cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

የዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ትምህርቶች

የዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ትምህርቶች መንፈሳዊ ትረካዎች ስብከቶች ለማግኘት ይቀላቀሉ። This channel is not run by D/n Henok Haile. YouTube https://www.youtube.com/@Min22111 Telegram Group https://t.me/dn_henok Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=100064756446431&mibextid=ZbWKwL

Show more
Advertising posts
5 746
Subscribers
+524 hours
+867 days
+24130 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

መዝሙረ ዳዊት Psalms 90፡(91)። የዳዊት፡የምስጋና፡መዝሙር። 1፤በልዑል፡መጠጊያ፡የሚኖር፡ዅሉን፡በሚችል፡አምላክ፡ጥላ፡ውስጥ፡ያድራል። 2፤እግዚአብሔርን፦አንተ፡መታመኛዬ፡ነኽ፡እለዋለኹ፤አምላኬና፡መሸሸጊያዬ፡ነው፥በርሱም፡ እታመናለኹ። 3፤ርሱ፡ከአዳኝ፡ወጥመድ፡ከሚያስደነግጥም፡ነገር፡ያድንኻልና። 4፤በላባዎቹ፡ይጋርድኻል፥በክንፎቹም፡በታች፡ትተማመናለኽ፤እውነት፡እንደ፡ጋሻ፡ይከብ፟ኻል። 5፤ከሌሊት፡ግርማ፥በቀን፡ከሚበር፟፡ፍላጻ፥ 6፤በጨለማ፡ከሚኼድ፡ክፉ፡ነገር፥ከአደጋና፡ከቀትር፡ጋኔን፡አትፈራም። 7፤በአጠገብኽ፡ሺሕ፡በቀኝኽም፡ዐሥር፡ሺሕ፡ይወድቃሉ፤ወዳንተ፡ግን፡አይቀርብም። 8፤በዐይኖችኽ፡ብቻ፡ትመለከታለኽ፥የኃጥኣንንም፡ብድራት፡ታያለኽ። 9፤አቤቱ፥አንተ፡ተስፋዬ፡ነኽና፤ልዑልን፡መጠጊያኽ፡አደረግኽ። 10፤ክፉ፡ነገር፡ወዳንተ፡አይቀርብም፥መቅሠፍትም፡ወደ፡ቤትኽ፡አይገባም። 11፤በመንገድኽ፡ዅሉ፡ይጠብቁኽ፡ዘንድ፡መላእክቱን፡ስለ፡አንተ፡ያዛ፟ቸዋልና፤ 12፤እግርኽም፡በድንጋይ፡እንዳትሰናከል፡በእጆቻቸው፡ያነሡኻል። 13፤በተኵላና፡በእባብ፡ላይ፡ትጫማለኽ፤አንበሳውንና፡ዘንዶውን፡ትረግጣለኽ። 14፤በእኔ፡ተማምኗልና፥አስጥለዋለኹ፤ስሜንም፡ዐውቋልና፥እጋርደዋለኹ። 15፤ይጠራኛል፥እመልስለትማለኹ፤በመከራውም፡ጊዜ፡ከርሱ፡ጋራ፡እኾናለኹ፤አድነዋለኹ፥አከብረውማለኹ። 16፤ረዥምን፡ዕድሜ፡አጠግበዋለኹ፥ማዳኔንም፡አሳየዋለኹ። https://t.me/hinokhayla https://t.me/hinokhayla
Show all...
ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ትምህርቶች

የዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ትምህርቶች መንፈሳዊ ትረካዎች ስብከቶች ለማግኘት ይቀላቀሉ። This channel is not run by D/n Henok Haile. YouTube

https://www.youtube.com/@Min22111

Telegram Group

https://t.me/dn_henok

Facebook

https://www.facebook.com/profile.php?id=100064756446431&mibextid=ZbWKwL

5
Show all...
"አትክለተኛ መሠሏት ነበር" ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ

ድንቅ አስተማሪ ፅሁፍ በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ አትክልተኛ መሥሏት ነበር።

ዲ/ን አቤል ካሳሁንን ፍና ላይ
Show all...
👍 18 4
ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ እና ዮሐንስ ዘደማስቆ ሐዋርያው ጴጥሮስ ጌታ በዐረገ በዓመቱ (34 ዓ.ም.) ቅዱሱን እሳት በመቃብሩ ስፍራ ማየቱን ጽፈዋል። ይህ ተአምር አሁን እስካለንበት ዘመን የቀጠለ ሲሆን፣ ሁል ጊዜም በትንሣኤ በዓል ዋዜማ ቅዳሜ ቀን ይታያል። ስለዚህ የሚያስደንቅ ተአምር ብዙ የማያምኑ ሰዎች በራሳቸው መንገድ ለማጣራት ሞክረዋል። እስኪ ከእነዚህ ውስጥ አንዱን ታሪክ ላጫውታችሁ። በአንድ ወቅት እንዲህ ሆነ… ዕለቱ ቅዳሜ ጠዋት 4 ሰዓት የትንሣኤ ዋዜማ ነው። የእስራኤል አይሁድ ፖሊሶች እና የከተማዋ ከንቲባ  ይህ እሳት ይፈልቅበታል የተባለውን የጌታን መቃብር እውነትነት ማረጋገጥ ስለ ፈለጉ በውስጡ ለእሳቱ መነሣት ምክንያት የሚሆኑ ተቀጣጣይ ነገሮች ካሉ በሚል ለሁለት ሰዓታት ያህል ሦስት ጊዜ ጥብቅ ፍተሻ አደረጉ። ግን ምንም ሊያገኙ አልቻሉም። ቀጥሎም ሁለት መቃብሩን የሚጠብቁ ሙስሊሞችን በማምጣት ልክ የቀድሞዎቹ አይሁድ የጌታን መቃብር እንዳተሙ እነርሱም መቃብሩን ዘግተው በሰም እንዲያትሙት አደረጉ። ይህንም ተከትሎ በቦታው የነበሩ አረብ ክርስቲያኖች ቱርክ እስራኤልን በተቆጣጠረችበት በ13ኛው ክፍለ ዘመን ከቤተ ክርስቲያን ውጭ በየትኛውም ቦታ ቢሆን እንዳይዘምሩ የተከለከሉትን ቆየት ያለ ዝማሬ በኅብረት ከፍ ባለ ድምፅ መዘመር ጀመሩ። መዝሙሩም:- “እኛ ክርስቲያኖች ነን። ለብዙ መቶ ክፍለ ዘመናትም ክርስቲያኖች ነበርን። እስከ ዘላለምም እንዲሁ እንሆናለን፣ አሜን!” የሚል ነበር። እኩለ ቀንም ሲሆን የግሪኩና የአርሜንያው ፓትርያርክ፣ የግብፁ ሜትሮፖሊታንት እንዲሁም  ቀሳውስት እና ዲያቆናት ወደ ታተመው የክርስቶስ መቃብር መጡ። ከብዙ ጸሎት እና ምስጋናም በኋላ የታተመው የክርስቶስ መቃብር እንዲከፈት አደረጉ። ፓትርያርኩም ሞጣህቱን ብቻ አስቀርተው ከላይ የለበሱትን ልብሰ ተክህኖ በማውለቅ በክርስቶስ የዕድሜ ቁጥር ልክ ሦስት 33 ያልበሩ ሻማዎችን ይዘው ጨለማ ወደ ነበረው መቃብር ገቡ። ምእመናኑም ከውጭ ሆነው በአንድ ድምፅ ኪርዬሌይሶን (አቤቱ ይቅር በለን) እያሉ በመዘመር ይጠባበቁ ጀመር። ወደ ቅዱሱ መቃብር ገብተው የነበሩትም የግሪኩ ፓትርያርክ ያን በሰው ያልተቀጣጠለ እና የክርሰ‍ቶስን የትንሣኤ ብርሃን የሚያበሥረውን አምላካዊ እሳት ይዘው ብቅ አሉ። ይህን ጊዜ ጎልጎታ በእልልታ ተሞላች የቤተ ክርስቲያኑም ደወል በሐሴት ይደወል ጀመር። ትንሣኤከ ለእለ አመነ ብርሃነከ ፈኑ ዲቤነ እንኳን አደረሰን!!! ዲያቆን አቤል ካሳሁን https://t.me/hinokhayla https://t.me/hinokhayla
Show all...
13👍 2👏 2
ፋሲካ አልባ ፋሲካ ለሃምሳ ቀናት ጾመን ደርሰን ከኀዘን አጽናፍ በስግደት በለቅሶ ከርመን ቆመን ከሰቆቃ ጫፍ እንደ ሐዲስ ኪዳንናዊ ሰው ከርመን ወንጌል ስናጠና እግዚኦ መሐረነ ጌታ ብለን ጮኸን ሆሳዕና ሕማምህ መከራህ አልፎ ትንሣኤህ ሲመጣ ፋሲካ ልክ እንደ ኦሪት ሰው ሆንን ሮጥን እንስሳ ፍለጋ እንደ ክርስቲያኖች ወግ ሥጋህንበልተን እንደመዳን በግና ዶሮ ልናሳድድ ሔድን ወደ ብሉይ ኪዳን ስንት ሰዓት ልቁረብ ማለት ትተን የእርዱ ነገር አስጨነቀን ከትንሣኤህ ዕለት ቆመን የልብ ትንሣኤ ራቀን የመቃብርህን ውጪ ቆመው ደጅ ደጁን ከጠበቁ ሕያው ጌታ መሆንህን ክብርህን ጭራሽ ካላወቁ ከሮማውያን ወታደሮች በምን ተለየን እኛ ሥጋህን ተቀብለን ካልሆነን የነፍስ መዳኛ ከቶ እንዴት ይከበራል ወደ አንተ ሳይቀርቡ ትንሣኤ? ለእኛ አልነበረም ወይ ያ ዕንባ ያ ሁሉ ኤሎሄ ኤሎሄ የከበረው ሥጋህ ዛሬ በእኛ ውስጥ ካልተቀበረ ምኑን ትንሣኤ ተበሰረ ምኑን ፋሲካ ተከበረ? ይቅር በለን ጌታችን ሆይ በዶሮ ሥጋ ላከበርንህ የሥጋችንን ስናሳድድ በትንሣኤህ ቀን ለቀበርንህ በሞትህ ሙት ያስነሣህ ሆይ እኛንም አስነሣን ዛሬ ደርቀን አንቅር በኃጢአት አድርገን የትንሣኤህ ፍሬ ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ቀዳም ስዑር ሚያዝያ 2016 ዓ.ም.
Show all...
👍 17 6💔 2
“አትደንግጡ፤ የተሰቀለውን የናዝሬቱን ኢየሱስን ትፈልጋላችሁ፤ ተነሥቶአል፥ በዚህ የለም፤ እነሆ እርሱን ያኖሩበት ስፍራ" ማርቆስ 16:6 "እንኳን አደረሳችሁ! " ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ https://t.me/hinokhayla https://t.me/hinokhayla
Show all...
26👏 2🥰 1
✝ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላምና በፍቅር አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †
✝ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
           ብርሃነ ትንሣኤ    ✝ የዓለማት ሁሉ ፈጣሪ : የዘለዓለም አምላክ ወልድ ዋሕድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህች ዕለት መግነዝ ፍቱልኝ : መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል በባሕርይ ኃይሉና ሥልጣኑ ተነስቷልና እንኳን ደስ አለን:: ††† ከዚህ በኋላ ለ50 ቀናት እንዲህ እያልን ሰላምታ እንለዋወጣለን:-
††† ክርስቶስ ተንስአ እሙታን! ¤በዐቢይ ኃይል ወስልጣን! ††† አሠሮ ለሰይጣን! ¤አግዐዞ ለአዳም! ††† ሰላም! ¤እምይእዜሰ! ††† ኮነ! ¤ፍሥሐ ወሰላም!
በእርግጥም አምላካችን በሞቱ ሞትን ገድሎ : በትንሣኤው ሕይወትን አድሎናልና ደስታ ይገባናል:: መድኃኔ ዓለም በኅቱም ድንግልና እንደ ተወለደ በኅቱም መቃብር ተነስቷል:: ለደቀ መዛሙርቱም "ሰላም ለእናንተ ይሁን" ሲል በዝግ ደጅ ገብቷል:: በዕለተ ትንሣኤው የመጀመሪያውን ደስታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተካፍላለች:: የእርሷን ያህል በሃዘን የተጐዳ የለምና:: ቀጥለው ቅዱሳት አንስት እነ ማርያም መግደላዊት ትንሣኤውን አይተዋል:: ሰብከዋልም:: † በዚሕች ቀን ማዘን አይገባም:: በትንሣኤው የደነገጡና የታወኩ የአጋንንትና የአይሁድ ወገኖች ብቻ ናቸውና::
††† አምላካችን ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ከትንሣኤው በረከት አይለየን:: በዓሉንም የሰላም : የፍቅርና የበረከት ያድርግልን::
† የጌታችን በጐ ምሕረቱ በሁላችን ትደርብን::
††† "ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነስቷል እንጂ በዚህ የለም:: 'የሰው ልጅ በኃጢአተኞች እጅ አልፎ ሊሰጥና ሊሰቀል: በሦስተኛውም ቀን ሊነሣ ግድ ነው' እያለ ገና በገሊላ ሳለ ለእናንተ እንደተናገረ አስቡ::" ††† (ሉቃ. ፳፬፥፭-፰)
††† "አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነስቷል:: ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኗልና:: ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና::" [፩ቆሮ. ፲፭፥፳]   † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † https://t.me/hinokhayla https://t.me/hinokhayla
Show all...
16👍 6
መዝሙረ ዳዊት Psalms 89፡(90)። የእግዚአብሔር፡ሰው፡የሙሴ፡ጸሎት። 1፤አቤቱ፥አንተ፡ለትውልድ፡ዅሉ፡መጠጊያ፡ኾንኽልን። 2፤ተራራዎች፡ሳይወለዱ፥ምድርም፡ዓለምም፡ሳይሠሩ፥ከዘለዓለም፡እስከ፡ዘለዓለም፡ድረስ፡አንተ፡ነኽ። 3፤ሰውን፡ወደ፡ኀሳር፡አትመልስም፤የሰው፡ልጆች፡ሆይ፥ተመለሱ፡ትላለኽ፤ 4፤ሺሕ፡ዓመት፡በፊትኽ፡እንዳለፈች፡እንደ፡ትናንት፡ቀን፥እንደ፡ሌሊትም፡ትጋት፡ነውና። 5፤ዘመኖች፡የተናቁ፡ይኾናሉ፥በማለዳም፡እንደ፡ሣር፡ያልፋል። 6፤ማልዶ፡ያብባል፡ያልፋልም፥በሠርክም፡ጠውልጎና፡ደርቆ፡ይወድቃል። 7፤እኛ፡በቍጣኽ፡አልቀናልና፥በመዓትኽም፡ደንግጠናልና። 8፤የተሰወረውን፡ኀጢአታችንን፡በፊትኽ፡ብርሃን፥በደላችንንም፡በፊትኽ፡አስቀመጥኽ። 9፤ዘመናችን፡ዅሉ፡ዐልፏልና፥እኛም፡በመዓትኽ፡አልቀናልና፤ዘመኖቻችንም፡እንደ፡ሸረሪት፡ድር፡ይኾናሉ። 10፤የዘመኖቻችንም፡ዕድሜ፡ሰባ፡ዓመት፥ቢበረታም፡ሰማንያ፡ዓመት፡ነው፤ቢበዛ፡ግን፡ድካምና፡መከራ፡ ነው፤ከእኛ፡ቶሎ፡ያልፋልና፥እኛም፡እንገሠጻለንና። 11፤የቍጣኽን፡ጽናት፡ማን፡ያውቃል፧ከቍጣኽ፡ግርማ፡የተነሣ፡አለቁ። 12፤በልብ፡ጥበብን፡እንድንማር፥ቀኝኽን፡እንዲህ፡አስታውቀን። 13፤አቤቱ፥ተመለስ፥እስከ፡መቼስ፡ነው፧ስለ፡ባሪያዎችኽም፡ተሟገት። 14፤በማለዳ፡ምሕረትኽን፡እንጠግባለን፤በዘመናችን፡ዅሉ፡ደስ፡ይለናል፡ሐሤትም፡እናደርጋለን። 15፤መከራ፡ባሳየኸን፡ዘመን፡ፈንታ፥ክፉም፡ባየንባቸው፡ዘመኖች፡ፋንታ፡ደስ፡ይለናል። 16፤ባሪያዎችኽንና፡ሥራኽን፡እይ፥ልጆቻቸውንም፡ምራ። 17፤የአምላካችን፡የእግዚአብሔር፡ብርሃን፡በላያችን፡ይኹን፦የእጆቻችንንም፡ሥራ፡በላያችን፡አቅና። https://t.me/hinokhayla https://t.me/hinokhayla
Show all...
11👍 1