en
Feedback
Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Open in Telegram

This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.

Show more
4 479
Subscribers
+324 hours
-27 days
+2930 days
Posts Archive
ይህ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው:: በቻናሉ ከዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጋር ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮች እና የህብረቱ የዕለት ተዕለት ክዋኔዎች ይቀርባሉ:: በአላህ ፍቃድ እና እርዳታ ከዚያም ከሙስሊም ተማሪዎች ጋር በሚኖር መናበብና መተጋገዝ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያሉ ሙስሊም ተማሪዎች መብታቸው ተከብሮ ይማሩ ዘንድ እንተጋለን:: መረጃዎች ለሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ይደርሱ ዘንድ ቻናሉን ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ:: @EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU

ሒጃቧ - ማንነቷ! መገለጫዋ ነው ማንነት ምስጢሩ፥ የተወጠነበት፣ የሴትነት ሀሁ የተፈጥሮ ሚዛን፥ ጸንቶ የቆመበት። እሷነት ነው ሒጃብ ጥንት የተሰጠችው፥ የገጿ ላይ አርማ፣ በወቅት አይደበዝዝ አረጀብኝ ብላ፥ እትጥለው ከርማ። እቃዋም አይደለም ሲያሻት የምትጥለው፥ ደግሞ 'ምታነሳው፥ የመኖር ምሷ ነው ከራሷ ተገምዶ፥ እሷው የምትለብሰው። ማንነት ነውና ነፍስና ስጋዋን፥ ተዋሕዶ ያለ፣ እሷን ከሂጃቧ የምትነጥልበት፥ ጉልበት ወዴት አለ? https://t.me/EHEMSU

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በዩኒቨርሲቲው በኒቃባቸው ምክንያት ከትምህርት ከምግብ እና ከመጠለያ እንዲገለሉ የተደረጉ ተማሪዎች እስከ ኒቃባቸው ወደ ትምህርት እንዲመለሱ ከዩኒቨርሲቲው ጋር ከስምምነት ደረሰ! የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በዩኒቨርሲቲው ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ላይ ላለፉት ወራት ሲደረግ የነበረውን መገፋት እና ጭቆና በሰላማዊ መንገድ ይፈታ ዘንድ ሲታገል እንደነበር አሳውቋል:: በተደረገው ሰላማዊ ትግል እና ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች ጋር በተደረገ ውይይት በዛሬው እለት ላለፉት 10 ቀናት ከምግብ ከመጠለያ እና ከትምህርት በኒቃባቸው ምክንያት እንዲርቁ የተደረጉ ሙስሊም ተማሪዎች ኒቃባቸውን ለብሰው ወደ ትምህርት ገበታቸው ይመለሱ ዘንድ ከስምምነት እንደተደረሰ አሳውቋል:: ይህ ይመጣ ዘንድ ለመብታቸው የታገሉ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችና መላው ለሰብዓዊ መብት መከበር ትብብራቸውን ያሳዩ አካላትን በሙሉ አመስግኖም በዩኒቨርሲቲው ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ለደረሰውና ለሚደርሱ የመብት ጥሰቶች ሁሉ ፍትሕ እንዲሰፍን በማድረግ ረገድ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታውቋል:: https://t.me/EHEMSU

ሒጃቧ - መብቷ! እኩል ግብር ከፍሎ እኩል ደሙን ሰጥቶ፥ ባጸናት ሐገሩ ልጄን ላስተምር ሲል አይሆንም ሲባል ግን፥ አለመታፈሩ?! የነጻነት ምድር ቀበርኩት ብትልም፥ ጭቆናን ምድሯ ላይ አይኗ ተሸፍኗል ልማር የምትላት፥ ልጇን ዞራ እንዳታይ። ለስሙ እኩልነት ሲሰበክ ቢውልም፥ መድረክ ተፈልጎ የታለ እኩልነት ያ'ገሪቷን ግማሽ፥ ወደ ጎን አድርጎ?! ትዝብት እንጂ ትርፉ ፍትሕ ስሟ ቀርቶ፥ ግብሯ ቢሆን ኦና፣ ሀገር አትሰራም ከግለሰቦች ደጅ፥ መብት እየተጠና። ሌሎች እኩዮቿን መብት እንደሆናቸው፥ ትምህርትና ስራ፣ እሷም ትማራለች (እሷም ትሰራለች) እምነቷን አክብራ፥ መብቷን አስከብራ። https://t.me/EHEMSU

ዲላ ዩኒቨርሲቲ በራሱ የፌስቡክ ፔጅ የሀሳብ መስጪያ ሳጥንና በራሱ ተማሪዎች ላይ የጀመረውን ጭቆና እንደቀጠለ ነው:: ተማሪዎቹ ከምግብ ከመጠለያ እና ከትምህርት እንዲርቁ ከተገደዱ ሳምንት አልፏቸዋል:
ዲላ ዩኒቨርሲቲ በራሱ የፌስቡክ ፔጅ የሀሳብ መስጪያ ሳጥንና በራሱ ተማሪዎች ላይ የጀመረውን ጭቆና እንደቀጠለ ነው:: ተማሪዎቹ ከምግብ ከመጠለያ እና ከትምህርት እንዲርቁ ከተገደዱ ሳምንት አልፏቸዋል:: ተማሪዎቹ ድምፃቸውን ማሰማታቸውን ተከትሎ የሀሳብ መስጪያ ሳጥኑን ከዘጋም ቀናት ተቆጥረዋል:: ይህ በመሐይምነት ተዘፍዝፎ የደረቀ ጭካኔ ነው:: በሀገራችን አሉ ከሚባሉት የልሕቀት ማዕከላት አንዱን ሆኖ ይህንን አይነት የመብት ጥሰት መፈፀምና የተማሪን ሀሳብ ተቀብሎ ላለመወያየት የሚደረግ ትንቅንቅ ከትዝብት ውጭ ምንም ትርፍ የለውም:: ትምህርት ሚኒስቴር በስሩ ስላሉ ተቋማት ያስብበት:: እየተደረገ ያለው የመብት ጥሰት የእርሱም አቋም ከሆነ ደግሞ ያሳውቅ:: የዚያኔ ህዝቡ ያስብበታል:: ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ! ፍትሕ ለትምህርት ሚኒስቴር! ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች! ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች! @MohammadamminKassaw

ሒጃቧ - ክብሯ! አይቻለውም ዘመን እየሸነገለ፥ ከስፍሯ ሊያጎድላት፣ ትገዝፍበታለች በጨዋነት ሚዛን፥ ልመዝንሽ ላላት። እንዲህ ባ'ለው ጊዜ ዓለም በልቅነት፥ ተሳክሮ ባለበት፣ የብልግና ፀሀይ አይጠልቅም እስኪባል፥ ገንኖ በወጣበት፣ ህዝብ ቁልቁል ሲጓዝ አምላክ ሲ'ዘነጋ፥ ድንበሩ ሲ'ነካ፣ እንደውም እንደውም ጨዋነት በሷ ነው፥ ምግባሩ ሚ'ለካ። ከብዳ ብታስፈራው ተገላልጣ ሊያያት፥ ነውረኛ ቢወድም፣ ታውቃለች ቦታዋን ለስሜት ቃጠሎው፥ ክብሯን አትማግድም። ታሰጋለች ቢልም ለየት ስላለች፥ ከተማሪው ሁላ፥ በንዴት በግኖ ነው በጎደሉት መሐል፥ ብቻዋን ስትሞላ። ለባለጌ አትመች እንዳሻው ሊያደርጋት፥ አይሆን ተፈጥሮዋ፥ ጥበበኛው ጌታ ሒጃብ አብሮ ሰጥቷት፥ ለመጠበቂያዋ። በጥ'ብቅነቷ የመልካም ምግባር ጸር፥ ደርሶ ቢብከነከን፣ ሲፈልግ ቢውልም ከምሉዕ ገጿ ላይ፥ አያወጣም እንከን። "አውልቂ!" "ልበሺ!"ን ማዘዝ አይቻለውም፥ ማንም እየመጣ፣ ሒጃቧ ክብሯ ነው አትደራደርም፥ የገዘፈ ክብሯን ሊያስጥላት ከመጣ። https://t.me/EHEMSU

Bara 2005 A.L.Itti ministeerri barnootaa "Qajelfama haala Uuffannaaa, nyaataa  fi barnoota" jeedhun qajeelfama muslimoota ittin cunqursuu eerga baasee booda, Yunivarsiitin diillaa barattoota dubaraa 43 niqaaba waan Uuffataniif qoofa  barnootarraa ari'eera. Yunivarsiiti bahar daar barattoota mutanaqqiibaa 13 fi Amiira(bakka bu'aa)  jama'a yunivarsiiticha , Yunivarsiiti jimmaa barattoota mutanaqqiibaa 5, Akkasumas Yunivarsiiti Arbaaminc barattoota mutanaqqiibaa 45 ari'ee turee. Ammas, Yunivarsiitin diillaa qajeelfama cunqursaa San irra deebin hojiitti oolchuufi laata? Moo ministeerri barnootaa namu osoo hin beekin kan ittin hoojjatu qajelfama hin barroofneetu jira. Bifa kaminu haa ta'u har'a kaleessa miiti. Boorus har'a hin ta'u. Dhaloota, Hanga bilisummaan dhufuutti qabsaa'uutu dhufee jiraa.

Prezdaanti Yunivarsiiti Dillaa kan ammaa D.r Eliyaas bara 2017 A.L.Itti dura yeroo prezdaanti itti aanaa yunivarsiiti jinkaa tureetti barattoota mutanaqqiibaa irratti rakkoowwan itti aanan geessaniiru. • Bara 2013 yunivarsiiti jinkaatti barattun mutaniqqabaa sababa niqaaba isheetin ari'amteetti. Barattoonni mutaniqqibaa haraa yunivarsiitichatti dhufuf turanis, eerga odeeffannoocha dhagahan booda osoo hin dhufin hafaniiru. • bara 2014-2015 A.L.Itti yunivarsiiti jinkaatti barattoota mutaniqqiibaa sadi galani turan. Isaanis niqaaba isaani dhorkamun, qabsoo baay'ee taasifamus osoo hin milkaa'in hafee akka ari'aman ta'eera. Ammas Seenaa gurraacha kana yunivarsiiti dillaattis irraa deebi'an rawwachu barbaadu laata? Abadan hin ta'u, dhaloonni amma kun mirga isaa kabachiisuf kan dubatti hin deemnee fi bilisummaa isaa eegsiisudhaf eejjanno guddaa kan qabu Abukaatoo haqaati. Haqa barattoota musliima diillaaf! Haqa barattoota Muslima Itoophiyaaf!

"ወረርሽኝ አለ እንዴ ማስክ የምትለብሱት?" ••• የዲላ ዩኒቨርሲቲ ጥበቃዎች እህቶችን ሲያናግሩ የሚገርመው ከኒቃብ አልፈው ጥቁር ነጭ እያሉ ማስክንም መከልከል ይዘዋል:: በአላህ ፈቃድ በሕግ አግባብ ፍትሕን ያገኛሉ:: ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች! ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች!! @MohammadamminKassaw

በ2005 ዓ.ል ትምህርት ሚኒስቴር "የአለባበስ የአመጋገብ እና የትምህርት መመሪያዎች!" በሚል መመሪያ ካወጣ ቡሃላ የዲላ ዩኒቨርሲቲ 43 ሙስሊም ሴት ተማሪዎችን ኒቃብ ስለለበሱ ብቻ ከትምህርት አባሮ ነበር:: ባህርዳር ዩኒቨርሲቲም 13 ኒቃቢስቶችንና የጀመዓውን አሚር: ጅማ ዩኒቨርሲቲ 5 ኒቃቢስቶችን እንዲሁም አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ 45 ኒቃቢስት ተማሪዎችን አባረው ነበር:: እና አሁንም የዲላ ዩኒቨርሲቲ ያንን ጨቋኝ መመሪያ ዳግም ተግባራዊ ሊያደርግ ነው? ወይንስ ትምህርት ሚኒስቴር ማንም ሳያውቅ የሚያዘዋውረው ያልተፃፈ መመሪያ አለ? ያም ሆነ ይህ ዛሬ ትላንትን አይደለም:: ነገም ዛሬን አይሆንም:: ነፃነት እስኪመጣ ድረስ የሚታገል ትውልድ ተፈጥሯል:: ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች! ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች!! @MohammadamminKassaw

የዲላ ዩኒቨርሲቲ የአሁን ፕሬዚዳንት ዶክተር ኤልያስ ከ2017 ዓ.ል በፊት በጂንካ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ም/ፕሬዚዳንት በነበረበት ወቅት የሚከተሉት ግፎች በኒቃቢስት ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ተፈፅመዋል::
የዲላ ዩኒቨርሲቲ የአሁን ፕሬዚዳንት ዶክተር ኤልያስ ከ2017 ዓ.ል በፊት በጂንካ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ም/ፕሬዚዳንት በነበረበት ወቅት የሚከተሉት ግፎች በኒቃቢስት ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ተፈፅመዋል:: • በ2013 ዓ.ል በጂንካ ዩኒቨርሲቲ አንዲት ኒቃቢስት ተማሪ በኒቃቧ ምክንያት ተባራለች:: ሌሎች ኒቃቢስት አዲስ ገቢ ተማሪዎች መረጃው እንደደረሳቸው ሳይመጡ ቀርተዋል:: • ከ2014 - 2015 ዓ.ል በጂንካ ዩኒቨርሲቲ 3 ኒቃቢስት ተማሪዎች ገብተው ነበር:: እነርሱም ተከልክለው ብዙ ትግል ቢደረግም ሳይሳካ ቀርቶ እንዲባረሩ ሆነዋል:: እና አሁንም ይህንን ጥቁር ታሪክ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ሊደግሙት ነው? በፍፁም አይሳካም:: የአሁኑ ትውልድ በመብቱ የማይደራደር ነፃነቱን ለማስከበር ቆርጦ የተነሳ የፍትሕ ጠበቃ ነው:: ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች! ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች!! @MohammadamminKassaw

Sagantaa Mata duree"Sagalee ishee haa dhagahamu" jeedhun, majliisaa Finfinneetin qopha'ee Gidduu gala Aadaa Oromootti gaggeeffamaa jiruu irratti hoggantoota Gamtaa barattoota musliima dhaabbilee Olaanoo Ityoophiyaa kan hirmaatan yoo ta'u Prezdaantin gamtiicha Muhammad amin kaasaaw mata dure "Cunqursaa fi Qabsoo Barattoota musliima Ityoophiyaa" jeedhun barreeffama qorannoo dhiyesseera. Sagaleen ishee haa dhagahamu! Akkuma Uuffatteetti barattii! https://t.me/EHEMSU

ድምጿ ይሰማ!" በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ መጅሊስ አማካኝነት በኦሮሞ ባህል አዳራሽ እየተካሄደ ባለው ፕሮግራም ላይ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ከፍተኛ አመራሮች
+2
ድምጿ ይሰማ!" በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ መጅሊስ አማካኝነት በኦሮሞ ባህል አዳራሽ እየተካሄደ ባለው ፕሮግራም ላይ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ከፍተኛ አመራሮች የተሳተፉ ሲሆን የህብረቱ ፕሬዚዳንት ሙሐመድአሚን ካሳው "የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች ሰቆቃ እና ትግል!" በሚል ርዕስ ጥናታዊ ፅሁፍ አቅርቧል:: ድምጿ ይሰማ! እንደለበሰች ትማራለች!

"እንደ ሀገር ትልቅ ፈተና የሆነብን የመልካም ስነ-ምግባር መጥፋት ነው:: ሒጃብ ተለብሶ ሲኬድ ደግሞ ጥብቅነትን ያመላክታል:: ሒጃብ የምትለብስ ልጅ ትምህርት ቤት ስትሄድ መልዕክቷ ከትምህርት ውጭ አልፈልግም ጥብቅ ነኝ የሚል ነው:: ይህ መብታችን ሊከበር ይገባል::" - ወ/ሮ ፋጡማ (የፌደራል መጅሊስ የሴቶች ጉዳይ ሀላፊ) @MohammadamminKassaw

"እስልምና ሶላት እና ፆምን እንዳዘዘው ሁሉ ሒጃብን አዟል:: ከዚያ ሲቀጥል እውቀትን መፈለግ በሁሉም ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው:: ሒጃብ ከልካዮች ሲከለክሉ እየጣሱ ያሉት ሰብዓዊ መብቷን ነው:: እየተዳፈሩ ያሉት ሐይማኖታዊ መብቷን ነው:: የእኛም መልዕክት ለኢትዮጵያ መንግስት:- ሰብዓዊ እና ሐይማኖታዊ መብታችንን የሚጥሱ አካላትን በሕግ ይቅጣልን ነው:: ወደ ሕግም እንወስዳቸዋለን::" - ወ/ሮ ፋጡማ (የፌደራል መጅሊስ የሴቶች ጉዳይ ሀላፊ) @MohammadamminKassaw

"ሙስሊም ሴት አለመማር አትችልም!" - ወ/ሮ ፋጡማ (የፌደራል መጅሊስ የሴቶች ጉዳይ ሀላፊ) @MohammadamminKassaw

"ሒጃብ ትርጉሙ ለራሴ ለማህበረሰቤ ለሐይማኖቴ እና ለሀገሬ ታማኝ ነኝ ማለት ነው::" - ወ/ሮ ፋጡማ (የፌደራል መጅሊስ የሴቶች ጉዳይ ሀላፊ) @MohammadamminKassaw

ድምጿ ይሰማ ንቅናቄ ጀምሯል! ኒቃቧን ለብሳ ትማራለች! ነገ ሰኞ ለትምህርት ሚኒስትር ስለ ኒቃብ ደብዳቤ ይገባል:: በቀጣይ ማክሰኞ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስለ ኒቃብ ጥያቄ ይገባል:: ረቡዕ ከፍተኛ የማህበራዊ ሚዲያ ንቅናቄ ይኖራል:: ድምጿ ይሰማ ንቅናቄ ጀምሯል! ኒቃቧን ለብሳ ትማራለች! @MohammadamminKassaw

"የፈለጉት እንዳንማር ነው:: በጅህልና ከመቀጣት በላይ ደግሞ መቀጣት የለም:: ግን አይሳካላቸውም:: እንለብሳለን እንማራለን::" - የጉንችሬዋ አህት @MohammadamminKassaw

"አብረን ስንበላ ስንጠጣ ያወቁን አካላት ትምህርት ቤት ስንገባ አናውቅሽም:: እናውቅሽ ዘንድ ኒቃብሽን አውልቂ የሚሉት በምንድን ነው?" - የጉንችሬዋ እህት @MohammadamminKassaw