Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union
Open in Telegram
This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.
Show more4 479
Subscribers
+324 hours
-27 days
+2930 days
Posts Archive
"በየትኛውም ሚዛን እለብሳለሁና አትለብሽም እኩል ሊሆን አይችልም::"- የጉንችሬዋ እህት
@MohammadamminKassaw
"መነኮሳት ሲሸፋፈኑ የቅድስና መገለጫ ተደርጎ በሚወሰድበት ሀገር ሙስሊሞች ሲሸፋፈኑ ሽብር ተደርጎ የሚወሰደው ለምንድን ነው?" - ዳርሰማ ኑሪ (የአዲስ አበባ መጅሊስ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ)
@MohammadamminKassaw
"ሒጃብ ለአጭር ጊዜ የሚቆይ የፋሽን ልብስ አይደለም::" - ዳርሰማ ኑሪ (የአዲስ አበባ መጅሊስ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ)
@MohammadamminKassaw
እስከመቼ???
በቃላት ሽንገላ
እኩል ናችሁ ብለው፥ ሕግ እያረቀቁ፣
አስከ መች ነው ኑሮ
ግዳጅ የተጋራን፥ መብት እየነጠቁ?
ሀገሩን አቤት ሲል
ከርስቱ ሲያጋራ፥ ሁሉም በርታ ካለ፣
ለምን ይሆን ታዲያ
እኔም ልጠቀም ሲል፥ ዞር በል የተባለ?
በከፈለው ግብር
ልጁን ለማስተማር፥ አሻፈረኝ ያሉ፣
በምን ስሌት ነው ግን
የ'ሱ ከሆነው ላይ፥ የሚገለገሉ?
እስከ መቼ ሀዘን?
እስከ መቼ ለቅሶ? እስከ መች ልመና?
በጋራ ሐገር ላይ
መብቴን ስጥ ተብሎ፥ ማን ይጠ'የቅና?
በመቻቻል ስሌት
አብሮ በመኖር ወግ፥ ለዘመናት ጸንታ፥ የቆመችው ሀገር፣
ልጆቿን ከገፋች
ምን ተረፋትና፥ ያልተኖረን ተረት፥ ከመደስኮር በቀር?
መፍትሔ ካልመጣ
ችግሩን የሚያደርቅ፥ ላንዴ እስከ ወዲያኛው፣
ስልት ይቀየር እንጂ
ይቀጥላል በደል፥ ደግሞ በሌላኛው።
https://t.me/EHEMSU
አብዱረሂም አህመድ በ2012 ዓ.ል ETV ላይ የተናገረው:-
"በዩኒቨርሲቲዎች ዙሪያ ያሉ መጠጥ ቤቶች እና ጫት ቤቶች እንደዚህ ተደረግን ሲሉ ሰምተን አናውቅም:: በተቃራኒው ግን ተማሪዎች ሶላት መስገድ ተከለከልን: ሒጃብ መልበስ ተከለከልን ሲሉ እንሰማለን:: መንግስት በሐይማኖት ዙሪያ ያለውን አመለካከት ሊያስተካክል ይገባል::"
@MohammadamminKassaw
BTW ዲላ ዩኒቨርሲቲ በ2006 ዓ.ል በግቢው ሲማሩ የነበሩ 46 ሙስሊም ተማሪዎችን በኒቃብ ምክንያት አባሮ ነበር::
ዛሬም ያንን ጥቁር ታሪክ ለመድገም መንገድ የጀመረ ይመስላል ••• ግን በአላህ ፈቃድ አይሳካም::
ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች!
@MohammadamminKassaw
This is a press release from Dilla university Muslim Students' Union about the Niqab ban in Dilla university!
Share it!
@MohammadamminKassaw
የፌደራል መጅሊስ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መስተዳድር ጋር ተወያይቷል:: የጋራ መግባባት ላይም ደርሰናል ብሏል::
ውጤቱን የምናይ ይሆናል::
መብት በትግል እንጅ በልመና አይገኝም!
https://t.me/EHEMSU
"ሒጃብ በዲላ ዩኒቨርሲቲ አልተከለከለም:: ኒቃብ ከሆነ ከዚህም በፊት አይፈቀድም::" ላለው የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ኤልያስ አድርሱልኝ::
የዩኒቨርሲቲው የጥበቃ ሀላፊ አቶ ተረፈ ተማሪዎችን ከበር ላይ አስቁመው ""ተማሪ ነሽ? እንደዚህ ለብሰሽ እንዴት ገባሽ? ወይንስ ከገባሽ ቡሐላ ነው የምትለብሽው? ትምህርት ቤት ሐይማኖት የለም:: ከፈለግሽ ከትምህርት ቤት ውጭ ልበሺ::" ሲል ይሰማል:: ሌላዋ ጥበቃ ደግሞ እርሱን ተከትላ "አባሩ ነው የተባልነው:: ተመለሺ!" ስትል ትሰማለች::
ስለ ክልከላው ከመጀመሪያው ጀምሮ ሙሉ መረጃ አለ:: ከፈለጉ ይላክላቸዋል:: Share አድርጉት::
@MohammadamminKassaw
Efforts by Addis Standard to contact the Dilla University administration for comment were unsuccessful.
However, in a brief statement posted on its social media page, the university denied allegations that “Muslim female students have been banned from wearing the hijab,” describing the circulating reports as false.
“We want to clarify that, both in the past and present, wearing the hijab has not been prohibited at our university,” the statement added.
The issue at Dilla University comes amid similar grievances reported in Axum town,located in the Central Zone of Tigray region, where 160 Muslim grade 12 students were excluded from registering for national exams earlier this month after refusing to remove their hijabs. Despite court rulings and directives from the Tigray Regional Education Bureau guaranteeing their right to wear religious attire, schools in Axum reportedly defied these orders.
Subsequently, thousands of Muslims protested in Mekelle on 21 January , 2025, demanding action. Sheikh Adam Abdulkadir, President of the Tigray Islamic Affairs Supreme Council, criticized authorities for failing to enforce the rulings. “Our daughters are still being denied access to education despite clear rulings and directives,” he said. AS
Addis standard
Muslim students at Dilla University allege niqab ban, forcing some to stay in Mosque for days
January 25, 2025
Addis Abeba– Forty-four female Muslim students at Dilla University have alleged that they were barred from entering the campus for wearing the niqab, a religious attire, with some reportedly staying in a mosque for over five days.
According to students interviewed by Addis Standard, wearing the niqab was allowed in previous years. However, they claimed the university recently prohibited it without prior notice, citing “security concerns.”
One student, who requested anonymity, said the ban started about a month ago but was initially not strictly enforced. “Initially, it wasn’t strictly enforced,” she said, adding, “Our ID cards used to be confiscated, but when student leaders intervened, the guards would return them to us.”
The student further noted that the issue escalated late last week. “One of our friends was returning from buying food outside the campus when she was told to remove her black mask and show her face,” she said, adding that the student was informed she “couldn’t wear a black mask while wearing a hijab.”
She also claimed that later in the afternoon, two other female students attempting to enter the campus through the university gate located near the mosque were reportedly denied entry for wearing niqabs.
“Since then, students wearing the niqab have been repeatedly told to either remove it or refrain from entering the campus,” she said, adding that despite submitting multiple written complaints to the university administration, they had not received any response.
Another student, who also requested anonymity, alleged that the university has ignored their formal complaints. “Our complaint letter has been dismissed under the pretext of ‘we’ll respond soon,’ but no resolution has been provided,” she told Addis Standard.
She explained that the situation intensified on Monday, 20 January, 2025, when “the chairperson of the Muslim Students’ Association was summoned and informed that anyone wearing a black mask or niqab would not be allowed to move freely within the campus or leave and return.” She added that students were warned, “Those who disobey this directive would face action.”
The student further alleged that on Monday evening, “students wearing black masks were allowed entry after receiving warnings. However, seven of us who wear the niqab were denied entry and have been staying in the mosque for over five days.”
Nuredin Abdela, Chairperson of the Muslim Students’ Association at Dilla University, confirmed to Addis Standard that repeated efforts to resolve the matter with university officials, both in writing and in person, had not produced solutions.
“Many Muslim students have been staying in the mosque for the past five days. During this time, they have not been able to sit for exams or complete assignments required of them,” he said. He also alleged that students wearing black masks who attempted to enter the campus faced intimidation from security personnel.
The Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council, in a letter dated 23 January, 2025, addressed to the Ministry of Education, called for a permanent resolution to what it described as the “violation of Muslim students’ rights at all educational levels, solely due to their Islamic attire.”
The council said it had been engaged in discussions to address the exclusion of Muslim female students due to their attire. It also reminded the Ministry that it had sent three letters this month alone concerning the issue but stated that no adequate response had been received.
The council emphasized the need for an immediate and lasting resolution to allow Muslim female students at Dilla University to resume their studies without obstruction.
+1
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በወቅታዊ ጉዳዮች መግለጫ አውጥቷል:: በመግለጫውም የዩኒቨርሲቲው ህዝብ ግንኙነት በፌስቡክ ገፁ "ሒጃብ በዲላ ዩኒቨርሲቲ አልተከለከለም!" ማለቱ ከእውነት የራቀ ከመሆኑም ባሻገር ሙስሊም ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው አመራሮች ላይ ያላቸውን እምነት ያሳጣል ብሏል:: በተጨማሪም የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል "ኒቃብ ከድሮ ጀምሮ የተከለከለ ነው:: ሒጃብ ግን ድሮም ጀምሮ ይፈቀዳል::" ማለታቸው ከእውነት የራቀ ሲሆን ስለ ሐይማኖታችን የውስጥ ጉዳይ ለመተንተን መሞከራቸው ሴኩላሪዝምን የሚጣረስ ነው ብሏል:: የተፈጠረውን ችግር የተጎዱ ተማሪዎች ተክሰው በሕግ አግባብ እንዲፈታም አሳውቋል::
ጫናው የበረታበት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ኤሊያስ ከዚህ በፊት ለሐሩን ሚዲያ: ለDW: ለADDIS STANDARD እንዲሁም ለሌሎች ሚዲያዎች ቃላቸውን ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቢቀሩም ለመጀመሪያ ጊዜ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን ሰጥተዋል:: እንዲህም አሉ:-
"በዩኒቨርሲቲው የከለከልነው ኒቃብ እንጂ ሒጃብን አይደለም:: ኒቃብ ደግሞ ከዚህ በፊትም አይፈቀድም:: ዩኒቨርሲቲያችን እንደ ሀገራችን ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ በሴኩላሪዝም ያምናል:: ብዝሐነትንም ይቀበላል::"
ፕሬዚዳንቱ አይናቸውን በጨው አጥበው የጀመሩትን የጥላቻ እንቅስቃሴ ለመቀጠል የቆረጡ ይመስላል::
1ኛ:- በየትኛው አግባብ ነው በኒቃብ እና በሒጃብ መካከል ልዩነት ለመፍጠር የሚሞክሩት? እሳቸው የእስልምና ሀይማኖት መምህር ናቸው? ተቋማቸው ስለየትኛውም ሀይማኖት መመሪያ ማብራሪያ እንዲሰጡ ይፈቅዳል? ይህ ሴኩላሪዝምን መጣስ አይሆንም? እንዴትስ ቢንቁ እና በጥላቻ ቢነከሩ ነው የጌዴኦ ዞን እስልምና ጉዳይ "የእስልምና አለባበስ ከጥንት ጀምሮ ራሱን የቻለ ሊቃውንቶች ያስቀመጡት ነው። ኒቃብ የተሻለውና ተመራጭ የሆነው አለባበስ ነው::" ብሎ ሳለ መጅሊሱን ተላልፎ ስለ እስልምና ለማብራራት የሚሞክረው?
2ኛ:- ዲላ ዩኒቨርሲቲ ዘንድሮ እርሳቸው መምጣታቸውን ተከትሎ በእርሳቸው ትዕዛዝ ኒቃብን ከልክሎ ሳለ ከድሮ ጀምሮ ይከለከል ነበር ሲሉ ሌላው ቢቀር እድሜያቸውን አያፍሩም? ጥላቻ የዚህን ያክል ያውራል?
3ኛ:- ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም ይከለክላሉ ሲሉ ስለ ጎንደር: ባህር ዳር: ወልቂጤ: ወራቤ: ሐረማያ: ድሬ ዳዋ እና መሠል ዩኒቨርሲቲዎች መረጃ ሳይኖራቸው ቀርቶ ነው? ወይንስ ለእርሳቸው ዩኒቨርሲቲ ተብሎ የሚጠራው ኒቃብን የሚከለክል ብቻ ነው?
4ኛ:- ትምህርት ሚኒስቴር እስከ መች ነው ሙስሊም ጠልነትን የሚያንፀባርቁ ሰዎችን በሁሉም ኢትዮጵያዊ ሀብት በተገነቡ ተቋማት ውስጥ እንደሾመ የሚኖረው?
እነርሱ በውሸት እና በጥላቻ ተነክረው ለማፈን እየሞከሩ እኛ በእውነት ላይ ሆነን ዝም የምንልበት ምክንያት አይኖርም::
ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች!
ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች!!
https://t.me/EHEMSU
+2
#Update
🔴 “ 44 ሴት ተማሪዎችን ‘ጥቁር ማስክ አድርጋችኋል አናስገባም’ ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን ” - ሙስሊም ተማሪዎች
🔵 “ የትምህርት ሚኒስቴር የተቋማትን አስተዳደርና መመሪያዎችን ተከትሎ የሚተዳደር ነውና ተቋሙ ያንን ነው እያደረግን ያለነው ” - ዲላ ዩኒቨርሲቲ
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ኒቃብ፣ ጥቁር ማስክ እንዳይለብሱ በመከልከላቸው ከትምህርታቸው እየተስተጓጎሉ በመሆኑ መፍትሄ እንዲሰጣቸው በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጠንከር ያለ ስሞታ አቅርበዋል።
የተማሪዎቹ ዝርዝር ስሞታ ምንድን ነው ?
“ ኒቃብና ጥቁር ማስክ እንዳንለብስ ነው የተከለከልነው። ክልከላው የጀመረው ከአንድ ወር በፊት ነበር። በዚህም ማመልከቻ አስገብተን ነበር መልበስ እንዲፈቀድልን። ሆኖም ግን ምላሽ ሳይሰጠን ቆዬ።
ትምህርታችን በስርዓት እንዳንከታተል አስተጓጎሉን። ቅዳሜ፣ አንዲት እህት ማስክ አድርጋ፣ ሂጃብ ለብሳ በምትገባበት ወቅት ኦዲያ ካምፓስ በሁለቱም በሮች እንዳትገባ ከልክለዋታል።
እንዲያውም ወንዶቹ የግቢው ጥበቆች አስፈራርተው ፊቷን አስከፍተዋታል። እንደዛም ሆኖ ማስክ ለብሳ ወደ ግቢ መግባት እንደማትችል ነግረው መልሰዋታል።
ቅዳሜ ከሰዓት ሁለት ኒቃብ የለበሱ ተማሪዎች ግቢ ሊገቡ ሲሉ ተከልክለዋል። ለምን እንደተከለከሉ ሲጠይቁ ‘ ለደህንነት ሲባል ፊታችሁ መሸፈን የለበትም ’ አሏቸው።
ለደኅንነት ሲባል ከሆነ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በሴት ጥበቃ ተፈትሸው፣ አይዲያቸውን አሳይተው እንዲገቡ ሲጠይቋቸው ‘ ያንችን ፊት ማየት ምንም አይሰራልኝም። ፊትሽን ለምታሳይው አሳይ ’ የሚል መልስ ተሰጠን።
ከዚያ በኋላም ሰኞ እለት ደግሞ ኒቃብ፣ ጥቁር ማስክ መልበስ እንደማይቻል በፕሬዜዳንቱ ጭምር ተወሰነ። የተማሪ ተወካዮች ጠርተው ይህን አሳወቋቸው።
ጥበቃዎቹም ውሳኔውን በመጥቀስ ‘አናስገባም’ አሉን። ማክሰኞ እለት ማታ 44 ሴት ተማሪዎችን ‘ጥቁር ማስክ አድርጋችኋል አናስገባም’ ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን።
ረቡዕ ጠዋትም ከለር ማስክ አድርገው የገቡትን በፌደራል ጭምር አስፈራርተው ፊታቸውን እንዲገልጡ አድርገው፣ ሂጃብም ማውለቅ እንዳለባቸው አሳሰቧቸው።
ከሰኞ ጀምሮ ክላስም እየተከታተልን አይደለም፣ ኤግዛም አልፎናል፣ አሳይመንትም እያለፈን ነው። ማውለቅ ስለማንችል ከግቢ ውጪ ነን። በቃ ከተማሪነት ውጪ ባለ ህይወት ነን። እንደ ሴትነታችን ትልቅ የመብት ጥሰት ነው የተፈጸመብን።
ከምሽቱ 3 ሰዓት እንዳንገባ ሲከለክሉን የት እንድናድር፣ ምን እንድንለብስ፣ ምን እንደምንምገብ ያሰቡትን አናውቅም። ስለዚህ እንደንገባ ቢፈቅዱም እንዲህ ያደርጉበት ምክንያትን ሊጠየቁ ይገባል ” ሲሉ ተናግረዋል።
ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅናቸው ስማቸው እንዲነገር ያልፈቀዱ የዩኒቨርሲቲው አካል፣ ስለጉዳዩ በዩኒቨርሲቲው ፌስ ቡክ ገጽ የወጣውን መረጃ እንድንጠቀም ጠቁመዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተማሪዎቹ ነቃብ፣ ማስክና ሂጃብ ለብሰው እንዳይገቡ ተከልክለው ከግቢ ውጪ በመሆናቸው ትምህርት እያለፋቸው እንደሆነ ገልጸዋል፤ መከልከሉ ልክ ነው ? የሚል ጥያቄ አቅርቧል።
በምላሻቸው፣ “ እንዲህ አይነት ነገር የለም። የተሳሳተ መረጃ ነው። ማንም ተማሪ እዚህ ግቢ በተፈቀደለት ሰዓት ይገባል፤ ይወጣል ” ሲሉ መልሰዋል።
“ የተቋሙንም ሆነ የትምህርት ሚኒስቴር የተቋማት አስተዳደር መመሪያዎችን ተከትሎ የሚተዳደር ነውና ተቋሙ ያንን ነው እያደረግን ያለነው ” ብለዋል።
ተማሪዎቹ በተጨባጭ ከግቢ ውጪ እንደሆኑ፣ ክላስ እያለፋቸው እንደሆነ በድጋሚ የገለጽንላቸው እኝሁ አካል፣ በድጋሚም “ የለም ” የሚል ማስተባበያ ነው የሰጡት።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ የጌዴኦ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትን ተማሪዎች ደረሰብን የሚሉት ክልከላ ምንድነው ? ዩኒቨርሲቲው “ ሀሰተኛ መረጃ ነው ” ብሏልና እናንተ ጉዳዩን አይታችሁት ነበር ? ሲል ማረጋገጫ ጠይቋል።
ምክር ቤቱ ምን መለሰ ?
“ ጉዳዩ ከወር በፊት ደርሶን ነበር። እየቆየ ከፍ እያለ መጥቶ ተማሪዎች ግቢ ለመግባት ሲከለከሉ እኛም ደብዳቤ ፅፈን ነበር ችግሩ እንዲፈታ።
ዩኒቨርሲቲው እርከን ያልጠበቀ ጉዳይ ተደርጎ ታይቶ ነው፤ ተማሪዎቹን እናገኛቸዋለን የሚል ጥሩ ስሜት ነበረው።
የእስልምና አለባበስ ከጥንት ጀምሮ ራሱን የቻለ ሊቃውንቶች ያስቀመጡት ነው። ይሄ የተሻለውና ተመራጭ የሆነው አለባበስ ነው ” ብሏል።
(ጉዳዩን የምንከታተለው ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ዲላ ዩኒቨርሲቲ "በግቢዬ ሒጃብ አልተከለከለም!" የሚልን መግለጫ አውጥቷል:: በዚህ ውስጥ እየሞከረ ያለው ኒቃብን ሒጃብ አይደለም ለማለት ነው:: ይህ ንቀት ከመሆኑም ባሻገር በአንድ ሐይማኖት ውስጥ ጣልቃ ገብቶ ስለ እምነቱ መሠረት ማብራሪያ ለመስጠት የመሞከር ጋጠወጥ ተግባር ነው::
ሙስሊም ተማሪዎች ሒጃብ ነው ብለው የለበሱትን ሒጃብ አይደለም ማለት ምን አይነት ብልግና ነው? የዞኑ መጅሊስ ሒጃብ ነው አትከልክሏቸው ያለውን ሒጃብ አይደለም እከለክላለሁ ማለት ምን አይነት ድፍረት ነው? የፌደራል መጅሊስ ሒጃብ ነው አትከልክሏቸው ያለውን ሒጃብ አይደለም እከለክላለሁ ማለት ምን አይነት እብደት ነው?
ይህ ከሙስሊም ጠልነት ውጭ ማብራሪያ የለውም:: ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች! ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች!
Haggantoonni majliisa fedeeraalaa, waa'ee barattoota musliima ilaalchisee ministeera barnoota akka ta'an dhageenyeerra.
Jumu'aa waan ta'ef du'aaii irratti haa jabaannu.
"እንዳንቺ አይነት መምህር ግቢያችን አያውቅም!" - የዲላ ዩኒቨርሲቲ ም/ፕሬዚዳንት ዶክተር ታምራት የተናገረው
በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምትገኝ ሌክቸር የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ም/ፕሬዚዳንት "ወይ ከትምህርትሽ ወይ ከኒቃብሽ ምረጪ አለኝ:: ኒቃቤን ብዬ በቀጠልኩ ማግስት ደግሞ እንደ አንቺ አይነት መምህር በግቢያችን ውስጥ አናውቅም አለኝ::" እያለች ታለቅሳለች::
ይሄንን ንግግር የተናገረው በምስሉ ላይ የሚታየው ዶክተር ታምራት ነው:: ቢላሂል አዚም ጥላቻቸው ከኒቃቡ ሳይሆን ከእስልምናችን ነው::
በአላህ ፈቃድ መብታችንን እስከ ጥግ ታግለን እናስከብራለን::
መብት በትግል እንጅ በልመና አይገኝም!
ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች!
ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች!
@MohammadamminKassaw
የፌደራል መጅሊስ አመራሮች ስለ ዲላዎች ለመወያየት ትምህርት ሚኒስቴር እንደሆኑ ሰምተናል::
ጁምዓ ነውና በዱዓ እንወጥር ••• መልካሙን ያሰማን!
ነፃነት በትግል እንጅ በነፃ አይገኝም!!
@MohammadamminKassaw
"Niqaaba Osoo hin baasin hin baatan!" Yunivarsiiti diillaa.
Barattoota Mutaniqqiba sababa godhachun jibbaa fi tuffi hawaasa musliima irratti kan banee yunivarsiitin diillaa, guyyaa guyyaatti cunqursaawwan kessuummaa ta'an raawwachaa jira. Mutaniqqiiboota mooraa irraa ari'un, baruumsa, nyaata fi siree irraa eerga isaan fageesse guyyaa jahaffaa isaa har'a guteera. Ministeera barnoota irraa kaase, dhaabbilee mindaan isaani gibiira hawaasa biyyattin kaffalamun of bulchaa jiranis callisani jiru. Kan nama ajaa'ibu, har'aa barattoni modeela qormaata bahumsa biyyoleessaa (Exit Exam) fudhachuf konkolaataadhan seenan eerga qormaaticha xumuran booda niqaaba uuffachu isaani qalbeessan eerga ilaalan booda "Niqaaba keessan Osoo hin baasin bahuu hin dandeessan" jeechun dhorkaa dabarsani Falmii baay'een booda bahan.
yeroo jibbi nama jaameessu akkana... Kan ala jiran yoo baastan malee hin seentan jeechun, nyaata, barnootaa fi sireen isaan sodaachiisaa. Kan keessa jiranis, yoo baastan malee hin baatan, jeechun hidhamaa dhaabbi goochun Sodaachiisu yaalaa.
Ta'ees hin milkaa'ani, Cunqursi ifaan mul'achaa dhufee, Dhaloota isaan caala baratee fi barsiisee karaa qaroomaatin qabsaa'uu dhufeera.
Haqa barattoota musliimaa yunivarsiiti dillaaf!
Haqa barattoota musliimaa yunivarsiiti Ityoophiyaaf!
https://t.me/EHEMSU
"ኒቃብ ሳታወልቁ አትወጡም!" - ዲላ ዩኒቨርሲቲ
ኒቃቢስት ተማሪዎችን አስታኮ በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ ጥግ የደረሰ የጥላቻ እና ንቀት ጦርነት የከፈተው ዲላ ዩኒቨርሲቲ ቀን ተቀን እንግዳ የሆኑ ጭቆናዎችን እየፈፀመ ነው:: ኒቃቢስት ተማሪዎችን ከግቢ አባሮ ከትምህርት ከምግብ እና ከመኝታ ካራቀ 6 ቀናት ዛሬ ደፍኗል:: ከትምህርት ሚኒስቴር ጀምሮ ከሀገሪቱ ህዝብ ግብር ደመወዝ የሚተነፍሱ ተቋማትም ፀጥ ረጭ ብለዋል::
የሚገርመው ዛሬ ለራሱ ከሌላ ቦታ የEXIT EXAM ሞዴል ለመውሰድ በመኪና የገቡ ኒቃቢስቶችን ፈተና እንደጨረሱ ኒቃብ መልበሳቸውን አስተውሎ "ኒቃባችሁን ካላወለቃችሁ ከዩኒቨርሲቲው አትወጡም!" የሚልን ክልከላ አስተላልፎ በብዙ ጭቅጭቅ ነበር ተማሪዎች የወጡት::
ጥላቻ ሲያውር እንዲህ ነው ••• ከውጭ ያሉትን ካላወለቃችሁ አትገቡም በማለት በምግብ በትምሀርት እና በማደሪያ ያስፈራራል:: ከውስጥ ያሉትንም ካላወለቃችሁ አትወጡም ብሎ የቁም እስረኛ በማድረግ ለማስፈራራት ይሞክራል::
ሆኖም አይሳካላቸውም ••• አግጥጦ የመጣን ጭቆና ከእነርሱ በተሻለ ተምሮ አስተምሮ በሰለጠነ መንገድ የሚታገል ትውልድ መጥቷል::
ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች!
ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች!
@MohammadamminKassaw
