5 088
مشترکین
+424 ساعت
-97 روز
-6630 روز
آرشیو پست ها
በመረሐቤቴ አውራጃ ሰፊ ሕዝባዊ መድረኮች እና የአደረጃጀት ሥራዎች መካሔዳቸውን ተገለፀ!!
ጳጉሜ 05/2018 ዓ.ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መረሐቤቴ አውራጃ በሚገኘው ሞረትና ጅሩ ወረዳ ሰፊ ሕዝባዊ መድረኮች እና የአደረጃጀት ሥራዎች በተሳካ ሁኔታ መካሄዳቸውን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ መርሀ-ቤቴ ስምሪት ቡድን አስታወቀ።
በመድረኮቹ ወቅት መሠረቱ ሕዝብ የሆነው የፋኖ ፖለቲካዊ ትጥቅ ትግል ከማህበረሰቡ ጋር በየዕለቱ በመወያየት ላይ ሲገኝ፣ በቀበሌዎች አዳዲስ ድርጅታዊ አሠራሮችንና መዋቅሮችን የማስፋፋት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ገለፁ።
የአገዛዙን ፀረ-አማራነት ጉዞ በመመከት፣ በፋኖ አሠራርና መርህ መሠረት ማህበረሰቡን በክላስተርና በአውራጃ ደረጃ በማደራጀት ወደ አንድ የተቀናጀ አደረጃጀት የማምጣት ሥራ በቋሚነት እየተሠራበት እደሚገኝ አክለው ገልፀዋል።
በሞረትና ጅሩ ወረዳ ከተከናወኑ ሰፊ የሕዝባዊ መድረክ እና የአደረጃጀት ሥራዎች መካከል የ"አብዲናጎ ክላስተር "እና "የውሎ ክላስተር" በርካታ ቀበሌዎችን በማቀናጀት አደረጃጀቶች የተዘረጉ ሲሆን፣ ከሕልውና ትግሉ ጎን ለጎን የሕዝቡን የመልካም አስተዳደር ችግሮች በሲቪል አስተዳደሩ በኩል በተሳካ መልኩ እዲፈቱ የሚያስችል ተሠርቷል ብለዋል።
በተካሄዱት ሕዝባዊ መድረኮች በየደረጃው ያሉ የድርጅቱ አመራሮች፣ በተለይም የዕዝና የኮር አመራሮች የተገኙ ሲሆን፣ አመራሮቹ ከማህበረሰቡ ለተነሱ አስተያየቶችና ጥያቄዎች አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት፤ ከወቅታዊ ሁኔታዎች አኳያ ሰፊ ዝርዝር ጉዳዮች ላይ በመወያየት ቀጣይ የትግል አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል።
በዚህም መሠረት አባት አርበኞች በአደረጃጀታቸው፣ ወጣቶች ደግሞ ወደ ስልጠና ማዕከላት እየገቡ በመሰልጠን የብልፅግናን አገዛዝ በጋራ ሊታገሉ እንደሚገባ መግባባት በመድረኩ የተሳተፉት የመላው ማህበረሰብ አባላት በትግሉና በአፋብን ሁሉን አቀፍ ውሳኔዎች መደሰታቸውን ገልጸዋል።
በመጨረሻም የዕዙ የስምሪት ቡድን፣ የአማራ ሕዝብ የትግሉ ዋና ባለቤት በመሆኑ በሚችለው አቅም ሁሉ በቁርጠኝነት አስተማማኝ ደጀን ሆኖ ሊታገል እንደሚገባ በመጠቆም መድረኮቹ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቃቸውን አሳውቋል።
" ክብር ለተሰውት ሰማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!!
+1
የአፄ ዓምደ ጽዮን ኮር በሸዋ ጠቅላይ ግዛት የፈፀመው ተጋድሎ፤ጠላት ላይ ከፍተኛ ሰብዓዊና ወታደራዊ ኪሳራ አስተናገደ!!
ጳጉሜ 05/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው 5ኛ ዕዝ፣ አፄ ዓምደ ጽዮን ኮር ከተጉለትና ቡልጋ እስከ መርሀቤቴ አውራጃዎች ባደረጉት ቆራጥ ተጋድሎ፣ የጠላትን ወራሪ ኃይል በመደምሰስ ከፍተኛ ወታደራዊና ሰብዓዊ ኪሳራ ማድረሳቸውን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን አስታወቀ።
ጠላት በሁለት ታላላቅ ግንባሮች ማለትም በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ ሳሲት ክላስተር እንዲሁም በመርሀቤቴ አውራጃ ሚዳና ሬማ ክላስተር ለዘረፋ ተግባር የተንቀሳቀሰው የአገዛዙ 112ኛ እና 101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር እንዲሁም 105ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር ከአርበኞች ጦር ሰራዊት ጋር በተደረገ የተቀናጀ ውጊያ ከባድ ኪሳራ ማስተናገዱ ተገለፀ።
በሳሲት እና በመርሀቤቴ ግንባሮች የተመዘገቡ ድሎች
ከጳጉሜ 03/2018 ዓ.ም ጀምሮ በሳሲት ቀጠና በተደረገው ውጊያ፤ የንጉስ ሣህለ ሥላሴ ክፍለ ጦር ልዩ ቦታው ብርቃ በተባለ ስፍራ በፈጸሙት የጨበጣ ውጊያ በ112ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲያደርሱ፤ በተመሳሳይ ሳሲት ክላስተር የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በተቀናጀ ውጊያ ይሕንኑ መፈፀማቸው ተገልጿል።
በሌላኛው ግንባር ትላንት ከጳጉሜ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ በመርሀቤቴ አውራጃ ሚዳና ሬማ ክላስተር በተካሄደው ተጋድሎ፣ አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በሬማ ከተማ ዘልቀው በመግባት የ101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር አመራርን አስደናቂ እርምጃ መውሰዳቸው ተገለፀ።
እንዲሁም በአዝማና ይጎቢያ ቀበሌ በተደረገው ውጊያ ከ12 በላይ የሚሆኑ የዘራፊ ቡድኑ አባላት ሲደመሰሱ፣ በቀጠናው በተካሄደው እልህ አስጨራሽ ውጊያ የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ሻለቆች፣ የኮሉ ብርጌድና የካራምሽግ ብርጌድ አርበኞች በትብብር ወራሪውን ኃይል መምታታቸው ተረጋግጧል።
የሀገር መከላከያ ሰራዊት ነኝ ብሎ፡ አጥፊና ዘራፊ ቡድን ከሳሲት ክላስተር ከ8 በላይ የአርሶ አደሮችን በሬዎችን በመዝረፍ፣ በጥቅሉ ከ15 በላይ ኩንታል ጤፍና ስንዴ እህል በአስገዳጅ መዋጮ መዝረፉ ሲገለፅ፣ በተመሳሳይ በሚዳና ሬማ ክላስተርም መጠነ ሰፊ የዝርፊያ ወንጀል መፈጸሙን የኮሩ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ክፍል አስታውቋል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
የአባት አርበኞች ጦር አደረጃጀቱን በማዘመን "ምኒልክ አርበኞች ክፍለ ጦር" በሚል ስያሜ በተጉለት በይፋ መመስረቱ ተገለፀ!!
ጳጉሜ 05/2018 ዓ.ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ተጉለት አውራጃ ሲንቀሳቀስ የቆየው የአባት አርበኞች ጦር አደረጃጀቱን በማዘመንና በማጠናከር "ምኒልክ ክፍለ ጦር" በሚል ስያሜ በይፋ መመስረቱ የተጉለት ቀጠና ስምሪት ቡድን አስታወቀ።
ክፍለ ጦሩ ይፋ በተደረገበት በዚህ መድረክ ላይ የዕዝ፣ የኮር እንዲሁም የክፍለ ጦር አመራሮች በተገኙበት ሲመሠረት፤ አደረጃጀትን በማዘመን እና የድርጅቱን የፖለቲካ ትጥቅ ትግሉን በማስረፅ አባት አርበኞቹ ለአካባቢው ሠላምና ደሕንነት እዲያረጋግጡ ታልሞ መዋቀሩ ተገለፀ።
በውይይቱ ወቅት አመራሮቹ እንዳመለከቱት፤ የአማራ ህዝብ የገጠመውን የህልውና አደጋ ለመመከትና ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት የአደጋውን ዘርፈ-ብዙነት መረዳት ተገቢ በመሆኑ፣ ለዚህም ዕድሜው ለትግል የደረሰ የህብረተሰብ ክፍል በሙሉ ባለው አቅም መታገል እንደሚኖርበትና፣ ትግሉም በዋናነት ቀጥተኛ ጥቃት እያደረሰ ባለው አገዛዝ ላይ ብቻ መነጣጠር እንዳለበት አስምረውበታል።
በሌላ በኩል አርበኞቹ በሰጡት አስተያየት፤ አሁን ያለው አገዛዝ በይፋ እድጠፋና ባወጀበት፣ ንብረታችን እዲወድም በዘመተበት፣ በስልታዊ መንገድ ወጣቱ በጦርነት እዲማገድ፣በጥቅም ማባበያ ሚሊሻና አድማብተና እያለ ትውልዱን እያመከነ በመሆኑ፤ ይሕንን የህልውና አደጋ ለመመከት ብቸኛውና የመጨረሻው አማራጫችን በተባበረ ክንድ አገዛዙን ማስወገድ ነው ሲሉ አቋማቸውን አስቀምጠዋል።
ሆኖም በርካታ ጀግኖችን አቅፎ በአባት አርበኞች አደረጃጀት ሲታገል የቆየው የተጉለት አውራጃ ጦር፣ የታጋዮቹን ፍላጎት መነሻ በማድረግና የትግሉን ህልውና ለማስቀጠል ሲባል አደረጃጀቱን ማዘመን አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ "ምኒልክ አርበኞች ክፍለ ጦር" በሚል ስያሜ መመስረቱን አስታውቀዋል።
አደረጃጀቱ በማደጉ የተደሰቱት የምኒልክ አርበኞች ክፍለ ጦር አባላት በበኩላቸው፤ የተካሄደው የምክክር መድረክ በትግል ሂደቱ ላይ የነበሩ ብዢታዎችን ያጠራ መሆኑን ገልጸው፣ እንደ ቀደምት አባቶቻችን በመታገል የሸዋ ምድር የድል መቋጫ እንድትሆን የድርሻችንን ለማበርከት ዝግጁ ነን ሲሉ አረጋግጠዋል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
Repost from N/a
የአስቴ ጎማ ተራራ ክፍለ ጦር ወታደራዊ ቁመናውን ተቋማዊ ሂደትን በተከተለ መልኩ ገምግሞ አሰራሮችን በማዘመን ለሚሰጡ ድርጅታዊ ተልዕኮዎች ራሱን በተሐድሶ አዘጋጀ!!
ጳጉሜ 04/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ መሐመድ ቢሆነኝ ኮር አስቴ ጎማ ተራራ ክፍለ ጦር ተቋማዊና ወታደራዊ ብቃቱን ይበልጥ የሚያጠናክርበትን የተሐድሶ መርሃ-ግብር በደማቅ ሁኔታ ማድረጉን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን አስታወቀ።
በመርሃ-ግብሩ ላይ የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱና፣ የአሳምነው 5ኛ ዕዝ ሰብሳቢ አርበኛ ደሳለኝ ሲያስብሸዋ፣ የዕዙ ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ አማን እሸቱ፣ የዕዙ ፖለቲካ መምሪያ ሃላፊ ዶክተር ታደሰ ገ/ፃድቅ፣ እንዲሁም ሌሎች የዕዝ፣ የኮርና የክፍለ ጦሩ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ጠላትን እንደ ንብ የሚነድፉት፡ አስቴ ጎማ ተራራ ክፍለ ጦር፤ ህዝቡን ከመጥፋትና ከውርደት ታድጎ ወደ ታሪካዊ የክብር ማማ ለማሸጋገር ራሱን በትግል ሜዳ ያስቀደመ አይበገሬ ጦር ሆኖ ተከስቷል።
ክፍለ ጦሩ ጠላት አካባቢውን በወረረበት የ42 ቀናት ውጊያ ታላቅ የበላይነት በማሳየት፣ ፈተናዎችን በማለፍ፣ የጠላትን ኃይል በማዝረክረክ የቆየ መሆኑ ሲታወቅ፧ የቻለ በእሳት የተፈተነ ስብስብ መሆኑ ተገልጿል። በሂደት ያጋጠሙትን ውስጣዊ ክፍተቶች በመሙላት፣ በአዳዲስ አመራሮችና አደረጃጀቶች ወታደራዊ ቁመናውን በማዘመን ለቀጣይ ግዳጆች በከፍተኛ ዝግጅት ራሱን አድሷል።
በመድረኩ የክብር እንግዳ ሆነው የተገኙት የአሳምነው 5ኛ ዕዝ ዋና መሪ አርበኛ ደሳለኝ ሲያስብሸዋ ባስተላለፉት መልዕክት፦" ይህ ትግል የህዝብ ትግል ነው። በዚህ ቅዱስ በሆነው ትግላችን የጀመርነውን የአማራ ህዝብ ህልውና በማረጋገጥ የኢትዮጵያን የወደፊት መፃኢ እጣፋንታ ለማስተካከል ነው" በመሆኑም ተቋማዊ አሰራርን ጠብቃችሁ በርቱ በማለት ሲቋጩ፤ የዕዙ ዋና ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ አማን እሸቱ በበኩላቸው የወታደራዊ ዝግጅቱን ደረጃ ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው፡ ሁልጊዜም የብቃት ደረጃችሁን በማሻሻል ነገም እንደወትሮው የሁልጊዜ ዝግጅትና ጥንካሬ ይኑራችሁ ሲሉ ደምድመዋል።
በመድረኩ ላይ ከክፍለ ጦሩ አባላት ለተነሱት ጥያቄዎች፦ ከአመራሩ በቂ ማብራሪያና ምላሽ ሲሰጥ፣ ለነበሩ ክፍተቶች በሙሉ በአዲሱ አሠራር እደማይደገሙ ተገልጿል።
በመጨረሻም የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ ባስተላለፉት መልዕክት፦ "የአንድነታችን ውጤት በጠንካራ አላማ እድንወያይና በጋራ እንድናቅድ አድርጎናል" ዕቅዳችንንም በአንድነት እናሳካለን በሚል መልዕክት የዕለቱ መርሀ-ግብር መጠናቀቁን ኮሩ አሳውቋል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ)ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
https://t.me/abeamoraw
በሕዝባችን ላይ ታሪካዊ ስሕተት ለመሥራት ሕሊናችን አልፈቀደም ያሉ የአገዛዙ ሠራዊት ፋኖን ተቀላቀሉ!!
ጳጉሜ 04/2018 ዓ.ም
በርካታ የአገዛዙ መከላከያ የአየር ወለድ፣ የኮማንዶና የአድማ ብተና አባላት፡ ከነ ሙሉ ትጥቃቸው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝን በገፍ እየተቀላቀሉ እደሆነ ተገለፀ።
የብልፅግና አገዛዝ ሥልጣኑን ለማስረዘም በሕዝብ ላይ እያካሄደ ያለውን ደም አፋሳሽ ስርዓትን የተረዱ ሠራዊቶቹ፣ ለእውነትና ለወገናቸው በመወገን ስርዓቱን ለቀው ሕዝባዊ ትግሉን በገፍ መቀላቀላቸውን ቀጥለዋል።
በመውደቂያ ማማው ላይ የሚገኘው የአብይ አህመድ ስርዓት፣ በግድም በውድም የስልጣኑ ጠባቂ ለማድረግ የጥላቻ ፖሊሲ አስተምሮ ያሠለፋቸው ሠራዊት፣ እኩይ ተግባርን በመጠየፍ "እኛ የሀገር ዘብና የሕዝብ ጠባቂዎች እንጂ የስርዓትሕ ጠባቂ አንሆንም" በማለት ፋኖን በክብር መቀላቀል ችለዋል።
በዚሕም መሠረት፦
👉 ወደ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር
1.አበባው ሀብታሙ — ከ27ኛ ሻለቃ አድማ ብተና
2.እሱባለው ገነት — ከ27ኛ ሻለቃ አድማ ብተና
3.መብራቱ ጥላዬ — የ31ኛ ሻለቃ መሪ (የአለባቸው አጃቢ)
4.ምትኩ ታይቸው — የ31ኛ ሻለቃ አባል
✔ ንብረቶች
● (3) ሶሥት ባለ ሁለት እግር ክላሽኮቭ መሣሪያዎች
● (1) አንድ ሰደፍ ክላሽኮቭ መሣሪያ
● (165) (መቶ ስድሳ አምስት) የክላሽኮቭ ጥይቶች
👉 ወደ 7ለ70 ክፍለ ጦር የተቀላቀለ
1. ምክትል ፲ አለቃ ማርቆስ በዳሳ -ከ102ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር
✔ ንብረቶች
● (1) አንድ ክላሽኮቭ መሣሪያ
● (90) ዘጠና የክላሽኮቭ ጥይቶች
● (1) አንድ የደረት ትጥቅ
● (1) አንድ ወታደራዊ ቦርሳ
👉 ወደ ከሠም ፪ኛ ኮር ቡልጋ ክፍለ ጦር የተቀላቀሉ
1. ፻ አለቃ አደራጀው አዱኛ- የ112ኛ አ/ወ/ክ/ር/ሻ/መሪ
2. **** የሻበል መሪው ጋርድ
✔ ንብረቶች
● (2) ሁለት ጥርጥር ክላሽኮቭ መሣሪያዎች
● (1) አንድ የደረት ትጥቅ
● (2) ሁለትF1 ቦምቦች
● (3) ሶሥት ካዝናዎች
● (120) መቶ ሃያ የክላሽኮቭ ጥይቶች
● (1) አንድ ወታደራዊ መገናኛ ሬዲዮ
እነዚሕ ንብረቶች በመያዝ የሕዝብን ትግል ተቀላቅለዋል። በቀጣይም የአገዛዙ ወታደሮች ይህንን ታሪካዊና ህሊናዊ ውሳኔ በመከተል ወደ ሕዝባዊ ኃይሉ እንድትቀላቀሉ፣ ዕዛችን ጥሪውን አቅርቧል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሰበር ዜና!
ጀብደኛው ምኒልክ 1ኛ ዕዝ በዋድላ-ደላንታ-ዳውንት ግንባር የአገዛዙን አንድ ክፍለጦር ሙሉ በሙሉ ደመሰሰ!
በምርኮ የተገኘ፦
✅ አራት (4) ዶሽቃ
✅ ዘጠኝ (9) ብሬን
✅ ሰባት (7) ስናይፐር
✅ ሁለት(2) አርፒጂ
✅ ከሶስት መቶ (300) በላይ ክላሽንኮቭ
✅እንዲሁም ከመቶ ሃምሳ (150) በላይ የሰው ሃይሉ ተማረከ!
በዚህ ከፍተኛ የግንባር ዉጊያ ወታደራዊ አዛዡ ጨምሮ፤ አንድ ክፍለጦር ሙሉ በሙሉ ተደ*ደምስሷል!
የጀብዱ ባለቤቶች 16ኛ ኮር(የቀድሞው ደጋው መብረቅ) እና የዕዙ ልዩ ዘመቻ አሃዶች ናቸው።
ምንጭ፦አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!
ቴሌግራም ገፃችን👉https://t.me/MerebMedia24
የ7/ለ70 ክፍለ ጦር፤የጦር አበጋዞች በብርቂቶ ቀበሌ ጠላትን ድባቅ በመምታት ታላቅ ድል ተቀዳጁ!!
ጳጉሜ 02/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ 7/ለ70 ክፍለ ጦር በኤፌሶን አጣዬ አላላ ክላስተር ብርቂቶ ቀበሌ በተደረገ ከፍተኛ ተጋድሎ የጠላትን ኃይል አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ድል መቀዳጀታቸው ታወቀ።
ለዐቢይ አህመድ አገዛዝ ታማኝ እንደሆነ የሚነገርለት 102ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር ከአጣዬ እና ከሰንበቴ አቅጣጫዎች በመነሳት በፋኖ ላይ ድንገተኛ ከበባ ለማድረግ ብርቂቶ የተከሰተውን ጠላት፤ ቀድመው በመዘጋጀት ስልታዊ የማጥቃት ውጊያ ያደረጉት አናብስቶች ታላቅ ድል አስመዝግበዋል።
በብርቂቶ ቀበሌ በተካሄደው ከባድ ውጊያ የጠላት ኃይል ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳቁሳዊ ውድመት ማስተናገዱን " ጫላ ስዩም" የተባለ አንድ የአገዛዙ አባል እጁን ለፋኖ ከሰጠ በኃላ እንዲሕ ሲል አብራርቷል፤ የአብይ አሕመድ ስርዓት በተሳሳተ ትርክት ከየስራ ቦታችን አፍሶ አምጥቶ፣ ከፋኖጋ በነበረው ውጊያ በጣም በርካታ አባሎቻችን ሙትና ቁስለኛ ሆነውብናል ሲል አረጋግጧል።
ይሕንን ታላቅ ገድል የክፍለ ጦሩ አካል ደመላሽ ሻለቃ ያስመዘገበች ሲሆን፣ ከጠላት የሚከተሉትን ንብረቶች ለክፍለ ጦሩ ገቢ አድርጋለች፦
✔ (2) ጥርጥር ክላሽንኮቭ መሳሪያ
✔ (120) የክላሽኮቭ ተተኳሽ
✔ (3) ወታደራዊ ቦርሳዎች
✔ (2) የውሃ ኮዳዎች
✔ (8) ካዝናዎች
✔ (4) F1 ቦንቦች
በመጨረሻም በዚሕ አውደ ውጊያ ክፉኛ የቆሰሉት የጠላት አባላት ወደ አጣዬና ሰንበቴ ለህክምና በሪፈር እደተላኩና ሌሎች ቀላል ቁስለኞች በአላላ ጤና ጣቢያ እየታከሙ እንደሆነ በውስጥ መረጃዎቹ ማረጋገጡን ገልጿል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
በመንዝ እና ግሼ አውራጃ የዕዙ ስምሪት አካላት የክላስተር አደረጃጀቶችን በመገምገም፡ በክላስተሩ የአባት አርበኞች ጦር መመስረቱ ተገለፀ!!
ጳጉሜ 03/2018 ዓ.ም
በመንዝ እና ግሼ አውራጃ ከአንድ ወር በፊት የተዋቀሩ ክላስተሮችንና አደረጃጀቶችን ወርሃዊ የስራ አፈጻጸም መገምገሙን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ የስምሪት ቡድን አስታወቀ።
ግምገማው በመንዝ እና ግሼ አውራጃ በሚገኙት ግራርአምባ እና ወጀድ ክላስተሮች ላይ የተካሄደ ሲሆን፣ በስራቸው የሚተዳደሩ ቀበሌዎችን ግልጽና ቀልጣፋ አሰራር በመከተል የህዝብ አገልግሎትን በማቀላጠፍ እንዲሁም የፍትህ ስርዓቱን በማሻሻል ረገድ የተከናወኑ ስራዎች ተገምግመዋል።
በርካታ ቀበሌዎችን እና አባት አርበኞችን ያቀፈው "ወዠድ ክላስተር" (014፣ 015፣ 016፣ 017፣ 018 እና 019) ቀበሌዎችን በቅንጅት ገምግሞ፡ ጠንካራና ግዙፍ፣ የአርበኞች ክፍለ ጦር መመስረቱን አስታውቀዋል።
የተመሠረተው የአርበኞች ክፍለ ጦሩ የአካባቢውን ሰላም ከመጠበቅ ባሻገር ለህልውና ትግሉ ስኬት ሚናውን እንደሚወጣ ተገልፆ፣ ይህ አዲስ የተመሰረተው ክፍለ ጦር በክብር በተሰዋው ታጋይ ስም " ካሳ አደፍርስ ክፍለ ጦር" ተብሎ ተሰይሟል።
ይሕ ክፍለ ጦር፡ ነብሮ ሻለቃ፣ልጅ ስዩም መኮንን ሻለቃና ሙላቱ ወልደሚካኤል ሻለቃዎችን በማጣመር የተዋቀረ ሲሆን፧ ለክፍለ ጦሩ ጠንካራና ታታሪ አመራሮችን ሠይሞ ተዋቅሯል።
በመጨረሻም ለክፍለ ጦሩ የተሰየሙት አመራሮች የተጣለባቸውን አደራ፡ የፍትህ እና የሰላም ማስከበር ኃላፊነት በቅንነት፣ በታማኝነትና በተጠያቂነት ለማገልገል ቃለ-መሀላ ፈጽመው ውይይቱ ተጠናቋል።
"ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
