራ ሕዝብ የትግል መነሻ ምክኒያት፣ ግብ እና መዳረሻ አላማ፣ የትግሉ ወቅታዊ ቁመና፣ ስለ ቀጠናዊ አሰላለፍ እንዲሁም ስለ ሲቨል መዋቅር ጥቅምና አስፈላጊነት ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል። በውይይቱ ላይ የምኒልክ 1ኛ ዕዝ የጤና መምሪያ ሃላፊ አርበኛ ዶክተር ኡስማን ሰይድ፣ የምኒልክ 1ኛ ዕዝ ምክትል አደረጃጀት መምሪያ ሃላፊ አርበኛ ሲሳይ ሳተናው፣ የምኒልክ 1ኛ ዕዝ ምክትል ሚዲያና ኮሚኒኬሽን መምሪያ ሃላፊ አርበኛ ዳሽን፣ የ141ኛ ክፍለጦር አስተዳደር አርበኛ ፍሰሃ እንዲሁም የወረዳው ሲቪል አስተዳደሮች ተገኝተዋል። በመጨረሻም ከቀበሌው ማህበረሰብ በርካታ ጥያቄዎች ያነሳ ሲሆን በምኒልክ 1ኛ ዕዝ አመራሮች አጥጋቢ ምላሽ ተሰጥቷል። ሕዝቡም በትግሉ ደስተኛ እንደሆነና በቀጣይም አገዛዙን ለመቅበር ዝግጁ መሆናቸኑን አስረድተዋል። የቀበሌው ሕዝብን ሊመሩና ሊያስተባብሩ የሚችሉ የቀበሌ አመራሮችን በማዋቀር መድረኩ ተጠናቋል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን መምሪያ! ጷግሜ:-03/ 2018 ዓ/ም

ሰበር ዜና የጀብደኛዉ ምኒልክ 1ኛ ዕዝ አሃድ የሆኑት 16ኛ ኮር እና ልዩ ዘመቻ የጠላት ሠራዊትን ዋጥ አድርገዉታል። አንድ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዥ ሲገደል ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች ወድመዋል! የምኒልክ 1ኛ ዕዝ አሃዶች ከትናንት ጳጉሜ 02/2018 ዓ/ም ጀምሮ በሦስት ግንባሮች እያደረጉት በሚገኘው ከባድ ተጋድሎ ለጊዜው ማዕረጉ በውል ያልተለየ አንድ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዥ ሲገደል በርካታ ተሽከርካሪዎች ወድመዋል። ዝርዝሩን እንመለስበታለን! መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ! ጷግሜ:-03/ 2018 ዓ/ም

በመንዝ እና ግሼ አውራጃ የዕዙ ስምሪት አካላት የክላስተር አደረጃጀቶችን በመገምገም፡ በክላስተሩ የአባት አርበኞች ጦር መመስረቱ ተገለፀ!! ጳጉሜ 03/2018 ዓ.ም በመንዝ እና ግሼ አውራጃ ከአንድ ወር በፊት የተዋቀሩ ክላስተሮችንና አደረጃጀቶችን ወርሃዊ የስራ አፈጻጸም መገምገሙን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ የስምሪት ቡድን አስታወቀ። ግምገማው በመንዝ እና ግሼ አውራጃ በሚገኙት ግራርአምባ እና ወጀድ ክላስተሮች ላይ የተካሄደ ሲሆን፣ በስራቸው የሚተዳደሩ ቀበሌዎችን ግልጽና ቀልጣፋ አሰራር በመከተል የህዝብ አገልግሎትን በማቀላጠፍ እንዲሁም የፍትህ ስርዓቱን በማሻሻል ረገድ የተከናወኑ ስራዎች ተገምግመዋል። በርካታ ቀበሌዎችን እና አባት አርበኞችን ያቀፈው "ወዠድ ክላስተር" (014፣ 015፣ 016፣ 017፣ 018 እና 019) ቀበሌዎችን በቅንጅት ገምግሞ፡ ጠንካራና ግዙፍ፣ የአርበኞች ክፍለ ጦር መመስረቱን አስታውቀዋል። የተመሠረተው የአርበኞች ክፍለ ጦሩ የአካባቢውን ሰላም ከመጠበቅ ባሻገር ለህልውና ትግሉ ስኬት ሚናውን እንደሚወጣ ተገልፆ፣ ይህ አዲስ የተመሰረተው ክፍለ ጦር በክብር በተሰዋው ታጋይ ስም " ካሳ አደፍርስ ክፍለ ጦር" ተብሎ ተሰይሟል። ይሕ ክፍለ ጦር፡ ነብሮ ሻለቃ፣ልጅ ስዩም መኮንን ሻለቃና ሙላቱ ወልደሚካኤል ሻለቃዎችን በማጣመር የተዋቀረ ሲሆን፧ ለክፍለ ጦሩ ጠንካራና ታታሪ አመራሮችን ሠይሞ ተዋቅሯል። በመጨረሻም ለክፍለ ጦሩ የተሰየሙት አመራሮች የተጣለባቸውን አደራ፡ የፍትህ እና የሰላም ማስከበር ኃላፊነት በቅንነት፣ በታማኝነትና በተጠያቂነት ለማገልገል ቃለ-መሀላ ፈጽመው ውይይቱ ተጠናቋል። "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር አጥናፋ ብርጌድ አባላትን ለማፈን በሌሊት የተንቀሳቀሰው የአገዛዙ ሚሊሻ በደረሰበት ድንገተኛ ምት ከፍተኛ ኪሳራ ደረሰበት! ጷጉሜ 2/2018ዓ.ም ከሌሊቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ በወገራ ወረዳ  ልዩ ቦታው ብራ ታዲወስ የጠላት ኃይል አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር አጥናፋ ብርጌድ አባላት ላይ አፈና ለመፈጸም እንቅስቃሴ አድርጎ የነበረውን የጠላት ኃይል የመልሶ ማጥቃት እርምጃ 3 የኃይል አባላትን ሲደመሰሱ 9 ያህሉን ደግሞ  ከቀላል እስከ ከባድ ቁስለኛ ሆነዋል። በዚህ ድንገተኛ ምት የተደናገጠው የጠላት ኃይል በርካታ ንብረቶችን  ጫማዎችን እና ትጥቆችን እያዝረከረከ ከአምባጊወርጊስ ከተማ ተጨማሪ የመከላከያ እና የአድማ ብተና ኃይል በማስገባት በብራ ታዲወስ እና ሰንበትየ ዙርያ  እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። በዚህ ድንገተኛ ምት ሽንፈት የደረሰበት ኃይል ​ተመስገን ጌታ የኋሌ የተባለ የ10 ዓመት ህፃን የተገደለ ሲሆን፣ በክረምት የግብርና እና የእንስሳት ጥበቃ ሥራ ላይ የነበሩ ከ28 በላይ ንፁሃን ዜጎች "የፋኖ ቤተሰብ ናችሁ" በሚል ሽፋን ታስረዋል። ከነዚህ መካከል እድሜ ጠገብ አዛውንቶች፣ ሴቶች እና ህፃናት እንደሚገኙበትና የአርሶ አደሩ እንስሳት ጭምር ማለትም ከብት፣ በግ፣ ፍየልና ዶሮዎችን የማረድ እና የመዝረፍ ድርጊት ዘግናኝ ችግሮችን እየተፈጸመ መሆኑን መረጃውን ያደረሰን የክፍለ ጦሩ የህዝብ ግንኙነት ነው። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ​አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

የአጣዬ ህዝብ በረጅም የጽናትና የመከራ ታሪኩ ውስጥ፣ በየዘመናቱ አብረውት ከበሉና ከአንድ ማህፀን ከወጡ የራሱ ወገኖች ብዙ ከሃዲዎችንና ባንዳዎችን አሳልፏል፤ ዛሬም ያሳልፋል፣ ነገም በታሪክ መዝገብ ውስጥ እያሳለፋቸው ይኖራል። ነገር ግን የዚህ ግለሰብ አረመኔያዊነትና ጭካኔ የተሞላበት ተግባር ግን ከማንኛውም የበደል ታሪክ በላይ ሆኖ የጠቅላላውን የአጣዬ ህዝብ ልብ በፅኑ ሀዘን የሚያደማ፣ ለመሸከም እጅጉን የሚከብድ መራራ እውነት ሆኗል። ​ወደ ኤፍራታ ግድም ፣ ለነገ ተስፋ የነበሩ ምንም የማያውቁ ንጹሃን የአጣዬ ወጣቶችን ያሳድዳል፤ ያለ አንዳች ጥፋታቸው በእስር ቤት ውስጥ እያፈነ ያሰቃያቸዋል። በላባቸው ያፈሩትን ንብረት፣ ጥረታቸውንና መላ ጥሪታቸውን ያለ አንዳች ርህራሄ እያወደመ ይዘርፋል። በዚህ ብቻ ሳይበቃ፣ አእምሮ የሚጸየፋቸውን፣ ሰብአዊነትንና የህዝባችንን ክብር የሚያዋርዱ እጅግ አላስፈላጊና ዘጋቢ ስራዎችን ይፈጽማል። ​ከሁሉም በላይ ግን የህዝቡን አንጀት የሚያቃጥለውና እንባን የሚያስቆርጠው የሴቶቻችን ሁኔታ ነው፤ የዚህ አበሳ ደራሽ የሆነውን የአጣዬን መልካም መልካም ሴቶች "ለመከላከል" በሚል መራራና አሳዛኝ ምክንያት፣ ፍላጎታቸውንና ክብራቸውን ረግጦ ለጀነራሎች በግዳጅ አሳልፎ ይሰጣል። ይህ በህዝባችን ላይ የደረሰ ውርደትና የእናቶቻችን እንባ ሰማይን የሚያንቀጠቅጥ ሀዘን ሆኖብናል። ​እውነት ለመናገር ወንድሙ ካሳ በገዛ ወገኑና በአጣዬ ህዝብ ላይ የሚሰራው ይህ አረመኔያዊ ስራ እጅጉን ከባድ፣ ህመም የሚያበዛና የታገሱትን ድንበር ያለፈ ነው። ነገር ግን ከዚህ በላይ መከራውን ዝም ብሎ ማየት አይቻልም። ምንም ይሁን ምን ከምንም ነገር በላይ ለአማራና ለአጣዬ ህዝብ ህልውና፣ ክብርና ታሪክ የሚበልጥ የለም። ​የአጣዬ ህዝብም ይህን መራራ ሀዘንና የበደል ጽዋ እያየ ከእንግዲህ እጁን አጣጥፎ አይቀመጥም፤ እኔም የዚህ ህዝብ አካል ነኝና በቀጥታ ወደ ስራ እገባለሁ። ከዚህ በኋላ ማን እንደሆንኩኝ፣ ለወገኔና ለህዝቤ የመቆም አቅሜ ምን ያህል እንደሆነ በተግባር አሳየዋለሁ! #Dave #Amhara

በፈቃዱ በላይ ክፍለ ጦር በወታደራዊ ብልሃትና ህዝባዊ ወገንተኝነት፡ አገዛዙ በግዳጅ ለጥይት ማብረጃ ያሰለፋቸውን ንጹሐን ዜጎች ሕይወት ታደገ!! ጳጉሜ 02/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት፣ መራቤቴ አውራጃ ደራ ወረዳ በሚገኘው ቱቲ ገብሮ (01 ቀበሌ) ሠቀዮ ጎጥ፣ ጨቋኙ የአበይ አህመድ አገዛዝ ወንበር አስጠባቂ የሚሊሻ ኃይል በህዝቡ ላይ የደቀነውን የግዳጅ ሰንሰለትና የጥይት ማብረጃ ሴራ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ፣ አፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር፣ በፈቃዱ በላይ ክፍለ ጦር አናብስቶች በላቀ ወታደራዊ ብልሃትና ጥበብ ማክሸፋቸውን የኮሩ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አስታወቀ። ገዥውን ስርዓት እያገለገሉ የሚገኘው ሚሊሻ፣ ትናንት ምሽት በ01 ቀበሌ የሚሊሻ ጠርናፊ ሻለቃ መሪ አቶ ደረጀ ተምትም ጥሩምባ በማስነፋት፣ ህዝቡ ማለዳ ላይ ወደ ማሳ ወጥቶ አረም እንዲያርምለት ትዕዛዝ አውርደው፤ ይሕንን የግዳጅ ትዕዛዝ በማይቀበሉ አካላት ላይ የ2,000 (ሁለት ሺህ) ብር የገንዘብ ቅጣት እንደሚጣልበት በመግለፅ ከፍተኛ ማስፈራሪያና ማስጠንቀቂያ አስተላልፎ ነበር። መረጃው በአግባቡ የደረሳቸው የበፈቃዱ በላይ ክፍለ ጦር የተሸረበውን ሴራ አስቀድሞ በመረዳት፣ ከከተማው ወጣ ብሎ በሚገኘው የአቶ ደረጀ ተምትም ማሳ አካባቢ ቀድሞ ስልታዊ ቦታ በመያዝ ደፈጣ አዘጋጅተው፤ ከተጣለበት የገንዘብ ቅጣት ለማምለጥ ማለዳ በልጁ ወደ ማሳው የተገደደውን ሕዝብ ያለምን ተኩስ ለመታደግ ተችሏል። ጥበቃ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቅ የነበረው ሚሊሻ ህዝቡን አሳልፎ ወደ ማሳ በመላክ አፋፍ ተኩስ እዲከፈትባቸው ያደረገ ቢሆንም በተሳካ የመረጃ ክትትል ሕዝቡን ሰብሰቦ ግንዛቤ በመስጠት የጠላትን እቅድ ሳይሳካ እዲመለሱ ተደርጓል።መታደግ ተችሏል። መረጃን ተጠቅማችሁ ላደረጋችሁት ወታደራዊና ፖለቲካዊ ጥበብ እጅግ እያደነቅን፣ እዲሕ አይነቱን የሴራ ፖለቲካ ግንዛቤውም ይሁን ጠላትን የመተባበር ፍላጎቱ ሳይኖረን በግዳጅና በቅጣት ማስፈራሪያ ተደርጎብን ነው ከዚሕ የተገኘንው ሲሉ ሃሳባቸውን ገልፀዋል። " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

መጥፎ ሰዎች እና እባብ የመመሳሰል ችግር የለባቸውም የማይለወጥ አንድ አይነት ባህሪያቸው በማይክሮ ሰከንድ መርዘው በደቂቃወች ውስጥ የመግደል አደገኛነት መለያቸው ነው። ውድ የሰራዊታችን አባላትና አመራር ውስጠ ማንነታቸው በማይታወቅ የሰው እባቦች  ተነድፎ ላለመውደቅ ዋነኛው መፍትሄ አስተውሎ በመራመድ ለጉዞአችን ልዩ ትኩረት በመስጠት ብቻ ነው። "እባብ ለመደ ተብሎ በኪስ አይያዝም" ገላጭ አባባል ነው። ክፉ ሰዎች አዘናግተው ክፉ ተግባራቸውን ከመፈፀም ላይመለሱ መራራትም ልክ አይሆንም። መጥፎ ሰውና እባብ ተፈጥሯቸው ሁለቱም በጸጥታ ይሳባሉ፡ ጥቃታቸውም ድንገተኛና መርዝ ያዘለ ነው። ​የመጥፎ ሰው እና የእባብ ተመሳሳይ ባህሪያት • ​እባብ በሳርና በድንጋይ መካከል ተሸሽጎ እንደሚድበሰብስ ሁሉ፡ መጥፎ ሰውም የእውነተኛ ማንነቱን (ክፋት) በውሸት ፈገግታና በለሰለሰ አንደበት ደብቆ ይንቀሳቀሳል። •  እባብ አደኑን ለመያዝ በጸጥታ እንደሚከታተልና አመቺ ጊዜ እንደሚጠብቅ፡ መጥፎ ሰውም የሰውን ድክመትና ምስጢር በጥንቃቄ ያጠናል። የቀረበህና የወደደህ የሚመስለው ጥቅም ለማግኘትና ጊዜውን ጠብቆ ለመውጋት ነው። •  የእባብ ዋነኛ መሳሪያው መርዙ እንደሆነ ሁሉ፡ የመጥፎ ሰው መርዝ ደግሞ ምላሱ ነው። ያመነከውና የተጠጋኸው መስሎህ ሳለ፡ ሳታስበው ከጀርባህ በሃሜት፡ በሴራና በክፋት ይወጋሃል። •  እባብን ያሞቀውና የተንከባከበው ሰው ቢኖር እንኳን ተፈጥሮውን ቀይሮ ከመንደፍ እንደማይመለስ ሁሉ፡ መጥፎ ሰውም የተደረገለትን መልካም ነገር አያውቅም። ፍቅርና ደግነት ቢሰጡትም ክፋቱን ከመተግበር አይቆጠብም። ​በአጠቃላይ፡ ከመርዛማ እባብ አጠገብ መቆም እንደሚያጋልጥ ሁሉ፡ ከመጥፎ ሰው ጋር የሚደረግ ቅርበትም ውሎ አድሮ ድርጅታዊ አላማን፣ የአንተን ህይወትንና ሰላምን መመረዙ አይቀርም። ይህ ፅሁፍ በራሳቸው ሰው ለተከዱ እና ከጀርባቸው ለተወጉ ለሁሉም  አርበኞች  ይሁን። 👉ከቅርቡ ያለውን ጓዱን ያልጠበቀ ትግል ከሩቅ ያለውን የተበተነ አማራ እንዴት ሊታደገው ይችላል!!!??? መልካም ግዳጅ በያላችሁበት!! #አርበኛ #ዝናቡ #ልንገረው