en
Feedback
Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Open in Telegram

This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.

Show more
4 474
Subscribers
-424 hours
-37 days
+2230 days
Posts Archive
"ሒጃብ በትምህርት ተቋማት አይከለከልም:: የሚከለከለው ኒቃብ ነው:: ኒቃብ ከሒጃብ ይለያል::"- ፕ/ር ብርሐኑ ነጋ ግን እንደው በምን አግባብ ነው ፕሮፌሰሩ ሒጃብ ወ ኒቃብ እያሉ ልዩነት በመስጠት ትንታኔ ለመስጠት የሚሞክሩት? ግን እንደው በየትኛው መስመር ነው አንድ የሌላ እምነት ተከታይ የሆነ የመንግስት ባለስልጣን በሌላ ሐይማኖት ጉዳይ ገብቶ ማብራሪያ የሚሰጠው? ያውቁት ዘንድ ••• ሒጃብ ከኒቃብ አይለይም:: ኒቃብም ከሒጃብ አይለይም:: መልበስ የፈለገ መልበሱ እንደ ሀገር በሕግ የፈለገ አካል መብት ነው:: @EHEMSU

ኒቃብን አስመልክቶ ሕጉም ሆነ የተማሪው አቋም አንድ እና አንድ ነው!   የሐይማኖት እኩልነት እና ነፃነት ይከበር ዘንድ የተጠየቀው የዛሬ 51 አመት በአደባባይ ነው:: ጠያቂው አንድ ወይም ሁለት ግለሰብ ሳይሆን 300 ሺህ የሚጠጋ ህዝብ ተሰባስቦ ባነር ሰቅሎ ነው:: ያንን ተከትሎ መንግስት ሁሉን ተቀብሎ የሐይማኖት ነፃነት መብት ••• የሐይማኖት እኩልነት መብት ብሎም ሴኩላሪዝም የሚባሉትን መርሆዎች በሕገ- መንግስት አፅድቋል:: ከዚያ ባሻገር የደርግ መንግስት መውደቅን ተከትሎም በኢሕአዴግ መንግስት የፀደቀው ሕገ-መንግስት የሐይማኖት እኩልነት --- የሐይማኖት ነፃነት ብሎም ሴኩላሪዝም የሚባሉትን አቃፊ መርሆዎች አፅድቋል:: ያንንም ተከትሎ ሙስሊሙ ማህበረሰብ እነዚህን ድንጋጌዎች ከደስታ ጋር ተቀብሎ ተግባራዊነታቸውን ሲከታተል ዘልቋል::   ሆኖም መንግስት ከውጭ ሀገራት ጋር በሚኖረው ግንኙነት ብሎም ሙስሊሙን ሊያስተናግድ በሚፈልገበት የተለያየ መልክ ሳቢያ ከኒቃብ ጀምሮ ያሉ መሠረታዊ ሕገ-መንግስታዊ ሰብዓዊ እና ሐይማኖታዊ መብቶችን በአዋጅ እና በመመሪያ ሕገ-መንግስቱንም ሆነ ሞራልን በመጣስ ሲያወጣ ከርሟል:: ለአብነትም በ2000 ዓ.ል እና በ2005 ዓ.ል የወጡትን መመሪያዎች መመልከት እንችላለን::   በ2000 ዓ.ል  የትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው መመሪያ ኒቃብን በስም ጠቅሶ የሚከለክል መመሪያ አውጥቶ ነበር:: ሆኖም የዚያኔ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የነበሩ ሙስሊም ተማሪዎች የወጣውን መመሪያ ኢሕገ- መንግስታዊ በማለት ተቃውመዋል:: በዚያም ምክንያት በወሎ ዩኒቨርሲቲ: በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ወዘተ... ትግሎች ነበሩ:: ከዚያ ባሻገር የኢሕአዴግ መንግስት ሙስሊሙን የጥቃት ኢላማ ውስጥ በከተተበት ጊዜ በ2005 ዓ.ል የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የሚባል የመንግስት አካል ኒቃብን የሚከለክል መመሪያ አውጥቶ ከብዙ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎች እንዲባረሩ ሆኗል:: ሆኖም ግን የዚያኔ የነበሩ ሙስሊም ተማሪዎች መመሪያውን የተቃወሙ ሲሆን መንግስት እየሰራው በነበረው ውንብድና ዙሪያ እና መመሪያውን ለማስቀየር ለመወያየት አዲስ አበባ ላይ ተሰባስበው የነበሩ የሙስሊም ተማሪዎች አሚሮች ለእስር እና ለስደት እንዲዳረጉ ሆኗል::    ከዚያ ቡሃላ በነበረው የለውጥ ጊዜ በየዩኒቨርሲቲዎች እንደታዘብነውና ከዩኒቨርሲቲ አመራሮች ጋር በነበረው ንግግር መመሪያዎቹ ኢሕገ- መንግስታዊ መሆናቸው ተግባቦት ተደርሶበት በሙስሊም ተማሪዎች መብት ዙሪያ መጠነኛ ለውጥ ነበር:: ሆኖም ያ ሁሉ ተረስቶ አሁን ላይ በኢሕአዴግ መንግስት በልዩ ፍላጎት ወጥቶ የነበረውን መመሪያ መቃብር ፈንቅሎ ለማውጣት በመሞከር በሙስሊም ተማሪዎች መብት ዙሪያ ዳግም አፈና ዳግም ጭቆና ለመፈፀም ዳር ዳር እየተባለ ነው:: ሆኖም ትላንትም ዛሬም ሆነ ነገ በዚህ ዙሪያ የሙስሊም ተማሪዎች አቋምም ሆነ ሕገ- መንግስታዊ መብታቸው ግልፅ ነው:: ሕገ- መንግስቱ የሐይማኖት ነፃነት መብትን: የሐይማኖት እኩልነት መብትንና ሴኩላሪዝምን ደንግጓል:: ሙስሊም ተማሪዎችም በመብታቸው ሊደራደሩ አይችሉም:: ካለመደራደር ባሻገር ግን በየጊዜው እነዚህን መሠረታዊ መብቶችን ምክንያት በመፈለግ ለማሳነስ የሚሞክሩና አደንዳ ለመስጠት የሚሞክሩ አካላትን ተጠያቂ ማድረግ ያሻል:: መፍትሔው ዘላቂ ካልሆነ በዘላቂነት አጀንዳ መስጠታቸው አይቀርም! መብት በትግል እንጅ በነፃ አይገኝም! በሕገ- መንግስት የፀና መብት በግለሰብ ሊነጠቅ አይችልም!! @EHEMSU

የጁምዓ ቀን የትምህርት ሰዓት ከ2:30 - 5:30 እንደሆነና ከሰዓት 7:30 እንደሚጀምር አዋጅ ቁጥር 43/1985 አንቀፅ 3 ቁጥር 1 ላይ ይናገራል:: እንዲህም ይላል:- "የመንግስት መስሪያ ቤቶች
+1
የጁምዓ ቀን የትምህርት ሰዓት ከ2:30 - 5:30 እንደሆነና ከሰዓት 7:30 እንደሚጀምር አዋጅ ቁጥር 43/1985 አንቀፅ 3 ቁጥር 1 ላይ ይናገራል:: እንዲህም ይላል:- "የመንግስት መስሪያ ቤቶች የስራ ቀንና ሰዓት እንደሚከተለው ይሆናል:: ለ) ዓርብ:- ከጠዋቱ 2:30-5:30 ከቀኑ 7:30 - 11:30 ጁምዓ ከ5:30 - 7:30 ባለው ትምህርትም ፈተናም ሆነ ሌላ ነገር ሊኖር አይገባም ማለት ነው:: በአዋጁ መሠረት ይህንን የሚያደርግ ወንጀለኛ ነው:: @EHEMSU

#አፄ ኃይለ ሥላሴ ፀረ ሙስልም። አፄ ተብዬዎች የሀገር ከንሰር ነበሩ !! 🌻🌻🌻🌻🌻🌸🌸🌸🌸🌸🌸 የአፄ ኃይለ ሥላሴን መንግሥት ፀረ-ኢስላም ስትራቴጂዎች በጣም በጥቂቱ ቀንጨብ በማድረግ አስነብባችኋለሁ። ኃይለ ሥላሴ ፀረ- ሙስሊም ዘመቻውን ማጧጣፍ የጀመረው ገና ሥልጣን ሳይቆናጠጥ ነበር። ወንበር አያያዙ ራሱ ሙስሊሙ ላይ በተሸረበ ሴራ ነበር። ‹‹እስላም አይነግስም!›› በሚል በመኳንንትና በቀሳውስት የጋራ ፀረ–ኢስላም አድማ ነበር ግንባር ፈጥረው ልጅ እያሱን የጣሉት። እንዲህ ሲሉ ነበር ያወጁት፡- ‹‹አዋጅ! የኢትዮጵያ ሕዝብ ስማ! መስሚያ አይንሳህና ልጅ እያሱ ወደ እስላም ሃይማኖት ስለገቡ መንግሥት አይገባቸውም… ከአዋጁ በላይ የእስላም ወገን ሆኖ ሲረዳ የተገኘ አይቀጡ ቅጣት ይቀጣል›› አፄ ኃይለ ሥላሴ ሥልጣኑን ከጨበጠ በኋላ በሕገ መንግስቱ ላይ በግልፅ ሥልጣን የሚገባው ለክርስቲያኑ ብቻ እንደሆነ ደንግጓል። ለይስሙላ ያህል ራሱን ለሁሉም ኢትዮጵያው ያንተ ተቆርቋሪ መሪ ለማስመሰል አስቂኝ ሙከራዎችን አድርጓል። የኃይለ ሥላሴ መንግሥት ፀረ-ሙስሊም ስትራቴጂዎች በርካታ ቢሆኑም ለዛሬ አሥራ አንዱን ብቻ ለማሳየት እጥራለሁ። መልካም ንባብ።

Ministeerri barnoota Guyyaa Iida Al-ad haa irratti Qorumsaa biyyooleessaa Remidiyaali keennuf Sagantaa baasee jiraa! Ministeerri barnoota Birhaanu naggaan hogganamu mirga barattoota musliimaa Sarbuun sagantaawwan biyyooleessaa guyya ayyaana isaanirratti akkasumas Sa'atii jumu'aatti irra deddeebin baasaa, komii fi Mormii keessummeessaa kan turee caamsa dhufuu guyyaa 26-30 qorumsa biyyooleessaa keennuf sagantaa baaseera. Kaalaandarri ityoophiyaa caamsa 29 Iida Al-Ad haa ta'uu isaa beeksiisus akkuma kanaan duraa, kana osoo yaada keessatti hin galfatiin saganticha raabsameera. Kun immoo qophin barattoota musliimaa qormaataaf taasiisan jeequun dabalatee mirga amantii isaani nii sarbaa. Yeroo qormaaticha gahee falmii hin barbaachisne keessatti seenun dura ministeerri barnoota biifa mirga barattoota musliimaa kabajeen saganticha irratti sirreffama taasiisutu irra jiraa. ■ Akkuma beekamu sarbiinsi mirgaa barattoota musliima irratti taasifamaa jiru akka haraatti deebi'aa kan jiruu yoo ta'uu yeroo dhihoo kanattis ministeerri barnoota prof. Birhaanu naggaa niqaaba Mirga namoomaa kan ta'ee "Soodaa nageenyaati" jeechun paarlaamaa keessatti dubbateera. Walitti qabsiisunis niqaabni hin eeyyamamu jeedhera. https://t.me/EHEMSU

وزارة التعليم تُجري امتحانات وطنية تعويضية في يوم عيد الأضحى المبارك أعلنت وزارة التعليم الإثيوبية عن برنامج للامتحانات الوطنية التعويضية يمتد من 26 إلى 7 يونيو 2025م، دون أي اعتبار للأعياد والمناسبات الدينية. ويُصادف يوم 6 يونيو 2025م عيد الأضحى المبارك، الموافق 10 ذو الحجة 1446هـ، وهو يوم من أعظم الأيام عند المسلمين، حيث يُقام فيه أهم شعائر الإسلام. إن قرار الوزارة بعقد امتحان وطني في هذا اليوم المقدس يُعد تجاهلًا صارخًا للمشاعر الدينية وحقوق الطلاب المسلمين، ويُشكّل عائقًا كبيرًا أمام مشاركتهم الكاملة في هذه المناسبة العظيمة. فبدلًا من أن يكونوا مع أسرهم في أجواء العيد الروحانية، سيُجبر العديد منهم على حضور الامتحانات، مما يُؤثر على أدائهم الأكاديمي ويقوّض حقهم في ممارسة شعائر دينهم بحرية. إن مثل هذه القرارات لا تؤدي فقط إلى الإرباك، بل تُعد انتهاكًا مباشرًا للحقوق الدينية والدستورية التي يكفلها القانون لجميع المواطنين، دون تمييز. ومن غير المقبول أن تستمر المؤسسات الحكومية في تجاهل المناسبات الدينية التي تهم شريحة واسعة من المجتمع. يجب على وزارة التعليم أن تُراجع هذا القرار فورًا، وتُعيد جدولة الامتحانات بما يضمن احترام العقيدة الإسلامية وحقوق الطلاب المسلمين. وللتذكير، فإن هذا ليس الحادث الأول من نوعه. فقد شهدت الساحة التعليمية في الآونة الأخيرة تصعيدًا ملحوظًا في التعدي على الحريات الدينية. ففي خطوة مثيرة للجدل، صرّح وزير التعليم، البروفيسور برهانو نيغا، في البرلمان بأن ارتداء النقاب "تهديد أمني"، وزعم أنه محرّم، في موقف يناقض مبدأ الحريات الدينية المكفولة قانونيًا. نطالب وزارة التعليم باحترام القيم الدينية والتنوع الثقافي في البلاد، وتحمّل مسؤولياتها تجاه جميع مكونات الشعب دون تمييز. @EHEMSU

የትምህርት ሚኒስቴር በኢደል- አድሃ ቀን የሪሜዲያል ብሔራዊ ፈተና ለመስጠት ፕሮግራም አውጥቷል! በፕሮፌሰር ብርሐኑ ነጋ የሚመራውና ከሙስሊም ተማሪዎችን መሠረታዊ መብቶች በመጣስ ከበዓላቸው ብሎም ከጁ
+1
የትምህርት ሚኒስቴር በኢደል- አድሃ ቀን የሪሜዲያል ብሔራዊ ፈተና ለመስጠት ፕሮግራም አውጥቷል! በፕሮፌሰር ብርሐኑ ነጋ የሚመራውና ከሙስሊም ተማሪዎችን መሠረታዊ መብቶች በመጣስ ከበዓላቸው ብሎም ከጁምዓ ሰዓት ጋር የሚጋጩ ብሔራዊ ፕሮግራሞችን በተደጋጋሚ እያወጣ ተደጋጋሚ ቅሬታዎችንና ተቃውሞዎችን ሲያስተናግድ የነበረው ትምህርት ሚኒስቴር በመጪው ግንቦት ከቀን 26-30 የሪሜዲያል ብሔራዊ ፈተና ለመስጠት ፕሮግራም አውጥቷል:: የኢትዮጵያ ካላንደር ግንቦት 29 ኢደል- አድሐ እንደሆነ ቢያስቀምጥም ልክ እንደከዚህ ቀደም ይህንን ታሳቢ ሳያደርግ ፕሮግራሙ ተሰራጭቷል:: ይህ መሆኑ ሙስሊም ተማሪዎች ለፈተና የሚያደርጉትን ዝግጅት ከማስተጓጎሉም ባሻገር መሠረታዊ ሐይማኖታዊና ሕገ- መንግስታዊ መብታቸውን የሚጥስ ይሆናል:: የፈተናው ሰዓት ደርሶ አላስፈላጊ መምታታት ውስጥ ከመግባት በፊት ት/ሚኒስቴር በፕሮግራሙ ላይ የተማሪዎቹን መሠረታዊ መብት ባከበረ መልኩ ሊያሻሽል ይገባል:: ■ እንደሚታወቀው ከቅርብ ጊዜ ወድህ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው የመብት ጥሰት እንደ አዲስ እያገረሸ ያለ ሲሆን በቅርቡም ሕገ- መንግስታዊ መብት የሆነውን ኒቃብ የትምህርት ሚኒስቴሩ ፕ/ር ብርሐኑ ነጋ የደህንነት ስጋት በማለት በመጥራት በፓርላማ ተናግረዋል:: አያይዘውም ኒቃብ መልበስ ክልክል ነው ብለዋል:: @EHEMSU

የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የነፃነት ትግል እና   መቋጫው 🪴🪴🪴🪴🪴🪴🪴🪻🪻🪻🪻🪻🪻   ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች እስልምና በሀገራችን ከገባበት ግዜ ጀምሮ አሁን እስካለንበት ግዜ ድረስ የነፃነት ትግል እያደረጉ ነው ። እስልምና ምንም እንኳ በሀገራችን ኢትዮጵያ በነብዩ ዘመን የገባ ቢሆንም እንደ እድሜ ጠገብነቱ የሙስሊሞች መብት ግን አልተከበረም ። ከድሮ ጀምሮ ዘርፈ ብዙ ጭቆናዎችን ፣ መገለሎችን ፣ ሰቃዮችን ፣ በደሎችን አስተናግደዋል ። ይሄን በደል ለመጋፈጥ ኢትዮጲያዊያን ሙስሊሞች  በተለያዬ ግዜ በተለያየ መልክ የነጻነት ትግል አድርገዋል ። ከፍተኛ የሆነ ዋጋ እና መስዋእትነት ከፍለዋል ። የትግሉ ውጤትስ  ምን ይመስል ነበር ?? ይቀጥላል .......

ስለ እውነት ••• ለህፃናት የደህንነት ስጋት የሚሆነው ኒቃብ ሳይሆን ••• ኒቃብ የደህንነት ስጋት ነው የሚለው ንግግር እና እሳቤ ነው! @EHEMSU

ከትምህርት ሚኒስቴር ሚንስትሩ ንግግር ••• ስለአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች! ጥያቄ አለን ••• ፍትሕንም እንሻለን!ፕሮፌሰር ብርሐኑ ነጋ "ስለአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች ዝም አላችሁ እንባላለን:: ግን እኛ ዝም አላልንም:: የ12ኛ ክፍል ፈተናን እንዲወስዱ በወቅቱ ከፈተናዎች ኤጀንሲ ጋር በመነጋገር ፎርም እንዲሞሉ አድርገናል:: አሁንም የ12ተኛ ክፍል ፈተናን እንዲወስዱ ይመቻቻል::" ብለዋል::    የአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች ደግሞ ቅፅ የሞላነው በጥር ወር ነው ብለዋል:: ጥር ወር ማለት ሌሎቹ ተማሪዎች ከሞሉበት ጊዜ አልፎ ማለት ነው:: እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ፕሮፌሰሩ ያልተሰራን እንደተሰራ አድርገው ማቅረብ ስለምን አስፈለጋቸው? የሚታዘብ ሕዝብ የሌለ መስሏቸው ነውን?   ከዚያ ባሻገር ደግሞ ተማሪዎች እስካሁን ድረስ ከትምህርት ገበታ ተፈናቅለው ሳለ በምን አግባብ ነው አመቱን ሙሉ ሲማሩ ከቆዩት ጋር እኩል የሚፈተኑት? አንደኛ ደረጃ እስካሁን ወደትምህርት አልተመለሱም:: ሁለተኛ ደረጃ አሁን እንኳ ይግቡና ይማሩ ቢባል ያለምንም ማካካሻና ፍትሕ ከሌሎች ጋር እኩል የሚፈተኑት በምን አግባብ ነው? ከዚህ ውጭ እርሳቸው እንዳሉት ተማሪዎቹን በመቅፀብት ፎርም አስሞልተው ከሆነ ስለምን እስካሁን ሳይናገሩ ቀሩ? ሙስሊሙም ሆነ ፍትሕን የሚሻ ሁሉ ተማሪዎቹ ፎርም እንዲሞሉ በተማሪዎቹ ዙሪያ ትምህርት ሚኒስቴር ያለውን አቋም እንዲያሳውቅ ደጋግመው ሲጠይቁ ስለምን ጆሮ ዳባ ልበስ አሉ? ግልፅነት እና ተጠያቂነት የተቋማቸው እሴት አይደለምን? ወይንስ ሕዝቡ ለእርሳቸው ምንም ነው? ያም ሆነ ይህ እንዲህ አይነት ማስተዛዘኛ አይናችሁን ጋርዱና ልሸውዳችሁ ከማለት አይተናነስም:: ሀላፊነታቸው የሚጠይቀው ፍትሕ ሰፍኖ ተማሪዎቹ እንዲማሩ ማድረግ ••• ይህ እንዲፈጠር ያደረጉ የፖለቲካ ቁማርተኞች እንዲጠየቁ ማስደረግ ብሎም ተጠቂዎቹ የሚገባቸው ካሳ እንዲሰጣቸው ማድረግ ነው:: ይህ እስኪሆን ድረስ ፍትሕ አይሰፍንም ••• ከተጠያቂነትም አያመልጡም! @EHEMSU

በኒቃብ ጉዳይ ኡስታዝ ካሚል እና ኸዲጃ ያሲን በፓርላማ ያነሱት ጥያቄ እና ብርሃኑ ነጋ የሰጡት መልስ! @EHEMSU

AAU ••• 5ኪሎ ጀመዓ ••• የጁሙዓህ ሶላት! ጁምዓ ቀን የትምህርት ሰዓት ከጧት እስከ 5:30 ከሰዓት ደግሞ ከ7:30 ጀምሮ እንዲሆን የሚደነግገው ሕግ እንዲከበር በአአዩሙተህ እና በዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት የተደረሰውን መግባባት ተከትሎ ሕጉ እንዲከበር ለሁሉም ካምፓሶች ኢሜይል እንደተላከላቸው ተገልፇ ነበር:: ይህንንም ተከትሎ እስካሁን ባለው የCommerce ካምፓስ ይፋዊ ማስተካከያ አድርጓል:: በ5ኪሎ ካምፓስ ማስተካከያ አለማድረጉን ተከትሎ የካምፓሱ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ በካምፓሱ ጉዳዩ ከሚመለከተው ዶክተር ሸጋው አህመድ ጋር ውይይት አድርገዋል:: ዶክተሩም ለሁሉም ት/ቤቶች ማስተካከያ እንዲያደርጉ ማሳወቂያ እንደላኩ ጠቅሰው በሚጪው ጊዜ የተስተካከለ ፕሮግራም እንደሚለቀቅ ገልፀዋል:: ■ በጁምዓ ቀን ከ5:30-7:30 ትምህርት እንደሌለ በሕግ የተደነገገ ጉዳይ ነው:: ሁሉም ካምፓስ ሁሉም ዩኒቨርሲቲ ሁሉም ትምህርት ቤት ሊያከብረው ይገባል:: እንዲያከብሩት መጠየቅና እስኪያከብሩ መታገል ደግሞ ግዴታችን ነው:: መብት በትግል እንጅ በልመና አይገኝምና! @EHEMSU

"ከነጻነቱ በላይ ምቾቱን የሚያስቀድም ሕዝብ ምቾቱንም፣ ነጻነቱንም ያጣል!" @EHEMSU

"ህፃናቶች ባሉበት ት/ቤት አንድ ሰው ፊቱን ተሸፍኖ (ኒቃብ ለብሶ) በሚገባ ጊዜ የደህንነት ስጋት አለበት::" - ፕ/ር ብርሐኑ ነጋ ይህ ግልፅ የሆነ ሙስሊም ጠልነትና ስድብ ነው:: በአንድ ሀገር በአንድ ሰፈር በአንድ መንደር ማህበራዊ ህይዎት ሲገፋ የደህንነት ስጋት ያልሆነ አለባበስ ት/ቤት ሲሆን የደህንነት ስጋት የሚሆነው በምን አግባብ ነው? በባንክ ቤት በቴሌ በሆስፒታል ሲለበስ የደህንነት ስጋት ያልሆነ ልብስ በት/ቤት ሲሆን ብቻ የደህንነት ስጋት የሚሆነው በምን አግባብ ነው? ይህ ለጥላቻቸው ያለበሱት ማስክ ነው:: በግልፅ ይንገሩን ••• እንድንማር እንደማይፈልጉ ••• እንድንለወጥ እንደማይፈልጉ ••• እኛም በግልፅ እንነግራቸዋለን ••• ያሉትን ቢሉ እንደምንማር ••• እስከ ክብራችን! @EHEMSU

የሙስሊም ሴቶች የትምህርት ቤት አለባባስ ጉዳይ ግልፅ የሆነ መፍትሄ እንዲሰጠው የፓርላማ አባሉ የተከበሩ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ ጠየቁ! 🔖 የትምህርት ሚኒስቴር በበኩሉ በትምህርት ቤት ኒቃብ ለብሶ መገኘት ፖሊሲው አይፈቅድም ብሏል፡፡ - ሀሩን ሚዲያ፣ ሚያዚያ 7/2017 ትምህርት ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት የ9 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርቱን ለኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ያቀረበ ሲሆን በቦታው የተገኙት የምክር ቤቱ አባል ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ የሙስሊም ሴት ተማሪዎች አለባበስ ጉዳይ መፍትሔ እስካላገኘ ድረስ እኛ መጠየቅ አይሰለቸንም፣ እናንተ ጥያቄው አይሰላቻችሁም ወይ? ሲሉ የምክር ቤት አባሉ የትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቀዋል። መንግስት በህገ መንግስት ላይ፣ በተቀበላቸው በአለም አቀፍ ስምምነቶችም ፍትሃዊ እና አካታች ትምህርት ለሁሉም ዜጎች የማቅረብ ግዴታ እንዳለበት የጠቆሙት የምክር ቤት አባሉ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ ባለፈው በምክር ቤቱ የወጣው የአጠቃላይ ትምህርትም አዋጅም አንቀጽ 8 ላይ በግልጽ የተቀመጠው ትምህርት ከማንኛውም አድልኦ አሰራር የፀዳ መሆን እንዳለበት በግልጽ የደነገገ ነው ብለዋል፡፡ “ይህንን ሲተነትን ደግሞ ብሄርን፣ በሃይማትን፣ ጾታን፣ እድሜን፣ አካል ጉዳተኞችን ወዘተ መሰረት ያደረገ ምንም ዓይነት ልዩነት መኖር የለበትም ይላል” ብለዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ግን በተለያዩ ቦታዎች የትምህርት ዘርፉም ሆነ አገሪቱ ብዙ አጀንዳ እያሏት ለምድነው የአለባበስ ጉዳይ አጀንዳ ሆኖ ሙስሊም ሴት ተማሪዎችን ፈተና በመጣ ቁጥር ጥያቄ የሚሆነው፣ ለምሳሌ በትግራይ ክልል 12ኛ ክፍል እስኪደርሱ ደረስ 12 ዓመታት ሙሉ ዝም ተብሎ የ12ኛ ክፍል ፎርም ለመሙላት ሲሄዱ ፎርም አትሞሉም ሂጃባችሁን ለብሳቹ ነው የተባሉት ይሄ ነገር እስከ መቼ ነው የሚቀጥለው?" ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ ሙስሊም ሴት እኮ ሂጃብ ስትለብስ፣ ኒቃብ ስትለብስ የምትሸፍነው ጸጉሯን እንጂ የውስጥ አይምሯዋን አይደለም ያሉት የምክር ቤት አባሉ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ ለማሳያም ባለፈው ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 3.87 የመጣቸውን ሴት ተማሪ አንስተዋል፡፡ አስተማሪዎችም ተማሪዎችም ሃይማኖት አላቸው፣ ስርዓቱ ነው ሴኩላር። የሙስሊም፣ የኦርቶዶክስ ወይንም የክርስትና እምነት በስርዓተ ትምህርት ውስጥ አይካተትም ማለት እና ተማሪዎችን ሃይማኖታችሁን ተው ማለት ሁለቱ ለየቅል ናቸው ብለዋል፡፡ በአለባበስ ላይ የሚነሱ ጉዳይች ግልጽ መፍትሄ ማግኝት አለባቸው ያሉት የምክር ቤት አባሉ እኛ ጭቆናው እስካልቆመ ድረስ ጥያቄ መጠየቅ እንቀጥላለን ብለዋል። እናንተ ጥያቄው እራሱ አይሰለቻችሁም ወይ?ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ለምን ይሄ ነገር ግልጽ የሆነ አቅጣጫ ተሰጥቶ ዜጎችን ባላገለለ አኳዃን ሴት ተማሪዎች ኒቃባቸውን ሂጃባቸውን እና ለብሰው ሲገቡ የደህንነት ጉዳይ ይነሳል ሴት ፈታሾች ወይንም ጠባቂዎች አስፈላጊ ቦታ ላይ ያንን ማድረግ ይቻላል ለምንድነው ሰፋ አድርገን ማየት ያልተቻለው?" ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ ለጥያቄው ምለሽ የሰጡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ህግ እና ደንቦች በዚህ ጉዳይ ሂጃብ ለብሶ ትምህርት መማርን የሚከለክሉ አይደሉም ኒቃብ ግን አይፈቀድም ብለዋል፡፡ ማንም ሂጃብ ለበሰ ተብሎ ከትምህርት ቤት መከልከል የለበትም ያሉት የትምህርት ሚኒስትሩ ኒቃብ ግን ከዚህ ይለያል ብለዋል፡፡ ህፃናቶች ልጆች ባሉበት ትምህርት ቤት አንድ ሰው ፊቱን ተሸፍኖ በሚገባ ጊዜ የደህንነት ስጋት አለ ሲሉ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል፡፡ © ሀሩን ሚዲያ @EHEMSU

ዛሬ በፓርላማ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ "የኒቃብ ጥያቄ ጥያቄ ሆኖ የሚዘልቀው እስከመች ነው? አይሰለቻችሁም ወይ?" ብለው የጠየቁ ሲሆን የትምህርት ሚኒስቴሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ "ኒቃብን ለብሶ መማር የኢትዮጵያ ሕግ እና ፖሊሲ አይፈቅድም!" ብለዋል:: @EHEMSU

ከጁሙዓ ሶላት ጋር ተያይዞ የፕሮግራም ማስተካከያ እንዲደረግ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በጠየቀው መሠረት በAAU School of commerce ማስተካከያ ተደርጓል:: በካምፓሱ
ከጁሙዓ ሶላት ጋር ተያይዞ የፕሮግራም ማስተካከያ እንዲደረግ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በጠየቀው መሠረት በAAU School of commerce ማስተካከያ ተደርጓል:: በካምፓሱ የት/ክ/ጊዜ ከጧት እስከ 5:30 የሚቆይ ሲሆን ከሰዓት ደግሞ 7:30 የሚጀምር ይሆናል:: ጥሩ ጅማሮ ነው ••• ሁሉም ካምፓስ ••• ሁሉም ዩኒቨርሲቲ ••• ከKG ጀምሮም ያሉ ትምህርት ቤቶች ሁሉ መሠል አርዓያነትን ሊከተሉ ይገባል:: ጁምዓ ቀን በሕግ እንደፀናው የትኛውም የመንግስት እንቅስቃሴ ከጧት እስከ 5:30 ሲሆን ከሰዓት ደግሞ ከ7:30 ጀምሮ ነው:: ይህንን መተላለፍ የሙስሊም ተማሪዎችን መብት ከመጣስ ባሻገር ሕግንም መተላለፍ ነው:: @EHEMSU

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ዩኒቨርሲቲው ከጁምዓ ሶላት ጋር ተያይዞ የሚወጡ ፕሮግራሞች ላይ የሙስሊም ተማሪዎችን መብት በሚጥሱ መልኩ ማውጣቱን ተከትሎ እንዲያስተካክል የሳምንት
+3
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ዩኒቨርሲቲው ከጁምዓ ሶላት ጋር ተያይዞ የሚወጡ ፕሮግራሞች ላይ የሙስሊም ተማሪዎችን መብት በሚጥሱ መልኩ ማውጣቱን ተከትሎ እንዲያስተካክል የሳምንት ቀነ- ገደብ መስጠቱን ተከትሎ የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ም/ፕሬዚዳንት ለኮሌጅ ዲኖች ማስተካከያ እንዲያደርጉ በኢሜይል አሳውቋል! እንደሚታወቀው በጁምዓ ቀን የትምህርት ተቋማትም ሆኑ የትኛውም የመንግስት ተቋማት የስራ ሰዓታቸው ከጧት እስከ 5:30 ሲሆን ከሰዓት ደግሞ ከ7:30 ጀምሮ ነው:: ሆኖም የትምህርት ተቋማትና አየር መንገድ በተደጋጋሚ ጥሰት ሲፈፅሙ ተስተውሏል::

የህዝብ ተወካይ ካሉ እንዲህ ነው ••• ወ/ሮ ኸዲጃ! ወ/ሮ ኸዲጃ በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈጉባዔን ተከራክራ የሙስሊም ተማሪዎችን ጥያቄ አቅርባለች:: "የሙስሊሙ በዓል በደረሰ ቁጥር ትምህርት ሚኒስቴር ፈተና በበዓል ቀን የሚያወጣው ለምንድን ነው?" ብላ ጠይቃለች:: ደጋግመው የሚሰሩትን ስህተት እስኪስተካከሉ ድረስ በአደባባይ ደጋግሞ መጠየቅ ያሻል ••• ጀግኒት! @EHEMSU

ከኢፍጣር መልስ ••• ከዒድ ማግስት ___ ዩኒቨርሲቲዎች! • ብዙ ዩኒቨርሲቲዎች በረመዳን የኢፍጣር ድግስ አሰናድተዋል:: ሙስሊም ተማሪዎች ከኢፍጣር ጋር በግቢ ውስጥ በጀመዓ በአደባባይ ሰግደዋል::
ከኢፍጣር መልስ ••• ከዒድ ማግስት ___ ዩኒቨርሲቲዎች! • ብዙ ዩኒቨርሲቲዎች በረመዳን የኢፍጣር ድግስ አሰናድተዋል:: ሙስሊም ተማሪዎች ከኢፍጣር ጋር በግቢ ውስጥ በጀመዓ በአደባባይ ሰግደዋል:: ሶላት ስለማያልፍ ሰው እያለም ለግል መስገዱ ክልክል ስለሆነ በጀመዓ ሰግደዋል:: ለምን በጀመዓ ሰገዳችሁ ብሎ የከለከላቸውም አልነበረም:: ለመከልከልም የተክለፈለፈ አልነበረም:: ይልቁኑም ዩኒቨርሲቲዎቹ ፎቶ ለማንሳት ተጣድፈው የተነሳውንም በይፋ ለሕዝብ ለቀዋል:: በዚያ ውስጥ የተረበሸም ሆነ መብቱ የተነካበት የዩኒቨርሲቲው የማህበረሰብ ክፍል የለም:: • ከሶላት ባሻገር ሁሉም ሙስሊም ለኢፍጣሩ ሐይማኖቱ ያዘዘውንና እርሱ ይሆነኛል ብሎ የለበሰውን አለባበስ ለብሶ ነው የተሰለፈው:: አለባበሱ የነካው ግለሰብም ሆነ ያጎደለው እሴት የለም:: ይልቁኑም የሙስሊም ተማሪዎችን እሴት አክብሮ ለዩኒቨርሲቲው ተጨማሪ ውበት ሆኗል:: • በዒድም ላይ የተስተዋለው ተመሳሳይ ነገር ነው:: ■ ከኢፍጣር መልስ _ ከዒድ ማግስት ያለውን ስናይ ግን አሁንም ድረስ ሶላት እና ኒቃብ ላይ ችግር ያለባቸው ዩኒቨርሲቲዎች አሉ:: አሁንም ድረስ የጀመዓ ሶላትን በመመሪያ የሚከለክሉ ኒቃብንም የሚከለክሉ ግቢዎች አሉ:: ቢቻል በረመዷኑ በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች የታየውን መከባበር አይተው ቢያከብሩ ጥሩ ነው:: ካልሆነ ደግሞ ሙስሊሙ ተማሪ በፍትሕ እና እውነት ላይ ቆሞ ፍትሕ እስኪሰፍን ሊጠይቅ እና ሊታገል ይገባል:: @EHEMSU