5 081
Subscribers
+1124 hours
-157 days
-7730 days
Posts Archive
የአባት አርበኞች ጦር አደረጃጀቱን በማዘመን "ምኒልክ አርበኞች ክፍለ ጦር" በሚል ስያሜ በተጉለት በይፋ መመስረቱ ተገለፀ!!
ጳጉሜ 05/2018 ዓ.ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ተጉለት አውራጃ ሲንቀሳቀስ የቆየው የአባት አርበኞች ጦር አደረጃጀቱን በማዘመንና በማጠናከር "ምኒልክ ክፍለ ጦር" በሚል ስያሜ በይፋ መመስረቱ የተጉለት ቀጠና ስምሪት ቡድን አስታወቀ።
ክፍለ ጦሩ ይፋ በተደረገበት በዚህ መድረክ ላይ የዕዝ፣ የኮር እንዲሁም የክፍለ ጦር አመራሮች በተገኙበት ሲመሠረት፤ አደረጃጀትን በማዘመን እና የድርጅቱን የፖለቲካ ትጥቅ ትግሉን በማስረፅ አባት አርበኞቹ ለአካባቢው ሠላምና ደሕንነት እዲያረጋግጡ ታልሞ መዋቀሩ ተገለፀ።
በውይይቱ ወቅት አመራሮቹ እንዳመለከቱት፤ የአማራ ህዝብ የገጠመውን የህልውና አደጋ ለመመከትና ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት የአደጋውን ዘርፈ-ብዙነት መረዳት ተገቢ በመሆኑ፣ ለዚህም ዕድሜው ለትግል የደረሰ የህብረተሰብ ክፍል በሙሉ ባለው አቅም መታገል እንደሚኖርበትና፣ ትግሉም በዋናነት ቀጥተኛ ጥቃት እያደረሰ ባለው አገዛዝ ላይ ብቻ መነጣጠር እንዳለበት አስምረውበታል።
በሌላ በኩል አርበኞቹ በሰጡት አስተያየት፤ አሁን ያለው አገዛዝ በይፋ እድጠፋና ባወጀበት፣ ንብረታችን እዲወድም በዘመተበት፣ በስልታዊ መንገድ ወጣቱ በጦርነት እዲማገድ፣በጥቅም ማባበያ ሚሊሻና አድማብተና እያለ ትውልዱን እያመከነ በመሆኑ፤ ይሕንን የህልውና አደጋ ለመመከት ብቸኛውና የመጨረሻው አማራጫችን በተባበረ ክንድ አገዛዙን ማስወገድ ነው ሲሉ አቋማቸውን አስቀምጠዋል።
ሆኖም በርካታ ጀግኖችን አቅፎ በአባት አርበኞች አደረጃጀት ሲታገል የቆየው የተጉለት አውራጃ ጦር፣ የታጋዮቹን ፍላጎት መነሻ በማድረግና የትግሉን ህልውና ለማስቀጠል ሲባል አደረጃጀቱን ማዘመን አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ "ምኒልክ አርበኞች ክፍለ ጦር" በሚል ስያሜ መመስረቱን አስታውቀዋል።
አደረጃጀቱ በማደጉ የተደሰቱት የምኒልክ አርበኞች ክፍለ ጦር አባላት በበኩላቸው፤ የተካሄደው የምክክር መድረክ በትግል ሂደቱ ላይ የነበሩ ብዢታዎችን ያጠራ መሆኑን ገልጸው፣ እንደ ቀደምት አባቶቻችን በመታገል የሸዋ ምድር የድል መቋጫ እንድትሆን የድርሻችንን ለማበርከት ዝግጁ ነን ሲሉ አረጋግጠዋል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
Repost from N/a
የአስቴ ጎማ ተራራ ክፍለ ጦር ወታደራዊ ቁመናውን ተቋማዊ ሂደትን በተከተለ መልኩ ገምግሞ አሰራሮችን በማዘመን ለሚሰጡ ድርጅታዊ ተልዕኮዎች ራሱን በተሐድሶ አዘጋጀ!!
ጳጉሜ 04/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ መሐመድ ቢሆነኝ ኮር አስቴ ጎማ ተራራ ክፍለ ጦር ተቋማዊና ወታደራዊ ብቃቱን ይበልጥ የሚያጠናክርበትን የተሐድሶ መርሃ-ግብር በደማቅ ሁኔታ ማድረጉን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን አስታወቀ።
በመርሃ-ግብሩ ላይ የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱና፣ የአሳምነው 5ኛ ዕዝ ሰብሳቢ አርበኛ ደሳለኝ ሲያስብሸዋ፣ የዕዙ ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ አማን እሸቱ፣ የዕዙ ፖለቲካ መምሪያ ሃላፊ ዶክተር ታደሰ ገ/ፃድቅ፣ እንዲሁም ሌሎች የዕዝ፣ የኮርና የክፍለ ጦሩ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ጠላትን እንደ ንብ የሚነድፉት፡ አስቴ ጎማ ተራራ ክፍለ ጦር፤ ህዝቡን ከመጥፋትና ከውርደት ታድጎ ወደ ታሪካዊ የክብር ማማ ለማሸጋገር ራሱን በትግል ሜዳ ያስቀደመ አይበገሬ ጦር ሆኖ ተከስቷል።
ክፍለ ጦሩ ጠላት አካባቢውን በወረረበት የ42 ቀናት ውጊያ ታላቅ የበላይነት በማሳየት፣ ፈተናዎችን በማለፍ፣ የጠላትን ኃይል በማዝረክረክ የቆየ መሆኑ ሲታወቅ፧ የቻለ በእሳት የተፈተነ ስብስብ መሆኑ ተገልጿል። በሂደት ያጋጠሙትን ውስጣዊ ክፍተቶች በመሙላት፣ በአዳዲስ አመራሮችና አደረጃጀቶች ወታደራዊ ቁመናውን በማዘመን ለቀጣይ ግዳጆች በከፍተኛ ዝግጅት ራሱን አድሷል።
በመድረኩ የክብር እንግዳ ሆነው የተገኙት የአሳምነው 5ኛ ዕዝ ዋና መሪ አርበኛ ደሳለኝ ሲያስብሸዋ ባስተላለፉት መልዕክት፦" ይህ ትግል የህዝብ ትግል ነው። በዚህ ቅዱስ በሆነው ትግላችን የጀመርነውን የአማራ ህዝብ ህልውና በማረጋገጥ የኢትዮጵያን የወደፊት መፃኢ እጣፋንታ ለማስተካከል ነው" በመሆኑም ተቋማዊ አሰራርን ጠብቃችሁ በርቱ በማለት ሲቋጩ፤ የዕዙ ዋና ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ አማን እሸቱ በበኩላቸው የወታደራዊ ዝግጅቱን ደረጃ ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው፡ ሁልጊዜም የብቃት ደረጃችሁን በማሻሻል ነገም እንደወትሮው የሁልጊዜ ዝግጅትና ጥንካሬ ይኑራችሁ ሲሉ ደምድመዋል።
በመድረኩ ላይ ከክፍለ ጦሩ አባላት ለተነሱት ጥያቄዎች፦ ከአመራሩ በቂ ማብራሪያና ምላሽ ሲሰጥ፣ ለነበሩ ክፍተቶች በሙሉ በአዲሱ አሠራር እደማይደገሙ ተገልጿል።
በመጨረሻም የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ ባስተላለፉት መልዕክት፦ "የአንድነታችን ውጤት በጠንካራ አላማ እድንወያይና በጋራ እንድናቅድ አድርጎናል" ዕቅዳችንንም በአንድነት እናሳካለን በሚል መልዕክት የዕለቱ መርሀ-ግብር መጠናቀቁን ኮሩ አሳውቋል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ)ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
https://t.me/abeamoraw
በሕዝባችን ላይ ታሪካዊ ስሕተት ለመሥራት ሕሊናችን አልፈቀደም ያሉ የአገዛዙ ሠራዊት ፋኖን ተቀላቀሉ!!
ጳጉሜ 04/2018 ዓ.ም
በርካታ የአገዛዙ መከላከያ የአየር ወለድ፣ የኮማንዶና የአድማ ብተና አባላት፡ ከነ ሙሉ ትጥቃቸው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝን በገፍ እየተቀላቀሉ እደሆነ ተገለፀ።
የብልፅግና አገዛዝ ሥልጣኑን ለማስረዘም በሕዝብ ላይ እያካሄደ ያለውን ደም አፋሳሽ ስርዓትን የተረዱ ሠራዊቶቹ፣ ለእውነትና ለወገናቸው በመወገን ስርዓቱን ለቀው ሕዝባዊ ትግሉን በገፍ መቀላቀላቸውን ቀጥለዋል።
በመውደቂያ ማማው ላይ የሚገኘው የአብይ አህመድ ስርዓት፣ በግድም በውድም የስልጣኑ ጠባቂ ለማድረግ የጥላቻ ፖሊሲ አስተምሮ ያሠለፋቸው ሠራዊት፣ እኩይ ተግባርን በመጠየፍ "እኛ የሀገር ዘብና የሕዝብ ጠባቂዎች እንጂ የስርዓትሕ ጠባቂ አንሆንም" በማለት ፋኖን በክብር መቀላቀል ችለዋል።
በዚሕም መሠረት፦
👉 ወደ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር
1.አበባው ሀብታሙ — ከ27ኛ ሻለቃ አድማ ብተና
2.እሱባለው ገነት — ከ27ኛ ሻለቃ አድማ ብተና
3.መብራቱ ጥላዬ — የ31ኛ ሻለቃ መሪ (የአለባቸው አጃቢ)
4.ምትኩ ታይቸው — የ31ኛ ሻለቃ አባል
✔ ንብረቶች
● (3) ሶሥት ባለ ሁለት እግር ክላሽኮቭ መሣሪያዎች
● (1) አንድ ሰደፍ ክላሽኮቭ መሣሪያ
● (165) (መቶ ስድሳ አምስት) የክላሽኮቭ ጥይቶች
👉 ወደ 7ለ70 ክፍለ ጦር የተቀላቀለ
1. ምክትል ፲ አለቃ ማርቆስ በዳሳ -ከ102ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር
✔ ንብረቶች
● (1) አንድ ክላሽኮቭ መሣሪያ
● (90) ዘጠና የክላሽኮቭ ጥይቶች
● (1) አንድ የደረት ትጥቅ
● (1) አንድ ወታደራዊ ቦርሳ
👉 ወደ ከሠም ፪ኛ ኮር ቡልጋ ክፍለ ጦር የተቀላቀሉ
1. ፻ አለቃ አደራጀው አዱኛ- የ112ኛ አ/ወ/ክ/ር/ሻ/መሪ
2. **** የሻበል መሪው ጋርድ
✔ ንብረቶች
● (2) ሁለት ጥርጥር ክላሽኮቭ መሣሪያዎች
● (1) አንድ የደረት ትጥቅ
● (2) ሁለትF1 ቦምቦች
● (3) ሶሥት ካዝናዎች
● (120) መቶ ሃያ የክላሽኮቭ ጥይቶች
● (1) አንድ ወታደራዊ መገናኛ ሬዲዮ
እነዚሕ ንብረቶች በመያዝ የሕዝብን ትግል ተቀላቅለዋል። በቀጣይም የአገዛዙ ወታደሮች ይህንን ታሪካዊና ህሊናዊ ውሳኔ በመከተል ወደ ሕዝባዊ ኃይሉ እንድትቀላቀሉ፣ ዕዛችን ጥሪውን አቅርቧል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሰበር ዜና!
ጀብደኛው ምኒልክ 1ኛ ዕዝ በዋድላ-ደላንታ-ዳውንት ግንባር የአገዛዙን አንድ ክፍለጦር ሙሉ በሙሉ ደመሰሰ!
በምርኮ የተገኘ፦
✅ አራት (4) ዶሽቃ
✅ ዘጠኝ (9) ብሬን
✅ ሰባት (7) ስናይፐር
✅ ሁለት(2) አርፒጂ
✅ ከሶስት መቶ (300) በላይ ክላሽንኮቭ
✅እንዲሁም ከመቶ ሃምሳ (150) በላይ የሰው ሃይሉ ተማረከ!
በዚህ ከፍተኛ የግንባር ዉጊያ ወታደራዊ አዛዡ ጨምሮ፤ አንድ ክፍለጦር ሙሉ በሙሉ ተደ*ደምስሷል!
የጀብዱ ባለቤቶች 16ኛ ኮር(የቀድሞው ደጋው መብረቅ) እና የዕዙ ልዩ ዘመቻ አሃዶች ናቸው።
ምንጭ፦አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!
ቴሌግራም ገፃችን👉https://t.me/MerebMedia24
የ7/ለ70 ክፍለ ጦር፤የጦር አበጋዞች በብርቂቶ ቀበሌ ጠላትን ድባቅ በመምታት ታላቅ ድል ተቀዳጁ!!
ጳጉሜ 02/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ 7/ለ70 ክፍለ ጦር በኤፌሶን አጣዬ አላላ ክላስተር ብርቂቶ ቀበሌ በተደረገ ከፍተኛ ተጋድሎ የጠላትን ኃይል አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ድል መቀዳጀታቸው ታወቀ።
ለዐቢይ አህመድ አገዛዝ ታማኝ እንደሆነ የሚነገርለት 102ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር ከአጣዬ እና ከሰንበቴ አቅጣጫዎች በመነሳት በፋኖ ላይ ድንገተኛ ከበባ ለማድረግ ብርቂቶ የተከሰተውን ጠላት፤ ቀድመው በመዘጋጀት ስልታዊ የማጥቃት ውጊያ ያደረጉት አናብስቶች ታላቅ ድል አስመዝግበዋል።
በብርቂቶ ቀበሌ በተካሄደው ከባድ ውጊያ የጠላት ኃይል ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳቁሳዊ ውድመት ማስተናገዱን " ጫላ ስዩም" የተባለ አንድ የአገዛዙ አባል እጁን ለፋኖ ከሰጠ በኃላ እንዲሕ ሲል አብራርቷል፤ የአብይ አሕመድ ስርዓት በተሳሳተ ትርክት ከየስራ ቦታችን አፍሶ አምጥቶ፣ ከፋኖጋ በነበረው ውጊያ በጣም በርካታ አባሎቻችን ሙትና ቁስለኛ ሆነውብናል ሲል አረጋግጧል።
ይሕንን ታላቅ ገድል የክፍለ ጦሩ አካል ደመላሽ ሻለቃ ያስመዘገበች ሲሆን፣ ከጠላት የሚከተሉትን ንብረቶች ለክፍለ ጦሩ ገቢ አድርጋለች፦
✔ (2) ጥርጥር ክላሽንኮቭ መሳሪያ
✔ (120) የክላሽኮቭ ተተኳሽ
✔ (3) ወታደራዊ ቦርሳዎች
✔ (2) የውሃ ኮዳዎች
✔ (8) ካዝናዎች
✔ (4) F1 ቦንቦች
በመጨረሻም በዚሕ አውደ ውጊያ ክፉኛ የቆሰሉት የጠላት አባላት ወደ አጣዬና ሰንበቴ ለህክምና በሪፈር እደተላኩና ሌሎች ቀላል ቁስለኞች በአላላ ጤና ጣቢያ እየታከሙ እንደሆነ በውስጥ መረጃዎቹ ማረጋገጡን ገልጿል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
በመንዝ እና ግሼ አውራጃ የዕዙ ስምሪት አካላት የክላስተር አደረጃጀቶችን በመገምገም፡ በክላስተሩ የአባት አርበኞች ጦር መመስረቱ ተገለፀ!!
ጳጉሜ 03/2018 ዓ.ም
በመንዝ እና ግሼ አውራጃ ከአንድ ወር በፊት የተዋቀሩ ክላስተሮችንና አደረጃጀቶችን ወርሃዊ የስራ አፈጻጸም መገምገሙን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ የስምሪት ቡድን አስታወቀ።
ግምገማው በመንዝ እና ግሼ አውራጃ በሚገኙት ግራርአምባ እና ወጀድ ክላስተሮች ላይ የተካሄደ ሲሆን፣ በስራቸው የሚተዳደሩ ቀበሌዎችን ግልጽና ቀልጣፋ አሰራር በመከተል የህዝብ አገልግሎትን በማቀላጠፍ እንዲሁም የፍትህ ስርዓቱን በማሻሻል ረገድ የተከናወኑ ስራዎች ተገምግመዋል።
በርካታ ቀበሌዎችን እና አባት አርበኞችን ያቀፈው "ወዠድ ክላስተር" (014፣ 015፣ 016፣ 017፣ 018 እና 019) ቀበሌዎችን በቅንጅት ገምግሞ፡ ጠንካራና ግዙፍ፣ የአርበኞች ክፍለ ጦር መመስረቱን አስታውቀዋል።
የተመሠረተው የአርበኞች ክፍለ ጦሩ የአካባቢውን ሰላም ከመጠበቅ ባሻገር ለህልውና ትግሉ ስኬት ሚናውን እንደሚወጣ ተገልፆ፣ ይህ አዲስ የተመሰረተው ክፍለ ጦር በክብር በተሰዋው ታጋይ ስም " ካሳ አደፍርስ ክፍለ ጦር" ተብሎ ተሰይሟል።
ይሕ ክፍለ ጦር፡ ነብሮ ሻለቃ፣ልጅ ስዩም መኮንን ሻለቃና ሙላቱ ወልደሚካኤል ሻለቃዎችን በማጣመር የተዋቀረ ሲሆን፧ ለክፍለ ጦሩ ጠንካራና ታታሪ አመራሮችን ሠይሞ ተዋቅሯል።
በመጨረሻም ለክፍለ ጦሩ የተሰየሙት አመራሮች የተጣለባቸውን አደራ፡ የፍትህ እና የሰላም ማስከበር ኃላፊነት በቅንነት፣ በታማኝነትና በተጠያቂነት ለማገልገል ቃለ-መሀላ ፈጽመው ውይይቱ ተጠናቋል።
"ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
በቡልጋ በተደረገ ውጊያ ቡልጋ ክፍለ ጦር፡ በሪፐብሊካን ጋርድ ኃይል ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ማድረሱ ተገለፀ!!
ጳጉሜ 02/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (፭ኛ) ዕዝ፣ ከሰም ፪ኛ ኮር ቡልጋ ክፍለ ጦር ለከበባ በተንቀሳቀሰው የሪፐብሊካን ጋርድ ኃይል ላይ ከፍተኛ ድል መቀዳጀቱን የኮሩ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አስታወቀ።
የአገዛዙ ስልጣን ጠባቂ የተባለው ሪፐብሊክ ኃይል ከምንጃር አረርቲ ከተማ በመነሳት ወደ በረኸት ወረዳ መተህብላ ከተማ የወረዳው አመራሮችንና የስንቅ አቅርቦት (ሬሽን) ለማድረስ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ሳለ፣ በቡልጋ ክፍለ ጦር አባላት ባልተጠበቀ ጥቃት ከፍተኛ ኪሳራ አስተናግዷል።
ከምንጃር የተነሳው የአገዛዙ ኃይል ሜጢ በተባለው ልዩ ቦታ ላይ ሲደርስ ከባድ ኪሳራ አስተናግዷል። በተመሳሳይ ሰዓት ከመተህብላ ከተማ በመውጣት የመጣውን ኃይል ለመቀበል ተሬ በተባለ ቦታ በተደረገው የጨበጣ ውጊያ፣ ያልጠበቀው ጥቃት ስለደረሰበት ወደ ኋላ ለማፈግፈግ ተገዷል።
ከ10 ሰዓታት በላይ በፈጀው በዚህ ውጊያ በመንግሥት ኃይል በኩል ከተራ ወታደር እስከ መስመራዊ መኮንኖች ድረስ ሙትና ቁስለኛ መሆናቸው ተገልጿል። በዚሕም አንድ (01) ጥርጥር ክላሽንኮቭ ጠመንጃ ከነ ሙሉ ተተኳሹ መማረኩ ታውቋል።
በዚሕ አውደ ውጊያ ፋኖ በከፍተኛ የስነ-ልቦና የበላይነትና በላቀ ብቃት መጠናቀቁ ተጠቅሷል። እንደ ኮሩ ሕዝብ ግንኙነት ገለፃ፡ የተገኘው ድል በቀጣይ ዘመቻዎች ከፍተኛ የሞራል የበላይነት የሚሰጥ መሆኑን አክሎ ገልጾታል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (፭ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
