cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ዮሐንስ አፈወርቅ✝✝✝

Advertising posts
208
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+330 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

#ይህንን_ያውቃሉ የሦስቱ ዲያቆናት ምሳሌነት ምንድን ነው ? ቅዳሴ ላይ እንደሚታወቀው ልዑካኑ  ከሁለት እስከ ሃያ አራት ድርስ ሊደርሱ ይችላሉ አምስቱ ልዑካን  ማለት ሁለት ካህን ሦስት ዲያቆናት በአጠቃላይ የአምስቱ አማዕደ ምሥጢራት ምሳሌ ናቸው ሦስቱ ዲያቆናት የየራሳቸው ምሳሌነት አላቸው 1. የዋና ዲያቆን (ሠራዒ ) ይህ ዲያቆን የቅዱስ እስጢፋኖስ ምሳሌ ነው መጾር ወይም መስቀል ይዟ መቀደሱ ቅዱስ እስጢፋኖስ የተቀበለውን ሰማዕትነት ለማሰብ ነው 2. ተጨማሪ (ንፍቅ ) ዲያቆን ይህ ዲያቆን ደግሞ መጥመቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ ምሳሌ ነው ከፊት ከፊት እየቀደመ  ካህናቱን መምራቱ ሊቀ ካህናት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከፊት ቀድሞ መጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ጥርጊያውን መንገድን የማዘጋጀቱ ይህ ዲያቆን መብራት ወይም ጠፋፍ የሚያዙ ከመስዋዕት ከማቅርብ አልፎ በዚህ ይመሰላል 3. ፍሬ ሰሞን (መጽሐፍ ገላጽ )   ይህ ዲያቆን የሐዋርያት አባቶቻችን ምሳሌ ነው እንዴት ቢሉ መጽሐፍ ይዞ በአራቱም አቅጣጫ ይዞራል ይህም ሐዋርያት በአራቱ አቅጣጫ ወንጌልን የመስበካቸው ምሳሌ ነው ꧁  ይ🀄 ላ 🀄ሉ꧁  https://t.me/yohanisafewerk30 https://t.me/yohanisafewerk30 https://t.me/yohanisafewerk30
Show all...
#ይህንን_ያውቃሉ የሦስቱ ዲያቆናት ምሳሌነት ምንድን ነው ? ቅዳሴ ላይ እንደሚታወቀው ልዑካኑ  ከሁለት እስከ ሃያ አራት ድርስ ሊደርሱ ይችላሉ አምስቱ ልዑካን  ማለት ሁለት ካህን ሦስት ዲያቆናት በአጠቃላይ የአምስቱ አማዕደ ምሥጢራት ምሳሌ ናቸው ሦስቱ ዲያቆናት የየራሳቸው ምሳሌነት አላቸው 1. የዋና ዲያቆን (ሠራዒ ) ይህ ዲያቆን የቅዱስ እስጢፋኖስ ምሳሌ ነው መጾር ወይም መስቀል ይዟ መቀደሱ ቅዱስ እስጢፋኖስ የተቀበለውን ሰማዕትነት ለማሰብ ነው 2. ተጨማሪ (ንፍቅ ) ዲያቆን ይህ ዲያቆን ደግሞ መጥመቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ ምሳሌ ነው ከፊት ከፊት እየቀደመ  ካህናቱን መምራቱ ሊቀ ካህናት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከፊት ቀድሞ መጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ጥርጊያውን መንገድን የማዘጋጀቱ ይህ ዲያቆን መብራት ወይም ጠፋፍ የሚያዙ ከመስዋዕት ከማቅርብ አልፎ በዚህ ይመሰላል 3. ፍሬ ሰሞን (መጽሐፍ ገላጽ )   ይህ ዲያቆን የሐዋርያት አባቶቻችን ምሳሌ ነው እንዴት ቢሉ መጽሐፍ ይዞ በአራቱም አቅጣጫ ይዞራል ይህም ሐዋርያት በአራቱ አቅጣጫ ወንጌልን የመስበካቸው ምሳሌ ነው ꧁  ይ🀄 ላ 🀄ሉ ꧂ @eotcy @eotcy @eotcy
Show all...
New Orthodox Tewahido Mezmur KIDANAMIRAT Zemari Kasahun Xilahun ##bikilt... https://youtube.com/watch?v=6Ceqk6kp9rg&si=Ey2iVk1WDPRaMdjO
Show all...

#ለማርያም ==== ለማርያም/2/ እንዘምራለን ለዘለዓለም/2/ አ.ዝ-----------------------// የተዘጋች ደጅ ለዘለዓለም ህዝቅኤል ብሏል ለዘለዓለም ንፅሕት ናት በእውነት ለዘለዓለም በፍጹም ድንግል ለዘለዓለም አብነት አድርገን ለዘለዓለም አኛም እርሱን ለዘለዓለም በፍፁም ፍቅር እንዘምራለን/2/ አ.ዝ-----------------------// የዋህይት ርግብ ለዘለዓለም ሰላም አብሳሪ ለዘለዓለም ለጨለማ ሕይወቴ ለዘለዓለም ብርሃንን አብሪ ለዘለዓለም እማጸንሻለሁ ለዘለዓለም ድንግል ለነፍሴ ለዘለዓለም አደራ ቅድስት አንቺ ነሽ ዋሴ/2/ አ.ዝ-----------------------// እጅግ የበዛ ነው ለዘለዓለም ያለኝ ፍቅር ለዘለዓለም አይወሰንም ለዘለዓለም አይነገርም ለዘለዓለም በእርሷ ደስ ይለኛል ለዘለዓለም ሐሴት አደርጋለሁ ለዘለዓለም ስሟን እየጠራሁ እዘምራለሁ/2/ አ.ዝ-----------------------// ነይ ነይ ስላት ለዘለዓለም ቀንና ሌሊት ለዘለዓለም አትለየኝም ለዘለዓለም ለእኔስ ቅርቤናት ለዘለዓለም እፁብ እፁብ ብለው ለዘለዓለም አመሰገኗት ለዘለዓለም ክብሯን ሊገልፁት ቢያጥራቸው ቃላት /
Show all...
ለማርያም_2_እንዘምራለን_ለዘለአለም_2_MP3_70K.mp35.11 MB
#ሚያዝያ_6 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሚያዝያ ስድስት በዚህችም ቀን #የአባታችን_አዳምንና #የእናታችን_ሔዋን መታሰቢያቸውን ነው፣ ከአባታችን አዳም ጀምሮ አሥረኛ ትውልድ የሆነ #ጻድቁ_ኖኅ ልደቱ ነው፣ ንጉሡ ልበ አምላክ #ቅዱስ_ዳዊት ልደቱ ነው፣ በበረሀ የምትኖር #ግብፃዊት_ማርያም አረፈች፣ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በትንሣኤው ሳምንት #ለሐዋርያው_ቶማስ ተገለጠለት፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱሳን_አዳምና_ሔዋን ሚያዝያ ስድስት በዚህችም ቀን የአባታችን አዳምን የእናታችን ሔዋንን መታሰቢያቸውን እናደርግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አዘዙን። ይህን አባታችን አዳምን ሳይፈጥረው አስቀድሞ በሰማይና በምድር ያለውን አዘጋጀለት። ሐዋርያው ጳውሎስ እንደተናገረ መላእክትንም ስለርሱ ፈጠረ። ከዚህም በኃላ በኤዶም ተክልን አዘጋጀለት እርሱም የፍሬው ጣዕም በየራሱ ልዩ ነው የሚአሻውን ሁሉ አከናውኖ እነሆ ከምድር መካከል ይኸውም ጎልጎታ ነው አፈር አንሥቶ በሦስት ሰዓት እርሱን ፈጠረው። ከአራት በሕርያት ይኸውም ውኃ እሳት ነፋስና መሬት ነው በአርአያውና በምሳሌው ራሱን አስመስሎ ፈጠረው በፊቱም እፍ ብሎ የሕይወት መንፈስን አሳድሮ የሚናገርና የሚያስተውል የሚያውቅ አደረገው የብርሃንንም ልብስ አልብሶ ንጉሥ ነብይ ካህን አስተዳደሪ አድርጎ በፈጠረው ሁሉ ላይ ሾመው። ከዚህም በኃላ አይቶ ስማቸውን ይሰይም ዘንድ አራዊትን እንስሳትን የሰማይ ወፎችን ሁሉ ወደርሱ አመጣ። አዳምም መንፈስ ቅዱስ እንዳናገረው ለሁሉም ስም አወጣላቸው። ከዚህም በኃላ በአዳም ላይ እንቅልፍን አመጣበትና አንቀላፋ ከጐኑም አንድ ዐጥንትን ነሣ ቦታዋንም በሥጋ መላው እግዚአብሔርም ሴት አድርጎ አሰምሮ ሠራት በአዳምም በፊቱ አኖራት። አዳምም ነቅቶ ይቺ ከዐጥንቴ ዐጥንት ከሥጋዬ ሥጋ ናት ሚስት ትሁነኝ ብሎ ተናገረ ስሟንም ሔዋን አላት። አዳምም በጎልጎታ ቁሞ የፈጣሪውን ቃል እየሰማ ሳለ እነሆ ከሚስቱ ከሔዋን ጋራ በፊት በኃላ ሁነው በየነገዳቸው አዳምን ስለ አከበረው መላእክት እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ደመና ተሸክማ ወሰደቻቸው በኤዶም ገነትም አኖራቸው። እግዚአብሔርም አዳምንና ሔዋንን በገነት ካለው ተክል ሁሉ ብሉ ግን ከገነት መካከል ዕፀ በለስን አትቡሉ ከእርሱ በበላችው ቀን ሞትን ትሞታላችሁ አላቸው። አዳምም ገነትን እያረሰና እየቆፈረ ከፍሬዋም እየተመገበ ከመላእክት ጋራ ሲያመሰግን ኖረ። የበጎ ሥራ ጠላት ሰይጣን ግን ከማዕርጉ በወደቀ ጊዜ በአዳም ጌትነትና ክብር ቀንቶ በእባብ አድሮ ወደሔዋን ሔደ። ያንን ዕፀ በለስንም ትበላ ዘንድ አታለላት አምላክ የመሆንንም ተስፋ አሳደረባትና አሳታት። ያንን ዕፀ በለስንም በአየችው ጊዜ አማራት በልታ ለባልዋም አበላችው ያን ጊዜ የብርሃን ልብሳቸው ከላያቸው ተገፈፈ። እነርሱም ራቁታቸውን እንደሆኑ አውቀው በበለስ ቅጠል ኀፍረተ ሥጋቸውን ሸፈኑ። እግዚአብሔርም ስሕተታቸውን አውቆ አስቀድሞ እባብን ረገመ በእርሷና በሴቲቱ ዘር መካከል ጠላትነትን አጸና። በሔዋንም ላይ በፃር በገዐር ውለጂ ወልደሽም መመለሻሽ ወደባልሽ ይሁን እርሱም ይግዛሽ ብሎ ፈረደባት። አዳምንም እንዲህ አለው ስለ አንተ ምድር የተረገመች ትሁን ጥረህ ግረህ እንጀራህን ብላ አንተ አፈር ነህና ወደ አፈርነት ትመለሳለህ። እግዚአብሔርም የቁርበትን ልብስ አዘጋጅቶ አለበሳቸው ሰባት ዓመት በተድላ ከኖሩ በኃላ በምሽት ጊዜ ከኤዶም ገነት ወጡ። አዳምም በማለዳ ፀሐይ ሲወጣ ነጭ ዕጣን ቀንዓት ሰሊሖት የሚባል ሽቱ ከሎሚ ውኃ ጋር አጠነ። አዳምም በኤዶም ገነት እንደተማረ ምድሪቱን እያረሰና እየቆፈረ ኤልዳ በሚባል ምድር ኖረ። አዳምም ሔዋንን በግብር አወቃት ቃየልን ከእኅቱ ጋር ወለደችለት ከእርሱም በኃላ አቤልን ከእኅቱ ጋራ ወለደችው ቃየልና አቤልም አድገው አካለ መጠን አደረሱ። ወደ እግዚአብሔርም መሥዋዕት በአቀረቡ ጊዜ ጌታ የአቤልን መሥዋዕት ተቀበለ ስለዚህም ቃየል ተቆጣ በአቤልም ቀንቶ ገደለው። አዳምም በልጁ በአቤል ሞት እያዘነና እያለቀሰ አራት የዘመን ሱባዔ ኖረ። ከዚህም በኃላ ሴት ተወለደለት በእርሱም መታሰቢያው ጸና ከእርሱም በኃላ ብዙዎች ወንዶችንና ሴቶች ልጆችን ወለደ። እግዚአብሔርም ንስሓውንና ልቅሶውን አይቶ የድኅነት ተስፋ ሰጠው። አምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም ወደ ዓለም መጥቼ ከልጅ ልጅህ እወለዳለሁ ሕፃንም ሆኜ በሜዳህ ውስጥ እድሀለሁ በመስቀሌና በሞቴም አድንሃለሁ አለው። አዳምም ከገነት በወጣ ጊዜ የወሰደውን ወርቅ ከርቤና ዕጣን ለልጁ ለሴት ሰጠው እንዲህም አለው በኃላ ዘመን የእግዚአብሔር ልጅ መጥቶ ከድንግል ይወለዳል ያን ጊዜ የጥበቡ ሰዎች ይህን ወርቁን ከርቤውንና ዕጣኑን እጅ መንሻውን ያመጡለታል እርሱም መዝግቦ በዕቃ ቤት አኖረው። ወደ ኖኅም እስኪደርስ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ ኖረ ከኖኅም የምሥራቅ ሰዎች ወደ ሆኑ የጥበብ ሰዎች እስኪ ደርስ ተላለፈ። እነርሱም ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በሥጋ በተወለደ ጊዜ አምጥተው ለእግዚአብሔር ልጅ እጅ መንሻ አድረገው አቀረቡለት እመቤታችንም ከእጃቸው ተቀበላ በኃላ ለቅዱስ ጴጥሮስ ሰጠችው ቅዱስ ጴጥሮስም ለቀሌምንጦስ ሰጠው። አዳምም የሚያርፍበትን ሰዓት በአወቀ ጊዜ ልጁ ሴትን ጠርቶ ከመሞቴ በፊት ልጆችህንና የልጅ ልጆችህን ወደእኔ አቅርባቸው አለው። የአባቱን ቃል ሰምቶ ዕንባው በጉንጩ ላይ እየፈሰሰ ወጣ ወደ አዳምም አቀረባቸው። አዳምም በአያቸው ጊዜ ከእሳቸው ስለ መለየቱ አለቀሰ። እነርሱም ሲያለቅስ በአዩት ጊዜ ሁሉም በአንድነት ወደ እግዚአብሔር በግምባራቸው ተደፍተው አለቀሱ ምድር እንዴት ትሸፈንሃለች ከዐይኖቻችንስ እንዴት ትሠወራለህ አሉ። ከዚህም በኃላ አባታችን አዳም ሁሉን ልጆቹን ባረካቸው መረቃቸው። ልጁን ሴትን እንዲህ አለው ይቺ ዓለም ድካምና ችግርን የተመላች ናትና በእግዚአብሔር እየታመንክ ዕውነትን ንጽሕናን ጠብቅ ሰይጣን ወደ ሚያሳይህ ምትሐቱና ወደ ነገሩ አታዘንብል። በሞትኩ ጊዜም ሥጋዬን ወስዳችሁ ሰሊክ ሚዓ በሚባል ሽቱ ገንዛችሁ በግምጃ ቤት አኑሩኝ የጥፋት ውኃ ይመጣ ዘንድ አለውና ፍጥረት ሁሉ ይሰጥማል ከስምንት ነፍስ በቀር የሚቀር የለም። ልጄ ሆይ ለወገኖችህ ቋሚ ሁነህ እግዚአብሔርን በመፍራት ጠብቃቸው የዕውነት መንገድንም ምራቸው ለስይጣንም እንዳይ ታዘዙና እንዳያጠፋቸው አደራ አስጠብቃቸው። ልጆችህንና የልጅ ልጆችህን ከቃየል ልጆች ለያቸው አንድ ይሆኑ ዘንድ ከቶ አትተዋቸው ወደ ሥራቸውና ወደ ጨዋታቸውም አይቅረቡ። ከዚህም በኃላ ወደ ልጁ ወደ ሴትና ወደ ሔዋን መለስ ብሎ ያንን ወርቅ ከርቤና ዕጣን ከእርሳቸው ጋራ አኑረው ይጠብቁት ዘንድ አደራ አላቸው። እንዲህም አላቸው የጥፋት ውኃ በመጣ ጊዜ ሥጋዬን ከወርቁ ከከርቤውና ከዕጣኑ ጋራ ወደ መርከብ ያስገቡ ከዚያም በኃላ በምድር መካከል ያኑሩት። ከብዙ ዘመናት በኃላም ያቺን አገር ይወርዋታል እሊህንም ወርቅ ከርቤና ዕጣን ከብዙ ምርኮ ጋር ይወስዱትና አካላዊ ቃል መጥቶ ሰው እስከሚሆን ድረስ በዚያ ይጠበቃል። ነገሥታትም ይዘው መጥተው ይገብሩለታል ወርቁ ስለ መንግሥቱ ዕጣኑ ስለ ክህነቱ ከርቤውም ማሕየዊት ስለሆነች ሞቱ ነው።
Show all...
ምን ሰማህ ዩሐንስ ❤️🌿 ምን ሰማ ዩሀንስ በማጸን ሳለህ/2/ ህፃን ሆነህ ነቢይ ለክብር የተጠራህ/2/ እንደ እንቦሳ ጥጃ ያዘለለህ ደስታ/2/ ምን አይነት ድምፅ ነው ምን አይነት ሰላምታ/2/ ከተፈጥሮ በላይ ያስገደህ ክብር እንዴት ቢገባው ነው የእናታችን ፍቅር/2/ ሌላ ድምፅ አልሰማም ከእንግዲህ በኋላ ለውጦኛልና የሰላምታ ቃሏ/2/         በረሀ ያስገባህ ለብዙ ዘመናት ምን ያለ ራዕይ እንዴት ያለ ብሥራት/2/ እንደ አዲስ ምስጋና ስልቱ የተዋበ ተደምጦ የማያውቅ ጭራሽ ያልታሰበ/2/              ከሴት ከተገኙ ከደቂቀ አዳም ድንግል ስለሆነ በህይወቱ ፍፁም/2/ ከማህፀን ሳለ ተመርጦ ከጌታ ለማዳመጥ በቃ የኪዳን ሰላምታ/2
Show all...
ሊቀ_መዘምራን_ይልማ_ኃይሉ_ምን_ሰማ_ዮሐንስ.m4a5.37 MB
በከበረች ጸሎቱ ይቅር ይበለንና ራሱን በትሕትና "ከጌቶች ልጆች የሚወድቀውን ፍርፋሪ የሚለምን ውሻ" ብሎ የሚጠራው ሶርያዊው ኮከብ ቅዱስ ኤፍሬም በየድርሰቶቹ መካከል እንዲህ እንዲህ አለ:- "ጌታችን ከሣምራዊትዋ ሴት ጋር በተነጋገረ ጊዜ በንግግራቸው መጀመሪያ ማንነቱን አልገለጠላትም። መጀመሪያ ያየችው ውኃ የጠማውን ሰው ነበር ፣ ከዚያ አይሁዳዊ ፣ ከዚያ መምህር (ረቢ) ፣ ቀጥሎ ነቢይ ከሁሉም መጨረሻ መሲህ መሆኑን አየች። ውኃ የተጠማውን ሰው በንግግር ልትረታ ስትሞክር በአይሁዳዊ ላይ ያላትን ጥላቻ አሳየች። ከመምህሩ ጋርም ተከራከረች ፣ ከነቢዩ እግር ስር ተንበረከከች ፣ መሲሁንም ወደደችው"        ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ (ስለ ሣምራዊቷ ሴት ዮሐ 4:1) ★ ★ ★ "ጌታ ሆይ ለእኛ ፊት ክብርን የሠጠ እንደ አንተ ያለ ማን አለ? የዕውሩን ዓይን ባበራህለት ጊዜ ላድነው ነህ ብለህ በፊቱ ላይ አልተፋህበትም። ነገር ግን አርኣያችንን አክብረህ በመሬት ላይ እንትፍ ብለው ፈወስከው። ጌታዬ ሆይ በእኔ ላይ ግን በፊቴ ላይ እንትፍ በልብኝ ፣ በፈቃዴ ያጠፋሁትን ዓይኔን በፈቃድህ አብራልኝ"                        ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ (ዕውር ሆኖ ስለተወለደው ዮሐ 9:30) ★ ★ ★ "ጌታ ሆይ ዕውሩን ሂድ ብለህ ወደላክህበት ወደ ሰሊሆም መጠመቂያ አሁን ልንሔድ አንችልም።  ነገር ግን ሕይወትንና ብርሃንን የተሞላው የከበረ ደምህ ያለበት ጽዋ በእኛ ዘንድ አለ። ከእርሱ በተቀበልን ቁጥር እንነጻለን"  ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ★ ★ ★ "ጌታዬ ሆይ በሔድኩበት ውጣውረድ የተሞላ መንገድ እምነቴ ደከመ ፣ መንገዱ የሚወስደኝም በግራ ወደሚቆሙት ፣ በደጅ ቆመው ክፈትልን ሲሉህ "አላውቃችሁም" ከምትላቸው ወገን ልሆን ነው። ጌታዬ ሆይ እኔ አውቅሃለሁ ፣ አንተ ግን አላውቅህም ትለኝ ይሆን? አቤቱ በአንተ ለማምን ለእኔ ለኃጢአተኛው ራራልኝ።  ብበድልህም እንኳን አሁንም በርህን እያንኳኳሁ ነው። እየተጎተትኩም ቢሆን አሁንም የምጓዘው ወደ አንተ ለመምጣት ነው"                                        ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ (ማቴ 7:7) ★ ★ ★ "ጌታ ሆይ እነዚህን በዕድሜ ሕፃናት የሆኑ የመንፈስ ልጆቼን ይቅር በላቸው። ሕፃን የነበርከው ሆይ የሕፃንነትህን ጊዜ አስብ። ልጅነታቸው ያንተን ልጅነት እንዲመስል አድርግላቸውና በቸርነትህ አድናቸው"                                         ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ከተለያዩ መዝሙራቱ (Hymns) በተርጓሚው ተለቃቅሞ የተሰበሰበ ኅዳር 26 2011 ዓ ም ክርስቲያን ሳንድ Deacon Henok Haile https://t.me/hinokhayla https://t.me/hinokhayla
Show all...
✝️ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ ማነው ብዬ ጠየቅሁ በረከት ፈልጌ ልሳለመው ናፈቅሁ ክብሩን ልመሰክር ተፈታ ምላሴ በደጁ ደርሼ ፍቅሩን በመቅመሴ/፪/ በኢቲሳ ምድር ዘር ሆነህ በቅለህ ተለየህ ለአምላክ ዓለምን ጥለህ ደብረ ሊባኖስ ህያው ምስክር ስለ አንተ ዝና ስለ አንተ ክብር ተክለሃይማኖት ወዳጄ ተባርኳል በአንተ ጓዳ ደጄ አዝ____ አክባሪው አምላክ ስላከበረህ ዛሬም ከኛ ጋር በመንፈስ አለህ ደጅ እንጠናለን በትህትና የጻድቅ ጸሎት ኃይል አላትና ተክለሃይማኖት ወዳጄ ተባርኳል በአንተ ጓዳ ደጄ አዝ____ ወደ ለምለም መስክ ሰብከህ መራኸን የቃሉን ወተት አጠጥተኽን ያቀጣጠልከው የወንጌል ችቦ የአምላክ አድርጓል ትውልዱን ስቦ ተክለሃይማኖት ወዳጄ ተባርኳል በአንተ ጓዳ ደጄ አዝ____ ሠላሳ ሥድሳ መቶ ያፈራህ በደብረ አስሶ ቆመህ በአንድ እግርህ የሞተለሚ መሻት ቀረና የጌታ መንገድ ጥርጊያውም ቀና ተክለሃይማኖት ወዳጄ ተባርኳል በአንተ ጓዳ ደጄ https://t.me/EthiopianOrthodoxTewahdoMezmurs
Show all...
ኢትዮጵያው ፃዲቅ .mp35.27 MB
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.