en
Feedback
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ

አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ

Open in Telegram
5 084
Subscribers
+1124 hours
-157 days
-7730 days
Posts Archive
+3
የእዙ ከፍተኛ አመራሮች ክፍለጦሩ በተሰማራበት የግዳጅ ቀጠና ላይ በመገኘት የተሳካ ውይይት አደረጉ!! ሀምሌ 4/2018 ዓ.ም አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አ/ ዕዝ የመሃመድ ቢሆነኝ ኮር የወንዱ አስቻለው ደሴ ክፍለጦር የግዳጅ ቀጠና ላይ ከተሰማሩ የክፍለጦሩ አመራሮችና የሻለቃ አዛዦች ጋር በመንዝና ግሼ አውራጃ ውጤታማ ውይይት ተካሄደ። በውይይቱ ላይ የአሳምነው ዕዝ ከፍተኛ አመራር አርበኛ አዶናይ አበበ፡አርበኛ ዳመን ወርቁን ጨምሮ ሌሎች የእዙ መሪዎች የተገኙ ሲሆን፥ በዋናነት የሸዋ አንድነት፣ ወቅታዊ የትግል ሁኔታ፣ የሀገሪቱን የሀይል አሰላለፍ፣ በሰራዊቱና በህዝቡ መካከል ሊኖር ስለሚገባው ግንኙነት... ሰፊ ውይይቶችን የተደረገ ሲሆን በመጨረሻም የትግሉን አሁናዊ ቁመና በመገምገም በቀጣይ ክፍለጦሩ ማከናወን ስላለበት ዋና ዋና ተግባራት ላይ በጋራ በመምከር ወሳኝ የግዳጅ አቅጣጫዎችን በማውረድ ውይይቱ በስኬት ተቋጭቷል። ክብርና ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት! ድል ለአማራ ህዝብ!! ​ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ​

በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፤ የአፄ ዘርዓ ያዕቆብ ፩ኛ ኮር የአፄ ይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር ወታደራዊ ግምገማ አካሔደ!! ቀን 03/11/2018 ዓ.ም የታጠቀ ሕዝባዊ ኃይሎች የትጥቅ ትግል ጉዟቸውን ስኬታማ ለማድረግ ካላቸው ቁልፍ ስትራቴጂዎች አንዱ የውስጥ ጥንካሬን መፈተሽ፣ ድክመቶችን ማረም እና ቀጣይ ወታደራዊ ግዳጆችን በንቃት ማቀድ ነው። ይህንን መርህ መሠረት በማድረግ፣ በዕለቱ 03/11/2018 ዓ.ም በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ስር የሚገኘው የአፄ ዘረያዕቆብ ፩ኛ ኮር፣ አፄ ይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር ከፍተኛ ወታደራዊ ግምገማ አካሂዷል። በትጥቅ ትግል ስነ-ልቦና ውስጥ የአዛዦችና የሰራዊቱ መግባባት ለውጊያ ዝግጁነት ወሳኝ ሚና ይጫወታል። በዚህ መድረክ ላይ የኮሩ ወታደራዊ ዋና አዛዥ፣ የክፍለ ጦሩ ዋና መሪ ፣ የክ/ሩ ወታደራዊ አዛዡ፣ የሻለቃ አመራሮች እና ሻምበል መሪዎች ድረስ ያሉ ሁሉም የጦር መኮንኖች በሙሉ ተገኝተዋል። ይህ አይነቱ የተዋረድ መሪዎች ጥምረት በትግሉ መስመር ውስጥ ያለውን የዕዝ ሰንሰለት ለማጠናከር እና መመሪያዎችን እስከ ታችኛው የሰራዊት አባል ድረስ በግልፅ ለማውረድ ትልቅ አቅም ይፈጥራል። መድረኩ በኮሩ ወታደራዊ ዋና አዛዥ መቶ አለቃ ተፈሪ የተመራ ሲሆን በመድረኩ እንደገለፀው፣ የተካሄደው ጥልቅ ወታደራዊ ግምገማ እጅግ አመርቂና ስኬታማ ነበር።ለቀጣይም የተሻለ ቁመና እንድኖረን እና ወትሮም ለድርጅታዊ ተልዕኮ የሚያነሳሳ ግምገማ ነው ። በትጥቅ ትግል ሂደት ውስጥ የሚገጥሙ ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎችን በወታደራዊ ሳይንስ መነጽር የገመገመው ይህ መድረክ፣ ሠራዊቱ ለቀጣይ ተልዕኮዎችና ግዳጆች በአዲስ መንፈስና በላቀ ዝግጁነት እንዲነሳሳ አድርጓል ብሏል። ይህ ግምገማ ክፍለ ጦሩ በስትራቴጂካዊና በታክቲክ ረገድ ያለውን ቁመና ያጠናከረበት ሲሆን፣ መላው የክ/ጦር አመራሮችም ለቀጣዩ የትግል ምዕራፍና ለሚሰጡ ማናቸውም ወታደራዊ ግዳጆች ሙሉ ዝግጁ መሆናቸውን በጽናት አንፀባርቀዋል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

#ሰበር ዜና❗️21 የሚሊሻ አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮርን ተቀላቀሉ! ሃምሌ 01/2018ዓ.ም ህዝባቸውንና የነፃነት ታጋይ ፋኖ ልጆቻቸውን ያስቀደሙ የአገዛዙን የሴራ ፖለቲካ በሂደት ጠንቅቀው የተረዱ ፣ ከሰሞኑ በርካታ የሚሊሻ አባላትን ወደ መከላከያ ሰራዊት ለማካታት በአስገዳጅ ሁኔታ ወደ ማሰልጠኛ ተቋም መላክ መጀመሩን ተከትሎ ዛሬ ሃምሌ 01 ቀን 2018ዓ.ም ቁጥራቸው 21 የሚሆን የሚሊሻ አባላት የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር አካል የሆኑ ክፍለጦሮችን መቀላቀላቸውን ኮሩ በመረጃው አስታውቋል። በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ መነሻቸውን ከሚዳ ወረዳ መራኛ ከተማ ያደረጉ 17 የሚሊሻ አባላት የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦርን ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ሲቀላቀሉ፣ ከሞረትና ጅሩ ወረዳ እንዋሪ ከተማ የተነሱ 3 የሚሊሻ አባላት እንዲሁም ከእንሳሮ ወረዳ ለሚ ከተማ የወጣ አንድ የሚሊሻ አባል የራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦርን ከነ ሙሉ ትጥቃቸው መቀላቀላቸውን የአፄ አምደ ፅዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል በላከው የግንባር መረጃ ገልጿል። የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ከአገዛዙ ጋር እስካሁን ድረስ አብረው ለተሰለፉ የፀጥታ ሀይሎች ያቀረበውን ተደጋጋሚ ወንድማዊ ጥሪ ተከትሎ በርካታ የሚሊሻ፣ የአድማ ብተና እንዲሁም የፖሊስ አባላት የዕድሉ ተጠቃሚ መሆናቸውን እየገለፀ ዛሬም ዕዙ የምህረት እጆቹ የተዘረጉ መሆኑን ይገልፃል። "ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!" የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

በተጉለት አውራጃ ደረፎ ክላስተር የገዥው ጥምር ጦር በንጹሃን ላይ ዘረፋ ሲፈፅም፡ አድማ ብተና ሀይሎች ፋኖን ተቀላቅለዋል!! 01/11/2018 ዓ.ም ከደብረ ብርሃን ተነስቶ ወደ አንኮበር ቀጠና ደረፎ
+3
በተጉለት አውራጃ ደረፎ ክላስተር የገዥው ጥምር ጦር በንጹሃን ላይ ዘረፋ ሲፈፅም፡ አድማ ብተና ሀይሎች ፋኖን ተቀላቅለዋል!! 01/11/2018 ዓ.ም ከደብረ ብርሃን ተነስቶ ወደ አንኮበር ቀጠና ደረፎ ቀበሌ ያመራውና ራሱን "ጥምር ጦር" ብሎ የሚጠራው የመከላከያና አድማ ብተና ሰራዊት፣ የፋኖ ኃይላችን በሌሉበት የህዝብ ንብረት መዝረፉ ታወቀ። ሰራዊቱ ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በየቀበሌው በመግባት አርሶ አደሮች ለክረምት ዝግጅት ያከማቹትን 10 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እንዲሁም አቶ ኪዳኔ ከተባለ አርሶ አደር ቤት በመግባት ሥስት(3) ጭነት ባቄላ ዘርፎ መውሰዱ ተረጋግጧል። በዚህ የዘረፋ ተግባር ላይ ለሆዳቸው ያደሩ የአካባቢው ሚሊሻዎችም የተሳተፉበት መሆናቸው ተረጋግጧል። ድርጊቱ እንደተሰማ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ መሐመድ ቢሆነኝ ኮር እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር በፍጥነት ወደ ስፍራው ቢያመራም፣ የገዥው አካል ጦር የዘረፈውን ንብረት ጭኖ ወደ ደብረ ብርሃን ለመፈርጠጥ ተገዷል። ይሕ በእንዲሕ እዳለ አገዛዙ በንፁሀን ላይ የሚፈፅመውን ግፍና ዘረፋ የሠሙት የአገዛዙ ደጀን የነበሩት አድማ ብተና ኃይሎች ፋኖን ተቀላቅለዋል። በዚሕም ሁለት የአድማ ብተና አባላት የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደጽዮን ኮር ራንቦ ክፍለ ጦርን ከነ ሙሉ ትጥቃቸው በቀን 01/11/2018 ዓ.ም ተቀላቅለዋል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

አስቴጎማ ተራራ ክፍለጦር በመኮይ ከተማ በአገዛዙ ጦር ላይ  መብረቃዊ ጥቃት በመሰዘር ታላቅ ገድል ፈፅሟል!!               ቀን 30/10/2018 ዓ.ም ከሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በትጥቅ ትግሉ መስመር አዲስ አንጸባራቂ ድል ተመዝግቧል። በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋትና ጥሙጋ አውራጃ አንፆኪያ ገምዛ ክላስተር  መኮይ ከተማ «44ቱ» ተብሎ በሚጠራው ልዩ ቦታ ላይ ሰፍሮ በነበረው የአገዛዙ ጥምር ጦር ላይ የተቀናጀና ስልታዊ ድንገተኛ ጥቃት ተፈጽሟል።  በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ስር የሚገኘው የሙሀመድ ቢሆነኝ ኮር «አስቴጎማ ተራራ ክፍለጦር» ይህንን የላቀ ወታደራዊ ኦፕሬሽን አስደማሚ ገድል ፈፅሟል። የክፍለጦሩ የቁርጥ ቀን ታጋዮች በከፈቱት ፈጣን ማጥቃት የአገዛዙን ዙፋን አስጠባቂ ሠራዊትና ተባባሪ ጥምር ኃይሎች ከጥቅም ውጪ ተደርገዋል።  በጠላት ላይ የደረሰው ወታደራዊ ኪሳራ፦ . 10 የመከላከያ ሠራዊት አባላት የተደመሰሰ . ከ13 በላይ የቆሰሉ  ሲሆን በርካቶቹ የጠላት ኃይል ተበታትኗል። የክፍለ ጦሩ አባላት የተሰጣቸውን ግዳጅ በአስተማማኝ ሁኔታ ከፈጸሙ በኋላ፣ ያለምንም የሰውና የማተርያል ጉዳት ሳይደርስባቸው በሰላም ወደ ምሽጋቸው ተመልሰዋል።  ሽንፈት የገጠመው ጠላት የበቀል በትሩን በንጹኃን ዜጎች መኖሪያ መንደሮች ላይ የ«ዙ-23» ፀረ-አውሮፕላን መሣሪያን በዘፈቀደ ሲተኩስ በነበረው አሸባሪ ኃይል ላይ የተወሰደው እርምጃ፣ የትጥቅ ትግሉን የህልውናና የነጻነት ጉዞ ይበልጥ ያፋጠነ ሆኗል። የሙሀመድ ቢሆነኝ ኮር ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ክፍል እንደገለጸው፣ የሕዝብን ሙሉ ነጻነትና ደህንነት እስኪረጋገጥ ድረስ የተባበረው የፋኖ ክንድ በአገዛዙ ላይ ማረፉን ይቀጥላል ሲል ገልጿል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

በመንዝ አውራጃ ፤ ጥርጥራ ቀበሌ የደፈጣ ጥቃት፤ የአገዛዙ 104ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር በፋኖ መብረቃዊ እርምጃ ጉዳት አስተናገደ!! ሰኔ 30/2018 ዓ.ም በትጥቅ ትግሉ ስትራቴጂካዊ የደፈጣ ውጊያ መርህ መሰረት፣ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር ስር የሚንቀሳቀሰው የአፄ ምኒልክ ክፍለጦር (በአባተ ፩ኛ ሻለቃ) በመንዝ ላሎ ክላስተር ጥራጥር ቀበሌ ወታደራዊ የበላይነትን በማድረግ አንጸባራቂ ድል አስመዝግቧል። ከሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 12:00 ድረስ በተካሄደው የሰዓታት ጠንካራ ውጊያ፣ ከመንዝ ላሎ ወገሬ ከተማ ተነስቶ ወደ ጥርጥራ ቀበሌ ለመንቀሳቀስ የሞከረው የብልፅግናው 104ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር "ሀያደጋ" በተባለ ልዩ ቦታ ላይ በታቀደ ድንገተኛ የደፈጣ ጥቃት እቅዱ ከሽፏል። የኮሪ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ለዕዙ ባስተላለፈው ግንባር መረጃ መሰረት፣ የፋኖ ስልታዊ ጥቃት የወታደራዊ ግዳጅ አፈጻጸሙን ሙሉ በሙሉ ያሳካ ነበር። በዚህም የአገዛዙ የጥምር ጦር አባላት የነበሩ አንድ የ፶ አለቃ ማዕረግ ያለው የሚሊሻ አመራርን ጨምሮ ከ10 በላይ ወታደሮች የተደመሰሱ ሲሆን፣ በርካቶች ቆስለው በአምቡላንስና በሕዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ወደ ሞላሌ ከተማ ሆስፒታል እደላከ ተረጋግጧል። በሜዳው ፍልሚያ ከፍተኛ የሰው ኃይልና የሞራል ስብራት የገጠመው የአገዛዙ ሰራዊት፣ ሽንፈቱን ለመቀልበስ ከመንዝ ቀያ  ዘመሮ ከተማ የኃይል ማዛባት (ማጠናከሪያ ኃይል) ለማንቀሳቀስ ቢሞክርም በምኒልክ ልጆች ፅኑ መከላከል ወደ ኋላ እንዲያፈገፍግ ተገዷል። ሰራዊቱ ወታደራዊ ግዳጁን ማሳካት ሲያቅተው፣ የክፍለ ጦሩ አስተዳደር ኃላፊ የፋኖ ልዑል እሱባለውን ቤተሰቦች መኖሪያ ቤት በር በመስበርና ንብረት በመዝረፍ የተለመደውን የውንብድና ተግባሩን ፈፅሟል። ይህ በመንዝ ላሎ ቀጠና የተመዘገበው ድል፣ በትጥቅ ትግሉ ሂደት የፋኖን የደፈጣ ውጊያ ብቃት፣ የመረጃ የበላይነት እና የተደራጀ አቅም በተግባር ያሳየ ሲሆን፣ የአገዛዙ ኮማንዶ ክፍለ ጦር መራር ሽንፈት አከናንቦ ወደ መጣበት እንዲፈርጠጥ አድርጎታል። "ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!" የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!!

በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ ፡ ሳሲት ክላስተር የዓመታዊ ሥራ አፈፃጸምን ገምግሞ የዕውቅና መድረክ ሲያካሂድ፡ በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ የብልፅግናው ሠራዊት ንፁሀንን በግፍ ረሸነ!! ሰኔ 30/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በቀን 29/10/2018 ዓ.ም በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ፣ ተጉለት ቀጠና ሳሲት ክላስተር ዓመታዊ የሥራ አፈፃጸም ግምገማ መድረክ አካሄደ ። በዚሁ መድረክ ላይ የዕዙ ከፍተኛ የፖለቲካ አመራሮች፣ የክላስተርና የቀበሌ አመራሮች በተገኙበት ድርጅታዊ ተልዕኮዎች፣ የማኅበረሰብ አገልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች በስፋት ተገምግመዋል ። 📌 ዋና ዋና የውይይት ነጥቦች ~ ቀጥተኛ የድጋፍና አርአያነት: የዕዙ ከፍተኛ የፖለቲካ አመራሮች እስከ ቀበሌ ድረስ በመውረድ ያደረጉት ድጋፍ የሚበረታታ ጅምር በመሆኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠይቋል ። ~ የተቋማት ነፃነት: ክላስተርና ቀበሌዎች ያለምንም ጣልቃ ገብነት የተሰጣቸውን ተቋማዊ ሥልጣን በነፃነትና በኃላፊነት እንዲተገብሩ የተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ተጨማሪ አቅም መፍጠሩ ተገልጿል ። ~ የተጣለባቸውን ሕዝባዊና ድርጅታዊ ኃላፊነት በተሻለ ሁኔታ ለተወጡ ቀበሌዎችና አመራሮች የምስጋናና የዕውቅና ሽልማት ተበርክቷል ። ይህ ሽልማት ጠንካራዎችን ለማበረታታትና ደካማ አፈፃጸም ያሳዩትን ደግሞ ለቀጣይ ሥራ ለማነቃቃት ያለመ ነው ። ✊ ለቀጣይ ትግል የቀረበ ጥሪ:- ~ የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች "ተጉለት በታሪክ የነበረውን ብሔራዊ ሚና በአማራ የሕልውና ትግል በድጋሚ በተግባር አሳይቶናል" በማለት ለአመራሩና ለማኅበረሰቡ ምስጋና አቅርበዋል ። ~ በመጨረሻም፣ በቀጣይ የሚሰጡ ድርጅታዊ ተልዕኮዎችንና ግዳጆችን በአግባቡ ለመወጣት እንዲሁም የተደቀነውን የሕልውና አደጋ ለመቀልበስ አመራሩና ሕዝቡ በተለመደው የጋራ አንድነትና ትውልዳዊ ኃላፊነት እንዲቆሙ ጥሪ ቀርቧል ። በሌላ ዜና በቀን 29/10/2018 ዓ.ም የብልፅግናው ሠራዊት በንፁሀን ደም ከመጨማለቁ ባለፈ የሰውን ልጅ በአሰቃቂና ፍፁም አረመኔ በተሞላ ተግባር አማራን እየተበቀለ ይገኛል። ይሕ ድርጊት በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ አርማኒያ ቀበሌ የተፈፀመ ሲሆን የአርማኒያ ቀበሌ ነዋሪ የሆነውን " አቶ ወንዳፍራሽ ንጉሴን" በጨለማ አራት ሰዓት(4:00) ከቤቱ አውጥተው ወደ ካምፕ በመውሰድ ለአንድ ቀን አሳድረው በማግስቱ "አይኑን" በማውለቅ እጁን በመቆራረጥ የገደሉት ሲሆን፤ ከገደሉም በኋላ እሬሳውን ለቤተሠቡ እዳይሠጥ የከለከለ የአለማችን አረመኔ ሆኗል። አቶ ወንዳፍራሽ ንጉሴ የሁለት ልጆች አባት ሲሆን፡ ልጆቹን ያለ እናት በስስት ሲያሳድግ የኖረ፣ ሚስቱ ሞታበት በሀዘን የተጎዳ ትጉሕ ገበሬ ነበረ። ይሕንን አረመኔዊ ድርጊት የተመለከቱት ዘመድ ጎረቤቶቹ ከሀዘን በላይ ሆኖባቸው ቤታቸውን ዘግተው በጫካ ይገኛሉ። ሌላኛው ደግሞ በቀን 28/10/2018 ዓ.ም በአንፆኪያ ገምዛ ክላስተር እዲሁ አንድ ንፁህ ገበሬ በአገዛዙ ተረሽኗል። አቶ መንገሽ ታዬ የተባሉ የ55 ዓመት ገበሬ ለህክምና ከአጋምሳ አምባ ቀበሌ ወደ መኮይ ከተማ ያቀኑ ሲሆን፡ ከሚታከሙበት ጤና ጣቢያ በማውጣት አስረው ከገረፉ በኋላ በግፍ በአገዛዙ ተረሽነዋል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

አፄ ምኒልክ ክፍለ ጦር በደፈጣ ጥቃት በጠላት ላይ ድል መቀዳጀቱን ሲገልፅ፡ የሀገር መሠረተ ልማቶች በሕዝብና አባት አርበኞች መሠራቱ ተገለፀ!! ቀን 29/10/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር ስር የሚንቀሳቀሰው የአፄ ምኒልክ ክፍለጦር በቅርቡ የሪፎርም ስራ ካከናወነ በኋላ፣ በአገዛዙ ኃይሎች ላይ የተሳካ የደፈጣ ጥቃት መፈፀሙን አስታወቀ ። ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ላይ ከመንዝ ቀያ ክላስተር ዘመሮ ከተማ በመነሳት ወደ ዘረት ሲንቀሳቀስ በነበረው የመከላከያ ሰራዊት ላይ የአፄ ምኒልክ ክፍለ ጦር 2ኛ ሻለቃ አባላት አስደናቂ ድል አስመዝግበዋል። በዚሕ የደፈጣ ጥቃት የጠላት ኃይል ክፉኛ መጎዳቱን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ከግንባር በደረሰው መረጃ አረጋግጧል። ጠላት የደረሰበት ጉዳት ፧ በተሰነዘረው የደፈጣ ጥቃት 6 የአገዛዙ ኃይሎች የተገደሉ ሲሆን፣ ቁጥራቸው በውል ያልተረጋገጠ ቁስለኞች በዘመሮ ከተማ ሆስፒታል በሕክምና ላይ እንደሚገኙ ዕዙ አረጋግጧል ። የብልፅግናው ሰራዊት የደረሰበትን ምት መቋቋም አቅቶት ሙትና ቁስለኛ ይዞ፣ ያሰበውን ዓላማ ሳያሳካ ወደመጣበት ለመመለስ ተገድዷል ። በቅርቡ የአመራር ሪፎርም ያደረገው የአፄ ምኒልክ ክፍለጦር፣ በአሁኑ ወቅት የተሻሉ ግዳጆችን በመፈፀም ላይ የሚገኝ ሲሆን፥ ክፍለ ጦሩ ራሱን ለግዳጆች በማዘጋጀት ላይ ከመሆኑም በላይ፣ በከፍተኛ የሰው ኃይል ግንባታ ላይ እንደሚገኝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል በሰጠው መግለጫ አመልክቷል ። በተያያዘ ዜና የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከትጥቅ ትግሉ ጎን ለጎን ሕዝቡን በማስተባበር የመሰረተ ልማት ስራ እየሰራ ይገኛል። ሰኔ 29/2018 ዓ/ም በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ቀወት ወረዳ ተሬ ክላስተር የጃበርና ጎልጎዲሳ ጎጥ ለመንገድ መሰረተ ልማት ስራ ዘመቻ በነቂስ በመውጣት ከትጥቅ ትግሉ ጎን ለጎን በሞራል ሲሰሩ ውለዋል። እንዲሁም በተጨማሪ በተመሳሳይ በቀን 29/10/2018 ዓ/ም በዚሁ አውራጃ ማጀቴ ክላስተር የ"አየለ አባተ ብርጌድ" አባት አርበኞች ክረምትን የዋጀ መሠረተ ልማት ተሠርቷል። የማህበረሰቡን እንቅስቃሴ እዳይገታ ተብሎ የታሠበው የጃራ ወንዝ ጋቢዮን ስራ አባት አርበኞቹ በሞራልና በትብብር የወንዙን ፍሰት መቆጣጠር የሚያስችል ስራ አከናውነዋል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!!

የአፋበን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር አካል የሆነው ጀብደኛዉ ራስ አበበ አረጋይ ክፍለጦር ከሰኔ 24/2018 ዓ.ም  ጀምሮ ለተከታታይ አምሥት(5) ቀናት ልዩ የተሃድሶ መርሀ ግብር ለክፍለጦሩ አመራርና አባላት ሰፊ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ግንባታ በመስጠት  የተሳካ የግንባታ መድረክ አካሒዷል! አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነዉ ዕዝ!

የራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር ልዩ የወታደራዊና ፖለቲካዊ አቅም ግንባታ ተሃድሶ መርሃ ግብር አከናወነ!!           ሰኔ 29/2018 ዓ.ም ተሃድሶ ለወታደር ዘርፈ ብዙ የስኬታማ ወታደራዊ ግንባታ ስራዎች የሚከናወኑበት የወታደራዊ ሳይንስ ክፍል አካል ሲሆን፣ ወታደራዊ ግዳጆችን በመገምገም፣ የአመርና የሰራዊቱን ወቅታዊ የፖለቲካ ግንዛቤ በማሳደግ ህዝባዊነትን የተላበሰ የፋኖ ሰራዊት መገንባትን ራዕይ ያደረገ ለየትኛውም ግዳጅ ብቁ እና በከፍተኛ የሞራል ስንቅ የተሞላ አማራዊ ስነልቦና የተላበሰ ዘመናዊ የአማራ ፋኖ ሰራዊት የማደራጀት ዓላማ አንግቦ የፖለቲካዊና የወታደራዊ ሳይንስ ትምህርቶች በጥምረት በአንድ መድረክ ላይ የሚሰጡበት ዘመናዊ የማታገያ ጥበብ ነው። የአፋበን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር አካል የሆነው ለራስ አበበ አረጋይ ክፍለጦር ከሰኔ 24/2018 ዓ.ም  ጀምሮ ለተከታታይ አምሥት(5) ቀናት  ልዩ የተሃድሶ መርሀ ግብር ለክፍለጦሩ አመራርና አባላት ሰፊ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ግንባታ በመስጠት   የተሳካ የግንባታ መድረክ ማካሄዱን የአፄ አምደ ፅዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ለዕዙ ዜና ክፍል በላከው የግንባር መረጃ አስታውቋል። ​በዚሁ የግምገማና የግንባታ መድረክ ላይ በየደረጃው የሚገኙ የድርጅትና የዕዝ አመራሮች በአካል ተገኝተው ለክፍለ ጦሩ አባላት ውጤታማ ስልጠናውን የሰጡ ሲሆን፣ የአፋብን ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ፊትአውራሪ  ባዩ አለባቸው እና የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ፋኖ  አከበር ስመኘው እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የአሳምነው ዕዝ አመራሮች በተዘጋጀው የተሃድሶ መርሀ ግብር ላይ በአካል ተገኝተው ለራስ አበበ አረጋይ ክፍለጦር አባላትና አመራሮች በቂ ግንዛቤ  መስጠታቸውን ኮሩ አክሎ ገልጿል። በመድረኩም ስለ ትግሉ አሁናዊ ሁኔታ፣ ስለ ማህበረሰብ አያያዝ እንዲሁም ስለ ውስጣዊ አንድነት ሰፊና ጥልቅ ውይይት በማድረግ በተለዬ አቀባበል ዓላማና ግብ ተኮር መግባባቶች የተፈጠሩበት የተሳካ መድረክ ሲከናወን ሰንብቷል። ​ይህንን ድርጅታዊ የሆነ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ግንባታ ተከትሎ፣ የሰራዊቱን ሞራል ይበልጥ ከፍ ያደረገ ደማቅ የተሃድሶ መርሀ ግብር ሲከናወን፣ ይህን የተግባር ተኮር ስልጠና እስከ ግንባር ምሽጎች ድረስ በመዝለቅ የሰራዊቱ የሞራል ማማ በመሆን የሚታወቁት የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ ዘረያዕቆብ ፩ኛ ኮር የናደው ክፍለ ጦር የባህል ቡድን አባላት የፕሮግራሙ ድምቀት ሆነው የተሳተፉበት መርሀ ግብር የተካሔደ ሲሆን፣ በዕለቱም የአማራን ማንነትና ባህል የሚገልጹ ልዩ ልዩ የባህል ጭውውቶችና ክዋኔዎች ቀርበው ለሰራዊቱ አባላት ከማነቃቃት አልፎ ለሰራዊቱ የሞራል ስንቅ በመሆን የተሳካ መድረክ ተከናውኗል። የስልጠናው ተሳታፊ ከሆኑት የራስ አበበ አረጋይ ክፍለጦር ሰራዊትና አመራሮች በሰጡት አስተያየት፣ ይህ ዓይነቱ ድርጅታዊ ስራና የግንባታ መርሃ ግብር ቀደም ሲል የነበሩ በርካታ ብዥታዎችን ያጠራ መሆኑን በመግለፅ፣ አያይዘውም ​ይህ መድረክ ቀጣይ ለምናደርገው የተቀናጀ ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግል ምቹ ሁኔታ የፈጠረ ነው፤ ትግላችንም ከተናጠል ወደ ህብረት የተሸጋገረበት በመሆኑ፣ በማንኛውም ሁኔታና ሰዓት ለህልውና ትግሉ የምንከፍለውን መስዋዕትነት በደስታና በሙሉ ልብ እንድንወጣ ያደርገናል ብለዋል። ራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር የተሰየመበት የጀግናው የራስ አበበ አረጋይ ስም ተራ ስያሜ ብቻ እንዳልሆነ የገለጹት አመራሮቹና አባላቱ፣ የህዝብ ፍቅርንና በፅናት ለዓላማ የሚደረግ ተጋድሎን ከክፍለ ጦሩ የአሁናዊ ህልውና ትግል ጋር በማቆራኘት የስልጠና ቆይታቸውን ከታሪክ ጋር አነፃፅረው ሀሳባቸውን ገልፀዋል። የራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦርም ከትንሽ የሰው ሃይልና ትጥቅ በመነሳት በከፍተኛ ፍጥነት አሁን ግዙፍ ከሚባሉ ክፍለ ጦሮች ተርታ እንድትሰለፍ ያስቻላት የአመራሮቿ እና ሰራዊቱ የአርበኛው ራስ አበበ አረጋይ የፅናት ፈለግን በመላበስ ሌት ከቀን ተግተው በመስራታቸው መሆኑንም በመድረኩ አስታውሰዋል። ታዋቂው አርበኛ ራስ አበበ አረጋይ በፋሺስት ጣሊያን ወረራ ወቅት የሸዋ አርበኞችን በማስተባበርና በመምራት፣ ለሀገር ሉዓላዊነትና ለህዝብ ነፃነት ያደረጉት ተጋድሎ ዛሬም ለክፍለ ጦሩ አባላት ታላቅ የፅናት ምንጭ መሆኑም ተነስቷል። ​በመሆኑም የክፍለ ጦሩ አባላት ትናንት በታሪክ እንደተደረገው ሁሉ፣ ዛሬም ሆነ ነገ ይህንን ታሪካዊ ስም በተግባርና በልዩ ልዩ የጦር ሜዳ ጀብዱዎች እንደሚያስጠሩት በጋራ ቃል በመግባት ለተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው የተሃዲሶ መርሀ ግብር በስኬት ተጠናቋል ሲል የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ገልጿል። ​በመጨረሻም የክፍለ ጦሩ አመራሮችና ሰራዊት ስለ ህዝብና ዓላማ፣ ስለ አማራ ታሪክና ፋኖነት እንዲሁም ስለ ድርጅትና ድርጅታዊነት ያላቸውን ግንዛቤ ይበልጥ በማሳደግ፣ ቀጣይ መርህን የተላበሱ አሰራሮችን በማስተካከል ተግተው በመስራት ድርጅቱ ካስቀመጠው ግብ ላይ ለመድረስ ዝግጁ መሆናቸውን በቁርጠኝነት አረጋግጠዋል ሲል ኮሩ በግንባር መረጃው አረጋግጧል።     " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት !     "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ እና የአፋብን ምኒልክ ዕዝ ወቅታዊ የጋራ የውይይትና ህዝባዊ መድረኮችን አካሄደ!! ቀን 29/10/2018 ዓ.ም ​በቀነ 28/10/2018 ዓ.ም በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ አፄ ዘረያዕቆብ ፩ኛ ኮር በአፄ ይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር ስር ብርጌዶች በተገኙበት በወቅታዊ የጠላት አሰላለፍ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል። ​በመድረኩ ላይ የክፍለ ጦሩ ዋና ሰብሳቢ ፋኖ አቡሽ ጌታሁን ሰራዊቱን የሚያነቃቃና የሞራል ዝግጁነት እንዲኖረው የሚያደርግ ንግግር ያደረጉ ሲሆን፣ ሌሎች የክፍለ ጦር አመራሮችም በተመሳሳይ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። በዕለቱ የተገኙት የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዘመቻ መሪ ፋኖ አሳልፍ ደስታ (ቀጭን) አባት አርበኛው የሰራዊቱ የኋላ ደጀን በመሆን ትግሉን መደገፍና ማታገል እንዳለበት ገልጿል፣ ለዚህም ከወትሮው በተለየ ሁኔታ መዘጋጀት እንደሚገባ አሳስበዋል። ​የዕለቱ የክብር እንግዳ የነበሩው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዋና መሪ እንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሸዋ በበኩላቸው በድርጅታዊ አንድነቱ መፈጠር የተሰማውን ደስታ ገልፆ፣ እኛ የአባቶቻችን ልጆች ነን" ካሉ በኋላ ጠላትን የማያዳግም እርምጃ ለመውሰድ ሞትን መፍራት እንደማይገባና ሞትን የማይፈራ ሰራዊት ሁልጊዜም እንደሚያሸንፍ ገልጿል ለዚህም ሁሉም ዝግጁ እንዲሆን ጥሪ አቅርቧል። አባት አርበኞቹም በበኩላቸው በተደረገው የማነቃቃትና ጠላትን በጋራ የመመከት ውይይት እንዲሁም በታየው የወትሮ ዝግጁነት ፕሮግራም እጅግ መደሰታቸውን አስታውቀዋል። ​በሌላ ዜና ከቀን 27-28/10/2018 ለተከታታይ ሁለት ቀን በግሼ ራቤል ወረዳ በጎልታ መዘራዝር ቀበሌ ከሁለቱም እዞች (ከአፋብን ምኒልክ እዝ እና ከአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው እዝ) የተወጣጡ አመራሮች የተገኙበት ህዝባዊ መድረክ ተካሂዷል። ከ700 በላይ የህዝብ ቁጥር የተገኘበትና ከእስልምናም ከክርስትናም የሃይማኖት አባቶች የተሳተፉበት ይህ ስብሰባ በጸሎት ተጀምሮ በጸሎት ተጠናቋል። በመድረኩ ማጠቃለያ ላይም ከማህበረሰቡና ከአመራሩ የተገኙ ጥንካሬዎችን በማስቀጠልና ያሉትን ክፍተቶች በመሙላት ከዚህ በላይ በጋራ ለመስራት ስምምነት ላይ ተደርሶ ስብሰባው በሰላም ተጠናቋል። የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት ዓሳምነው ዕዝ ህዝብ ግኑኝነት መምሪያ!!