5 084
Subscribers
+1124 hours
-157 days
-7730 days
Posts Archive
የብልፅግና ሰራዊት አባላት እርስ በርስ መገዳደላቸው ተገለጸ!!
ሐምሌ 08 ቀን 2018 ዓ.ም.
ብልፅግና የሠበሰበውን አጋፋሪ ኃይል ወደ አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት፣ አሳምነው ዕዝ፣ ከሰም ፪ኛ ኮር ቀጠና ለዘረፋ በኦህዴድ መራሹ ጦር አማራ ሕዝብ ላይ የጥፋት ተልዕኮውን እያከናወነ እንደሚገኝ ታውቋል።
ለምዝበራ ዘመቻ ከሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በእነ መካሻ አለማየሁ እና አባይ ግዛው የልመና ጥሪ ተሰባስቦ ወደ ከሰም የገባው ሰራዊት፣ ከአካባቢው ሚሊሻዎች ጋር በመቀናጀት በ32 የገጠር ቀበሌዎች ላይ ወረራ አካሂዶ "ፋኖን የማጥፋት ዘመቻ" በሚል የዘመተ ቢሆንም፣ ዘማቹ ኃይል በፋኖ ክንድ በመመታቱ ከባድ መስዋዕትነትን ከፍሎ ባለፉት 24 ቀናት ውስጥ ምንም ዓይነት ወታደራዊ ለውጥ ማምጣት አልቻለም ነበረ።
ሆኖም ካፈርኩ አይመልሰኝ በሚል ስሜት የዘመተው የአገዛዝ ኃይል የማህበረሰቡን መኖሪያ ቤቶች፣ ንብረቶች፣ ትምህርት ቤቶችና ጤና ኬላዎችን ሲዘርፍ መቆየቱ ተዘግቧል። በዚሕ የዘረፋ ተግባር ተጋላጭ የሆነችው ኮቱ ከተማ የደረሰው አሰቃቂ ድርጊት አንዱ ነው። በቀን 07/11/2018 ዓ.ም በኮቱ ታዳጊ ከተማ ውስጥ ሰራዊቱ በሴቶችና አዛውንቶች ላይ አሰቃቂ የአስገድዶ መድፈር ጥቃቶችን ሲፈጽም ከርሞባታል።
ከዚህም አልፎ በሚሊሻ ሚስቶች ላይ ጥቃት ለማድረስ የሞከረ ሲሆን፣ የአንድ ሚሊሻ ሚስትን አስገድዶ ለመድፈር ሲጎትት ባለቤቷ ለማስጣል ቢሞክርም ሕይወቱ ሊያልፍ ችሏል። አቶ ኃይሉ ሚሊሻ፣ ባለቤቱን እና ሌላ አንድ ሚሊሻን ጓዱን በአሰቃቂ ሁኔታ መከላከያ ተረሽነዋል። በዚሁ ጥቃት ከባድ ቁስለኛ ሆስፒታል የሚገኝ አንድ ሌላ የሚሊሻ አባል ይህንን የእምነት ቃል እንደሰጠ የከሠም ፪ኛ ኮር ሪፖርተር በውስጥ መረጃዎቼ ደርሰውኛል ሲል ገልፆል።
የአመራሮች ተሳትፎ እና ማሳሰቢያ፦
ይህ ጦር የተሰጠውን ተልዕኮ ማሳካት ሲያቅተው፣ በብአዴን ከፍተኛ አመራሮች ይሁንታ ማህበረሰቡን የመዝረፍ፣ የመግደል፣ እንዲሁም ሴቶችና ህፃናትን በአሰቃቂ ሁኔታ የመድፈርና አማራን የማጥፋት ዘመቻ እንዲያካሂድ እንደተፈቀደለት አውቃችሁ። እናንተ የአማራ ሚሊሻዎች ይህንን ሴራ ተገንዝባችሁ ከአረመኔውና ከዘራፊው አገዛዝ ተላቃችሁ ወደ ወገን ኃይል እድትቀላቀሉ እነሆ ጥሪያችን ነው።
"ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!"
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!"
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
በኤፍራታ ግድም ክላስተር "ሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር መብረቃዊ ጥቃት ፈፅማ ድል ተቀዳጀች!!
ሐምሌ 08/2018 ዓ.ም
በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት በአሳምነው ዕዝ ስር የሚንቀሳቀሰው 7ለ70 ክፍለ ጦር፣ ታሪክ የማይረሳውን ደማቅ ወታደራዊ ገድልና የድል ታሪክ መጻፉን ዛሬም በደመቀ ሁኔታ ቀጥሎበታል። ክፍለ ጦሩ በትናትናው ዕለት ማለትም በሐምሌ 07/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ኤፍራታና ግድም ክላስተር በተቆጣጠራቸው ቀጠናዎች ላይ የነበረውን ይዞታ በፅኑ መሠረት ላይ እያጠናከረ በጠላት ላይ አመርቂ ድል አስመዘገበ።
በአራት አቅጣጫዎች የተሰነዘረበትን ጥቃት ከካራ ለጎማ ቀበሌ እስከ አርሶ አባ ዘንቦ ድረስ በነበረው ውጊያ የክፍለ ጦሩ የደህንነትና የወታደራዊ መዋቅር እጅግ በተቀናጀና መብረቃዊ በሆነ ፍጥነት በአንድ ጊዜ በአራት አቅጣጫዎች የተቀናጀ እርምጃ ወስዷል ።
➡ በበርግቢ ቀበሌ ኦፕሬሽን፦ የክፍለ ጦሩ አባላት ከአርብ ገበያ በመነሳት፣ የጠላትን ወታደራዊ የደህንነት መረብ በመበጠስ በርግቢ ቀበሌ ውስጥ በስኬት ሰርገው መግባት ችለዋል ። በዚህም የህዝብን ደህንነት አደጋ ላይ ጥሎ የነበረውን የሚሊሻ አባል በቁጥጥር ስር በማዋል የጠላትን ዓይንና ጆሮ ሙሉ በሙሉ አሳውረዋል ።
➡ የሞሉ ባህር ፍልሚያ፦ በዚያው ተመሳሳይ ሰዓት ከአጣዬ ከተማ በ-2 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ልዩ ስሟ «ሞሉ ባህር» በተባለች ስፍራ ጀግኖቹ ባደረሱት ከባድ ጥቃት በርካታ የጠላት አባላት እስከመጨረሻው ሲሸኙ፣ ወታደራዊ አቅማቸውን የሚያዳክም ልዩ ልዩ ቁሳቁሶች ተማርከዋል ።
የተማረኩ የጦር መሣሪያዎች፦
1.ሁለት(2) ጥርጥር
2.አምስት (6) ካዝና
3.45 የክላሽ ጥይት
4.ሁለት የደረት ትጥቅ
ሲሆኑ በቁጥር በትክክል ያልታወቁ የጠላት ኃይሎች መደምሰሳቸውና መቁሰላቸው ተረጋግጧል ።
➡ በፈረዱሃ ቀበሌና
በተመሳሳይ ሰዓት ወደ ፈረዱሃ ቀበሌ የዘለቁት የነፃነት ታጋዮቹ፤ ከወገንና ከሀገር ደህንነት ይልቅ ሆዳቸውን ያስቀደሙ፣ ለጥቅም ያደሩ የባንዳ ሚሊሻዎችን አንገት የሚያስደፋና ዳግም እንዳያንሰራሩ የሚያደርግ ከባድ እርምጃ ወስደዋል ። በዚህም የቅጥረኛ ሚሊሻ ስብስብ ግማሹ ሲደመሰስ፣ የቀሩት ደግሞ በከባድ ቁስለኛ ሆነዋል።
1. ተኮላ ሰብስቤ (የተደመሰሰ)
2.ነጋሽ (የተደመሰሰ)
3.ኮማንደር መሀመድ ( ቁስለኛ )
4.ሰለሞን በከባድ ቆስሎ ሪፈር የተላከ ።
➡ በተጨማሪም በዚሁ ተመሳሳይ ሰዓት በሸዋሮቢት አካባቢ የአገዛዙን ወንበር ጠባቂዎች በማስከዳት፣ አንድ የሳይፐር (Sniper Rifle) የጦር መሣሪያ ከነሙሉ ተተኳሹ ለትግሉ ገቢ ማድረግ የተቻለበት ትልቅ ስኬታማ ሥራ ተሰርቷል ።
ክፍለ ጦሩ ላስመዘገበው ድል በማሕበረሰባችን የመረጃ ትብብር ነውና ሕዝባችንን ከዚሕ በላይ የሚያኮራ የነፃነት ገድል ለመስራት በሙሉ ዝግጅት ላይ ነን ሲል የክፍለ ጦሩ ሪፖርተር ገልፆል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!!
በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ አንኮበር ክላስተር እቴጌ ጣይቱ ክፍለጦር ከፍተኛ ድል ሲቀዳጅ ደጃዝማች ተሰማ ክ/ጦር ባንዳን በቁጥጥሯ ስር አዋለች!!
ሐምሌ 7/2018 ዓ.ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ተጉለትና ቡልጋ አውራጃ፣ አንኮበር ክላስተር ልዩ ስማቸው «ጥዳአምባ» እና «ሎዛ» በተባሉ ቦታዎች ላይ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ የአርበኛ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር ስር የሚንቀሳቀሰው የእቴጌ ጣይቱ ክፍለጦር (4ኛ ሻለቃ) በጠላት ኃይል ላይ መብረቃዊ ጥቃት ፈፅሞ ድል አስመዝግባለች።
በጠላት ላይ የተወሰደው እርምጃ ሌሊቱን ሙሉ የጠላትን ኃይል በመክበብ፣ ጠዋት 12፡00 ላይ ውጊያው ተጀምሮ እስከ ማርፈጃው 3፡00 ሰዓት ድረስ ቀጥሏል። በሁለት አቅጣጫዎች ወደ ጠላት በመጠጋት የጠላትን ምሽጎች ሰብሮ መግባት ሲሆን፤ በዚህም ከፍተኛ ሰብአዊ ኪሳራ የደረሰበት የጠላት ኃይል ሙትና ቁስለኛቸውን ተሸክመው ምሽጉን ጥሎ ለመፈርጠጥ ተገዷል።
በጠላት ላይ የደረሰ ጉዳት፦
. 4 የሞተ መከላከያ አባል
. 8 የቆሰለ መከላከያ አባል
በተያያዘ ዜና፦ የደጃዝማች ተሰማ እርገጤ ክፍለ ጦር የስርዓቱን ቅጥረኛ የሆነው አቶ አለሙ ደጀኔ ቀደም ሲል በሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር 03 ቀበሌ የሚልሻ አባል የነበረው ለአገዛዙ መረጃ ሲያቀብል በሸዋሮቢት 06 ቀበሌ በቁጥጥር ስር አውሏል። ይሕ ግለሠብ መሳሪያ የመሸከም አቅሙ ሲደክም በፋኖ ቀጣና በቀን ሰራተኛነት ተሠማርቶ መረጃ እንዲያቀብል ተልእኮ ተሰጥቶት ሲሰራ እንደነበር ግለሰቡ ቃሉን ሠጥቷል። በወር 1,500 ብር እየተከፈለው ግዳጁን ሲያሳካ 50,000ብር እደሚከፈለውም ተፈራርሞ እደመጣ ተናግሯል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!!
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋትና ጥሙጋ አውራጃ አንፆኪያ ገምዛ ወረዳ የኩሬ የጎደል ቀበሌ ህዝብ ጋር ሰፊ ህዝባዊ ውይይት ተደረገ።
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መሐመድ ቢሆነኝ ኮር አስቴጎማ ተራራ ክፍለጦር ነፃ ካወጣቸው ቀበሌዎች አንዷ የሆነችው በኩሬ የጎደል ቀበሌ አገዛዙ ከሚገኝበት የወረዳ ከተማ በስድስት ኪሎ ሜትርእርቀት ላይ የምትገኝ ቀበሌ ሲሆን በቀን 05/11/2018 ዓ/ም በኩሬ የጎደል ቀበሌ አቧር ከተማ ከቀበሌውህዝብ ጋር ሰፊ ህዝባዊ ውይይት ተደረጓል።
ህዝቡ ሴት ወንድ ሳይል በነቂስ ወጥቶ ስብሰባውን የተሳተፈ ሲሆን መድረኩን የመሩት የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አበበ ሙላቱ እና ሌሎችም የዕዝ ፥የኮር እና የክፍለ ጦር አመራሮች ተገኝተዋል።
ለመወያያ የተመረጡ አጀንዳዎች የትግላችን ገፊ ምክንያቶች፥ ትግላችን ያለበት ደረጃ ፥ልማትና ትግል እድሁም ህዝባዊ አደረጃጀትን ማጠናከር የሚሉ ናቸው።
ለማህበረሰባቸን የትግሉ ገፊ ምክንያቶች የተዘነጉ ባይሆንም ብልፅግና በየጊዜዉ ከሚሰራው ደባ አንፃር ለማህበረሰቡ አፅንኦት እየሰጡ ንቃተ ህሊናውን ማሳደግ ተገቢ መሆኑ ታምኖበት ነው በአጀንዳነት የቀረበው በማለት የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ አስረድተዋል።
የትግሉ ገፊ ምክንያቶች እና ትግላችን የደረሰበትን የእድገት ደረጃ ለተሰብሳቢው ማህበረሰብ በስፋት ያብራሩት የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላት በህዝቦች ላይ የተደቀነው የህልውና አደጋ አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ አማራጭ ወደለለው የትጥቅ ትግል ገብተናል ሲሉ ተናግረዋል።ቃል አቀባዩ አክለውም ይህ አሸባሪ የብልጽግና መንግስት ከስልጣን እስካልተወገደ ድረስ የአማራ ህዝቡ እደ ህዝብ ከምድረ ገፅ መጥፋቱ የማይቀር ነው በማለት የስርዓቱን አስከፊነት ምን ያክል ጨካኝ እደሆነ አስረድተዋል።
አርበኛ አበበ ሙላት እዳሉት የአማራ ህዝቡ በደረሰበት የህልውና አደጋ በተበታተነ መልኩ ትግል ቡንጀምርም የሴርኞችን ሴራ በጣጥሶ ዛሬ ላይ እውነተኛ አታጋይ የሆነውን ድርጀት የአማራን ቤት አፋብንን መመስረት ችለናል ብለዋል።
ይህ ድርጅት ብዙ ሙህራንንና የሰለጠነ ወታደራዊ አዛዦችን የያዘ ስለሆነ በአጭር ጊዜ ውስጥ በቀጠናው ተፅእኖ ፈጣሪ ድርጅት ለመሆን በቅቷል። ያሉት አርበኛ አበበ ሙላት አክለውም የድርጅት አሸባሪውንና ፀረ አማራ የሆነውን የብልፅግና መንግስት ከስልጣኑ እሲኪወገድ ድረስ አምርሮ ይታገላል ደግሞም ያስወግደዋል ብለዋል።
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የፍትህ መምሪያ ሃላፊ አርበኛ ፈለቀ ሙላቱ በትግል ላይ ሆነን ህዝባችን በፍትህ እጦት እዳይቸገር የፍትህ መዋቅሩን አስተካክለን የፍትህ አገልግሎት እየሰጠን እንገኛለን በማለት ገልፀዋል።
ስብሰባ የተሰበሰበውን ህዝብ በማዝናናት እና ስነልቦናውን በመገንባት ከፍ በማድረግ ከፍተኛውን ድርሻ ደግሞ የተወጣው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ወታደራዊ ባህል ቡድን አባል አርበኛ ንዋይ በቀረርቶና በፉካሮ ስብሰባውን አድምቆታል።
በስብሰባው የታደሙት ሃሳብ ሰጪዎች በቀረበላቸው ሃሳቦች መደሰታቸውን ገልፀው ለቀጣይ ከድርጅታችን ከአፋብን ጎን ሆነው እደሚታገሉ አረጋግጠዋል። ይህ በእንዲህ አንዳለ አንዳንድ አሉብን የሚሏቸውንም ጥያቄዎች ለመድረክ መሪዎች ለማቅረብ ችለዋል።በቀረቡት ጥያቄዎች ላይከመድረክ ተገቢ የሆነ መልስ ከተሰጠ በኋላ የማጠቃለያ ንግግር በአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አበበ ሙላት ተደርጎ የእለቱን ስብሰባ ተጠናቋል።
ክብር ለትግሉ ስማአታት
ህልውናችን በተባባረ ክንዳችን
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት
ሃምሌ 6/2018 ዓ/ም
አፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕ ከሰም ፪ኛ ኮር ኃይለማርያም ክ/ጦር እና አክሊሉ ኃብተወልድ ክ/ጦር በሚገኙበት ቀጠና በስምንት አቅጣጫ ወረራ ላማድረግ የሞከረው የአገዛዙ ቅጥረኛ ሰራዊት፤ በንፁሃን ዜጎች ላይ የግድያና ዘረፈ ድርጊቶችን ፈፀመ ።
ሃምሌ 05/2018 ዓ.ም፡ ሸ/ጠ/ግ/ አሳምነው ዕዝ ከሰም ፪ኛ ኮር በኃይለ ማርያም ማሞ ክፍለ ጦር እና በአክሊሉ ኃብተ ወልድ ክፍለጦር ላይ በስምንት አቅጣጫ ወረራ ለመፈፀም የሞከረው የብልፅግናው ሰራዊት አሰቃቂ የሆነ የዘረፋና የግድያ ድርጊቶችን እንደፈፀመ ተገልጿል ።
የአገዛዙ ሰራዊት ድርጊቱን የፈፀመባቸው አከባቢዎች፤ በቅዲሥ-ጌዬ ቀበሌ፣ ዛላ-ዘንባባ ቀበሌ፣ ውሃ ሜዳ ቀበሌ፣ በኮረማሽ ሸረር 3 አምባ እና የለጥ ታቦት ዋሻ፤ እንዲሁም በአክሊሉ ኃብተ ወልድ ክፍለ ጦር በቁልቋል አይብ አምባ ቀበሌ፣ አምፋር ጨመሪ ቀበሌ፣ በጎ ጥጥ አምባ ቀበሌዎች ወረራ ለማድረግ የሞከረው የብልፅግናው ሰራዊት፤ የፋኖ ክንድን መቋቋም ሲሳነው፤ በከፍተኛ ሁኔታ የህዝብ የጋራ መገልገያ የሆኑ ት/ቤቶችን እና ጤና ኬላዎችና የግብርና ቢሮችን ዘርፎ ሲያወድም በማህበረሰቡ መኖሪያ ቤቶችና የቤት እንሰሳ በዘረፋና በማውደም በንፁሃን ዜጎች ላይም ያነጣጠር ግድያ መፈፀሙ ታውቋል ።
▪ የተዘረፉ የንፁሃን ዜጎች ንብረቶችና ግድያዎች ፦
➢ ውሃ ሜዳ ቀበሌ የሁለት (2) ግለስብ፡ አራት (4) በሬዎችና የአንድ ግለሰብ ከ10 በላይ የእህል ማደበሪያ ተዘርፏል ።
➢ በሸረር 3 አምባ ቀበሌ የቀበሌውን ት/ት ቤት ሙሉ ለሙሉ ሲያወድም፤ እንደ ኮምፒውተርና የሶላር ሲስተም እቃዎች የመሳሰሉት ሲዘረፍ፤ ቀሪውን ቢሮችን በመሰባበር የተለያዩ ሰነዶች ወድመዋል ።
➢ ሁንያለው ጌታቸው የተባለ ግለሰብ ሲገደል፤ ምንጯ ሀይሉ የተባለች ባለግሮሰሪ ሙሉ በሙሉ እቃዎቿን በመሰባበርና ቀሪውን ንብረቶች ተዘርፈው ወድመዋል ።
➢ በቁልቋል አይብ አምባ ቀበሌ፤ አንድ (1) ንፁሃን አርሶ አደር በመኖሪያ ቤቱ አቅራቢያ ሆን ተብሎ በማነጣጠር ተገድሏል ።
ይህ የጥፋት ተልዕኮ ያነገበው ሰራዊት በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ በአቶ መካሻ አለማየሁ እና በወረዳው አሥተዳዳሪና አመራሮች፤ አቶ አባይ ግዛው እና ተገኝ አሠፋ አዛዥነት በሰራዊቱን ሆን ተብሎ ንፁሃን ዜጎች እንዲገደሉ እና ዘረፋ እንዲፈፀም አድርገዋል ።
ምንጭ-አፋብን ሸ/ጠ/ግ/ አሳምነው ዕዝ ከሰም ፪ኛ ኮር ሚዲያና ኮምኒኬሽን ክፍል ሀላፊ
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
ሸዋ ጠ/ግ/አ/ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሀምሌ 06/2018 ዓ.ም
+6
የንጉሥ ሣህለ-ስላሴ ክፍለ ጦር ለ3ኛ ዙር የፋኖ ሰራዊት አባላትን አስመረቀ!!!
ሐምሌ 06 ቀን 2018 ዓ.ም
በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር ስር የሚገኘው ንጉሥ ሣህለ-ስላሴ ክፍለ ጦር ለተከታታይ ወራት የፖለቲካና ወታደራዊ ስልጠና ሲሰጣቸው የነበሩትን የ3ኛ ዙር ምልምል መደበኛ የፋኖ ሰራዊት አባላትን ሐምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም አስመርቋል።
በሳሲት ክላስተር በተካሄደው የፋኖ ሰራዊት ምርቃት ፕሮግራም ላይ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች፣ የኮር፣ የክፍለ ጦር እንዲሁም የተጉለትና ቡልጋ አውራጃ የቀበሌ አመራሮች ተገኝተዋል።
የክፍለ ጦሩ ዋና አዛዥ መቶ አለቃ ደሞዝ አሽኔ ለተመራቂዎቹ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን፣ የሰልጣኞችን መታወቂያና ሰርተፍኬት አበርክተዋል። ለስኬቱ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላትም ምስጋና አቅርበዋል።
በምርቃ መርሃ ግብሩ የዕዙ የፖለቲካ አመራሮች የተገኙ ሲሆን አርበኛ መስፍን ተስፋዬ እና አርበኛ ሀኪም ግዛቸው ሣህለ ተጉለትና ቡልጋ የበርካታ ነገስታት መፍለቂያ መሆኑን በመጥቀስ፣ ተመራቂዎቹ የዚህ ታሪካዊ ማህበረሰብ አካል በመሆናቸው የተሰማቸውን ኩራት ገልጸዋል።
የተጉለትና ቡልጋ አውራጃ የሳሲት ክላስተር ዋና አስተዳደሪ አርበኛ ኃይሉ ለገሰ ለተመራቂዎቹ የቃል ኪዳን አደራ የሰጡ ሲሆን፣ ለአሰልጣኞች የማበረታቻ ሽልማት እንዲሁም ለክላስተርና ቀበሌ አመራሮች የክብር እውቅና በመስጠት በደማቅ ሁኔታ ተጠናቋል።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!!
ጀግና አይሞትም፤ ታሪክ ሁሌም ያዘክረዋል!
ቀን፦ ሐምሌ 05/2018 ዓ.ም
ክብር እና መፅናናት ለአርበኛ ፀጋው ታፈሰ እና ለቀኝአዝማች አቡ አሳመረው ቤተሰቦች፣ ጓዶችና ለመላው የአማራ ህዝብ!
ታሪክ ራሱን በጀግኖች ደምና አጥንት ይፅፋል። ትናንት በመርሐቤቴ አውራጃ፣ ላይ ቤት ወረዳ በኮላሽ ተራራማ ስፍራ በነበረው ታላቅ ፍልሚያ፤ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርዓያዕቆብ ኮር ናደው ክፍለ ጦር ባደረገው የላቀ ጀግንነት የአገዛዙ ትልቅ የቁም ምሽግ ሲሰባበር፣ የጠላት ዋይታ በየጉድጓዱ አንባርቋል። የአገዛዙን ቅልብ ኮማንዶ በያለበት ክፉኛ በመምታት፣ ለወሬ ነጋሪ እንኳ ሳይተርፉ በርካታ የጠላት ኃይሎችን በመደምሰስ የክብር ሰማዕትነት የተቀበሉት አርበኛ ፀጋው ታፈሰ እና ቀኝአዝማች አቡ አሳመረው ለሕዝባቸው ያላቸውን ፍቅር እና የገቡለትን ቃል በአንድያ ነፍሳቸው በተግባር አስመስክረዋል።
እነዚህ የቁርጥ ቀን ጀግኖች በፋኖ ማዕቀፍ ውስጥ በመሆን ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ለአማራ ሕዝብ ህልውና፣ ክብርና መብት ሲሉ በግንባር ቀደምትነት የተሰለፉ፣ ያዋጉ፣ የተዋጉና ሕዝብን በማደራጀት ረገድ የተዋጣላቸው የትግሉ አብሪ ኮከቦች ነበሩ። ዛሬም እንደ ትናንቱ በኮላሽ ጠንካራ የቁም ምሽግ ላይ ታሪክ ዘላለም ሲዘክረው የሚኖር የጀግንነት ሥራ ሠርተው አልፈዋል።
• አርበኛ ፀጋው ታፈሰ፦ መርሐቤቴ ሰራዊት በማደራጀት እስከ ምስራቅ አማራ ድረስ በግንባር ቀደምትነት የተሰለፈ፣ የታገለና ያታገለ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው።
• ቀኝአዝማች አቡ አሳመረው፦ የመጀመሪያውን የአጣዬና የደራን የጠላት ከበባ ከሰበሩ አብሪ የትግል መሪዎች አንዱ ሲሆን፤ ይመራው የነበረውንም ሰራዊት ለአማራ ሕዝብ ህልውና ሲባል "ምርጫችን ወይ ሞት ወይ ማሸነፍ!" በሚል መርህ ያታገለ ጀግና ነበር።
እነዚህ የሸንቁጥ ልጆች፣ አባቶቻቸው ከፋሺስት ጣሊያን ጦር ጋር ታሪክ በሠሩበት በታሪካዊቷ ላይ ቤት ወረዳ ኮላሽ ሰንሰለታማ ተራራ ላይ የብልፅግናን ሰራዊት ለወሬ ነጋሪ ሳይተርፍ ካረገፉ በኋላ፣ ውድ ሕይወታቸውን በጀግንነት ለአማራ ሕዝብ ህልውና ሲሉ ሰውተዋል።
በዕለቱ የነበረው ተጋድሎ ወደር የሌለው ነበረ፤ ጀግኖቹ ሙሉ አንድ ሻለቃ የጠላት አየር ወለድን ያንበረከኩ፣ በጀግንነት መሃል ገብተው የቦምብ ናዳ በማውረድ ታሪክ የሠሩ ብርቅዬዎች ነበሩ። ምንም እንኳ እነዚህ የቁርጥ ቀን ልጆች ሙሉ ድሉ ከመጠናቀቁ በፊት ቢሰዉም፣ ያፈሯቸው ሺህ ጀግኖች ግን ዓላማቸውን አንግበው ተልዕኮውን ፈጽመዋል። የጀግኖቹ ደም በከንቱ አልቀረም፤ የጀመሩት እና የመሩት ውጊያ በተተኪዎቹ የናደው ክፍለ ጦር አናብስት በተቀጣጠለ ወኔና ልዩ የመዋጋት ጥበብ ቀጥሎ፣ በጠላት ላይ ሙሉ በሙሉ በደረሰ የድምሰሳ ፍጻሜ ተጠናቋል። የጀግኖቹም ደም በድል ተክሷል። በዕለቱም ማትያስ ማድቦ ሲመራው የነበረ ጦር በጀግኖቹ ምት በኮላሽ ተራራ ተቀብሮ የብልፅግና ሹማምንቶችን ሀዘን ያስቀመጠ ክስተት ሆኖ አልፏል።
"ጀግና ቢወድቅም የጀመረው ዓላማና የለኮሰው የነጻነት እሳት መቼም ቢሆን አይጠፋም።"
• ለተከበሩ ቤተሰቦቻቸው፦ በእንዲህ ዓይነት የቁርጥ ቀን የህልውና ዋስትና የሆኑ ጀግኖችን ለአማራ ሕዝብ ያበረከታችሁ የጀግና ወላጆችና ቤተሰቦች፤ ሐዘናችሁ የሁላችንም ሐዘን ቢሆንም ማኅፀናችሁ በኩራትና በክብር ሊመሰገን ይገባዋል። ፈጣሪ ጽናቱንና መጽናናቱን ይስጣችሁ።
• ለትግል ጓዶቻቸው፦ የአብሮነት፣ የደምና የዓላማ ጓዶቻቸው የሆናችሁ የነጻነት ታጋዮች፤ የጀግኖቹ መውደቅ የትግል ወኔያችሁን የሚያጠነክር፣ የተረከባችሁትን አደራ በድል ለማጠናቀቅ ጉልበት የሚሆን ነው። የአማራ ሕዝብ ህልውና የሚረጋገጠው በጀግኖች መስዋዕትነት እና ጠላትን በየቦታው በመቅበር በመሆኑ፣ ከትናንቱ ነገ ይበልጥ እንድትጠነክሩ ያደርጋችኋል። ጀግንነታችሁ ይቀጥል!
• ለመላው የአማራ ሕዝብ፦ ሕዝባችን እንደነዚህ ያሉ ውድ ልጆቹን ለነጻነቱና ለህልውናው ሲል መስዋዕት አድርጓል። ታሪክ የማይረሳቸው እነዚህ ሰማዕታት የቁጭትና የድል አርማዎቻችን ናቸው።
የጀግኖቹ የአርበኛ ፀጋው ታፈሰ እና የቀኝአዝማች አቡ አሳመረው ስምና ታሪክ በትውልድ ልብ ውስጥ ለዘላለም ሕያው ሆኖ ይኖራል!
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! ፈጣሪ ለቤተሰቦቻቸውና ለጓዶቻቸው መፅናናትን ይስጥ!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት እና በወሎ ቤተ-አማራ የተመዘገቡ ወታደራዊ ድሎች
ሐምሌ 04 ቀን 2018 ዓ.ም።
1. የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ግንባሮች
ሀ. በመርሐቤቴ አውራጃ፦
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሥር የሚገኘው አፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር በናደው ክፍለ ጦር ጠላት ተደመሰሰ።
ኮላሽ ተራራማ ስፍራ እና አለም ከተማ ዙሪያ (በልዩ ስሙ ዘይታና አከያ መስክ) በተባለ ቦታ ላይ ከሌሊቱ 10:00 ጀምሮ በተወሰደ መብረቃዊ ጥቃት የጠላት ምሽግ ሙሉ በሙሉ ተሰብሯል። አንድ የጠላት ኃይል የጫነ 'ኦራል' ተሽከርካሪ በቦንብ ተመቶ ወድሟል። የኮላሹን ኃይል ለመታደግ ከፌጥራ እስከ አለም ከተማ የተንቀሳቀሰው ኃይል በደፈጣ ተመቷል።
በጠላት ላይ የደረሰ ኪሳራ፦
3 የኮማንዶ አመራሮች ተማርከዋል።
1 ብሬን፣ 7 ክላሽንኮቭ፣ 3 መውዜር፣ 2 ሬዲዮ መገናኛ፣ 2 ኤፍ-1 ቦንብ እና 360 ጥይቶችን ጨምሮ በርካታ ትጥቆች ተማርከዋል።
በሽንፈቱ የተበሳጨው የአገዛዙ ኃይል በዙ-23 እና ሞርተር በንፁሃን አርሶ አደሮች ላይ የበቀል ጥቃት እየሰነዘረ ይገኛል።
ለ. በደገም ወረዳ ግንባር፦ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሥር የሚገኘው አፄ አምደጽዮን ኮር በራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር - 2ኛ አሊ ሻለቃ
ልዩ ቦታው ሀሮ እና አቦ ለሊሳ (ግራሪያ/ፍቸ ሰላሌ) ላይ ከንጋቱ 12:00 እስከ ቀኑ 5:00 ድረስ በተወሰደ እርምጃ ህዝብን፣ ብሔርና ሃይማኖት ሳይለይ ሲዘርፍ በነበረው የሸኔ ቡድን ላይ የማያዳግም እርምጃ ተወስዷል።
በዚህም የጠላት ካምፕ ተሰብሮ በርካታ የቡድኑ አባላት ተደምስሰዋል። 7 የጦር መሣሪያዎች ሲማረኩ፣ ከተዘረፉት ውስጥ 9 የቀንድ ከብቶች እና 15 በግና ፍየሎች ተመልሰው ለአርሶ አደሩ ተሰጥተዋል።
ሐ. በመንዝ አውራጃ ግንባር፦ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሥር የሚገኘው አፄ አምደ ፅዮን ኮር በአፄ ምኒልክ ክፍለ ጦር ሞላሌ ከተማ (መንዝ ማማ ክላስተር) ላይ በሌሊት በተደረገ ሰርጎ የመግባት ኦፕሬሽን እና በአባት አርበኞች በተወሰደ አጸፋዊ እርምጃ የብልጽግና አገዛዝ ታጣቂዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።
በዚህም የወረዳው የሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ (አቶ ችላባለው) እና የሚሊሻ መቶ መሪው (ኃይሉ ከፈለውን) ጨምሮ ሌሎች አባላት ተደምስሰዋል። በርካታ የቆሰሉ የጠላት ኃይሎች በሞላሌ ሆስፒታል ይገኛሉ።
2. የወሎ ቤተ-አማራ ግንባር
ሀ. በላሊበላና አካባቢው ግንባር፦ የአፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ሥር የሚገኘው 303ኛ አሳምነው ኮር (በ21ኛ ተከዜ ክፍለ ጦር እና 16ኛ ነብሮ ተወርዋሪ ኮማንዶ ክፍለ ጦር) አማካኝነት መነሻውን ኩልመስክና ላሊበላ አድርጎ ወደ ገነተማርያም በተንቀሳቀሰው ኃይል ላይ በተወሰደ እርምጃ በዙ-23 እና በ107 የተደገፈውን የጁላ ሰራዊት ስቦ በማስገባት እና በመቁረጥ ከፍተኛ ኪሳራ ማድረስ ተችሏል።
በዚህም ከ55 በላይ ጠላት ሲደመሰስ፣ ከ30 በላይ ቆስሏል። 42 ጥቁር ክላሽንኮቭ፣ 1 ሬዲዮ መገናኛ፣ 27 የደረትና የወገብ ትጥቆች እንዲሁም 36 ሻንጣዎች ተማርከዋል።
ልዩ መረጃ፦ አንድ የአገዛዙ ሰራዊት አባል 1 ጥቁር ስናይፐር እና 1 ጥቁር ክላሽ ይዞ 16ኛ ነብሮ ተወርዋሪ ኮማንዶ ክፍለ ጦርን በራሱ ፍቃድ ተቀላቅሏል። ይቀጥላል.....
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አበበ ሙላት
የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ
ሰበር የድል ዜና ❗❗
ከኮላሽ ተራራማ ስፍራ እስከ አለም ከተማ ጫፍ በናደው ክፍለጦር ታሪክ ሰራ!
ሐምሌ 04 ቀን 2018 ዓ.ም
ሸዋ ጠቅላይ ግዛት — አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር ናደው ክፍለ ጦር በመርሐቤቴ አውራጃ በታሪካዊቷ የኮላሽ ተራራማ ስፍራና በአለም ከተማ ዙሪያ ሰፍሮ በነበረው የብልፅግና አገዛዝ ሰራዊት ላይ የናደው ክፍለጦር ጀግኖች መብረቃዊ ጥቃት በመሰንዘር አኩሪ ድል አስመዝግበዋል።
ዛሬ ከሌሊቱ 10:00 ጀምሮ በላይ ቤት ኮላሽ ተራራ ላይ የገባው የክፍለጦሩ ሻለቃ የጠላትን የቁም ምሽግ ሙሉ በሙሉ በመበተን አካባቢውን በቁጥጥሩ ስር በማድረግ ፤ በተጨማሪም በዞማ ዙሪያ እና ከአለም ከተማ መውጫ በአከያ መስክ ላይ የሠፈረውን የጠላት ኃይል ሌላኛዋ የክፍለጦሩ ሻለቆች በቅንጅት ተቆልፎ የተያዘ ሲሆን፣ በተደረገው የጨበጣ ውጊያ የጠላት ክፉኛ ተመቷል። በዚህ አስደናቂ ውጊያ አንድ ሙሉ የአገዛዙን ታጣቂ የጫነ ኦራል ተሽከርካሪ ልዩ ስሙ ዘይታ በተባለ ቀበሌ በቦንብ ተመቶ ከነጫነው የሰው ሀይል ወደ አመድነት ተቀይሯል።
ሽንፈቱን ተከትሎ ከፌጥራ እስከ አለም ከተማ ያለውን ጥምር ኃይል በማንቀሳቀስ የኮላሹን ኃይል ለመታደግ የሞከረው የጠላት እቅድ፣ በአለም ከተማ አቅራቢያ በተጣለበት አስደንጋጭ ደፈጣ መክኗል። በአሁኑ ሰዓት ጀግኖቹ ቦታቸውን ይበልጥ እያሻሻሉ ሲሆን፣ በጀግኖቹ የአልሞ ገዳይ (ስናይፐር) ቡድን ክፉኛ የተመታውና የተበታተነው የጠላት ኃይል ሙትና ቁስለኛውን ለመሰብሰብ በመወራጨት ላይ ይገኛል። ነገር ግን ከጀግኖቹ ባሩድ የተረፈ የለም።
የጠላት ኃይል በኮላሽ ተራራማ ቦታ ከአመራሮቹ ጋር ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የተደመሰሰ ሲሆን፣ የሚከተሉት ወታደራዊ ቁሳቁሶች እና የጠላት ሀይል በጀግኖቹ ቁጥጥር ስር ውለዋል፦
✔ 03 የኮማንዶ አመራሮች ተማርከዋል
✔.01 ብሬን (ከነሙሉ ሸንሸሉ)
✔.07 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ
✔.03 ማውዘር (መንቶፍ)
✔.02 መገናኛ ራዲዮ
✔.02 ኤፍ-1 ቦንብ
✔.12 ካዝና እና
✔. 07 የደረት ትጥቅ
360 የክላሽ ተተኳሽ ጥይቶችና ሌሎች ልዩ ልዩ ወታደራዊ ቁሳቁሶች መማረክ ተችሏል።
የተስፋ መቁረጥ እርምጃ
በጀግናው ናደው ክፍለጦር ክንድ የደረሰበትን ከባድ ኪሳራ መቋቋም ያልቻለው የአገዛዙ ኃይል፣ በተለመደው የሽንፈት ባህሪው ዙ-23 እና ሞርተር በመጠቀም በንፁሃን አርሶ አደሮች መኖሪያ ቤቶችና ንብረቶች ላይ የበቀል ጥቃት በመሰንዘር ላይ ይገኛል። ኮሩ ከግንባር ያደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ አሁን የተጀመረው ስልታዊ ማጥቃት ተጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን ጠላትን በእያንዳንዱ ምሽግ የመቅበሩ ስራ ይቀጥላል ሲል ገልጿል ።ሌሎች ተያያዢ ዝርዝር መረጃዎችን በሚደርሰን መረጃ ይዘን የምንመለስ ይሆናል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
+1
በመንዝ አውራጃ በሞላሌ ከተማ በተሰነዘረ ጥቃት የወረዳው የሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊና የመቶ መሪ መገደላቸው ተገለጠ!!
ሐምሌ 4 ቀን 2018 ዓ.ም
በመንዝ ማማ ክላስተር ሞላሌ ከተማ ውስጥ በብልጽግና አገዛዝ ሠራዊት ላይ በተሰነዘረ ድንገተኛ ጥቃት፣ የወረዳው የሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ እና የአንድ መቶ መሪ መገደላቸውን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር አስታወቀ።
የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ባወጣው መረጃ መሠረት፣ ዛሬ ሐምሌ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ሌሊት የአፄ ምኒልክ ክፍለ ጦር ቃኚዎች ወደ ሞላሌ ከተማ ሰርገው በመግባት በወሰዱት የማያዳግም እርምጃ የሚሊሻ መቶ መሪ የሆነውን ኃይሉ ከፈለውን እስከወዲያኛው ሸኝተውታል። በዚሁ ጥቃት በሌሎች የአገዛዙ ሠራዊት ላይም ከፍተኛ ጉዳት መድረሱ ተገልጧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የፋኖ ቤተሠብ ከብቶችን ዘርፈው በመሸሽ ላይ በነበሩ የሚሊሻ አባላት ላይ በአካባቢው የሚንቀሳቀሱት የአባት አርበኞች በወሰዱት አጸፋዊ እርምጃ፣ የመንዝ ማማ ወረዳ የሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ችላባለው የተባሉ ግለሰብና ሌሎች የሚሊሻ አባላትም ተገድለዋል። በጥቃቱ የቆሰሉ በርካታ የአገዛዙ ሠራዊቶች በአሁኑ ወቅት በሞላሌ ከተማ ሆስፒታል ገብተው በመታከም ላይ እንደሚገኙ የኮሩ መግለጫ ያመላክታል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
Repost from ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
+1
በመንዝ አውራጃ በሞላሌ ከተማ በተሰነዘረ ጥቃት የወረዳው የሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊና የመቶ መሪ መገደላቸው ተገለጠ!!
ሐምሌ 4 ቀን 2018 ዓ.ም
በመንዝ ማማ ክላስተር ሞላሌ ከተማ ውስጥ በብልጽግና አገዛዝ ሠራዊት ላይ በተሰነዘረ ድንገተኛ ጥቃት፣ የወረዳው የሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ እና የአንድ መቶ መሪ መገደላቸውን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር አስታወቀ።
የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ባወጣው መረጃ መሠረት፣ ዛሬ ሐምሌ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ሌሊት የአፄ ምኒልክ ክፍለ ጦር ቃኚዎች ወደ ሞላሌ ከተማ ሰርገው በመግባት በወሰዱት የማያዳግም እርምጃ የሚሊሻ መቶ መሪ የሆነውን ኃይሉ ከፈለውን እስከወዲያኛው ሸኝተውታል። በዚሁ ጥቃት በሌሎች የአገዛዙ ሠራዊት ላይም ከፍተኛ ጉዳት መድረሱ ተገልጧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የፋኖ ቤተሠብ ከብቶችን ዘርፈው በመሸሽ ላይ በነበሩ የሚሊሻ አባላት ላይ በአካባቢው የሚንቀሳቀሱት የአባት አርበኞች በወሰዱት አጸፋዊ እርምጃ፣ የመንዝ ማማ ወረዳ የሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ችላባለው የተባሉ ግለሰብና ሌሎች የሚሊሻ አባላትም ተገድለዋል። በጥቃቱ የቆሰሉ በርካታ የአገዛዙ ሠራዊቶች በአሁኑ ወቅት በሞላሌ ከተማ ሆስፒታል ገብተው በመታከም ላይ እንደሚገኙ የኮሩ መግለጫ ያመላክታል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
