ch
Feedback
Tabor Bible Study (ሐዋሳ ታቦር መካነ ኢየሱስ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት)

Tabor Bible Study (ሐዋሳ ታቦር መካነ ኢየሱስ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት)

前往频道在 Telegram

ሐዋሳ ታቦር መካነ ኢየሱስ ማህበረ ምዕመናን መጽሐፍ ቅዱስ የሚጠናበት የቴሌግራም ቻናል

显示更多
1 083
订阅者
+124 小时
+187 天
+4330 天

数据加载中...

相似频道
无数据
有任何问题?请刷新页面或联系我们的客服
标签云
无数据
有任何问题?请刷新页面或联系我们的客服
进出提及
---
---
---
---
---
---
吸引订阅者
九月 '26
九月 '26
+11
在1个频道中
八月 '26
+58
在1个频道中
Get PRO
七月 '26
+37
在1个频道中
Get PRO
六月 '26
+54
在1个频道中
Get PRO
五月 '26
+85
在2个频道中
Get PRO
四月 '26
+65
在1个频道中
Get PRO
三月 '26
+79
在1个频道中
Get PRO
二月 '26
+26
在2个频道中
Get PRO
一月 '26
+68
在1个频道中
Get PRO
十二月 '25
+50
在2个频道中
Get PRO
十一月 '25
+26
在2个频道中
Get PRO
十月 '25
+85
在3个频道中
Get PRO
九月 '25
+71
在1个频道中
Get PRO
八月 '25
+44
在2个频道中
Get PRO
七月 '25
+72
在4个频道中
Get PRO
六月 '25
+122
在2个频道中
Get PRO
五月 '25
+245
在2个频道中
Get PRO
四月 '250
在2个频道中
Get PRO
三月 '25
+91
在2个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
04 九月+1
03 九月+1
02 九月+2
01 九月+7
频道帖子
.    ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨               የዕለቱ ጥቅስ       ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ “እናንተ ግን፦ መምህር ተብላችሁ አትጠሩ፤ መምህራችሁ አንድ ስለ ሆነ እናንተም ሁላችሁ ወንድማማች ናችሁ።” ማቴዎስ 23፥8 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_29 የዕለቱ ንባብ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study

2
#ያልተለወጠው_የኦግስቡርግ_የሃይማኖት_መግለጫ ያልተለወጠው የኦግስቡርግ የሃይማኖት መግለጫ                 ክፍል-25 እንደ ገናም፣ የወጎቹ መሥራቾች ኃጢአትን ከምግብ፣ ከቀናትና ከመሳሰሉ ነገሮች ጋር በማያያዛቸውና በቤተ ክርስቲያን ላይ የሕግ እስራትን በመጫናቸው ጽድቅን ለማግኘት እነዚህን ማቋቋም በዘሌዋውያን እንደሚታዩት ያሉ የአምልኮ ተግባራት በክርስቲያኖች መካከል ሊኖሩ ይገባ ይመስል፣ ደግሞም እግዚአብሔር እነዚህን እንዲያቋቁሙ ሐዋርያትንና ጳጳሳትን ያዘዘ ይመስል፣ ይህን ሲያደርጉ ከእግዚአብሔር ትእዛዝ ጋር በተቃረነ መልኩ መንቀሳቀሳቸው ነው፡፡ ምክንያቱም አንዳንዶች በዚህ መንገድ ጽፈዋል ጳጳሳቱም በሙሴ ሕግ ምሳሌነት በተወሰነ ደረጃ የተታለሉ ይመስላሉ፡፡ ከዚህም የሚከተሉት ሽክሞች ተፈጠሩ፡- ሌሎችን ባያስቀይምም እንኳ በበዓላት ቀኖች የጉልበት ሥራ መሥራት ሞት የሚገባው ኃጢአት እንደ ሆነ፣ አንዳንድ ምግቦች ሕሊናን የሚያረክሱ እንደ ሆኑ፣ ጾም ተፈጥሮአዊ ባልሆነ ዳሩ ግን አካላዊ ሥቃይን በሚያስከትልበት ጊዜ እግዚአብሔርን የሚያስደስት ሥራ እንደ ሆነ፣ ቀኖናዊ ሰዓታትን ማስተጓጐል ሞት የሚገባው ኃጢአት እንደ ሆነ፣ ምንም እንኳ ቀኖናዎቹ ራሳቸው የሚናገሩት በደልን ስለ መያዝ ሳይሆን የቤተ ክርስቲያንን ቅጣቶች ስለ መያዝ ቢሆንም፣ ጒዳዩን ከያዘው ሰው ፈቃድ ውጭ በተያዘ ጒዳይ ላይ ኃጢአትን ይቅር ለማለት አይቻልም የሚሉት ናቸው፡፡ ጳጳሳት ሕሊናን ለማጥመድ እንደዚህ ያሉትን ወጎች በቤተ ክርስቲያን ላይ የመጫንን መብት ከወዴት አገኙ? ጴጥሮስ በደቀ መዛሙርት ላይ ቀንበር መጫንን የከለከለበት ሐቅ እያለ፣ እንዲሁም ጳውሎስ ለማፍረስ ያይደለ ነገር ግን ለማነጽ ሥልጣን የተሰጣቸው መሆኑን እየተናገረ፣ እነርሱ በእንደዚህ ያሉ ወጎች አማካይነት ኃጢአትን የሚጨምሩት ለምንድን ነው? የሆነ ሆኖ፤ የእግዚአብሔርን ቊጣ ለማብረድ ወይም ለድነት አስፈላጊ እንደ ሆኑ አድርጎ ወጎችን መመሥረትን የሚከለክሉ ግልጽ የሆኑ ምስክሮች አሉ፡፡ ጳውሎስ በቈላስይስ 2[፡16፣20-23]፦ «እንግዲህ በመብል ወይም በመጠጥ ወይም ስለ በዓል ወይም ስለ ወር መባቻ ወይም ስለ ሰንበት ማንም አይፍረድባችሁ»፤ ደግሞም «ከዓለማዊ ከመጀመሪያ ትምህርት ርቃችሁ ከክርስቶስ ጋር ከሞታችሁ እንደ ሰው ሥርዓትና ትምህርት አትያዝ አትቅመስ፣ አትንካ ለሚሉት ትእዛዛት በዓለም እንደምትኖሩ ስለ ምን ትገዛላችሁ? እነዚህ ሁሉ በመደረግ ሊጠፉ ተወስነዋልና፤ ይህ እንደ ገዛ ፈቃድህ በማምለክና በትሕትና ሥጋንም በመጨቈን ጥበብ ያለው ይመስላል» ይላል፡፡ ቲቶ 1[፡14]፦ «ስለዚህ ምክንያት የአይሁድን ተረትና ከእውነት ፈቀቅ የሚሉትን ሰዎች ትእዛዝ ሳያዳምጡ ...» ይላል፡፡ ክርስቶስ በማቴዎስ 15[፡14] ወጎችን ስለሚፈልጉ ሰዎች፡- «ተዉአቸው፤ ዕውሮችን የሚመሩ ዕውሮች ናቸው» ይላል፡፡ ደግሞም «የሰማዩ አባቴ ያልተከለው ተክል ሁሉ ይነቀላል» [ማቴዎስ 15፡13] በማለት እንዲህ ያሉትን የአምልኮ ተግባራት ይቃወማል፡፡ ጳጳሳት ሕሊናዎችን እንደዚህ ባሉ ወጎች ለመጫን መብት ካላቸው፣ መጽሐፍ ቅዱስ ወጎች መመሥረትን እንደዚህ በተደጋጋሚ የሚከለክለው ለምንድን ነው? ለምንስ የአጋንንት ትምህርቶች ብሎ ይጠራቸዋል? መንፈስ ቅዱስስ ስለ እነርሱ ያስጠነቀቀው በከንቱ ነውን? ይቀጥላል . . . ምንጭ፦ Kolb, R., & Wengert, T. J. (Eds.). (2000). The Book of Concord: The Confessions of the Evangelical Lutheran Church. Fortress Press. ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
123
3
ርዕስ፦ የቅዱስ አውግስቲን ኑዛዜ ክፍል፦ 2 ምንጭ፦ @Reading_Life_1 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
121
4
.    ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨               የዕለቱ ጥቅስ       ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ “. . . በአንድ በደል ምክንያት ፍርድ ለኵነኔ ወደ ሰው ሁሉ እንደ መጣ፥ እንዲሁም በአንድ ጽድቅ ምክንያት ስጦታው ሕይወትን ለማጽደቅ ወደ ሰው ሁሉ መጣ።” ሮሜ 5፥18 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_28 የዕለቱ ንባብ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
158
5
ርዕስ፦ የቅዱስ አውግስቲን ኑዛዜ ክፍል፦ 1 ምንጭ፦ @Reading_Life_1 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
173
6
.    ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨               የዕለቱ ጥቅስ       ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ “ስለዚህ ምክንያት ኃጢአት በአንድ ሰው ወደ ዓለም ገባ በኃጢአትም ሞት፥ እንደዚሁም ሁሉ ኃጢአትን ስላደረጉ ሞት ለሰው ሁሉ ደረሰ፤” ሮሜ 5፥12 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_27 የዕለቱ ንባብ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
186
7
ርዕስ፦ መጽሐፍ ቅዱስን እናጥና ጸሐፊ፦ ዮሴፍ ቸርች ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
151
8
没有文字...
145
9
.    ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨               የዕለቱ ጥቅስ       ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ “በልቅሶ ወጡ እኔም በማጽናናት አመጣቸዋለሁ፤ በወንዝ ዳር በቅን መንገድ አስኬዳቸዋለሁ፥ በእርሱም አይሰናከሉም፤ እኔ ለእስራኤል አባት ነኝና፥ ኤፍሬምም በኵሬ ነውና።” ኤርምያስ 31፥9 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_26 የዕለቱ ንባብ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
199
10
#አዲስ_ዓመት #New_Year 👉ርዕስ፦ መጽሐፍ ቅዱስን በሚገባ ለመረዳት ✍ጸሐፊ፦ ቲ. ኖርተን ስቴሬት 🗣ትርጉም፦ ተክሉ መንገሻ ይህ መጽሐፍ፣ መጽሐፍ ቅዱስን በሚገባ ለመረዳት በጣም ጠቃሚ መጽሐፍ ስለሆነ በአዲስ ዓመት ቅዱሳት መጻሕፍትን በአዲስ መልኩ ለማጥናት ሁነኛ መጽሐፍ እንደሆነ አምነን እነሆ ብለናችኋል። በውስጡም የሚከተሉትን ጉዳዮች አካቷል፦ መሠረታዊ አሳቦች 👉መጽሐፍ ቅዱስን ማን ሊረዳው ይችላል? 👉ለማጥናት ትክክለኛውን መሣሪያ እንዴት መጠቀም እችላለሁ? 👉ለማጥናት እንዴት መጀመር እችላለሁ? አጠቃላይ መመሪያዎች 👉አገባቡን፣ ቃላትን፣ ሰዋሰውን እና የደራሲውን ዓላማ እንዴት ልረዳው እችላለሁ? 👉ቅድመ ሁኔታውን ማጥናት 👉ቅዱስ ቃሉን በራሱ መተርጎም ልዩ መመሪያዎች 👉ዘይቤያዊ አነጋገር፣ ተምሳሌቶች(Symbols), አምሳያዎች (Types), ምሳሌዎችና ምሳሌያዊ ገለጣዎች 👉የዕብራይስጥ ቋንቋ ፈሊጦች፣ ሥነ-ግጥም መረዳት 👉ትንቢት እና ትምህርተ-ሃይማኖት መረዳት 👉የብሉይና የአዲስ ኪዳናት ግንኙነትን መረዳት በስተመጨረሻም ያጠናነውን ለግል ጥቅም ሥራ ላይ ማዋል እንዴት እንደሚቻል የሚያብራራ ድንቅ መጽሐፍ ነው። ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
156
11
.    ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨               የዕለቱ ጥቅስ       ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ “እግዚአብሔር . . . ስለ ያዕቆብ ደስ ይበላችሁ ስለ አሕዛብም አለቆች እልል በሉ፤ አውሩ፥ አመስግኑ፦ እግዚአብሔር ሕዝቡን የእስራኤልን ቅሬታ አድኖአል በሉ።” ኤርምያስ 31፥7 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_25 የዕለቱ ንባብ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
247
12
የእለቱ የመልእክትና የወንጌል ክፍል #የመልእክት_ክፍል ኤርምያስ 31 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁷ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፦ ስለ ያዕቆብ ደስ ይበላችሁ ስለ አሕዛብም አለቆች እልል በሉ፤ አውሩ፥ አመስግኑ፦ እግዚአብሔር ሕዝቡን የእስራኤልን ቅሬታ አድኖአል በሉ። ⁸ እነሆ፥ ከሰሜን አገር አመጣቸዋለሁ፥ ከምድርም ዳርቻ እሰበስባቸዋለሁ፥ በመካከላቸውም ዕውሩና አንካሳው ያረገዘችና የወለደችም በአንድነት ታላቅ ጉባኤ ሆነው ወደዚህ ይመለሳሉ። ⁹ በልቅሶ ወጡ እኔም በማጽናናት አመጣቸዋለሁ፤ በወንዝ ዳር በቅን መንገድ አስኬዳቸዋለሁ፥ በእርሱም አይሰናከሉም፤ እኔ ለእስራኤል አባት ነኝና፥ ኤፍሬምም በኵሬ ነውና። ሮሜ 5 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹² ስለዚህ ምክንያት ኃጢአት በአንድ ሰው ወደ ዓለም ገባ በኃጢአትም ሞት፥ እንደዚሁም ሁሉ ኃጢአትን ስላደረጉ ሞት ለሰው ሁሉ ደረሰ፤ ¹³ ሕግ እስከ መጣ ድረስ ኃጢአት በዓለም ነበረና ነገር ግን ሕግ በሌለበት ጊዜ ኃጢአት አይቈጠርም፤ ¹⁴ ነገር ግን በአዳም መተላለፍ ምሳሌ ኃጢአትን ባልሠሩት ላይ እንኳ፥ ከአዳም ጀምሮ እስከ ሙሴ ድረስ ሞት ነገሠ፤ አዳም ይመጣ ዘንድ ላለው ለእርሱ አምሳሉ ነውና። ¹⁵ ነገር ግን ስጦታው እንደ በደሉ መጠን እንደዚያው አይደለም፤ በአንድ ሰው በደል ብዙዎቹ ሞተዋልና፥ ነገር ግን የእግዚአብሔር ጸጋና በአንድ ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የሆነው ስጦታ ከዚያ ይልቅ ለብዙዎች በዛ። ¹⁶ አንድ ሰውም ኃጢአትን በማድረጉ እንደ ሆነው መጠን እንደዚያው ስጦታው አይደለም፤ ፍርድ ከአንድ ሰው ለኵነኔ መጥቶአልና፥ ስጦታው ግን በብዙ በደል ለማጽደቅ መጣ። ¹⁷ በአንዱም በደል ሞት በአንዱ በኩል ከነገሠ፥ ይልቁን የጸጋን ብዛትና የጽድቅን ስጦታ ብዛት የሚቀበሉ በአንዱ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በሕይወት ይነግሣሉ። ¹⁸ እንግዲህ በአንድ በደል ምክንያት ፍርድ ለኵነኔ ወደ ሰው ሁሉ እንደ መጣ፥ እንዲሁም በአንድ ጽድቅ ምክንያት ስጦታው ሕይወትን ለማጽደቅ ወደ ሰው ሁሉ መጣ። ¹⁹ በአንዱ ሰው አለመታዘዝ ብዙዎች ኃጢአተኞች እንደ ሆኑ፥ እንዲሁ ደግሞ በአንዱ መታዘዝ ብዙዎች ጻድቃን ይሆናሉ። ²⁰-²¹ በደልም እንዲበዛ ሕግ ጭምር ገባ፤ ዳሩ ግን ኃጢአት በበዛበት፥ ኃጢአት በሞት እንደ ነገሠ፥ እንዲሁ ደግሞ ጸጋ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የተነሣ በጽድቅ ምክንያት ለዘላለም ሕይወት ይነግሥ ዘንድ፥ ጸጋ ከመጠን ይልቅ በለጠ። #የወንጌል_ክፍል ማቴዎስ 23 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ለሕዝቡና ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ ብሎ ነገራቸው፦ ² ጻፎችና ፈሪሳውያን በሙሴ ወንበር ተቀምጠዋል። ³ ስለዚህ ያዘዙአችሁን ሁሉ አድርጉ ጠብቁትም፥ ነገር ግን እየተናገሩ አያደርጉትምና እንደ ሥራቸው አታድርጉ። ⁴ ከባድና አስቸጋሪ ሸክም ተብትበው በሰው ትከሻ ይጭናሉ፥ እነርሱ ግን በጣታቸው ስንኳ ሊነኩት አይወዱም። ⁵ ለሰውም እንዲታዩ ሥራቸውን ሁሉ ያደርጋሉ፤ ስለዚህ አሽንክታባቸውን ያሰፋሉ ዘርፉንም ያስረዝማሉ፥ ⁶ በምሳም የከበሬታ ስፍራ፥ በምኵራብም የከበሬታ ወንበር፥ ⁷ በገበያም ሰላምታና፦ መምህር ሆይ መምህር ሆይ ተብለው እንዲጠሩ ይወዳሉ። ⁸ እናንተ ግን፦ መምህር ተብላችሁ አትጠሩ፤ መምህራችሁ አንድ ስለ ሆነ እናንተም ሁላችሁ ወንድማማች ናችሁ። ⁹ አባታችሁ አንዱ እርሱም የሰማዩ ነውና በምድር ላይ ማንንም፦ አባት ብላችሁ አትጥሩ። ¹⁰ ሊቃችሁ አንድ እርሱም ክርስቶስ ነውና፦ ሊቃውንት ተብላችሁ አትጠሩ። ¹¹ ከእናንተም የሚበልጠው አገልጋያችሁ ይሆናል። ¹² ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳል፥ ራሱንም የሚያዋርድ ሁሉ ከፍ ይላል። ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
248
13
ከሥላሴ በኋላ 10ኛ እሑድ እውነተኛና ሐሰተኛ ጽድቅ 👉ኤር. 31፥7-9 👉ሮሜ 5፥12-21 👉ማቴ. 23፥1-12 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀ
ከሥላሴ በኋላ 10ኛ እሑድ እውነተኛና ሐሰተኛ ጽድቅ 👉ኤር. 31፥7-9 👉ሮሜ 5፥12-21 👉ማቴ. 23፥1-12 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_24 የዕለቱ ንባብ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
253
14
https://www.youtube.com/watch?v=CV7uNeLZU9k&list=RDCV7uNeLZU9k&start_radio=1
233
15
.    ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨               የዕለቱ ጥቅስ       ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ “እንዲህም አለ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ ነቢይ በገዛ አገሩ ከቶ አይወደድም።” ሉቃስ 4፥24 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_23 የዕለቱ ንባብ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
272
16
ነገረ ፍጻሜ (Eschatology)                             ክፍል-4 ድህረ ሚሊኒየማዊነት (Postmillennialism) የዚህ አስተምህሮ ማዕከላዊው ሀሳብ፣ በወንጌል ኃይል እና በመንፈስ ቅዱስ ሥራ የእግዚአብሔር መንግሥት ክርስቶስ ከመመለሱ በፊት በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ጉልህ የሆነ ድልን ያገኛል የሚል ነው። ቤተክርስቲያን ወንጌልን በታማኝነት ትሰብካለች፤ ሰዎች ወደ ክርስቶስ ዘወር እያሉ ይሄዳሉ እና የክርስቲያን መርሆዎች በማኅብረሰቡ እና ባህሎች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ያሳድራሉ። ይህ የወንጌል ወርቃማ ዘመን በተለምዶ የሺህ ዓመቱ ዘመን ይባላል። በዚህ ዘመን መጨረሻ ላይ ክርስቶስ በግልጽ እና በአካል ይመለሳል፤ ሙታንን ያስነሳል፤  ሰይጣንን እና ክፋትን ሁሉ ያሸንፋል እና ዘላለማዊውን መንግስት ማለትም አዲስ ሰማይ እና አዲስ ምድርን ያቋቁማል። በጣም አስፈላጊው ነጥብ ድህረ ሚሊኒየማዊነት ክርስቲያኖች ኢየሱስ ከመመለሱ በፊት ዓለም ሙሉ በሙሉ ፍጹም እንደምትሆን ያምናሉ ማለት አይደለም። ይልቁንም ኃጢአት እና ሞት እስከ ክርስቶስ የመጨረሻ መምጣት ድረስ ሊኖሩ የሚችሉ ሲሆን፣ እነዚህ ሁነቶች የወንጌልን አስደናቂ እና ሰፊ ድል ይጠብቃሉ። በድህረ ሚሊኒየም እምነት "ሚሊኒየም" ማለት ምን ማለት ነው? ሚሊኒየም የሚለው ቃል የመጣው ከራዕይ 20፥1-6 ሲሆን ዮሐንስ ሰይጣን የሚታሰርበትንና ቅዱሳን ከክርስቶስ ጋር የሚገዙበትን የአንድ ሺህ ዓመት ጊዜ የሚገልጽ ነው። የድህረ ሚሊኒየም እምነት ተከታዮች "ሺህ ዓመታት" የሚለው ቃል እንደሚከተለው ሊተረጎም እንደሚገባ እርስ በእርሳቸው ይከራከራሉ፦ 👉ቃል በቃል የሺህ ዓመት ጊዜ ወይም 👉ያልተለመደ የወንጌል በረከት ዘመንን የሚወክል ምሳሌያዊ/የተራዘመ የጊዜ ዘመን። ስለዚህ፣ የድህረ ሚሊኒየም እምነት የሚገለጸው እያንዳንዱ የድህረ ሚሊኒየም እምነት ተከታዮች 1,000 ቁጥር ቃል በቃል መሆኑን በማመን ሳይሆን የሁነቶች ቅደም ተከተል ነው። መሠረታዊው ቅደም ተከተል፦ አሁን ያለው የቤተክርስቲያን ዘመን → እየጨመረ የመጣ የወንጌል ስኬት → ሚሊኒየም → የክርስቶስ ሁለተኛ መምጣት → ትንሣኤ → የመጨረሻው ፍርድ → ዘላለማዊ ግዛት ይህ ክርስቶስ ከሺህ ዓመቱ በፊት የሚመለስበት የpremillennialism (ቅድመ ሚሊኒየም) አስተምህሮ ተቃራኒ ነው። ማዕከላዊው ሀሳብ፦  የክርስቶስ መንግሥት በታሪክ ድል ያደርጋል ከድህረ ሚሊኒየም እምነት ጠንካራ ባህሪያት አንዱ የወንጌልን ኃይል በተመለከተ ያለው ብሩህ አመለካከት ነው። ድህረ ሚሊኒየም አማኞች ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን ጉልህ ውጤቶችን ሳይጠብቅ አሕዛብን እንድትሰብክ እንዳላዘዛት ያምናሉ። ኢየሱስ እንዲህ ብሏል፡- “ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ። እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።"           ማቴዎስ 28፥18-20 የድህረ ሚሊኒየም መከራከሪያ ነጥብ ክርስቶስ ሁሉንም ሥልጣን እንዳለው ስለዚህ ቤተክርስቲያን ወንጌል በመጨረሻ በአሕዛብ መካከል ሰፊ ለውጥ እንደሚያመጣ መጠበቅ እንዳለባት ነው። ይህ ማለት እያንዳንዱ ግለሰብ ክርስቲያን ይሆናል ማለት አይደለም። ይልቁንም የድህረ ሚሊኒየም አማኞች ክርስትና ከጊዜ ወደ ጊዜ ተጽዕኖ እያሳደረ እና የሰው ልጅ ብዙ ክፍሎች እንደሚለወጡ ይጠብቃሉ። ይቀጥላል . . . ምንጭ፦ Gentry, K. L., Jr. (1992). He shall have dominion: A postmillennial eschatology. Institute for Christian Economics. Hodge, C. (1871–1873). Systematic theology (Vols. 1–3). Scribner, Armstrong, and Co. Hoekema, A. A. (1979). The Bible and the future. Eerdmans. ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
241
17
.    ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨               የዕለቱ ጥቅስ       ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ “እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።” ኤፌሶን 2፥10 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_22 የዕለቱ ንባብ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
295
18
📔ርዕስ፦ የወንጌላት ስምምነትና ንጽጽር 👤ጸሐፊ፦ ሮበርት ኤል ቶማስ እና ስታንሊ ኤን ጉንድሪ 📑የገጽ ብዛት፦ 303 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
302
19
.    ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨               የዕለቱ ጥቅስ       ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ “ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤” ኤፌሶን 2፥8 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_21 የዕለቱ ንባብ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
339
20
.    ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨               የዕለቱ ጥቅስ       ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ “ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥” ኤፌሶን 2፥5 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_20 የዕለቱ ንባብ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
359