en
Feedback
Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Open in Telegram

This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.

Show more
4 479
Subscribers
+324 hours
-27 days
+2930 days
Posts Archive
በአባጅፋሯ ጅማ ተተብትቦ የነበረው የኒቃብ ጥላቻ በዛሬው እለት ተፈቷል:: ተማሪዎቹ እስከ ኒቃባቸው ገብተዋል:: ይህ የነፃነት ጮራ ሳይደበዝዝ እንዲቀጥል ሁሉም ሊተጋ ይገባል! ነፃነት በነፃ አይገኝም! https://t.me/EHEMSU

ጅማ ዩኒቨርሲቲ ለአመታት ኒቃቢስት ተማሪዎችን "ወይ ኒቃብ አውልቁ ወይ ትምህርታችሁን አቁሙ!" የሚል ምርጫ እያስመረጠ ነበር:: ነፃነታቸውን ሲገፍ ነበር! የእኩልነት መብታቸውን ሲነጥቅ ነበር! የሴኩላሪዝምን መርሆ ሲጥስ ነበር! ሆኖም ለሁሉም መጨረሻ አለውና የአባጅፋር ልጆች "እንለብሳለን እንማራለን!" በማለት ለብሰው ከትመዋል:: በዛሬው እለት ለብሶ መማር መብትም ግዴታም ነው ብለዋል:: መብት በትግል እንጅ በልመና አይገኝም!" የተባለው ለዚህስ አይደል? እንደለበሱ ይማራሉ ••• ከነፃነታቸው ጋር ይማራሉ ••• ከሐይማኖታቸው ጋር ይማራሉ! https://t.me/EHEMSU

የአክሱም ፍርድ ቤት ከዚህ በፊት ሒጃብ በከለከሉ ት/ቤቶች ላይ የተመሠረተውን ክስ እና ውሳኔ ውድቅ ማድረጉ ተገልፇል:: ይህንንም የትግራይ መጅሊስ እና ተማሪዎች ተቃውመዋል:: ይህ የሆነው እንግዲህ
የአክሱም ፍርድ ቤት ከዚህ በፊት ሒጃብ በከለከሉ ት/ቤቶች ላይ የተመሠረተውን ክስ እና ውሳኔ ውድቅ ማድረጉ ተገልፇል:: ይህንንም የትግራይ መጅሊስ እና ተማሪዎች ተቃውመዋል:: ይህ የሆነው እንግዲህ የፍርድ ቤቱ ዳኛ መቀየሩን ተከትሎ ነው:: የሴትን ልጅ የክብር ልብስ የፖለቲካ መቆመሪያ ቦታ ማድረግ የሚያሳዝንም የሚያሳፍርም ተግባር ነው:: ፍትሕ እስኪመጣ መጮህ መታገል መፍትሔ መፈለግ ያሻል:: ፍትሕ ለአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች! ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች!!

ረመዳን ገብቷል:: እንኳን አደረሰን:: ከወንጀላችን ታጥበን የምንወጣበት ያድርግልን! https://t.me/EHEMSU

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ነበር:: ኒቃብ ስለለበሱ ብቻ ከትምህርት አገዷቸው:: ከምግብ አገዷቸው:: ከትምህርት አገዷቸው:: ግን ታገሉ ••• በፅናት በትዕግስት በጥበብ ታገሉ ••• መብታቸውን ወሰዱ ••• ወደ
ዲላ ዩኒቨርሲቲ ነበር:: ኒቃብ ስለለበሱ ብቻ ከትምህርት አገዷቸው:: ከምግብ አገዷቸው:: ከትምህርት አገዷቸው:: ግን ታገሉ ••• በፅናት በትዕግስት በጥበብ ታገሉ ••• መብታቸውን ወሰዱ ••• ወደ ትምህርት ተመለሱ ከኒቃባቸው ጋር ••• ወደ ግቢ ተመለሱ ከክብራቸው ጋር ••• ወደ ካፌ ተመለሱ ከእስልምናቸው ጋር ••• ያለፋቸውን ትምህርትንም ሆነ ያለፋቸውን ፈተና ወሰኑ ከመስዋዕትነት ጋር •••ይኼው ነው የትግል ፍሬ! https://t.me/EHEMSU

የፌደራል መጅሊስ በሒጃብ እና መሠል የሙስሊም ተማሪዎች መብቶች ዙሪያ የመጨረሻ ያለውን ደብዳቤ ለትምህርት ሚኒስቴር ካስገባ ወር ከ4 ቀን ሞልቷል! ትምህርት ሚኒስቴር መልስ አልሰጠም! በአክሱም የሚገ
የፌደራል መጅሊስ በሒጃብ እና መሠል የሙስሊም ተማሪዎች መብቶች ዙሪያ የመጨረሻ ያለውን ደብዳቤ ለትምህርት ሚኒስቴር ካስገባ ወር ከ4 ቀን ሞልቷል! ትምህርት ሚኒስቴር መልስ አልሰጠም! በአክሱም የሚገኙ 159 ሙስሊም ተማሪዎች በሒጃብ ምክንያት ከትምህርት ውጭ ከሆኑ 100 ቀናት አልፈዋል! ፍትሕ ለአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች! ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች!!

በአክሱም ያሉ 159 ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በሒጃብ ምክንያት ከትምህርት ከታገጁ 100 ቀናት አልፈዋል! ህፃናትን በእምነታቸው ምክንያት ከትምህርት አገዱ:: የነገ ሀገር ተረካቢዎችን ፀጉራችሁን ለምን
በአክሱም ያሉ 159 ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በሒጃብ ምክንያት ከትምህርት ከታገጁ 100 ቀናት አልፈዋል! ህፃናትን በእምነታቸው ምክንያት ከትምህርት አገዱ:: የነገ ሀገር ተረካቢዎችን ፀጉራችሁን ለምን ሸፈናችሁ ብለው እውቀትን ከመሸመት አገዷቸው:: ይህ ሁሉ ሲሆን መንግስት ዝምታን መርጧል:: ይህ ሁሉ ሲሆን ከሚመለከታቸው አካላት ብዙሃኑ ዝምታን መርጠዋል:: በዚህ ውስጥ ሰብዓዊነት የሐይማኖት እኩልነት የሐይማኖት ነፃነት አብረው ተቀብረዋል:: አሁንም ቢሆን ግን የሒጃብ ጉዳይ ትኩረት እስኪያገኝ ድረስ ሊጮህ ይገባል:: በሒጃብ ሳቢያ የሚመጣ የመብት ድፍጠጣ እስኪቆም ድረስ መታገል ያሻል:: ፍትሕ ለአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች! ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች!!

Obboleettiwwan keenya Mutaniqqiboota yunivarsiiti Hawaasaa irraa haala nama hawwatun eebifamaniiru! Husniyaa husayn "midwifery" irraa 3.86 fiduun 1ffaa yeroo baatu, zabiibaa miftaah immoo 3.82 fiduun "Health informatics" irraa 3ffaa bahun eebifamaniiru. Niqaabnii fuula malee sammuu hin aguuguu. Warreen niqaabstiin hin barattuu jeedhaniif, " barattee eebbifamteetti" jeechuun ittii eergaa. Baga gammaddan! Baga gammannee! https://t.me/EHEMSU

Niqaaba+baruumsa + badhaafamuu + hogganuu nii danda'amaa. Niqaabni fuula malee, ssmmuu hin aguuguu. Yunivarsiiti Arbaaminc ir
Niqaaba+baruumsa + badhaafamuu + hogganuu nii danda'amaa. Niqaabni fuula malee, ssmmuu hin aguuguu. Yunivarsiiti Arbaaminc irraa warqii medaaliyaa kan badhaafamtee obboleetti keenya mutanaqqiibaa, Dr Zaakiraa  tabaarak. https://t.me/EHEMSU

በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲም ኒቃቢስት እህቶቻችን ደምቀው ተመርቀዋል!   ሁስኒያ ሁሴን ከሚድዋይፈሪ 3.86 በማምጣት አንደኛ ስትወጣ ዘቢባ ሚፍታህ ደግሞ ከHealth informatics 3.82 በማምጣት 3ተኛ ሆና ተመርቃለች:: ኒቃብ ፊትን እንጅ አዕምሮን አይሸፍንም!" የሚባለው ለዚህ ነው:: ኒቃቢስት አትማርም ለሚሉት "ተምራ ተሸልማለች!" ብላችሁ ላኩለት:: እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለንንን!! https://t.me/EHEMSU

እህት ኸውለት ••• ከOther health (radiology) 3ኛ በመውጣት ተሸላሚ ሆናለች! በዛሬው የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ምርቃት ፕሮግራም ላይ የጀመዓ እህቶች ደምቀው ውለዋል:: ሁለቱ አሚራ ዶክተሮች በወርቅ እና በ3ኛ ደረጃነት እንደ አጠቃላይ ተሸላሚ ሲሆኑ እህት ኸውለት ደግሞ ከother health 3ኛ በመውጣት ተሸላሚ ሆናለች:: አላሁ አክበርርር! እንኳን ደስ አለሽ! እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን!! Congratulations to all of you 🎉 🎉 https://t.me/EHEMSU

መልበስም መማርም ግድ ነው:: ሳይለብሱ መማርም ሆነ ተምሮ አለመልበስ ያጎድላል:: https://t.me/EHEMSU

ኒቃብ + ትምህርት + መሸለም + መምራት ይቻላል:: ኒቃብ ፊትን እንጅ አዕምሮን አይሸፍንም! ከአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ በወርቅ ሜዳሌያ የተሸለመችው ኒቃቢስቷ ዛኪራ ተባረክ! @MohammadamminKas
ኒቃብ + ትምህርት + መሸለም + መምራት ይቻላል:: ኒቃብ ፊትን እንጅ አዕምሮን አይሸፍንም! ከአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ በወርቅ ሜዳሌያ የተሸለመችው ኒቃቢስቷ ዛኪራ ተባረክ! @MohammadamminKassaw

ተሸላሚዋ ራህማ አንሷርም ••• ኒቃብ ከመማር ከመሸለም ከመምራት አያግድም ብላለች::   እርሷም ከአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሜዲስን የተመረቀች ሲሆን ከአጠቃላይ ተማሪዎች 3ተኛ ከሴቶች ሁለተኛ በመውጣት ተሸላሚ ሆናለች:: እንኳን ደስ አለሽ! እንኳን ደስ አላት! እንኳን ደስ አለንንንን!!! https://t.me/EHEMSU

የወርቅ ሜዳለያ ተሸላሚዋ ዛኪራ ተባረክ ••• ኒቃብ ከመማር ከመሸለም ከመምራት አያግድም ብላለች! ከአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሜዲስን 3.87 አምጥታ በዛሬው እለት ተመርቃለች:: መመረቅ ብቻ ሳይሆን ደግሞ በሶስት ዘርፍ ተሸላሚ ሆና ነው የተመረቀችው:: ከሁሉም የህክምና ተማሪዎች አንደኛ ወጥታ ተሸልማለች:: ከሁሉም ሴቶች አንደኛ ወጥታ ተሸልማለች:: ከሁሉም ተማሪዎች አንደኛ ወጥታ የወርቅ ሜዳለያ ተሸልማለች:: እንኳን ደስ አለሽ! እንኳን ደስ አላት! እንኳን ደስ አለንንንን!! https://t.me/EHEMSU

የመቱ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ ዩኒቨርሲቲው በጁምዓ ቀን ከ5:30 ቡሃላ ምንም አይነት ፕሮግራም እንዳይኖር እንዲሁም ከሰዓት ከ7:30 ብቻ እንዲጀምር ጠይቋል:: ህብረቱ እንደገለፀው የዩኒቨ
የመቱ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ ዩኒቨርሲቲው በጁምዓ ቀን ከ5:30 ቡሃላ ምንም አይነት ፕሮግራም እንዳይኖር እንዲሁም ከሰዓት ከ7:30 ብቻ እንዲጀምር ጠይቋል:: ህብረቱ እንደገለፀው የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ህብረት አካዳሚክ ክፍል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመወያየት ማስተካከያ እንደሚያደርግ አሳውቋቸውል:: ••• እንደሚታወቀው በሕግ ደረጃ ከ1985 ጀምሮ በጁምዓ ቀን ከ5:30 - 7:30 በመንግስት መስሪያ ቤቶች የእረፍት ሰዓት ነው:: ሆኖም ግን ትምህርት ቤቶች እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዚህ ሕግ ውጭ በመሆን በዚህ ሰዓት አገልግሎት በመስጠት የሙስሊሞችን መብት በተደጋጋሚ ሲጥሱ ተስተውሏል:: https://t.me/EHEMSU

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የሰላም ሚኒስትር በዩኒቨርሲቲው አዲሱ የተማሪዎች የስነ ምግባር መመሪያ ውስጥ ያሉ አድሎኣዊ ድንጋጌዎችን እና አሰራሮችን እንዲመረምር ጠየቀ! ህብረቱ
+2
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የሰላም ሚኒስትር በዩኒቨርሲቲው አዲሱ የተማሪዎች የስነ ምግባር መመሪያ ውስጥ ያሉ አድሎኣዊ ድንጋጌዎችን እና አሰራሮችን እንዲመረምር ጠየቀ! ህብረቱን ጥያቄውን ያቀረበው ለሚኒስትር መስሪያ ቤቱ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ በተለይም ከኒቃብ እና የጀመዓ ሰላት ጋር ተያይዞ እየደረሱ ስላሉ የመብት ጥሰቶች ለማብራራት በጻፈው ደብዳቤ ነው። ህብረቱ ችግሩ ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ ለወራት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቢጥርም በዩኒቨርሲቲው በኩል ችግሩን የመፍታት ፍላጎት ባለመኖሩ እንዳልተሳካም አውስቷል። ህብረቱ እና ሙስሊም ተማሪዎች ለሰላምና ሰላማዊ ትግል ካላቸው ጽኑ አቋም የተነሳም በአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሙሉ ወጪ የጣት አሻራ መመርመሪያ ማሽኖችን ለዩኒቨርሲቲው ለማስገባት ዝግጁ ቢሆኑም ነገር ግን የዩኒቨሪሲቲው አስተዳደር ችግሩን ከመፍታት ይልቅ ችላ በማለት እንዲባባስ እያደረገ ይገኛል ሲል ደብዳቤው አብራርቷል። አሁንም ድረስ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ በተለይም ኒቃብ በሚለብሱ እህቶች ላይ በተለይም ግቢ መግቢያ በሮች ላይ ትንኮሳዎች እየተካሄዱ በመሆኑ ጉዳዩ በአስቸኳይ እልባት የማያገኝ ከሆነ ወዳልተፈለገ ደረጃ ሊያመራ እንደሚችልና ወደዚያ ቢያመራም ብቸኛ ተጠያቂ ዩኒቨርሲቲው እንደሚሆን አሳስቧል። በመሆኑም የሰላም ሚኒስትር የሐገሪቱን ሰላምና መረጋጋት እንዲያስጠብቅ ኃላፊነት የተሰጠው ተቋም በመሆኑ ችግሩን ለመፍታት አስቸኳይ እና ቆራጥ እርምጃ እንዲወስድ ጠይቋል። aaumsu https://t.me/EHEMSU

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በዩኒቨርሲቲው ያሉ ሙስሊም ተማሪዎችን መብት እና ክብር ለማስጠበቅ ቆራጥ እና አስቸኳይ እርምጃ እንዲ
+2
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በዩኒቨርሲቲው ያሉ ሙስሊም ተማሪዎችን መብት እና ክብር ለማስጠበቅ ቆራጥ እና አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ ጠየቀ! ህብረቱ ለምክር ቤቱ በጻፈው ደብዳቤ በዘንድሮው አመት በዩኒቨርሲቲው አዲስ ከጸደቀው የተማሪዎች ስነምግባርና ዲሲፕሊን መመሪያ ጋር በተያያዘ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ በተለይም ከኒቃብ እና የጀመዓ ሰላት ጋር ተያይዞ እየደረሰ ስላለው ችግር በሰፊው አብራርቷል። ህብረቱ ችግሩ ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ ለወራት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቢጥርም በዩኒቨርሲቲው በኩል ችግሩን የመፍታት ፍላጎት ባለመኖሩ እንዳልተሳካም አውስቷል። ይህም በእንዲህ እንዳለ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ በተለይም ኒቃብ በሚለብሱ እህቶች ላይ በተለይም ግቢ መግቢያ በሮች ላይ አሁንም ድረስ ትንኮሳዎች እየተካሄዱ እንዳሉ በመጥቀስ ጉዳዩ በአስቸኳይ እልባት የማያገኝ ከሆነ ወዳልተፈለገ ደረጃ ሊያመራ እንደሚችል ተብራርቷል። በተጨማሪም ህብረቱ ፕሬዝደንቱና ስራ አስፈጻሚውን ጨምሮ ምክር ቤቱን በተደጋጋሚ በጉዳዩ ዙሪያ ለማነጋገር ቢሞክርም ከምክር ቤቱ ምላሽ አለማግኘቱ እና በዚህ ወቅት ምክር ቤቱ ከተማሪዎች ጎን አለመቆሙ ኃላፊነቱን አለመወጣት ብቻ ሳይሆን ሙስሊሙ ማህብረሰብ በምክር ቤቱ ላይ የጣለውን አደራ መክዳት እና የታሪክ ተወቃሽ መሆንም ጭምር በመሆኑ ምክር ቤቱ በአፋጣኝ መፍትሄ ያበጅ ዘንድ ጠይቋል። ህብረቱ የደብዳቤውን ግልባጭ ለዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ጽ/ቤት፣ ለአዲስ አበባ እ/ጉ/ከ/ም/ቤት፣ ለኢትዮጵያ ኃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እና ለኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት አስገብቷል። ©️ aaumsu https://t.me/EHEMSU

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የጁምዓ ሰላት ሰዓት እንዲከበር አሳሰበ። ህብረቱ ለዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ህብረት እና በግልባጭ ለአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ባስገባው ደብዳቤ የሐ
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የጁምዓ ሰላት ሰዓት እንዲከበር አሳሰበ። ህብረቱ ለዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ህብረት እና በግልባጭ ለአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ባስገባው ደብዳቤ የሐገራችን መንግስት ሙስሊም ሰራተኞች የጁምአ ሰላትን እንዲሳተፉ ለማድረግ የመንግስት መስሪያ ቤቶች አርብ ከ 05፡30 እስከ 07፡30 እንዲዘጉ መመሪያ ያወጣና የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንትን ጨምሮ የዩንቨርስቲው አመራሮች ለመመሪያው መተግበር ቁርጠኛ መሆናቸው የገለጹ ቢሆንም ባለፉት ጊዜያት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በውጤታማነት አለመተግበሩን ጠቅሷል። ህብረቱ የትምህርት ዘመኑ ሁለተኛ ሴሚስተር እየተጀመረ በመሆኑ የተማሪዎች ህብረት እና ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ሁሉም የአካዳሚክ መርሃ ግብሮች የጁሙዓ የሰላት ጊዜን በሚመለከት የመንግስት እና የዩኒቨርሲቲ መመሪያዎችን መተግበራቸው እንዲከታተሉና ስህተቶችን እንዲያርሙ አጥብቀን አሳስቧል። ህብረት በየካምፓስ ተወካዮቹ አማካኝነት ሁኔታውን በቅርበት የሚከታተል እና የሚፈጸሙ ጥሰቶችን የሚያሳውቅ መሆኑንና ከዚህ መመሪያ ውጭ የሆነ ማንኛውም አካል ተጠያቂ የሚሆንበትም መንገድ እንዲመቻች ጠይቋል። የህብረቱ ተወካዮች ከተማሪዎች ህብረት ጋር በጉዳዩ ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን የተማሪዎች ህብረትም ጥያቄው ተገቢ መሆኑን በመጥቀስ አፈጻጸሙን እንድሚከታተል ገልጿል። የአአዩሙተህ በካምፓስ ጀመዓዎቹ አማካኝነት አተገባበሩን የሚከታተል ሲሆን የዩኒቨርሲቲያችን ሙስሊም ተማሪዎች በየትምህርት ክፍሎቻቸው እንዲከታተሉ እና ለህብረቱ እንዲያሳውቁ እናሳስባለን። ©️ AAUMSU https://t.me/EHEMSU

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ተወካዮች በዩኒቨርሲቲው የረመዳን ዝግጅት ዙሪያ ከዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ህብረት ጋር ተወያየ። በውይይቱም ወቅት የህብረቱ ተወካዮች መደረግ ስላለባቸ
+1
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ተወካዮች በዩኒቨርሲቲው የረመዳን ዝግጅት ዙሪያ ከዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ህብረት ጋር ተወያየ። በውይይቱም ወቅት የህብረቱ ተወካዮች መደረግ ስላለባቸው ዝግጅቶችና ከዚህ በፊት ስለነበሩ ችግሮች ማብራሪያ ሰጥተዋል። ተወካዮቹ የካፌ እና ለተራዊህና ተሃጁድ ሰላቶች የበር መውጫና መግቢያ ሰዓቶች ልክ እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ እንዲስተካከሉ አስታውሰዋል። በተጨማሪም የመጀመሪያ ቀን የሱህር ምግብ አለመዘጋጀት ወይም በቂ ያለመሆንን ባለፉት አመታት ሲታይ የነበረ ችግር በመሆኑ እንዲፈታ ያሳሰቡ ሲሆንም የተማሪዎች ህብረትም ዘንድሮ ችግሩ ሙሉ በሙሉ እንዲቀረፍ እንደሚሰራ አሳውቋል። ሌላው ከምግብ ጥራት ጋር በተያያዘ በተለይ በሱህር ሰዓት የሚዘጋጁ ምግቦች በአብዛኛው ጥራታቸውን ያልጠበቁ መሆናቸውን የተገለጸ ሲሆን የተማሪዎች ህብረት በየጊዜው ቁጥጥር እንዲያደርግ ስምምነት ተደርሷል። ከዚያም በተጨማሪ ከተማሪዎች ህብረት ከሚመደቡ ተቆጣጣሪዎች በተጨማሪ በየካምፓሱ ከሙስሊም ተማሪዎች አንድ አንድ ተቆጣጣሪ እንዲመደብ ከስምምነት ተደርሷል። ሌላው በውይይቱ የተነሳው ነጥብ የሸዋልን ስድስት ቀናት ለሚጾሙ ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲው አገልግሎት እንዲሰጥ የሚል ሲሆን ከሚመለከታቸው አካላት ውይይት እንዲደረግ በመስማማት ውይይቱ ተጠናቋል:: ©️ AAUMSU https://t.me/EHEMSU