ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
前往频道在 Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
显示更多2 904
订阅者
+10524 小时
+3357 天
+33630 天
帖子存档
እንኳን ለ2019 አዲስ ዓመት በሰላም፣ በጤና እና በህይወት አደረሳችሁ!!
ውድና የተከበራችሁ የፍኖተ አማራ ሚዲያ ቤተሰቦች፣ የጽናት አርማ የሆናችሁ ተከታታዮቻችን እና መላው የአማራ ህዝብ፤
ከፈተናዎች ማዕበል፣ ከመከራው እሳት እና ከጽናቱ መንገድ ተገናኝተን እንኳን ለ2019 አዲስ ዓመት በሰላም፣ በጤና እና በህይወት አደረሳችሁ! ይህ አመት የብርሃን፣ የጽናት እና የድል ዘመን ይሁንላችሁ ይሁንልን!
ያለፈው ስምንት ዓመታት ህዝባችን በአቢይ አሕመድ አረመኔያዊ ሥርዓት የሚፈጸምበትን ግፍ፣ ጭፍጨፋ እና መከራ በጽናት የታገለበት እየታገልንበት ያል የደምና የእንባ ዘመን ሆኖ የተመዘገበ መሆኑ አለም ህዝብ ጥቁሩም ነጩም የሚያዉቀዉ ሃቅ ነዉ። ሆኖም በእዚያ ሁሉ የሥርዓቱ የጨካኝነትና የግፍ ማዕበል ውስጥ የአማራ ህዝብ በግፍ እየተገደለም ቤሆን በአብይ አህመድ ስርዓት አልተንበረከከም! የአማራ ልጅ ፋኖ እምቢተኝነትና የብረት ጽናት፣ የትኛውም አረመኔያዊ ኃይል የህዝባችንን ክብርና ህልውና ማንበርከክ እንደማይችል ለአለም አሳይተዋል እሰከ ነፃነትም ይህ የአባቶቻችን ጀግንነት ተላብሶ ትግላችን ይቀጥላል።
ይህ አዲሱ 2019 ዓመት፦ የህልውና እና የሉዓላዊነት ዘመን የአብይ አህመድ አረመኔያዊ ስርዓት በህዝባችን ላይ የጫነው የወረራና የግፍ ወይን አብቅቶ፣ የወደቀው ክብራችን የሚመለስበትና ህልውናችን የሚረጋገጥበት፤የአማራ ልጅ ፋኖ ፍትሃዊ ትግል ፍፃሜ ለዉዱ ህዝባችን ነፃ የሚያወጣበት ነው።
አረመኔውን የአብይ አህመድ ሥርዓት ለመመከት በየበረሃውና በየተራራው የሚፋለመው የአማራ ልጅ ፋኖ መስዋዕትነት ፍሬ አፍርቶ ታሪካዊውን የድል ማክተሚያ የሚያበስርበት፤የፍትህና የመልሶ ማቋቋም ዘመን፦ በስርዓቱ የግፍ ፖሊሲ ምክንያት በየካምፑ የሚሰቃዩ ወገኖቻችን በክብር ወደ ቀያቸው የሚመለሱበት እና ንጹሃን ከእስር ነፃ የሚወጡበት፤ የብርሃንና የእውነት መድረክ እነደሚሆን አንጠራጠርም ሚዲያችን «ፍኖተ አማራ» የአረመኔውን ስርዓት በደልና ጭካኔ በማጋለጥ፣ የህዝባችንን እውነተኛ ድምፅ በማስተጋባት እና የድሉን የምስራች በኩራት የሚያበስርበት፤እንዲሆንልን በፍኖተ አማራ ሚዲያ ስም ከልብ እንመኛለን!
ጨለማው ይገፈፋል፤ የአረመኔዎች ስርዓት ያበቃል፤ የታገለው ህዝባችን በእርግጥ ያሸንፋል! ፍኖተ አማራ ሚዲያ (Finote Amhara Media) ቴሌግራም / ሶሻል ሚዲያ፦https://t.me/httpsuYkZrGfSZrNjNjFk
ከከበር ሰላምታ ጋር
Finote Amhara Media
መልካም አዲስ ዓመት 2019
የአፄ ዓምደ ጽዮን ኮር በሸዋ ጠቅላይ ግዛት የፈፀመው ተጋድሎ፤ጠላት ከፍተኛ ሰብዓዊና ወታደራዊ ኪሳራ አስተናገደ!!
ጳጉሜ 05/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው 5ኛ ዕዝ፣ አፄ ዓምደ ጽዮን ኮር ከተጉለትና ቡልጋ እስከ መርሀቤቴ አውራጃዎች ባደረጉት ቆራጥ ተጋድሎ፣ የጠላትን ወራሪ ኃይል በመደምሰስ ከፍተኛ ወታደራዊና ሰብዓዊ ኪሳራ ማድረሳቸውን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን አስታወቀ።
ጠላት በሁለት ታላላቅ ግንባሮች ማለትም በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ ሳሲት ክላስተር እንዲሁም በመርሀቤቴ አውራጃ ሚዳና ሬማ ክላስተር ለዘረፋ ተግባር የተንቀሳቀሰው የአገዛዙ 112ኛ እና 101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር እንዲሁም 105ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር ከአርበኞች ጦር ሰራዊት ጋር በተደረገ የተቀናጀ ውጊያ ከባድ ኪሳራ ማስተናገዱ ተገለፀ።
በሳሲት እና በመርሀቤቴ ግንባሮች የተመዘገቡ ድሎች ከጳጉሜ 03/2018 ዓ.ም ጀምሮ በሳሲት ቀጠና በተደረገው ውጊያ፤ የንጉስ ሣህለ ሥላሴ ክፍለ ጦር ልዩ ቦታው ብርቃ በተባለ ስፍራ በፈጸሙት የጨበጣ ውጊያ በ112ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲያደርሱ፤ በተመሳሳይ ሳሲት ክላስተር የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በተቀናጀ ውጊያ ይሕንኑ መፈፀማቸው ተገልጿል።
በሌላኛው ግንባር ትላንት ከጳጉሜ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ በመርሀቤቴ አውራጃ ሚዳና ሬማ ክላስተር በተካሄደው ተጋድሎ፣ አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በሬማ ከተማ ዘልቀው በመግባት የ101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር አመራርን አስደናቂ እርምጃ መውሰዳቸው ተገለፀ።
እንዲሁም በአዝማና ይጎቢያ ቀበሌ በተደረገው ውጊያ ከ12 በላይ የሚሆኑ የዘራፊ ቡድኑ አባላት ሲደመሰሱ፣ በቀጠናው በተካሄደው እልህ አስጨራሽ ውጊያ የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ሻለቆች፣ የኮሉ ብርጌድና የካራምሽግ ብርጌድ አርበኞች በትብብር ወራሪውን ኃይል መምታታቸው ተረጋግጧል።
የሀገር መከላከያ ሰራዊት ነኝ ብሎ፡ አጥፊና ዘራፊ ቡድን ከሳሲት ክላስተር ከ8 በላይ የአርሶ አደሮችን በሬዎችን በመዝረፍ፣ በጥቅሉ ከ15 በላይ ኩንታል ጤፍና ስንዴ እህል በአስገዳጅ መዋጮ መዝረፉ ሲገለፅ፣ በተመሳሳይ በሚዳና ሬማ ክላስተርም መጠነ ሰፊ የዝርፊያ ወንጀል መፈጸሙን የኮሩ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ክፍል አስታውቋል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
+4
የብልፅግናው ጦር እየፈረሰ ፋኖን እየተቀላቀለ ይገኛል!
የምኒልክ ዕዝን መብረቃዊ ምት መቋቋም ያቃተው የአገዛዙ ጦር ከመዋጋት ይልቅስ በሰላም እጅ መስጠትን እየመረጠ ይገኛል። በሰሜን ወሎ ዞን ደጋማ አካባቢዎች የወረዳ ከተማዎች ላይ ብቻ ተወሽቆ የሚገኘው የስርዓቱ ቀለብተኛ ወታደር የ16ኛ ኮርን ምትሃታዊ ገድል ምት መቋቋም አልቻለም።
በዚህም በዛሬው እለት አንድ ዘመናዊ የሞርተር መነፀርን ጨምሮ ጥቁር ክላሽን በመያዝ 16ኛ ኮር 163ኛ ክፍለጦርን ተቀላቅሏል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ 16ኛ ኮር ቃል አቀባይ
ጷግሜ፦ 05/ 2018 ዓ/ም
የአባት አርበኞች ጦር አደረጃጀቱን በማዘመን "ምኒልክ አርበኞች ክፍለ ጦር" በሚል ስያሜ በተጉለት በይፋ መመስረቱ ተገለፀ!!
ጳጉሜ 05/2018 ዓ.ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ተጉለት አውራጃ ሲንቀሳቀስ የቆየው የአባት አርበኞች ጦር አደረጃጀቱን በማዘመንና በማጠናከር "ምኒልክ ክፍለ ጦር" በሚል ስያሜ በይፋ መመስረቱ የተጉለት ቀጠና ስምሪት ቡድን አስታወቀ።
ክፍለ ጦሩ ይፋ በተደረገበት በዚህ መድረክ ላይ የዕዝ፣ የኮር እንዲሁም የክፍለ ጦር አመራሮች በተገኙበት ሲመሠረት፤ አደረጃጀትን በማዘመን እና የድርጅቱን የፖለቲካ ትጥቅ ትግሉን በማስረፅ አባት አርበኞቹ ለአካባቢው ሠላምና ደሕንነት እዲያረጋግጡ ታልሞ መዋቀሩ ተገለፀ።
በውይይቱ ወቅት አመራሮቹ እንዳመለከቱት፤ የአማራ ህዝብ የገጠመውን የህልውና አደጋ ለመመከትና ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት የአደጋውን ዘርፈ-ብዙነት መረዳት ተገቢ በመሆኑ፣ ለዚህም ዕድሜው ለትግል የደረሰ የህብረተሰብ ክፍል በሙሉ ባለው አቅም መታገል እንደሚኖርበትና፣ ትግሉም በዋናነት ቀጥተኛ ጥቃት እያደረሰ ባለው አገዛዝ ላይ ብቻ መነጣጠር እንዳለበት አስምረውበታል።
በሌላ በኩል አርበኞቹ በሰጡት አስተያየት፤ አሁን ያለው አገዛዝ በይፋ እድጠፋና ባወጀበት፣ ንብረታችን እዲወድም በዘመተበት፣ በስልታዊ መንገድ ወጣቱ በጦርነት እዲማገድ፣በጥቅም ማባበያ ሚሊሻና አድማብተና እያለ ትውልዱን እያመከነ በመሆኑ፤ ይሕንን የህልውና አደጋ ለመመከት ብቸኛውና የመጨረሻው አማራጫችን በተባበረ ክንድ አገዛዙን ማስወገድ ነው ሲሉ አቋማቸውን አስቀምጠዋል።
ሆኖም በርካታ ጀግኖችን አቅፎ በአባት አርበኞች አደረጃጀት ሲታገል የቆየው የተጉለት አውራጃ ጦር፣ የታጋዮቹን ፍላጎት መነሻ በማድረግና የትግሉን ህልውና ለማስቀጠል ሲባል አደረጃጀቱን ማዘመን አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ "ምኒልክ አርበኞች ክፍለ ጦር" በሚል ስያሜ መመስረቱን አስታውቀዋል።
አደረጃጀቱ በማደጉ የተደሰቱት የምኒልክ አርበኞች ክፍለ ጦር አባላት በበኩላቸው፤ የተካሄደው የምክክር መድረክ በትግል ሂደቱ ላይ የነበሩ ብዢታዎችን ያጠራ መሆኑን ገልጸው፣ እንደ ቀደምት አባቶቻችን በመታገል የሸዋ ምድር የድል መቋጫ እንድትሆን የድርሻችንን ለማበርከት ዝግጁ ነን ሲሉ አረጋግጠዋል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
#ለአብይ #አህመድ እና #ለምስኪን #እናታቸው ሼር እያደረጋችሁ ከምርኮኞቹ በከፊል ጀባ ተብላችኋል! ቴሌግራም ሊንካችን ይወዳጁት!!https://t.me/httpsuYkZrGfSZrNjNjFk
የምኒልክ 1ኛ ዕዝ በዋድላ ደላንታ ዳዉንት ግንባር በተደረገው ከባድ ዉጊያ የጠላትን አንድ ክፍለጦር በመደምሰስ በርካታ የአገዛዙን ሰራዊት እና መሳሪያዎችን መማረኩ ይታወቃል።
ከተገኙ የመሳሪያ ምርኮዎች መካከል በከፊል የምስል ማስረጃዎችን አቅርበናል!
ነገ ሙሉ የሰዉ እና ተጨማሪ የቁስ ምርኮ ምስሎችን እናጋራለን!
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!!
ጷግሜ:-04/ 2018 ዓ/ም
የማንነት ሰንደቅ የሚኒልክ ትንፋሽ፦ አርበኛው እንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሽዋ ፅናት!!
የዳግማዊ አፄ ሚኒልክ መናገሻ፣ የሀገር ሉዓላዊነትና የጀግንነት እምብርት የሆነችው ታሪካዊቷ የሸዋ ምድር፤ ዛሬም እንደ ትላንቱ የነፃነት ቀንበጦችና የቁርጥ ቀን ልጆች መፍለቂያ መሆኗን በተግባር እያስመሰከረች ትገኛለች። ታሪክና ሰንበር አድረገው በሳሏት፣ ፅናትና ክብር በታደለችው የሸዋ መንዝ እምብርት ውስጥ፣ የአማራን ሕዝብ ታሪካዊ ክብርና የማንነት ህልውና ለማስጠበቅ የተነሳው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምየው ዕዝ ዋና ሰብሳቢ አርበኛ ደሳለኝ፤ የዚህ ዘመን የፋኖ እምቢተኝነት ሕያው ማህተም ሆኗል። ዛሬ በዱር በገደሉ፣ በጋራና በሸለቆው የሚሰማው የፋኖ የነፃነት ክንድ እና የምድር አንበሶች ተጋድሎ፤ የእነ አርበኛ እንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሽዋ የመርህ ፅናትና የስትራቴጂ ውጤት ነው።
እናም እውነታው ግን ግልጽ ነው ለጊዜያዊ ሥልጣን ፍርፋሪና ለከርሳቸው ጥቅማጥቅም ሲሉ የሕዝባቸውን ሰላምና ክብር አሳልፈው የሰጡ፣ የጥፋትን አጀንዳ ተሸክመው የሚኳትኑ “ጥቁር ሆድ አደሮች” ይህንን አርበኛና እርሱ የሚመራውን የአማራ ልጅ ፋኖ እጅጉን አብዝተው ይጠሉታል።የፋኖ አይበገሬነቱን ያሳየው ይህ የአማራ ልጅ ጀግና በአማራ ህዝብ ላይ ክህደት፣ ባንዳነትና ሆድ አደርነት የፈፀሙትን የብልፅግና አሽከሮች የብአዴን ቅጠረኞች በየቀኑ የእግር እሳት ሆኖባቸዋልና! ነገር ግን ለማንነታቸውና ለታሪካቸው የሚቆረቆሩ እውነተኛ የአማራ ልጆች፣ የፋኖን የነፃነት ክንድና የአርበኛ ደሳለኝን አመራር አብዝተው በሚሳሱላቸው፣ በፍቅርና በኩራት በሞሉ ዓይኖቻቸው ይመለከቱታል። በደማቸውና በህይወታቸውም ይደግፉታል። ምክንያቱም ይህ ንቅናቄ የአማራ የቁርጥ ቀን ደራሽ፣ የሚኒልክ የታሪክ ትንፋሽና ከምንም ዓይነት ምድራዊ ሥልጣንና ማዕረግ ይልቅ “አማርነትን፣ ነፃነትንና የሕዝብን ክብር” ያስቀደመ የቁርጥ ቀን ታጋይ ኃይል ስለሆነ።
ለጥላቶቹና ለባንዳዎች የሚገርመውና የሚያስደነግጠው እውነታ ግን ይህ ነው፤ አርበኛ ደሳለኝንና እርሱ የሚመራውን የፋኖን ስም አፍ አውጥቶ መሳደብና መዳፈር ቀርቶ፣ በሃሳብ እንኳ ነክቶ ማማት የማይታሰብ መሆኑ ነው። የፋኖ ፅናትና የአርበኛው መሪ ጥበብ የሸዋ ምድር ዛሬም እንዳልመከነች ሕያው ምስክር ነው። የዚህ ትልቁ ማረጋገጫ ደግሞ ጠላቶቹ ሊያጠፉትና ሊያሸብሩት ቢመኙም አርበኛ እንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሽዋ ዛሬም በሕይወትና በጤና በመስዋዕትነት ሜዳው ላይ በጽናት መቆሙ ነው! ዛሬም በዕድሜውና በጉልበቱ ሳይበገር የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝን ከፊት ሆኖ በመምራት ላይ ይገኛል። በቅርቡ በጦር ግንባሮች በተመዘገበው አስደናቂ የጀግንነት ውሎ፣ የአርበኛ ደሳለኝ ሲያስብ ሽዋ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መሪዎችና የአሳምነው አናብስት ፋኖ በጠላት ምሽግ ላይ እንደ መብረቅ ተከስተው፣ የክህደትን ኃይል የነቀሉበትና ታሪክ ያደነቀው ወታደራዊ ድል አስመዝግበዋል።
አርበኛ እንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሽዋ በቁርጥ ቀን ልጆቹ ጋር በመሆን፣ ወደ ሽዋ ምድር የዘመተውንና ንፁሃንን የሚጨፈጭፈውን የአብይ አህመድን ወራሪና አራዊት ሰራዊት እግር በእግር እየተከታተለ ድባቅ እየመታው ይገኛል። በነዛ አስፈሪ ጋራዎች ላይ የተሰማው የፋኖ ቀረርቶና ፉከራ፣ የጠላትን አጥር ሰብሮ የገባው አንበሳዊ ተወርዋሪነት፣ የሸዋን ምድር ወደማይደፈር የነፃነት አምባነት ቀይሮታል። ይህ የጦር ሜዳ ጀግንነት፣ የጠመንጃቸው ኃይልና የፅናት ማዕበል የማንነታችን ሰንደቅ ዓላማ በጀግኖቻችን ትከሻ ላይ ከፍ ብሎ ለዘላለም እንደሚወለብል ማረጋገጫ ነው። የፋኖ ጀግንነትና የአርበኛው ደሳለኝ ገድል የትውልዳችን የነፃነት አዋጅ ነው ታሪክ በደማቅ ቀለም እየፃፈ፣ ጠላት በሽብር የሚረበሽበት፣ ወዳጅ በኩራት አንገቱን የሚያቀናበት የዘመናችን እውነተኛው የድል ታሪክ እየሰራ ይገኛል።
የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዋና ሰብሳቢ አርበኛ እንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሽዋ ፈጣሪ እንዲጠብቅህ እመኛለሁ። #Dave #Amhara
የአማራ ልጅ ፋኖ የጀግንነት የፅናት ተምሳሌት!!
በነፃነት የመኖር ማንነቱና የታሪክ አደራው የተቀበለው የአማራ ልጅ ፋኖ ማለት የጥንካሬ፣ የኩራትና የታሪክ ምስክር ነው። ከቀደሙት አባቶች የተረከበውን የነፃነትና የክብር አደራ አንግቦ፣ የነገውን ብሩህ ተስፋ ለመቅረጽ የሚተጋ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው። ስሙ የነፃነት ጥሪ፣ መገኘቱ ደግሞ የፍትህና የጽናት ጋሻ የሚገርመው የጀግንነት መገለጫ በፈተናዎች ውስጥ የማይናወጥ፣ በግርማ ሞገሱ ፈተናዎችን የሚያስደነግጥ ኃይል አለው።
እንደ አለት የጠነከረ ጽናት ማዕበልና አውሎ ንፋስ የማይበግረው፣ ለእውነትና ለወገኑ እምነት የቆመ የቁርጥ ቀን ጀግና። የማይፈራ ልብ ለማንነቱና ለህዝቡ ክብር ሲል ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ወደኋላ የማይል።የኩራት መገለጫ በአካሄዱ ግርማ ሞገስ፣ በንግግሩ ደግሞ እምነትና ተስፋ የሚታይበት እውነተኛ የክብር ምልክት። የሚያስደምመው ታላቅ ዓላማ የፋኖ ዓላማ ግልጽና መሠረተ-ጽኑ ነው፤ እሱም ፍትህ፣ እኩልነት፣ ማንነትና ዘላቂ ሰላም ማስፈን ነው። ዓላማችን የግፍ ቀንበርን ሰብሮ፣ በእኩልነትና በነፃነት የሚኖሩ፣ በአለማችን የተከበሩ ማህበረሰብ መገንባት ነው። ይህ ጉዞ ለራስ ብቻ ሳይሆን፣ ለትውልድ የሚተርፍ የፍትህና የክብር አሻራ ለመተው የሚደረግ የታሪክ ጉዞ ነው። የአማራ ልጅ ፋኖ የትላንት ታሪክ ኩራት፣ የዛሬ የጽናት መሠረት፣ የነገ የሰላምና የነፃነት ዋስትና የሆነው የአማራ ልጅ ፋኖ ብቻ ነው!!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው እዝ ወታደራዊ እቅድና እስትራቴጂ ዋና መምሪያ መቶ አለቃ ልመነው ሻወል ደመቀ
የቴሌግራም ሊንካችን ሸርና ጆይን በማድረግ ይወዳጁን፦
https://t.me/httpsuYkZrGfSZrNjNjFk
እኛን የሚገልፀን አንድ ታላቅና የማይናወጥ እውነት አለ...
እኛ የዚች ታሪካዊት ምድር ኩሩ የአማራ ልጆች ነን! በራሳችን ሰማይ ስር በፍቅር፣ በክብርና በሰላም መኖርን እንጂ፣ የሰውን ክፉ መመኘትም ሆነ የሌላውን ድንበር መድፈር በተፈጥሯችን የለም። ተፈጥሮ በውበት፣ በንጽሕናና በጽናት የሰራችን የእውነት ሕያው እንቁዎች ነን!
ክብራችንን የሚነካ፣ ማንነታችንን የሚደፍርና ሰላማችንን የሚያደፈርስ ማንኛውም እጅ ሲመጣ በጭራሽ አንታገስም! የፍቅራችንን ያህል ቁጣችን ታላቅ፣ የትዕግስታችንን ያህል እሳታችን የበረታ ነው!
በታሪካችን ታይቶ በሚታወቅ ዳግማዊ ድልና የበላይነት እንጂ፣ በሽንፈት የሚባል ጥቁር ጥላ ማንነታችን ላይ እንዲያርፍ አንፈቅድም።
ማንነታችን ንጹሕና የወርቅ ያህል የጠራ ነው፤ ጽናታችን ደግሞ ተራራ የሚያናውጥ፣ ከድንጋይ የጠነከረ ነው! የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላት #Dave #Amhara
