5 084
Subscribers
+1124 hours
-157 days
-7730 days
Posts Archive
Repost from ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
+9
በጥዋት ዜና እወጃችን የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር በነጎድጓድ ክ/ጦር በተካሄደው የአንጨቆረር ከተማ ጀብድ የምርኮ ዝርዝር ይፋ እንደሚከተለው አቅርበናል!!
ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ቀን 14/11/2018 ዓ.ም በዛሬው ዕለት ጠዋት በወጣው ዜና በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርያዕቆብ ኮር ነጎድጓድ ክ/ጦር በአገዛዙ ሀይል ላይ በወሰደው እርምጃ የአገዛዙ ጅምላ ተጋላቢ የሚሊሻ አባላት ላይ አመርቂ ድል መቀዳጀቱ ይታወሳል። አሁን ከሰዓት በደረሰን ተጨማሪ መረጃ መሠረት የተማረኩ አካላት እና የቁሳቁስ ዝርዝር መረጃ ይፋ ሆኗል።
የተማረኩ አካላት እና ቁሳቁሶች ዝርዝር
1ኛ.የተማረኩ የሚሊሻ ብዛት 5 አባላት
2ኛ.12 ክላሽኒኮቭ ጠመንጃዎች
3ኛ.4 ኤስ-ኬ-ኤስ (SKS): ጠመንጃ
4ኛ.1 መትረዬስ ክላሽ
5ኛ. ልዩ ልዩ የወገብ ትጥቅና ተተኳሾች ናቸው።
የኮሩና ክ/ጦሩ አመራሮች እንዳስታወቁት፣ በዚህ አውደ ውጊያ ላይ ለተሳተፉ አመራርና ሰራዊት አባላት ምስጋናቸውን በማቅረብ ይህና መሰል ስራዎችን ተጠናክረው በመቀጠል የድርጅታችን አፋብንን ጥሪ ባልተቀበሉ የአማራ ህዝብ ጠላቶች ላይ ሁሉ እርምጃው ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግኑኝነት መምሪያ
Repost from Mereb Media መረብ ሚዲያ
+3
በነጎድጓድ ክ/ጦር በተካሄደውየአንጨቆረር ከተማ ጀብድ የምርኮ ዝርዝር ይፋ ሆነ !!
ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ቀን 14/11/2018 ዓ.ም በዛሬው ዕለት ጠዋት በወጣው ዜና በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርያዕቆብ ኮር ነጎድጓድ ክ/ጦር በአገዛዙ ሀይል ላይ በወሰደው እርምጃ የአገዛዙ ጅምላ ተጋላቢ የሚሊሻ አባላት ላይ አመርቂ ድል መቀዳጀቱ ይታወሳል። አሁን ከሰዓት በደረሰን ተጨማሪ መረጃ መሠረት የተማረኩ አካላት እና የቁሳቁስ ዝርዝር መረጃ ይፋ ሆኗል።
የተማረኩ አካላት እና ቁሳቁሶች ዝርዝር
1ኛ.የተማረኩ የሚሊሻ ብዛት 5 አባላት
2ኛ.12 ክላሽኒኮቭ ጠመንጃዎች
3ኛ.4 ኤስ-ኬ-ኤስ (SKS): ጠመንጃ
4ኛ.1 መትረዬስ ክላሽ
5ኛ. ልዩ ልዩ የወገብ ትጥቅና ተተኳሾች ናቸው።
የኮሩና ክ/ጦሩ አመራሮች እንዳስታወቁት፣ በዚህ አውደ ውጊያ ላይ ለተሳተፉ አመራርና ሰራዊት አባላት ምስጋናቸውን በማቅረብ ይህና መሰል ስራዎችን ተጠናክረው በመቀጠል የድርጅታችን አፋብንን ጥሪ ባልተቀበሉ የአማራ ህዝብ ጠላቶች ላይ ሁሉ እርምጃው ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።
ምንጭ፦ በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ጎርጎ ክላስተር የመጀመሪያውን ጠቅላላ ጉባኤ በታላቅ ድምቀት አካሄደ!!
ሐምሌ 14/2018 ዓ.ም
በአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት የክላስተር ጠቅላላ ጉባኤ ተካሄደ። ቀን 13/11/2018 ዓ.ም በአፋብን የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ተጉለትና ቡልጋ አውራጃ፣ አንኮበር ቀጠና ጎርጎ ክላስተር ያሰናዳው ይህ ጉባኤ፤ የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች እና የክላስተሩ ስራ አስፈፃሚዎች በተገኙበት በታላቅ ወታደራዊና ድርጅታዊ ስነ-ስርዓት ተካሂዷል።
ጉባኤው የወደፊት የትግል አቅጣጫዎችንና የህዝቡን ህልውና የሚያረጋግጡ ቁልፍ አጀንዳዎችን በጥልቀት የመከረ ሲሆን፣ በዋናነትም በሚከተሉት አራት አበይት ነጥቦች ላይ ትኩረቱን አድርጓል፡-
1ኛ.የአፈጻጸም ሪፖርት ማቅረብ፡ የአጠቃላይ የክላስተሩንና የቀበሌዎችን የስራ እንቅስቃሴ የሚያሳይ ዝርዝር ሪፖርት ቀርቦ አጠቃላይ ዳሰሳ ተደርጎበታል።
2ኛ.ጥልቅ ግምገማ፡ ያለፉትን ወታደራዊ፣ ድርጅታዊና ህዝባዊ ስራዎችን ጥንካሬንና ክፍተትን በመለየት አጠቃላይ ግምገማ ተካሂዷል።
3ኛ. በወቅታዊ ጉዳዮችና በቀጣይ አቅጣጫዎች፡ የትግሉን መንፈስ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩና የህዝቡን ደህንነት የሚያረጋግጡ የወደፊት ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።
በጉባኤው ማጠቃለያ ላይ የተገኙት ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት፤ የትግሉን ፈጣን ዕድገትና ጥንካሬ አጉልተው አሳይተዋል። ትግሉ በአጭር ጊዜ ውስጥ እየጎመራ ነው። ከሰፈርና ከቀበሌ አደረጃጀት ተሻግሮ፣ መላውን ህዝብ ያስተባበረ ታላቅ የአማራ ድርጅት መፍጠር መቻሉን ገልፀው ድላችንም ሩቅ አይመስልም ሲሉ ገልፀውታል። ህዝብን እንደ ህዝብ፣ ጦርን ደግሞ እንደ ጦር አደራጅቶ ዓመታዊ የክንውን ሒደትን በጉባዔ ደረጃ መገምገም መቻሉ የትግሉን ብስለትና የደረሰበትን ከፍተኛ የለውጥ ደረጃ የሚያሳይ ህያው ማረጋገጫ መሆኑን አስምረውበታል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት"!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሰበር የድል ዜና!!
ነጎድጓድ ክፍለጦር በአገዛዙ ሀይል ላይ በወሰደው እርምጃ አስደናቂ ድል ተቀዳጀ!
ሀምሌ 14/11/2018 ዓ.ም
----------------------------------
ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘረያዕቆብ ኮር ነጎድጓድ ክ/ጦር በወሰደው ፈጣን ስልታዊ የማጥቃት እርምጃ አንፀባራቂ ድል ተቀዳጀ ።
በአንጨቆረር ከተማ ዛሬ ሌሊት 11:00 የጀመረው አውደ ውጊያ የጀግኖቹ ወታደራዊ ወኔ ጨምሮ በጠላት ኃይል ላይ ከፍተኛ ምት ሲያሳርፍ የቆየው ነጎድጓድ ክፍለጦር፣ በተካሄደው ወታደራዊ እርምጃ ታሪካዊና አንፀባራቂ ድል ተቀዳጅቶ የአገዛዙ ሚሊሻና አድማ ብተና ማራገፊያ የነበረችውን አንጨቆረር ከተማን በተወሰደው መብረቃዊ የማጥቃት እርምጃ ሙሉ ለሙሉ ተቆጣጥሯል።
ክፍለጦሩ ወኔ በተሞላበት ስልታዊ ውጊያ የጠላትን ምሽግ በማፍረስ ፣ የጠላት ኃይልን በመበደምሰስ እና በመማረክ ግዛቱን በመቆጣጠር ረገድ ከፍተኛ የበላይነት መቀዳጀቱን ሲገልፅ የአገዛዙ ሀይል ለመመከት ቢሞክርም በተወሰደ ፈጣን የከተማ ውስጥ እርምጃ ሙት እና ቁስለኛ እንድሁም ምርኮኛ በማድረግ አዝረክርከነዋል እኛን መመከት አልቻለም ብለዋል።
የነጎድጓድ ክፍለጦር አባላት ላሳዩት የማይናወጥ ፅናት፣ የውጊያ ብቃት ከፍተኛ ምስጋናና አድናቆት በአዋጊወቻቸው የተቸራቸው ሲሆን ይህ ፈጣን ስልታዊ የማጥቃት እርምጃ ቀጥሎ ጠላታችንን በየቦታው የመቅበር ስራ ይቀጥላል ብለዋል።
ይህ በነጎድጓድ ክፍለጦር የተመዘገበው ታላቅ ድል የሰራዊታችንን የማይበገር ፅናትና ከፍተኛ ብቃት አሁንም በግልፅ ያሳየበት አጋጣሚ ሆኗል። ጀግናው ሰራዊታችን የተጣለበትን ድርጅታዊና ህዝባዊ አደራ በላቀ ጀግንነትና ቁርጠኝነት መወጣቱን አሁንም አጠናክሮ ይቀጥላል!
የቀሩ ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎችን እንደደረሱን ይዘን እንመለሳለን።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በደረፎ ክላስተር የመጀመሪያውን ጠቅላላ ጉባኤ በታላቅ ድምቀት አካሄደ!!
ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም
በአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት የክላስተር ጠቅላላ ጉባኤ ተካሄደ። በአፋብን የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ተጉለት አውራጃ፣ አንኮበር ቀጠና በደረፎ ክላስተር ያሰናዳው ይህ ጉባኤ፤ የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች እና የክላስተሩ ስራ አስፈፃሚዎች በተገኙበት በታላቅ ወታደራዊና ድርጅታዊ ስነ-ስርዓት ተካሂዷል።
ጉባኤው የወደፊት የትግል አቅጣጫዎችንና የህዝቡን ህልውና የሚያረጋግጡ ቁልፍ አጀንዳዎችን በጥልቀት የመከረ ሲሆን፣ በዋናነትም በሚከተሉት አራት አበይት ነጥቦች ላይ ትኩረቱን አድርጓል፡-
1ኛ.የአፈጻጸም ሪፖርት ማቅረብ፡ የአጠቃላይ የክላስተሩንና የቀበሌዎችን የስራ እንቅስቃሴ የሚያሳይ ዝርዝር ሪፖርት ቀርቦ አጠቃላይ ዳሰሳ ተደርጎበታል።
2ኛ.ጥልቅ ግምገማ፡ ያለፉትን ወታደራዊ፣ ድርጅታዊና ህዝባዊ ስራዎችን ጥንካሬንና ክፍተትን በመለየት አጠቃላይ ግምገማ ተካሂዷል።
3ኛ.ወቅታዊ ሁኔታዎችና የአደረጃጀት ማሻሻያ፡ አሁን ባለው የትግል እንቅስቃሴ፣ ወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታዎች እና ድርጅታዊ አደረጃጀቶችን የበለጠ ለማጠናከር በሚያስችሉ ማሻሻያዎች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
3ኛ.ቀጣይ አቅጣጫዎች፡ የትግሉን መንፈስ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩና የህዝቡን ደህንነት የሚያረጋግጡ የወደፊት ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።
በጉባኤው ማጠቃለያ ላይ የተገኙት ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት፤ የትግሉን ፈጣን ዕድገትና ጥንካሬ አጉልተው አሳይተዋል። ትግሉ በሶስት ዓመታት አጭር ጊዜ ውስጥ ከሰፈርና ከቀበሌ አደረጃጀት ተሻግሮ፣ መላውን ህዝብ ያስተባበረ ታላቅ የአማራ ድርጅት መፍጠር መቻሉን ገልጸዋል። ህዝብን እንደ ህዝብ፣ ጦርን ደግሞ እንደ ጦር አደራጅቶ ዓመታዊ የክንውን ሒደትን በምክር ቤት ደረጃ መገምገም መቻሉ የትግሉን ብስለትና የደረሰበትን ከፍተኛ የለውጥ ደረጃ የሚያሳይ ህያው ማረጋገጫ መሆኑን አስምረውበታል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት"!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!!
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት 5 የጉድኝት ክላስተሮችን ያሳተፈ ታሪካዊ መድረክ ተካሄደ!
በቀን 11/11/2018 ዓ.ም በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ በተሬ ክላስተር በተደረገው ታሪካዊ መድረክ ላይ፤ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት የአሳምነው ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች፣ የአባት አርበኞች መምሪያ አመራሮች፣ በቀጠናው የሚገኙ የፖለቲካ መምሪያ አስተባባሪዎች እንዲሁም የኮር እና ከ5ቱም ክላስተሮች የተውጣጡ አመራሮች በተገኙበት የትግሉን እድገት የሚመጥን የ6 ወር የሥራ ሪፖርትና ውይይት ተደርጓል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሥር የሚገኙትን አምስት (5) የጉድኝት ክላስተሮች፣ እነሱም፦
1.የተሬ ክላስተር
2.መዘዞ ክላስተር
3.የባሽ ክላስተር
4.የኤፍራታና ግድም ክላስተር
5.የአሎሎ ክላስተር
የእነዚህን ክላስተሮች አስተዳደሮች ወደ አንድ መድረክ በማምጣት የ6 ወር የሥራ ሪፖርት እንዲያቀርቡ ተደርጓል። በዚህ ውይይት ላይ በክላስተሮቹ የተሰሩ ስራዎች ቀርበው፤ በሕዝብ አስተዳደር፣ በፍትህ፣ በሰላምና ደህንነት እንዲሁም በአባት አርበኛ ታጋዮች መጠርነፍና ማደራጀት ዙሪያ ውጤታማ ስራዎች እንደተከናወኑ ተገልጿል። በተጨማሪም በየክላስተሮቹ የነበሩ የአሰራር እቅፋቶችና የሕዝብ ጥያቄዎች ቀርበው ጥልቅ ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በሁሉም ወገን ከሕዝብና ከመሪዎቹ ለተነሱት ጥያቄዎች የአባት አርበኞች መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ማሞ ማስረሻ እና የዕዙ ከፍተኛ አመራር አርበኛ ዮናስ ባባው ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በመድረኩ የሙሐመድ ቢሆነኝ ኮር ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ፋኖ ምናሉ ከበደ በመገኘት በወታደራዊ ጉዳዮች ላይ ለተነሱ የሕዝብ ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ ሰጥቷል።
በመጨረሻም፣ የፖለቲካ መምሪያ የቀጠናው አስተባባሪዎች መድረኩን በመምራትና በማስተባበር፣ ለቀጣይ የትግል እንቅስቃሴ አቅጣጫ በመስጠት እንዲሁም ለአምስቱ ክላስተሮች መልካም አፈፃፀምና የትግል ንቅናቄን በበሰለ መልኩ በመምራታቸው የዕውቅና ምስክር ወረቀት እና የአርበኞች ምስል በሽልማት መልክ ተበርክቶላቸው መድረኩ በስኬት ተጠናቋል።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
አባት አርበኞች ከህልውና ትግሉ ጎን ለጎን የሀገር መሠረተ ልማት ማከናወናቸው ተገለፀ!!
ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መንገድና ኮንስትራክሽን ክፍል በራሳ ጉባ ክፍለ ጦር አባት አርበኞች ትብብር የተቀናጀ ጥረት በርካታ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የራሳ ክላስተር አስታውቋል።
በዚህም መሠረት በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋትና ጥሙጋ አውራጃ፣ ራሳ ክላስተር አባዬ አጥር ቀበሌ የሚገኘውን የመኪና መነሀሪያ ለአገልግሎት ዝግጁ የማድረግ ሥራ ተጠናቋል። ይህ በ1 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የመኪና መነሀሪያ በሕብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎና የገንዘብ መዋጮ የተገነባ ሲሆን፣ በ330 ሜትር የጋቢዮን ሽቦና የብረት አጥር የመከለል ሥራው ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል።
ይህ የተጠናቀቀው የልማት ፕሮጀክት በይፋ አገልግሎት መስጠት እንዲጀምር ለማድረግ የክላስተር አመራሮች የመክፈቻ መርሐ-ግብር ባዘጋጁበት ወቅት፣ የዕዝ፣ የኮር እና የአባት አርበኞች ከፍተኛ አመራሮች በቦታው ተገኝተው ሥራውን አስጀምረዋል።
የክላስተሩ አስተባባሪ አክሎ እንደገለጸው፣ ድርጅቱ ማኅበረሰቡን መሠረት ባደረገ መልኩ የሕዝብ መገልገያ የሆኑ ንብረቶችንና መሠረተ ልማቶችን በትብብር በማስጨረስ ላይ ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል ሲል ገልጿል። የኮንስትራክሽን ክፍል ኃላፊ በበኩላቸው አሁንም በመሠራት ላይ ያሉና በቀጣይ ተጠናቀው ለሕዝብ አገልግሎት ክፍት የሚሆኑ ታላላቅ ሌሎች የልማት ሥራዎች መኖራቸውንና በጊዜው በዜና ይፋ እንደሚደረጉ አስታውቋል።
"ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!"
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!"
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ለአማራ ህዝብ ህልውና እና ነፃነት በድል ጓዳና ከሚገሰግሰው ፋኖ የሚጠበቁ ቁልፍ ነገሮች:-
**
በሀገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ እኩልነት፣ ፍትሃዊነት እና ሰላም የሰፈነባት ሀገር እና ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ድርጅታዊ አሰራርን በጠበቀ መንገድ ሁልጊዜም በጽናት መታገል እና አንድነት ወሳኝ ቁልፍ መሳሪያዎች ናቸው ።
ይህንን ታላቅ ህዝባዊ ዓላማ ዳር ለማድረስ ግን አሁን በትግል ላይ ያለው አመራርና እና ጀግናው ሰራዊታችን ወጥ አስተሳሰብ፣ የጋራ ራዕይ፣ ግልጽ ተልዕኮ እና የማይናወጥ ግብ ሊኖረው ይገባል።
👉 ወንዛዊነት ይውደም፤ ብሔራዊ አንድነታችን ይለምልም!
ጠላቶቻችን እኛን ለመደምሰስ የሚንቀሳቀሱት የአማራነት ማንነታችንን እንጂ የሸዋ፣ የጎንደር፣ የጎጃም ወይም የወሎ ልጆች መሆናችንን መርጠው አይደለም። ጠላት ሲገድለን በአማራነታችን ብቻ ነው። ስለዚህ የእኛ መዳኛም ሆነ ድላችን የሚረጋገጠው በወጥ አማራነታችን እና በአንድነታችን ብቻ ነው።
▸የወንዛዊነትን ጠባብ አጥር እንስበር!
▸ለጋራ ድርጅታዊ መርሆዎች እንገዛ!
▸የበታች ለበላይ መሪዎች ያለውን መከባበርና ወታደራዊ ዲሲፕሊን እናጥብቅ!
🔑ጠላታችን በሞራልም በተግባርም ውድቀት ላይ ነው።
የአማራን ህዝብ ህልውና ለመቅጨት የተነሳው የአገዛዙ ኃይል አሁን ባለበት ሁኔታ ህዝባዊ ቅቡልነቱን ያጣ፣ በሞራልም ሆነ በተግባር ክስረት ውስጥ የገባና የተሸነፈ ኃይል ነው። ይህንን የከሰረ ኃይል ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማንበርከክ የሚያስፈልገን ብቸኛው መሳሪያ የተዋሃደ ሰራዊት እና በአንድ አቅጣጫ የሚመራ ጠንካራ አመራር መፍጠር ብቻ ነው።
እኛ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ታጋዮች በጉዟችን ሁሉ :-
⤵የወጣንለትን የተጨቆነ ህዝባችንን ከጥቃት መጠበቅና ማክበር ቀዳሚ ተግባራችን ነው።
⤵የሌሎች ወንድም ህዝቦችን ባህል፣ ቋንቋ እና እምነት ማክበርና ማስከበር የአማራነት መለያችን ነው።
⤵ዋነኛ ጠላታችን የአማራን ህዝብ እያጠፋ ያለው ፣ ህዝብን እርስ በርስ የሚያጋጨው እና ሀገርን እያፈረሰ ያለው የብልጽግና አገዛዝ በመሆኑ፣ ትኩረታችንና መሣሪያችን ሁሉ ወደዚህ አምባገነን ሥርዓት ላይ በማነጣጠር ጉዟችንን ማፍጠን ይጠበቃል።
"አንድ ዓላማ፣ አንድ መስመር፣ አንድ አቅጣጫ!"
በአማራነት ወጥ በሆነ ራዕይና ተልዕኮ ወደፊት በመገስገስ የህዝባችንን ህልውና እናረጋግጣለን!
ድል ለአማራ ህዝብ!
አርበኛ አከበር ስመኘው
