en
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Open in Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Show more
2 767
Subscribers
+3524 hours
+447 days
+5030 days
Posts Archive
Repost from N/a
ኪነ_ጥበብ 1

Repost from N/a
አርበኛ አበበ ሙላቱ መዝጊያ ንግግር 6

Repost from N/a
100 አለቃ ልመን 5

Repost from N/a
ሻለቃ ሞገስ 4

Repost from N/a
ዶክተር ታደሰ 3

Repost from N/a
አርበኛ ኢሳያስ 2

Repost from N/a
የፀሎት እና የመክፈቻ ንግግር

በታሪክ ውስጥ አንዳንድ አጋጣሚዎች ይመጣሉ፤ ብዙዎች ሁኔታዎችን በዝምታና በፍርሃት በሚታዘቡበት፣ ማንም በየሰፈሩ መደራጀትና እጁን ማንሳት ባልደፈረበት በዚያ ፈታኝ ወቅት ነበር የነፃነት ጥሪ የታሰበው። ​ ​የአማራ ልጅ ፋኖ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው 5ኛ ዕዝ ምክትል ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ኢሳያስ ደመቀ! ​የዛሬ ስምንት ዓመት፣ መንገዱ በስጋትና በችግር በተከበበበት ቅጽበት፣ ቁርጠኝነቱን በመያዝ እስከ ጎንደር መተማ ድረስ ዘለቀ። እዚያ በርሃ ላይ ከጀግኖቹ ወንድሞቹ ጋር በመቀላቀል፣ በአራቱም ማዕዘን ለተበተኑትና ዛሬ ድምፃቸው ተተጠብቆ ለማይሰማው በርካታ የአማራ ልጆች መከታና ድምፅ በመሆን ሸዋን ወከለ። ​ይህ ታሪካዊ ጉዞና ውሳኔ፣ የአማራ የመኖርና የነፃነት ህልውና እንዲረጋገጥ ከተደረጉት የትግል ምዕራፎች መካከል አንዱና ዋነኛው ሲሆን፣ አርበኛ ኢሳያስ ደመቀ በዚያ ታሪክ ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ በመውሰድ ስሙን በወርቅ ቀለም ጽፏል።" ​ ​"ዛሬም ቢሆን ያ የፅናትና የጀግንነት ጉዞ አልቆመም። የትግሉ መሪ፣ የነፃነት አርማና የአማራ ልጅ ፋኖ ድምቀት ከሆኑት ውስጥ አንዱ የሆነው አርበኛ ኢሳያስ ደመቀ በርታልን!! አዲስና ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኙበታል ይህንን ፊስቡክ ይወዳጁት!! Dave Amhara https://t.me/httpsuYkZrGfSZrNjNjFk

#እኛ አማራዎች ነን፤ #ማንንም አንነካም፤ደፍራችሁ መጣችሁ ከነካችሁን ግን አንፋታችሁም፤ ለምን በፍፁም መሸነፍን ተፈጥሮ አትፈቅድልንም ሙሉን አሁንም ቴሌግራም ላይ ታገኙታላችሁ ሊንኩን ንኩት https
+3
#እኛ አማራዎች ነን፤ #ማንንም አንነካም፤ደፍራችሁ መጣችሁ ከነካችሁን ግን አንፋታችሁም፤ ለምን በፍፁም መሸነፍን ተፈጥሮ አትፈቅድልንም ሙሉን አሁንም ቴሌግራም ላይ ታገኙታላችሁ ሊንኩን ንኩት https://t.me/httpsuYkZrGfSZrNjNjFk ። Dave Amhara

የአስቴ ጎማ ተራራ ክፍለ ጦር ወታደራዊ ቁመናውን ተቋማዊ ሂደትን በተከተለ መልኩ ገምግሞ አሰራሮችን በማዘመን ለሚሰጡ ድርጅታዊ ተልዕኮዎች ራሱን በተሐድሶ አዘጋጀ!!           ጳጉሜ 04/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ መሐመድ ቢሆነኝ ኮር አስቴ ጎማ ተራራ ክፍለ ጦር ተቋማዊና ወታደራዊ ብቃቱን ይበልጥ የሚያጠናክርበትን የተሐድሶ መርሃ-ግብር በደማቅ ሁኔታ ማድረጉን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን አስታወቀ። በመርሃ-ግብሩ ላይ የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱና፣ የአሳምነው 5ኛ ዕዝ ሰብሳቢ አርበኛ ደሳለኝ ሲያስብሸዋ፣ የዕዙ ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ አማን እሸቱ፣ የዕዙ ፖለቲካ መምሪያ ሃላፊ ዶክተር ታደሰ ገ/ፃድቅ፣ እንዲሁም ሌሎች የዕዝ፣ የኮርና የክፍለ ጦሩ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። ጠላትን እንደ ንብ የሚነድፉት፡ አስቴ ጎማ ተራራ ክፍለ ጦር፤ ህዝቡን ከመጥፋትና ከውርደት ታድጎ ወደ ታሪካዊ የክብር ማማ ለማሸጋገር ራሱን በትግል ሜዳ ያስቀደመ አይበገሬ ጦር ሆኖ ተከስቷል። ክፍለ ጦሩ ጠላት አካባቢውን በወረረበት የ42 ቀናት ውጊያ ታላቅ የበላይነት በማሳየት፣ ፈተናዎችን በማለፍ፣ የጠላትን ኃይል በማዝረክረክ የቆየ መሆኑ ሲታወቅ፧ የቻለ በእሳት የተፈተነ ስብስብ መሆኑ ተገልጿል። በሂደት ያጋጠሙትን ውስጣዊ ክፍተቶች በመሙላት፣ በአዳዲስ አመራሮችና አደረጃጀቶች ወታደራዊ ቁመናውን በማዘመን ለቀጣይ ግዳጆች በከፍተኛ ዝግጅት ራሱን አድሷል። በመድረኩ የክብር እንግዳ ሆነው የተገኙት የአሳምነው 5ኛ ዕዝ ዋና መሪ አርበኛ ደሳለኝ ሲያስብሸዋ ባስተላለፉት መልዕክት፦" ይህ ትግል የህዝብ ትግል ነው። በዚህ ቅዱስ በሆነው ትግላችን የጀመርነውን የአማራ ህዝብ ህልውና በማረጋገጥ የኢትዮጵያን የወደፊት መፃኢ እጣፋንታ ለማስተካከል ነው" በመሆኑም ተቋማዊ አሰራርን ጠብቃችሁ በርቱ በማለት ሲቋጩ፤ የዕዙ ዋና ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ አማን እሸቱ በበኩላቸው የወታደራዊ ዝግጅቱን ደረጃ ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው፡ ሁልጊዜም የብቃት ደረጃችሁን በማሻሻል ነገም እንደወትሮው የሁልጊዜ ዝግጅትና ጥንካሬ ይኑራችሁ  ሲሉ ደምድመዋል። በመድረኩ ላይ ከክፍለ ጦሩ አባላት ለተነሱት ጥያቄዎች፦ ከአመራሩ በቂ ማብራሪያና ምላሽ ሲሰጥ፣ ለነበሩ ክፍተቶች በሙሉ በአዲሱ አሠራር እደማይደገሙ ተገልጿል። በመጨረሻም የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ ባስተላለፉት መልዕክት፦ "የአንድነታችን ውጤት በጠንካራ አላማ እድንወያይና በጋራ እንድናቅድ አድርጎናል" ዕቅዳችንንም በአንድነት እናሳካለን በሚል መልዕክት የዕለቱ መርሀ-ግብር መጠናቀቁን ኮሩ አሳውቋል። " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ)ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

#በዳውንት_ግምባር_የጁላ_አመራር‼️ ይህ በምስሉ የምታዩት በዳውንት ግምባር ወድቆ የቀረ የሻምበል ማዕረግተኛ የክፍለጦር አመራር ነው‼️ጳጉሜ 04/2018 ዓ.ም
+1
#በዳውንት_ግምባር_የጁላ_አመራር‼️ ይህ በምስሉ የምታዩት በዳውንት ግምባር ወድቆ የቀረ የሻምበል ማዕረግተኛ የክፍለጦር አመራር ነው‼️ጳጉሜ 04/2018 ዓ.ም

ከአፋብን 1ኛ ምኒልክ ዕዝ ዋና ሰብሳቢ አርበኛ ድርሳን ብርሃኔ የተላለፈ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት!! ለጀብደኛው የምኒልክ ዕዝ ሁሉም ኮሮች፣ ለመላው ሰራዊታችን እና ለምኒልክ ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች በሙሉ፣ እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ ያለን! መራራው የአማራ ህዝብ ትግል በድል እስከሚጠናቀቅ ድረስ ህዝባችን እና ድርጅታችን የጣሉብንን አደራ በቁርጠኝነት ለመወጣት ዛሬም እንደ ትላንቱ በትጋት እንታገላለን። ዕዛችን አፋብን 1ኛ ምኒልክ ዕዝ እያደረገ ያለው ተጋድሎ በታሪክና በትውልድ ሲዘከር ይኖራል። በህልውና ትግሉ ውስጥ አንጸባራቂ ድሎች እየተመዘገቡ ነው። በተለይም «ዘመቻ አደም አሊ»፣ «ዘመቻ ራንቦ» እና የአሁኑ «ዘመቻ መሐመድ ቢሆነኝ» በአማራ ተጋድሎ ዘመን ከፍተኛ ታሪካዊ ጀብዱ የፈጸምንባቸውና የጠላትን ቅስም የሰበርንባቸው አኩሪ ታሪኮቻችን ናቸው። ይህ ድል እንዲጻፍና ወታደራዊ ገድል እንዲፈጸም ላደረጋችሁ የሰራዊታችን አባሎችና በየደረጃው የምትገኙ አመራሮች ልፋታችሁ ትጋታችሁ ፍሬ አፍርቶ በማየታችሁ ልትኮሩ ይገባል። የተመዘገቡትን ወታደራዊ ድሎች ጠብቀን አዳዲስ ድሎችን እናመጣ ዘንድ በተሻለ መደማመጥና የሌት ተቀን ትጋት የሚጠይቅ በመሆኑ፣ ሁላችንም ጠላትን በመምታትና የወገን ሃይልን በማጠናከር ላይ ልናተኩር ይገባናል! «ስንከባበርና ስንደማመጥ ከባዱ ይቀላል» እንደሚባለው፤ በጶጉሜ 03 2018 ዓ.ም. በዕዛችን ልዩ ዘመቻ እና በ16ኛ ኮር (የደጋው መብረቅ) የተሰራው አንጸባራቂ ወታደራዊ ድል በጣም የሚያኮራ ነው። በተለይም በአውደ ውጊያ ያሳያችሁት አሸናፊነት፣ ወደር የሌለው ፅናትና ከፍተኛ ቁጭት ጠላትን ደምስሳችሁ ድልን የተቀዳጃችሁ የአማራ ህዝብ የቁርጥ ቀን ልጆች በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ! በውጊያው ወቅት ያሳያችሁት አስደናቂ ወታደራዊ የትግል ብቃት፣ የትዕዛዝ አፈጻጸም ጥራት እና እርስ በእርስ የመደጋገፍ የጓዳዊነት መንፈስ አንጸባራቂ ድሎችን አስመዝግቧል። በ«ዘመቻ መሐመድ ቢሆነኝ» የታወጀው ይህ ዘመቻ በርካታ ሁነቶችና ወታደራዊ ብልጫዎች የታዩበት ሲሆን፣ በተለይም የወገን ሃይልን የመፈጸም ብቃት ያረጋገጠ ነበር። በአውደ ውጊያውም ፩. የውጊያ የበላይነትን በማረጋገጥ የጠላትን ወታደራዊ ስትራቴጂ እና የመከላከል ምሽግ በጥበብና በወሳኝ ደፋር እርምጃ ሙሉ በሙሉ መደምሰስ ተችሏል! ፪.በጽናትና ቁርጠኝነት አስቸጋሪ የአየር ጠባይና የመሬት አቀማመጥን በመቋቋም የተሰጣችሁን የውጊያ ግብ በላቀ ሁኔታ ማሳካት ተችሏል! ፫.የህይወት መስዋዕትነትና ጀግንነት ለአማራ ህዝብ ህልውና፣ ለህዝብ ደህንነት እና ለክብራችን ሲባል ያሳያችሁት ወታደራዊ ወኔና ተጋድሎ ለትውልድ የሚሻገር የታሪክ ድርሳን ነው። ይህ የተመዘገበው አስደናቂ ድል ለህልውና ትግላችን የተስፋ ብርሃን፣ ለቀሪው ሰራዊት የመንፈስ ጥንካሬ፣ ለጠላት ደግሞ የቁም ቅዠት ሆኗል። ድርጅታችን አፋብን እና የአማራ ህዝብ በጀግንነታችሁ፣ በዲሲፕሊናችሁና በከፈላችሁት መስዋዕትነት ላቅ ያለ ኩራትና ክብር አለው። የጀግንነት ገድላችሁ በወታደራዊ ታሪካችን ውስጥ በወርቅ ቀለም ተጽፎ ይኖራል! ክብርና ሞገስ በአውደ ውጊያ ታሪክ ለሰሩት ጀግኖቹ አሃዶቻችን! ፊት አውራሪ ድርሳን ብርሃኔ የአፋብን 1ኛ ምኒልክ ዕዝ ዋና ሰብሳቢ