cheffie primary school 2013
Open in Telegram
260
Subscribers
No data24 hours
+47 days
+930 days
Posts Archive
#የ6ኛ እና #8ኛ ክፍል ደረጃ የተማሪዎች ጥያቄ እና መልስ ውድድር ተደረገ
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 አስተዳደር ትምህርት ፅ/ቤት የ2017 ትምህርት ዘመን በሁለቱም ስርዓተ ትምህርት #የ6ኛ እና #8ኛ ክፍል ደረጃ የተማሪዎች ጥያቄ እና መልስ ውድድር አደረገ።
የወረዳው የትምህርት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ታደለ ዱሬሳ እንደተናገሩት ውድድሩ በአስተዳደራችን ተገድቦ የሚቆም ብቻ ሳይሆን በክፍለ ከተማ ደረጃ እንደሚከናወን በመጠቆም በጥያቄና መልስ ውድድሩ አሸናፊዎቹ ተማሪዎች ብቻ ሳይሆኑ መምህራን እና ወላጅም ጭምር እንደሆኑ አስረድተዋል።
በየክፍል ደረጃ እና ትምህርት ቤት ደረጃ ከ1ኛ-3ኛ የወጡትን ተማሪዎችን እና ትምህርት ቤቶችን በመሸለም ውድድሩን ተጠናቋል።
በትምህርት ቤት ደረጃ 1ኛ ጨፌ 2ኛ ምስራቅ 3ኛ ማሪዞና በመውጣት የዋንጫ እና የሰርተፊኬት ተሸላሚ ሆነዋል።
በ8 ክፍል 1ኛ ዲቦራ ወርቅነህ 2ኛ ሱመያ መሀመድ 3ኛ ሀናን ሙስጠፋ
በ6 ክፍል በአፋን ኦሮሞ 1ኛ ዮናስ ደኑ
2ኛ ሀብታሙ ደኑ 3ኛ ሴና ባለሚ
በ6 ክፍል አማርኛ 1ኛ ኬናን ጭንዲ
2ኛ ኤልዳና እንዳሻው 3ኛ ሀበን ፍቃዱ በመሆን አሸናፊ ሆነዋል።
ለሚ ኩራ ወረዳ 03 ኮሙኒኬሽን
ታህሳስ 8/2017 ዓ/ም
+6
ቀን 05/04/2017ዓ.ም
በጨፌ ቅድመ አንደኛ, አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከተማሪ ወላጆች ጋር ውይይት ተደረገ።
የውይይቱ አጀንዳዎች
1:- የሒሳብ እና እንግሊዝኛ ትምህርት የአንደኛ ዙር አጋማሽ ፈተና ውጤት ትንተና ቀርቧል።
2. እየተሰጠ ያለውን ማጠናከሪያ ትምህርት ትምህርት እያመጣ ያለውን ለውጥ መገምገም
3. የአራትዮሽ ስምምነት ያለበትን ደረጃ መገምገም ናቸው።
በውይይቱ ላይ የወረዳ 03 ትምህርት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ታደለ ዱሬሳ ተገኝተው የእንግሊዝኛ እና የሒሳብ ትምህርት የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት የጋራ ርብርብ ማድረግ አለባቸው ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ሃላፊው አክለውም በስነምግባር የታነፀ ተማሪ በውጤቱም የተሻለ ይሆናል በማለት ወላጆች የልጆቻቸው የስነ ምግባር ሁኔታ መከታተል እንዳለባቸውም አሳስበዋል።
በውይይቱ ላይ ከወላጆችም ጥያቄዎች እና አሰተያየት ተነስተው
ርዕሰ መምህርት ኤልሳቤጥ አማካኝነት ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።
Liul Abat:
ቀን-12/03/2017ዓ.ም
ለጨፌ ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በሙሉ
የ2017ዓ.ም የትም/ዘመን የ1ኛው ወሰነ ትምህርት አጋማሽ ፈተና የሚሰጠው ከህዳር 18-20/03/2017ዓ.ም መሆኑን እያሳወቅን ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።
ት/ቤቱ!
Guyyaa 12/03/2017
Barattoota mana barumsaa caffee sadarkaa 1 ffaa duraa, sadarkaa 1 ffaa fi giddu-galeessaa hundaaf.
Bara barnootaa 2017 qormaatni walakkeessa nuusa waggaa sadaasa 18-20/03/2017 waan kennamuuf amma irraa jalqabuun qophii barbaachisu akka taasistan isin yaadachiisna.
Mana barumsaa irraa.
Repost from N/a
አለም አቀፍ የህፃናት ቀን በጨፌ ትምህርት ቤት ውስጥ
ህፃናት የሚሉት አላቸው እንስማቸው በሚል መሪ ቃል ተከበሯል።
