Wolkite University Muslim students jeme'a official channel
Open in Telegram
ይህ ቻናል ትክክለኛው የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሲሆን፣ በቻናሉም፦ ➲ ሙስሊም ተማሪዎችን የተመለከቱ መረጃዎች ➲ በዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች መስጂድ ስለሚደረጉ ሀይማኖታዊ እንቅስቃሴዎች ለምሳሌ ➩ የዳዕዋ ፕሮግራም ➪ የቂርአት እንቅስቃሴ ➪ ሌሎችም ዝግጅቶች ሲኖሩ የሚለቀቁ ይሆናል በአላህ ፍቃድ። @Wku_ibnuabbas_bot https://t.me/Wku_ms_Official_Channel
Show more5 530
Subscribers
-124 hours
-277 days
-11630 days
Posts Archive
በአላህ ፍቃድ በኢብኑ ዐባስ በ2019 በ1st semester የሚሰጡ ዱሩሶች።
ዐቂዳ
- ኪታቡ ተውሂድ (የሸይኽ ሷሊህ አል-ፈውዛን)
- ሚን ኡሱሊ ዐቂደቲ አሕሊ-ሱነቲ ወል-ጀመዐህ (የሸይኽ ሷሊህ አል-ፈውዛን)
ፊቅሕ
- መንሓጁ ሳሊኪን የሸይኽ ዐብዱራህማን አስ-ሲዕዲይ (ሰዕዲይ)
አዳብ
- አድ-ዳእ ወድ-ደዋእ (ኢብኑል ቀይም)
ሌሎችም አሉ።
ማንኛውም አይነት ከሸሪዓ ጋር የማይጋጩ የስራ ማስታወቂያዎችን በአንድ ፕላትፎርም ላይ ማግኘት ከፈለጉ Halal Jobsን ይቀላቀሉ!
አዲስ ስራ ለሚፈልጉ፣ ስራ መቀየር ላሰቡና የተሻለ የስራ አማራጭ ለሚፈልጉ ሐላል ጆብስ ቤታቸው ነው። እንዲሁም ቀጣሪዎች የስራ ማስታወቂያቸውን በነፃ እንዲለቁበት በማሰብ የተዘጋጀ ፕላትፎርም ነው!
ይወዳጁን! ይከታተሉን! ወዳጅዎንም ይጋብዙ! ያተርፉበታል!
ቻናል👉 https://t.me/+TkaBJvWQ8PAxMmY8
Aselamualeykum Werahmetulahi weberekatuh
በአሏህ ፍቃድ ካሸነፍኩኝ ብሩ ምንም ሳይቀነስበት ለኢብኑ አባስ መስጅዳችን ገቢ አደርገዋለሁ
እና እናንተም የአጅሩ ተካፋይ እንድትሆኑ linku በመንካት join እንድትሉና ለሌሎችም share እንድታደርጉ በትህትና እጠይቃቹሀለሁ!
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
📢 ልዩ የቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም!
❝ሰይድ ቁጥብ ማን ነው? ለተሳሳቱ ውዳሴዎችና ማደናገሪያዎች የሚሰጥ ምላሽ❞
🎙 አቅራቢ፦ ኢብኑ ሙነወር
🗓 ቀን፦ ነገ ማክሰኞ
⏰ ሰዓት፦ ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ
◇ የቀጥታ ስርጭት አድራሻ👇
t.me/IbnuMunewor
t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
"በሰሞኑ የሰይዪድ ቁጥብ ጉዳይ ከተመቸኝ ዛሬ ከመግሪብ በኋላ በድምፅ ለመግባት አስቤያለሁ" ብዬ ነበር። አሁን ላይ ስላልቻልኩኝ ከቻልኩ ምሽት 3:00 ላይ በቴሌግራም ቻናሌ ( https://t.me/IbnuMunewor ) በቀጥታ (live) ለማቅረብ እሞክራለሁ ኢንሻ አላህ።
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የ “ዘመን መለወጫ” ኮተቶች
~
ኢትዮጵያ በምትከተለው ክርስቲያናዊው የዘመን አቆጣጠር መሰረት አዲስ አመት ሊገባ የያዝነው አመት እየተጠናቀቀ ነው። በያመቱ በዚህ ሰሞን የሚፈፀሙ ከሃይማኖታችን ጋር የማይሄዱ በርካታ ነገሮ አሉ። ከነዚህም ውስጥ:-
1. ድግምትና ጥንቆላ፦
በሃገራችን የተለያዩ አካባቢዎች ነሐሴ ሊጠናቀቅ ሲል በየጠንቋዩ ቤት የሚልከሰከሱት ብዙ ናቸው። ከዚያም አምስቱ ወይም ስድስቱ የጳጉሜ ቀናት መንገዶች በድግምት ስራዎች ይሞላሉ። በነዚህ ቀናት ማልዶ የወጣ ሰው እንዲረግጣቸው/ እንዲራመዳቸው ታስቦ በጎረቤት መተላለፊያ እና ህዝብ በሚያዘወትራቸው መንገዶች ላይ የሞቱ ፍየሎች፣ ዶሮዎች፣ ድመቶች፣ ጥንቸሎች ወዘተ ታርደው ይጣላሉ። በደም የተነከሩ ሳንቲሞች፣ ብሮች፣ ጌጣ ጌጦች፣ የተለያዩ ቁሳቁሶች እዚህም እዚያም ወድቀው ይታያሉ።
* ጥንቆላና ድግምት ከኢስላም የሚያስወጡ ከባባድ ወንጀሎች ናቸው፡፡
وَاتَّبَعُوا مَا تَتْلُو الشَّيَاطِينُ عَلَى مُلْكِ سُلَيْمَانَ وَمَا كَفَرَ سُلَيْمَانُ وَلَكِنَّ الشَّيَاطِينَ كَفَرُوا يُعَلِّمُونَ النَّاسَ السِّحْرَ
“በሱለይማን ዘመነ-መንግስት ሸይ ^ጧኖች የሚያነቡትንም (ድግምት) ተከተሉ። ሱለይማን ግን አልካደም (ድግምተኛ አልነበረምና።) ግና ሸይ^ጧኖች ሰዎችን ድግምት የሚያስተምሩ ሲሆኑ ካዱ።” [አል-በቀራህ፡ 102]
ነብዩም ﷺ {ጠንቋይ ዘንድ ሄዶ በሚናገረው ያመነ፣ በሙሐመድ ላይ በወረደው ክዷል} ብለዋል። [አስ-ሶሒሐህ፡ 3387]
* ደጋሚዎችና ከነሱ ዘንድ የሚመላለሱ ሰዎች መቼም ቢሆን ስኬት የላቸውም። ጌታችን “ድግምተኛም በመጣበት ስፍራ ሁሉ አይቀናውም” ብሏል። [ጦሃ፡ 69]
* ጠንቋይና ደጋሚ ዘንድ የሚሄድ ሰው የተነገረውን ባያምን እንኳን ከባድ ቅጣት ይከተለዋል። ነብዩ ﷺ {ጠንቋይ ዘንድ ሄዶ ስለሆነ ነገር የጠየቀው የአርባ ቀን ሶላቱ ተቀባይነት የለውም} ብለዋል። [ሙስሊም፡ 5957]
2. ሎሚ መምጠጥ እና ፌጦ መብላት:-
በአንዳንድ አካባቢዎች ከድግምትና ጥንቆላ ለመጠበቅ በማሰብ ወላጆች ልጆቻቸውን ጳጉሜ ላይ ሎሚና ፌጦ ይመግባሉ። ድግምትና ጥንቆላ ሸይ^ ጧናዊ ተግባራት ናቸው። መጥጠበቂያ መንገዶቹ አዝካር፣ አየቱል ኩርሲይ፣ ሱረቱል ኢኽላስን (ቁል ሁወላሁ አሐድ)፣ ሙዐዊዘተይን (ቁል አዑዙ ቢረቢል ፈለቅ፣ ቁል አዑዙ ቢረቢናስ) ከሶላት በኋላ እና ጧትና ማታ መቅራት፣ እንዲሁም ከሱረቱል በቀራ የመጨረሻዎቹን ሁለት አንቀፆች መቅራት፣ ሩቅያ ማድረግ ናቸው። አጉል እምነት ላይ የተመሰረቱ ሰበቦችን መጠቀም ከሺርክ ነው።
በተረፈ የተጣለ የድግምት ስራ ቢያጋጥመን ምንም መደናገጥ አያስፈልግም። በአላህ ላይ ጠንካራ እምነት ማሳደር (ተወኩል) ቀዳሚው መከላከያ መንገድ ነው። አጉል መጨናነቅ ለችግር ይዳርጋል። ከዚያም የድግምት ስራውን ሙዐዊዘተይን በመቅራት ማስወገድ ነው (ማቃጠል፣ መቆራረጥ ወይም ቆፍሮ መቅበር)።
3. የጳጉሜ ዱዓእ የሚል ቢድዐ:-
በአንዳንድ አካባቢዎች የጳጉሜ ዱዓእ “መቅቡል ነው” (ተቀባይነት ያለው ነው) የሚል እምነት አለ። ይሄ አጉል እምነት ነው። በጣም የሚገርመው ለዱዓእ የሚጣዱት እስልምናን ያውቃሉ ሰዎችን ያስተምራሉ የሚባሉት ሰዎች መሆናቸው ነው። ነብዩ ﷺ “አላህ እውቀትን ከባሪያዎቹ መንጠቅን አይነጥቅም። ይልቁንም ዑለማዎችን በመውሰድ (በመግደል) እውቀትን ይወስዳል። ከዚያም ዓሊም እስከማይቀር ድረስ። በዚያኔ ሰዎች መሀይማንን መሪዎች አድርገው ይይዛሉ። ሲጠየቁም ያለ እውቀት ፈትዋ ይሰጣሉ። በዚህም ይጠማሉ፣ ያጠማሉም” ብለዋል። [ሶሒሕ አልቡኻሪይ፡ 100] [ሶሒሕ ሙስሊም፡ 2673]
4. የጳጉሜ ጸበል (ጥምቀት)፦
ጳጉሜ 3 ቀን በኦርቶዶክስ ክርስትና የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ በዓል ነው ይላሉ። በዚህ ዕለት "የሰማይ ደጆች ይከፈታሉ፣ ዝናቡም የበረከትና የፈውስ ውሃ ሆኖ ይወርዳል" ተብሎ ይታመናል። በዚህም የተነሳ ሕዝቡ ሕፃናትን ጨምሮ ከሰማይ የሚወርደውን ዝናብ (የጳጉሜን ዝናብ) እንደ ጸበል በመቁጠር ሰውነታቸውን ይጠመቁበታል። ሙስሊሞች ከንደዚህ ዓይነት እምነቶችና ተግባራት ሊርቁ ይገባል።
5. እንቁጣጣሽ ማክበር:-
ሌላኛው የ “ዘመን መለወጫን” ተከትሎ የሚፈፀመው ጥፋት መስከረም አንድን ወይም እንቁጣጣሽን ማክበር ነው። ዕለቱ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነት መሠረት "ቅዱስ ዮሐንስ" በመባል የሚጠራ ሲሆን፣ የመጥምቁ ዮሐንስ መታሰቢያ እና የቅዱሳን አበው መታሰቢያ ይደረግበታል። በቤተክርስቲያን ደረጃ የማህሌት፣ የቅዳሴ እና የምስጋና ሥርዓት ይፈጸምበታል።
በተጨማሪም የበዓሉ ስም (እንቁጣጣሽ የሚለው) ከንግሥተ ሳባ እና ከንጉሥ ሰሎሞን አፈ ታሪክ ጋር ይያያዛል። ንግሥተ ሳባ ከኢየሩሳሌም ስትመለስ መኳንንቶቿ "እንቁ ለጣጣሽ" (ለጌጥሽ ይሁን) በማለት በዕንቁ ስለተቀበሏት ይህ ስም እንደወጣ ይነገራል።
አቆጣጠሩ ሀገራዊ እንጂ እምነታዊ መሰረት እንደሌለው ሊያሳምኑ የሚሞክሩ ሰዎች አሉ። ነገሩ ግልፅ ቢሆንም ድንገት የሚሰወራቸው ካሉ ለማስታወስ ያህል:-
* አቆጣጠሩ ከግብፅ ኮፕቲክ ቤተክርስቲያን የተቀዳ ነው።
* አመቱ ሲፃፍ መጨረሻ ላይ “ዓመተ ምህረት” የሚባለውም ክርስቲያናዊ ስለሆነ ነው።
* የነብዩ ዒሳን (ሰላም በሳቸው ላይ ይስፈንና) መወለድ መሰረት ያደረገ እንደሆነ የሚታመን ነው።
* በእለቱም የሚፈፀሙት የተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓቶችም በዓሉ ክርስቲያናዊ እንደሆነ በሚገባ አጉልተው ያሳያሉ፦
- የዋዜማ ጸሎትና ማኅሌት፦ በበዓሉ ዋዜማ (ጳጉሜን 5 ወይም 6) ሌሊቱን ሙሉ በቤተክርስቲያን ልዩ የቅዱስ ዮሐንስ ማኅሌትና ጸሎት ይቆማል።
- የቅዳሴ ሥነ-ሥርዓት፦ በዕለቱ ጠዋት ምዕመናን አዲስ ልብስ ለብሰው ወደ ቤተክርስቲያን በመሄድ በቅዳሴና በዕለቱ ትምህርተ ወንጌል ላይ ይሳተፋሉ።
- ዘመነ ዮሐንስን መቀበል፦ በቤተክርስቲያን ዘመን መለወጫን አስመልክቶ ልዩ ጸሎት ይደረጋል፤ የወንጌላዊው ዘመንም (ዘመነ ማቴዎስ፣ ማርቆስ፣ ሉቃስ ወይም ዮሐንስ) ይታወጃል። “እንኳን ከዘመነ ማቲዎስ ወደ ዘመነ ማርቆስ፣ ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ፣ ... አደረሳችሁ” ማለታቸው አቆጣጠሩና በዓሉ ሃይማኖታዊ መሆናቸውን አጉልተው የሚያሳዩ ነጥቦች ናቸው፡፡
ይህንን ስንል የሚጎረብጣቸው አሉ። እኛ'ኮ የኛን ዒድ አብራችሁን ካላከበራችሁ አላልንም። ይልቁንም የኛን እምነታዊ መገለጫ ካላንፀባረቃችሁ ብሎ ሌሎችን መወረፍ አክራሪነት ነው። እምነታችን የሌሎች ህዝቦች #መለያ በሆኑ እምነቶችና ልማዶች መመሳሰልን አይፈቅድም። ነብያችን ﷺ “በሰዎች የተመሳሰለ ከነሱው ነው” ብለዋል።
(ኢብኑ ሙነወር፣ 18/11/1436)
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from N/a
የ "አንብብ" ከዋሻው መውጣት ሲደንቀኝ ከዋሻው ያልወጡ ትውልዶች መምጣት ይናፍቀኛል
በሚል መሪ ቃል
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
በኢትዮጲያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው
ጛሩ ሒራ አለም አቀፍ የንባብ ወድድር ተጀመረ
➖➖➖➖➖➖➖➖➖
ቢሮአችን አዲስ አበባ አብነት አካባቢ የሚገኝ ሲሆን ማንኛውንም ጥያቄ በአካል በመምጣጥ መስተናገድ ይችላሉ ፣ ሙሉ መረጃውን እና የምዝገባ ሂደቱን በዌብሳይታችን (sulmahira.et) ላይ ማግኘት ይቻላል። ስለዚህ ምንም አይነት ጥርጣሬ ሳይኖራችሁ መመዝገብ እና መሳተፍ ትችላላቹ
ለመጀመሪያ ዙር ንባብ ውድድሩ የተመረጠው የኢማም ሙሐመድ ቢን ዓብዱልወሃብ የሕይወት ታሪክ መፅሐፍ አለም አቀፍ ተደራሽ አንዲሆን ለተወዳዳሪ ምቹ በሆነ መልኩ በ አፕልኬሽን ተሰርቶ።
የምዝገባ ሂደቱ የተጀመረ ሲሆን
💸በ499 ብር ብቻ………▶️ መፅሐፉን ያውርዱ ▶️ የንባብ ውድድሩን ይመዝገቡ ▶️ የማጠቃለያ ሽልማትና የመጽሐፍ ዳሰሳ • ፕሮግራም ትኬት ይቁረጡ ➡️ለ1 ወር ያህል በእርጋታ ያንብቡ ከመፅሐፉ የተዘጋጁ ጥያቄዎችን በመፈተን ይወዳደሩ ➡️ጛሩ ሒራ የንባብ ውድድር ያዘጋጀው ልዩ ልዩ ስጦታዎች ይሸለሙ ! 1️⃣ኛ ለወጣ የቤተሰብ ዑምራ🕋 2️⃣ኛ iphone 13 promax 🎒 3️⃣ኛ Brand ላፕቶፕ (PC) 💻 ከ4️⃣ኛ–1️⃣0️⃣ኛ ለሚወጡ ልዩ ልዩ ሽልማቶች!
⬇️ለመመዝገብ⬇️🌐https://sulmahira.et/register?ref=011 ❤️በቴሌግራም ቦት ለመመዝገብ = https://t.me/gharuhirabot?start=ref=011 ደውለው መመዝገብ ይችላሉ። 🌟0946248626 🌟0942189967 የቴሌግራም አድራሻ👇 https://t.me/sulmahira
Repost from ትዳር እና ኢስላም 🌷🌹🥀
✔️በዚህ ክረምት ነፃ የቋንቋ እድል
የምታገኙበት ቻሌጅ ልጠቁማችሁ
1️⃣ኛ ለወጣ ነፃ የቋንቋ ስልጠና እና ብር 1500
2️⃣ኛ ለወጣ ነፃ የቋንቋ ስልጠና እና ብር 1000
3️⃣ኛ ለወጣ ነፃ የቋንቋ ስልጠና እና ብር 500
🏪ቻሌንጁ ለመሳተፍ ሙሉ ማብራሪያ🔣
https://t.me/Ihsan_language/315
https://t.me/Ihsan_language/315
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
"የ19 ዓመት የዩንቨርስቲ ተማሪ ወደ ህክምና ማዕከል በሄደችበት ማደንዘዣ በመውጋት አስገድዶ መድፈር የፈፀመው ዶ/ር በ21 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ" የሚል ዜና አየሁኝ።
"በሃኪም እንዴት ይሄ ይፈጸማል?" ማለት ሞኝነት ነው። በሃኪም ቀርቶ በሃይማኖት አስተማሪም ይፈጸማል። መፍትሄው አጭርና ቀላል ነው። ማንኛዋም ሴት ከባዳ ወንድ ጋር ተገልላ ልትገኝ አይገባትም። ነብያችን ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
لا يخلوَنَّ رجلٌ بامرأةٍ فإنَّ الشيطانَ ثالثُهما
"አንድ ወንድ ከባዕድ ሴት ጋር ብቻውን አይነጠል፤ ምክንያቱም ሶስተኛቸው ሸይ^ጧን ነውና።" [ቲርሚዚይ፡ 2165]
"ሶስተኛቸው ሸይ^ጧን ነው" የሚለው አጉል መልካም እምነት እንዳያዘናጋን ጥብቅ ማሳሰቢያ ነው። ስለዚህ ያልታሰበ ከባድ ጥፋት የመድረስ እድሉ ከፍተኛ ነው ማለት ነው።
ህክምናን በተመለከተ ሴቶች አማራጭ ካለ በሴቶች ታከሙ። አስገዳጅ ሁኔታ ከገጠመ ከቤተሰብ ጋር እንጂ ብቻችሁን ወንድ ሃኪም ዘንድ አትግቡ። ወይም ሴቶች ነርሶች ካጠገባችሁ እንዲሆኑ አናግሩ። እዚህ ላይ "ውጭ ቆዩ" የሚሉ ሃኪሞች ይኖራሉ። (መግቢያየ ላይ የጠቀስኩትም ክስተት በዚህ መልኩ የተፈፀመ ነው።) እንዲህ አይነት ሃኪም ሲገጥመን ቢቻል ማስረዳት፣ ካልሆነ መጋፈጥ ይገባል። ፈቃደኛ የማይሆኑ ሃኪሞችና ሃኪም ቤቶች ዘንድ አትሂዱ። ቆራጥ ከሆንን ለራሳቸው ሲሉ ያስተካክላሉ።
ለሃኪሞች ማሳሰቢያ፦
ከባዳ ሴት ጋር ተገልሎ መቆየት እንደማይቻል አትዘንጉ። ስለዚህ ስታክሙ ቤተሰብ በቅርብ እንዲኖር አድርጉ። ወይም ረዳቶች ባቅራቢያችሁ ይኑሩ። አስገዳጅ ሁኔታ ከገጠማችሁ የምትሰሩበትን ክፍል በሩን ክፍት አድርጉት።
በነገራችን ላይ እንኳን ባዳ የሆነ አካል በቤተሰብ መሀል ራሱ መጥፎ ነገር ሊከሰት ይችላል። ለዚያም ነው ኢስላም በዚህ ጉዳይ ላይ ጥብቅ መመሪያ ያስቀመጠው። ነብያችን ﷺ ልጆችን አስር አመት ሲሆናቸው መኝታቸውን ለያዩዋቸው ብለዋል። ለአስር ዓመት ልጆች! ስለዚህ ቤተሰብ አላህ ባገራለት ልክ መኝታቸውን ሊለያያቸው ይገባል። ሁሉም አንድ ክፍል ውስጥ የሚተኙ ከሆነ ሴቶችን አንድ ጥግ፣ ወንዶችን ደግሞ ሌላ ጥግ ማድረግ ይገባል። በቂ ክፍሎች ካሉ ሴቶችን የብቻ አንድ ክፍል፣ ወንዶችን የብቻ ሌላ ክፍል ማድረግ ይገባል። ከተቻለ ወንዶችን ከወንዶች፣ ሴቶችንም ከሴቶች ፍራሻቸው ቢለያይ ጥሩ ነው።
አጉል መልካም ግምት ሊያዘናጋን አይገባም። "የዘመድ ልጅ ነው"፣ "ቤተሰብ ነው"፣ "ሸይኽ/ ኡስታዝ ነው"፣ "የጎረቤት ልጅ ነው"፣ "እንግዳ ነው"፣ "ስርአት ያለው ጨዋ ልጅ ነው"፣ "ትልቅ ሰው ነው"፣ የመሳሰሉ የዋህ ድምዳሜዎች ከባድ ዋጋ ያስከፍላሉ። እንኳን ሴቶችን ከወንድ፣ ወንዶችን ከወንድም መኝታቸውን መለየት ይገባል። ሌላው ቀርቶ አባት ወይም ወንድም ቢሆኑ እንኳ ጥሩ ያልሆነ አዝማሚያ የሚያሳዩ ከሆነ የሚቻለውን ሁሉ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿إنَّ مِن أفضَلِ أيّامِكم يومَ الجُمعةِ، فأكْثِروا عليَّ الصلاةَ فيه؛ فإنَّ صلاتَكم مَعروضةٌ عليَّ.﴾
“ከቀናችሁ ሁሉ በላጩ የጁምዓ ቀን ነው። በዚህ ቀን በኔ ላይ ሰለዋት ማውረድ አብዙ። ሰለዋታችሁ ለኔ ይቀርብልኛልና።”
አቡ ዳውድ ሶሂህ ብለውታል: 1531
የሰለዋቱ ሁኔታ
«اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ،
كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ،
اللَّهُمَّ بَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ،
كَمَا بَارَكْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ
ነሕውን ከዘዋጅ ጋር የሚያያይዝ አባባል፦
"present form of a verb በመርፉዕነት፣በመንሱብነት እና በመጅዙምነት መካከል በነፃነት እና ያለ ገደብ እድሜውን ያሳልፋል(ላጤ)::አንስታይ ፆታ አመልካች 'ن' እስክትቀጠልበት:(ስትቀጠልበት)በስኩን ይገነባል"-ይረጋጋል።
አንዱ ይህንን አባባል ሲሰማ "አላህ ሆይ፥ይህችን 'ن' ከጎኔ አድርግልኝ"ብሎ ዱዓ አድርጓል።
🎉الْحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي بِنِعْمَتِهِ تَتِمُّ الصَّالِحَاتُ
✨አልሃምዱሊላህ!
✨አልሃምዱሊላህ!
✨አልሃምዱሊላህ!
«ድብቁ ገዳይ እና የተስፋው ጋሻ»!
~ ተለቀቀ~
ሰው ነኝና ከስህተት ከጥፋት አልጠራም
እርምት እና አስተያየት ካላችሁ
በዚህ ንገሩኝ @Abu_Hulud22
ሚስኪኑ ወንድማችሁ ⎛አቡ ሑሉድ.⎫
Repost from ትዳር እና ኢስላም 🌷🌹🥀
😵🤔🙁😝😤☹️🙁☹️
🛜የመጀመሪያው ፕሮግራማችን ▶️
🙁☹️😭🙁😭🙁☹️🙁
🎤ስለ ሒጃብ ግዴታነት
ተ🎁
ጀ▶️
መ ▶️
ረ▶️
➡️አቡ ሂበቲላህ ሁሰይን ✅
ገባ ገባ በሉ ባረከሏሁ ፊኩም! ‼
➘ ➘ ➘ ➘➘ ➘ ➘ ➘ ➘ ➘ ➘
t.me/tdarna_islam?livestream
t.me/tdarna_islam?livestream
Repost from ትዳር እና ኢስላም 🌷🌹🥀
🙁🙁🙁🙁🙁🙁☹️🥳
😃ታላቅ የደዕዋና የቁርአን ኸትሚያ ፕሮግራም ⭐️
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
🌿 የእህታችን ኡሙ አብዱል ወሃብ የቁርአን ኽትሚያ በማስመልከት የተዘጋጄ ደማቅ የደዕዋ ፕሮግራም
⭐️ የሚጋበዙ ኡስታዞቻችን ⭐️
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
✅ ሸይኽ ሁሴን አቡ ሀኒፋ (ሀፊዘሁሏህ
✅ ሸይኽ አቡ ፋጢማ(ሀፊዘሁሏህ
✅ ኡስታዝ አቡ ሀኒፋ ሀፊዘሁሏህ
✅ ኡስታዝ አቡ ሻኪራ ሀፊዘሁሏህ
✅ ኡስታዝ አቡ ኸውላ ሀፊዘሁሏህ
✅ ኡስታዝ አቡ ሙሀመድ ሀፊዘሁሏህ
✅ወንድም አቡ ሂበቲላህ ሀፊዘሁሏህ
✅ወንድም አቡ ሹራ ሀፊዘሁሏህ
✅ወንድም ኑረዲን አቡፋሩቅ ሀፊዘሁሏህ
📖 የቁርአን ቲላዋ የሚጋብዙን
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
⭐️ ወንድም አቡ ኢምራን ሀፊዘሁሏህ
⭐️ ወንድም አቡ አፍናን ሀፊዘሁሏህ
⭐️ ወንድም ሙሀመድ ሲራጅ ሀፊዘሁሏህ
🔧 የፕሮግራሙ መሪ
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
✅ ወንድማችን አቡ ማሒ ሀፊዘሁሏህ
🗺 ቀን እና ሰአት፦ የፊታችን ሰኞ ማታ ከምሽቱ 3:00 ሰአት ጀምሮ
❤️ ፕሮግራሙ የሚተላለፍበት ቻናል
🔗 https://t.me/tdarna_islam
🔗https://t.me/tdarna_islam
ﻗَﺎﻝَ ﺷَﻴْﺦُ ﺍﻹﺳْﻼَﻡِ ﺍﺑﻦُ ﺗَﻴْﻤِﻴَّﺔَ، ﺭَﺣِﻤَﻪُ ﺍﻟﻠﻪُ ﺗَﻌَﺎﻟَﻰ :
" ﻣَﻦْ ﺗَﺪَﺑَّﺮَ ﺍﻟْﻘُﺮْﺁﻥَ ﻃَﺎﻟِﺒًﺎ ﻟِﻠْﻬُﺪَﻯ ﻣِﻨْﻪُ، ﺗَﺒَﻴَّﻦَ ﻟَﻪُ ﻃَﺮِﻳﻖُ ﺍﻟْﺤَﻖِّ ."
[ﻣﺠﻤﻮﻉ ﺍﻟﻔﺘﺎﻭﻯ ( ١٣٧ /٣ ) ]
ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ ﺭَﺣِﻤَﻪُ ﺍﻟﻠﻪُ ﺗَﻌَﺎﻟَﻰ
እንዲህ ይላሉ ፦"ቁርአንን ለመመራት ብሎ ያስተነተነ ሰው የሐቁ መንገድ ግልፅ ይሆንለታል"
📚
መጅሙዑል ፈታዋ (3/137)
አላህ ቁርአንን እያስተነተኑ ከሚቀሩ ሰዎች ያድርገን
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
ስለ ክረምት ደርሳችን የመጨረሻ ማስታወሻዎች:
1,መደበኛ ምዝገባ የተጠናቀቀ ቢሆንም ቂርኣቱን መከታተል ለሚፈልግ ምዝገባው ለ1 ሳምንት ያህል ይቀጥላል።
2,በፕሮግራማችን መሠረት በአላህ ፈቃድ የመጀመርያ ደርሳችን የሚሆነው الأصول من علم الأصول ዛሬ(ሰኞ) አመሻሽ11:45 ላይ ይሆናል።
3,ለደርሱ በጊዜ መገኘት፣ሙጣለዓ ማድረግ እና live መከታተል ያልቻለ ሪከርዶችን በተገቢው ሁኔታ መከታተል ዋና ዋና አዳቦች ናቸውና ባትዘናጉ።ያለ በቂ ምክንያት ላለማቋረጥ ቆራጥ ሁኑ።አላህ ይርዳን!!።
4,ከዚህ በኋላ አስገዳጅ ካልሆነ በስተቀር ስለ ደርሱ እዚህ ቻነል ላይ ምንም ነገር አይለቀቅም።የደርሱ channel link፦ https://t.me/mibnabas
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
ስለ ኮርሶቹ ጥቂት ማስታወሻዎች:
በመጀመርያ ወኔ እና ቆራጥነታችሁ እጅግ በጣም አስደስቶኛል:ፍፁም ከጠበኩት በላይ ነው።አላህ ያስደስታችሁ ያስደስተን ፅናቱንም ይወፍቀን።በመቀጠል የናንተንም አስተያየት ከግምት በማስገባት የሚከተሉት ውሳኔዎች ላይ ደርሰናል።እነዚህም፦
1,ኪታቦቹ
A,ሙስጦለሑል ሐዲስ(የሸይኽ ኢብኑ ዑثይሚን)
B,ኧልኡሱሉ ሚን ዒልሚል ኡሱል(በተመሳሳይ የሸይኽ ኢብኑ ዑثይሚን رحمه الله) እና
C,ከሶርፍ ደግሞ መትኑል ቢናእ(ሸይኽ አቡ ዚያድ ሙሀመድ ቢን ሀሰን)...ለጀማሪ ከነሕው ይልቅ ሶርፍ ቀለል ስለሚል እና ነሕው በቅርብ ስለቀራን ነው ሶርፍ የተመረጠው።
*pdf የቂርኣቱ ግሩፕ ላይ ተለቋል።
*ኪታቦቹን በhardcopy ይዛችሁ ብትከታተሉ በላጭ ነው።ምናልባት ቢናእ ለብቻው ላይኖር ስለሚችል مجموعة الصرف ሚል መጠነኛ ጥቅል ኪታብ መግዛት ትችላላችሁ።
2,ምዝገባ ሚደረገው ዛሬ(ቅዳሜ)እና ነገ ስለሆነ ወንዶች በዚ username- @zidni1 እህቶች ደግሞ በዚኛው- @Umuayan2
መመዝገብ ይኖርባችኋል።attendance ክትትል ይደረጋል እና እንዳትዘናጉ።
3,ሁሌም ላይመቻችሁ ስለሚችል record ተደርጎ ይለቀቃል።
4,የቂርኣቱ ግሩፕ link፦ https://t.me/mibnabas ነው እናም ከዚ ሰዓት ጀምራችሁ join ማድረግ ትችላላችሁ።
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
ያ ጀማዐተል ኸይር እንዴት ናችሁ;የረፍት ቀናት ጅማሮ እና ቤተሰብ ሁሉ ሰላም?...
الحمد لله(على كل حال)
ይነበብ፡ባረከሏሁ ፊኩም!(ሙሉ ብታነቡት)
የክረምት ኮርስ በኢብኑ ዐባስ!!
አንድ ነገር ላዋያችሁ ነበር...ይሀውም ለቀጣይ 2ወራት የሚቆይ የonline ኮርስ ለማዘጋጀት በኔ በኩል ፈቃደኛ እና ደስተኛ ነኝ።ተሳክቶ ብናስኬደው እኔም እናንተም ቢያንስ አራት ዋና ዋና ጥቅሞች ስለምናገኝበት ነው።
1,ሸሪዓዊ እውቀትን እና በዒባዳ አጅር ማግኘት።
2,የውመል ቂያማ ከምንጠየቅባቸው ነገሮች መካከል እድሜያችን:ወጣትነታችንን እና ገንዘባችንን አላህ በሚፈልግብን ሁኔታ ማዋል።
3,ጊዜያችን በሚጠቅመን ነገር ስናውል ጥፋት እና ወንጀል ላይ ከመውደቅ በአላህ ፈቃድ ስለምንጠበቅ።
4,ከዚ በፊት በየአመቱ ወይም በየአጋጣሚው ክፍት ጊዜ ሲኖረኝ እጠቀምበታለሁ እያልን ላመለጡን እድሎች ማካካሻ እና ለቀጣይ ክፍት ጊዜያትም ጥሩ ትዝታን ማኖር ነው።
የኮርሶቹ ይዘት;ብዙ ቦታ ላይ እድሉን ማናገኝባቸውን መርጫለሁ።እነዚህም፦
1,ኡሱሉል-ፊቅህ
2,ሙስጦለሑል ሐዲث
3,ሶርፍ(probably ነሕውም ሊሆን ይችላል)
ፈተና እና ሰርተፊኬት ይኖራቸዋል።
ቀን እና ሰዓት:ከቅዳሜ እስከ ሐሙስ አመሻሽ 11:45-12:30
ማስታወሻ:
1,ብዙዎች በዚህ ወቅት በአካል መስጅድ በመገኘት ወይም በኦንላይን ለመቅራት ፕሮግራም ይዛችሁ ሊሆን ስለሚችል ሀሳቡ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊሉ ሊቀየር ይችላል።
2,ሀሳብ አስተያየት ካላችሁ በዚህ username- @zidni1 ብታቀርቡ።
3,መጀመር ላይ ከወሰንን ነገ እና ከነገ ወድያ ምዝገባ አድርገን ከ2ቀናት በኋላ ሰኞ የምንጀምር ይሆናል።(ክፍያ የለውም)
🎉الْحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي بِنِعْمَتِهِ تَتِمُّ الصَّالِحَاتُ
✨አልሃምዱሊላህ!
✨አልሃምዱሊላህ!
✨አልሃምዱሊላህ!
«ድብቁ ገዳይ እና የተስፋው ጋሻ»!
~ ተለቀቀ~
ሰው ነኝና ከስህተት ከጥፋት አልጠራም
እርምት እና አስተያየት ካላችሁ
በዚህ ንገሩኝ @Abu_Hulud22
ሚስኪኑ ወንድማችሁ ⎛አቡ ሑሉድ.⎫
