1 087
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-2630 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+1
in 0 channels
August '26
+10
in 0 channels
Get PRO
July '26
+335
in 2 channels
Get PRO
June '26
+11
in 0 channels
Get PRO
May '26
+13
in 0 channels
Get PRO
April '26
+4
in 0 channels
Get PRO
March '26
+3
in 0 channels
Get PRO
February '26
+9
in 1 channels
Get PRO
January '26
+5
in 0 channels
Get PRO
December '25
+2
in 0 channels
Get PRO
November '25
+3
in 1 channels
Get PRO
October '25
+14
in 0 channels
Get PRO
September '25
+3
in 2 channels
Get PRO
August '25
+15
in 1 channels
Get PRO
July '25
+25
in 0 channels
Get PRO
June '25
+77
in 0 channels
Get PRO
May '25
+18
in 0 channels
Get PRO
April '25
+178
in 1 channels
Get PRO
March '25
+35
in 0 channels
Get PRO
February '25
+27
in 1 channels
Get PRO
January '25
+42
in 1 channels
Get PRO
December '24
+120
in 3 channels
Get PRO
November '24
+134
in 2 channels
Get PRO
October '24
+484
in 3 channels
Get PRO
September '24
+63
in 1 channels
Get PRO
August '24
+163
in 4 channels
Get PRO
July '24
+176
in 2 channels
Get PRO
June '24
+11
in 0 channels
Get PRO
May '24
+9
in 0 channels
Get PRO
April '24
+43
in 0 channels
Get PRO
March '24
+492
in 1 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 08 September | 0 | |||
| 07 September | 0 | |||
| 06 September | 0 | |||
| 05 September | 0 | |||
| 04 September | 0 | |||
| 03 September | +1 | |||
| 02 September | 0 | |||
| 01 September | 0 |
Channel Posts
ሰበር መረጃ!
በምክክር ኮሚሽኑ አጀንዳዎች ላይ ጠንካራ ተቃውሞ ያነሱ ከ300 በላይ ተሳታፊዎች፣ በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ መታሰራቸው ተገለጸ።
በብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን የውይይት መድረክ ላይ በአዲስ አበባ፣ በድሬዳዋ እና በሌሎች ቁልፍ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም የነበራቸውና የኦህዴድ/ብልፅግና አገዛዝ ያቀረበውን አጀንዳ ለመቀበልና ለማስፈጸም አስቸግረዋል የተባሉ 300 የሚደርሱ ተሳታፊዎች በዛሬው ዕለት መታፈናቸው ታወቋል።
ከስፍራው ከተገኙ የዓይን እማኞች በተገኘው መረጃ መሠረት፣ የታፈኑት ተሳታፊዎች ከአማራ፣ ደቡብ፣ ሶማሌ፣ ቤንሻንጉል እና አፋር ክልሎች እንዲሁም ከተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች የተወጣጡ የምክክር ኮሚሽኑ ተሳታፊዎች ናቸው።
የታፈኑት ተወካዮች በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ተወስደው መታሰራቸው ተረጋግጧል።
ይህ የሃይልና የእገታ እርምጃ የተወሰደበት ዋና ምክንያት አገዛዙ በምክክር ኮሚሽኑ በኩል ለማስጸደቅ ያቀደው የፖለቲካ አጀንዳ በእነዚህ ተሳታፊዎች በኩል ባጋጠመው ከፍተኛ ተቃውሞና እምቢተኝነት በመሰናከሉ እንደሆነ ተመልክቷል።
በተለይም ነገ በሚካሄደው የምክክር ኮሚሽኑ ምላተ ጉባኤ ላይ እነዚህ ጠንካራ ተቃዋሚ ተሳታፊዎች በሌሉበት አዲስ አበባን የኦሮሚያ የማድረግ አጀንዳን ጨምሮ የታቀዱ ውሳኔዎችን ያለተቃውሞ ለማሳለፍ ታስቦ የተፈጸመ መሆኑ ተገልጿል።
ድርጊቱ ኮሚሽኑ የአገዛዙን ፍላጎት ብቻ የሚያስፈጽም መሣሪያ መሆኑን ዳግም ያረጋገጠ ክስተት እንደሆነ ተጠቅሷል።
| 2 | "በአዲስ አበባ ከተማ እና ነዋሪወቿ ላይ የተደቀነው የህልውና አደጋ በድርጅታችን ቁርጠኝነት፣ በህዝባችን ፅናትና በፀረ ብልፅግና ብሔራዊ ኃይሎች ትብብር በሚታጀበው የትግላችን አይቀሬ ድል የሚመመከት ይሆናል"
ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን)፤ በአዲስ አበባ ጉዳይ የተሰጠ የአቋም መግለጫ !
ነሐሴ 09/2018 ዓ.ም
ዘረ ፈጁ የብልፅግና አገዛዝ ''አገራዊ ምክክር'' በሚል ስም በኢትዮጵያ፤ በአዲስ አበባ ከተማ የሚያካሂደው የድራማ መድረክ የህዝብ ውክልና የሌለበት፣ ተጨማሪ ቀውስ የሚያዋልድ እና የአገዛዙን ዕድሜ ለማራዘም የተነደፈ የአረመኔው አገዛዝ የፖለቲካ አሻጥር መሆኑን ከዚህ በፊት ባወጣነው መግለጫ አቋም መውሰዳችን ይታወቃል።
ሆኖም ግን አገዛዙና አጋሮቹ ይህንን ከጥፋት መንገዳቸው እንዲመለሱ ያቀረብንላቸውን ጥሪ በመተው ''በምክክር'' ስም የከተሞችንና አካባቢዎቻቸውን የታሪክ፣ የዴሞግራፊ፣ መልክአምድራዊና የይዞታ ቅርፃቸውን ለማዛባትና በተለይም ነባር የአዲስ አበባ ከተማ ኗዋሪዎችንና የአማራን ህዝብ ህልውና አደጋ ላይ ለመጣል የጥፋት መንገድ ላይ መሆናቸውን ተገንዝበናል።
አዲስ አበባ ከተማ እንደገና ከመቆርቆሯና ከአሁኑ መጠሪያዋ ቀደም ብሎ ''በራራ'' በመባል የምትታወቅ፣ በመካከለኛው ክፍለ ዘመን በጦርነት ሳቢያ እስከወደመችበት ጊዜ ድረስ የአማራ ነገስታት መቀመጫና የአማራ ህዝብ ጥንተ-ርስት እንደሆነች የታሪክ መዛግብትና አርኪዮሎጂያዊ ማስረጃዎች በግልፅ ያረጋግጣሉ።
ዳግማዊ አፄ ምኒልክ እና እቴጌ ጣይቱ ብጡል አዲስ አበባ ከተማን በድጋሚ ሲቆረቁሯት፣ ባዶ መሬት ላይ ሳይሆን የአባቶቻቸውን ታሪካዊ ይዞታ፣ ርስትና ውርስ መነሻ በማድረግ ነው። ይህ ታሪካዊ እውነት ሊሸረሸርም ሆነ ማንም አምባገነናዊ አገዛዝ በጊዜያዊ ስልጣን ህዝብ ባላመነበት ፖለቲካዊ ውሳኔ ሊሰርዘው የማይችለው ፅኑ የታሪካችን አንድ አካል ነው።
ከተማዋ የአማራ ጥንተ-ርስት መሆኗ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ በሂደት የሁሉም የኢትዮጵያ ህዝብ መኖሪያ፣ የባህልና የኢኮኖሚ ማዕከል፣ እንዲሁም የአንድነት ተምሳሌት ሆና ተገንብታለች። ከዚህ አኳያ ድርጅታችን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) አዲስ አበባ የኗዋሪዎቿ፣ የሁሉም ኢትዮጵያዊያን መኖሪያ፣ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ፣ የአፍሪካ መናገሻና የዓለም አገራት የዲፕሎማሲ ማዕክል መሆኗን ሙሉ በሙሉ ያምናል፤ ይቀበላልም።
በዚህ መነሻ፣ ከተማዋ የብዝኃነትና የጋራ እድገት ማዕከል እንጂ የአንድ ዘረ ፈጅ አገዛዝ ብቸኛ መጫወቻ ስፍራ ልትሆን እንደማትችልም ድርጅታችን ያረጋግጣል። የአማራ ህዝብ፣ አዲስ አበባን ጨምሮ በመላ አገሪቱ በስፋት በሚኖርባቸው አካባቢዎች፤ ፍትሐዊ የስልጣንና የሀብት ተጠቃሚነቱ መረጋገጥ እንዳለበት ድርጅታችን ያምናል።
በአሁኑ ወቅት፣ የኦህዴድ ብልፅግና አገዛዝ አዲስ አበባን በብቸኝነት የአንድ ወገንና ብሔር በበላይነት እንዲቆጣጠራት ለማስቻል የሚሰራው ሕግን የጣሰ፣ የዴሞግራፊና የጂኦግራፊ ለውጥ በምንም መልኩ ሕጋዊ፣ ሞራላዊ፣ ፖለቲካዊና ታሪካዊ ተቀባይነት የሌለው መሆኑን እንገልፃለን።
አገዛዙ ''አገራዊ ምክክር'' በሚል የፖለቲካ ሽፋን በከተማዋ ላይ የሚያካሄደው ሴራና አሻጥር
የከተማዋን ነባር ኗዋሪዎች መብት የሚጥስ፣ የሁሉም ኢትዮጵያዊያን የጋራ መኖሪያነቷን የሚክድና ታሪካዊ እውነታውን ለማዛባት የተሸረበና የአንድ ቡድን የበላይነትን በህዝባችን ላይ በኃይል ለመጫን ያለመ በመሆኑ፣ የዚህን አምባገነን አገዛዝ ዕድሜ ለማሳጠር መላው የአዲስ አበባ ከተማ ኗዋሪዎችን ጨምሮ ኢትዮጵያውያን ድርጊቱን እንዲያወግዙት፣ እንዲቃወሙትና እንዲታገሉት በድርጅታችን አፋብን ስም ጥሪ እናቀርባለን።
እንዲሁም በከተማዋ ቀደም ብለው ይኖሩ የነበሩትም ይሁን አሁንም የሚኖሩት 80 በመቶ ( በ1999 ዓ.ም በተካሄደው ህዝብና ቤት ቆጠራ መሰረት) የሚሆኑት ነባር ኗዋሪዎች አማራዎች ናቸው። በመሆኑም የህዝብ ስብጥርንም ሆነ ታሪካዊ እውነታን በኃይልና በተሳሳተ ፖለቲካዊ ውሳኔ ለመቀየር የሚደረገውን ማንኛውም የአገዛዙን ሴራ አጥብቀን የምንታገለው መሆኑን እንገልፃለን።
የአማራ ህዝብ በገዛ አገሩ ከገጠመው ሁለንተናዊ የህልውና አደጋ ባሻገር ድርጅታችን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) የትጥቅ ትግል ውስጥ ለመግባት ካስገደዱት ምክንያቶች መካከል፦
በአዲስ አበባ ከተማ በአገዛዙ የተደቀነው የዴሞግራፊ ለውጥ አደጋ፣ የከተማዋን ቀደምት ባለቤቶችና ነባር ኗዋሪዎች በማፈናቀልና ማንነታቸውን በማጥፋት፣ የአማራ ህዝብ ከከተማዋ ጋር ያለውን ታሪካዊ እና ማህበራዊ ትስስር በመበጣጠስ ከህዝቦች ተፈጥሯዊ መስተጋብር ውጭ በሆነ መልኩ የባህል፣ የቋንቋና የተለያዩ አመለካከቶችን በኃይል ለመጫን የሚደረገው ሩጫ ይገኝበታል።
በመሆኑም፣ ድርጅታችን አፋብን ከምንጊዜውም በላቀ ሁኔታ ውስጣዊ አንድነቱንና አደረጃጀቱን ጠብቆ በመጓዝ፣ አምባገነኑና ከፋፋዩን አገዛዝ በጀመርነው ትግል ከስሩ ነቅለን በመጣል፣ ለአማራ ህዝብ ብሎም ለሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚስማማ፣ የዜጎችን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች የሚያከብር ሥርዓተ መንግስት በመገንባት ፍትህ፣ እኩልነትና የሕግ የበላይነትን ከመትከል ባሻገር አዲስ አበባ የኗዋሪዎቿ፤ የሁሉም ኢትዮጵያዊያን የጋራ መኖሪያና ዋና ከተማ፤ የአንድነትና የእድገት ማዕከል ሆና እንድትቀጥል ይታገላል።
አገሪቱ ከገባችበት ጥልቅ የህልውና፣ የፍትህና የእኩልነት ቀውስ መውጣት የምትችለው የህዝቧን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በኃይል በማፈን፣ አገሪቱን የማያቋርጥ እርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ በማስገባት ወደ ገደል እየመራት ያለውን ዘረ ፈጁን የብልፅግና አገዛዝ፤ በሕዝባዊ ትግል ሙሉ በሙሉ መገርሰስ ሲቻል ብቻ መሆኑን አፋብን በፅኑ ያምናል።
በስተመጨረሻ የኦህዴድ ብልፅግና አገዛዝ በአዲስ አበባ ከተማና በህዝባችን ላይ በምክክር ስም የጠነሰሰው ዓይን ያወጣ የፖለቲካ አሻጥር የፈጠረው የህልውና በድርጅታችን ቁርጠኝነት፣ በህዝባችን ፅናትና በፀረ ብልፅግና ብሔራዊ ኃይሎች ትብብር በሚታጀበው የትግላችን አይቀሬ ድል የሚመመከት ይሆናል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) | 398 |
| 3 | No text... | 338 |
| 4 | https://youtu.be/QpAdAhl7dbo?si=S8FJa59Ub2WlPHtQ | 585 |
| 5 | ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የቴዎድሮስ ዕዝ የአመራር ሪፎርም መጠናቀቅን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የቴዎድሮስ ዕዝ ላለፉት ወራት የአመራር ሪፎርም ለመስራት ከፍተኛ ስራ ሲሰራ የቆየ መሆኑ ይታወቃል። በዚህ ሂደት ዕዙ መዋቅራዊ አንድነቱ ተጠብቆ ጤናማ ሽግግር እንዲያደርግ ሂደቱን በጥንቃቄ እና በትዕግሥት መምራት አስፈላጊ በመሆኑ በሚፈለገው መልኩ በፍጥነት ሳይጠናቀቅ ቆይቷል።
የአደረጃጀት ፈተና ከድርጅት ዕድገት ጋር ተያይዞ በየጊዜው የሚፈጠር ቢሆንም ከውጭ ወደ ውስጥ የሚሰነዘሩ ከፋፋይ ጥቃቶችን እየመከቱ ተፈጥሯዊውን ውስጣዊ ትግል ለመዋቅራዊ ዕድገት በሚጠቅም መልኩ ለማዋል በጥበብ የተመራ ትግል ተደርጓል።
ድርጅታዊ መስመርን ለማስጠበቅ የተሄደበት ውስጠ ድርጅታዊ አሰራር ተገቢ እና ትክክል መሆኑ የዕዙን መዋቅራዊ አንድነት አስጠብቆ ለላቀ ግዳጅ የሚያበቃ ውጤት ላይ እንዲደረስ አስችሏል።
ይህ የዕዝ አመራር ሪፎርም በተለያዬ ደረጃ ውስጥ ያለፈ እና የመዋቅሩ ተዋረዳዊ ተሳትፎ የነበረበት ነው። የዕዙ ስራ አስፈጻሚ የሪፎርም ስራ አፈጻጸም ሂሩት ላይ የዕዙ ተወካይ በሆኑ የፖሊት ቢሮ አባላት አማካኝነት የኮር እና የክፍለ ጦር አመራሮች ጋር ውይይት ተደርጓል። ቀጥሎም ምክትል መምሪያ ሀላፊዎች እና ሌሎች የክፍል ሀላፊዎችን አወያየቷል። በመጨረሻም በነዚህ መድረኮች የተገኘውን ግብአት በመውሰድ የዕዙ ስራ አስፈጻሚ የሪፎርም ኮሚቴ እንዲዋቀር ወስኖ፣ የአወቃቀር ሂደቱ የሚመራበትን መመሪያ አዘጋጅቶ ወደ ስራ ገብቷል።
በዚህ መሠረት ከክፍለጦሮች፣ ከኮር እና ከምክትል መምሪያ ሀላፊዎች የተውጣጣ ኮሚቴ በማዋቀር የሪፎርም ኮሚቴው ተመሰርቷል። የዕዝ ስራ አስፈፃሚው በሰጠው መመሪያ እና ስልጣን መሠረት የሪፎርም ኮሚቴው የዕዙን የአመራር ሪፎርም ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ስራውን ጨርሶ ፕሮፖዛሉን ለዕዙ ስራ አስፈጻሚ አቅርቧል። ስራ አስፈጻሚው የቀረበለት ፕሮፖዛል መነሻ አድርጎ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ የኮሚቴው ፕሮፖዛል ላይ መጠነኛ ማሻሻያ አድርጎ የዕዙን የአመራር ሪፎርም የመጨረሻ ዝርዝር አጽድቋል።
በዚህም መሠረት የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ - ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ የአፋብን መተዳደሪያ ደንብ አንቀፅ 60 ስር በተቀመጠው መዋቅር መሰረት ከዚህ በታች በተዘረዘረው መልኩ ተደራጅቷል።
1) ሰብሳቢ:- አርበኛ ተፈሪ ካሳሁን
2) ም/ሰብሳቢ:- አርበኛ ጎበዜ ጌታቸው
3) ወታደራዊ አዛዥ:- ሻለቃ የኔአለም ዘለቀ
3.1) ምክትል ወታደራዊ አዛዥ:- መቶ አለቃ እሱባለው ዋለ
4)ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ:- አርበኛ ግሩም ምሳሌ
4.1) ምክትል:- አርበኛ አማረ ካሴ
5) ፅህፈት ቤት ኃላፊ:- አርበኛ ናትናኤል ስናማው
5.1)ምክትል:- አርበኛ ብዙነህ እምቢያለ
6) አደረጃጀት መምሪያ ኃላፊ:- አርበኛ እስቲበል አለሙ
6.1) ምክትል:- አርበኛ ደመላሽ አንድነው
7) የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ:- አርበኛ ወግደረስ ጤናው
7.1)ምክትል:- አርበኛ ታደሰ አስማረ
8)ጥናትና ስትራቴጂ ጉዳዮች መምሪያ:- አርበኛ ዳሞት አለኸኝ
8.1)ምክትል:- አርበኛ መንግስቱ አማረ
9)ፋይናንስ እና ግዥ አስተዳደር:- አርበኛ ይትባረክ አንዳርጌ
9.1)ምክትል:- አርበኛ ያሬድ በቀለ
10)የሕዝብ አስተዳደር መምሪያ:- አርበኛ ዘመን ተሻለ
10.1)ምክትል:- አርበኛ በለጠ ልየው
11) ሴቶች ጉዳይ መምሪያ- ፋኒት አትጠገብ አጥናፉ
11.1)ምክትል:- ፋኒት ክብራለም አያልነህ
12) ማሕበራዊ ጉዳይ መምሪያ:- አርበኛ ላይችሉህ ገበየሁ
12.1) ምክትል:- አርበኛ በላይነህ አለምነህ
13) የሰው ሃብት -ዳኛው ሽባባው
13.1) ምክትል:- አርበኛ በረከት አጥናፉ
14)ት/ት እና ስልጠና መምሪያ:- አርበኛ ክንፈመላክ ካሳ
14.1)ምክትል:- አርበኛ ዘውዳለም አዱኛ
15) መካናይዝድ ጦር መምሪያ:- ኮሎኔል አደመ ልጃለም
15.1) ምክትል:- መቶ አለቃ ሳሙኤል አታላይ
16)ህግ እና ስነስርዓት መምሪያ:- አርበኛ ዘማርያም እስከዚያ
16.1) ምክትል:- አርበኛ ቻላቸው ታፈረ
17) ሀብት አፈላላጊ መምሪያ- አርበኛ ሀይለሚካኤል ባዬህ
17.1) ምክትል:- አርበኛ ደሴ ጌታሁን
18) እቅድ ዝግጅትና ግምገማ መምሪያ:- አርበኛ የሻነው መለሰ
18.1) ምክትል:- አርበኛ አታላይ ሞሴ
19) ዘመቻ መምሪያ-አምሳ አለቃ ታደሰ ልንገሬ
19.1) ምክትል:- መቶ አለቃ አጃናው ጥላሁን
20) ሎጀስቲክ መምሪያ:- አርበኛ ይርሳው ደምስ
20.1) ምክትል:- መቶ አለቃ አስረስ ምህረቴ
21) ወ/አስተዳደር መምሪያ- መቶ አለቃ ያሬድ ጫኔ
21.1) ምክትል:- 50 አለቃ ይበልጣል መልካሙ
22)ወ/ስልጠና መምሪያ:- ሻምበል ጌትነት ንጉሴ
22.1) ምክትል:- አምሳ አለቃ ዘላለም ደሴ
23) ልዩ ዘመቻ መምሪያ- መቶ አለቃ ማርቆስ አሞኜ
23.1)/ምክትል:- ሻለቃ በላይ ብዙ አየሁ
24) መረጃ - ----------
24.1) ምክትል-- --------
25)ኢንዶክትርኔሽን መምሪያ:- መቶ አለቃ ጊዮን ጀንበሬ
25.1) ምክትል- መቶ አለቃ ገረመው አጋዠ
26) ወታደራዊ እቅድ እና ስትራቴጅ:- ሃምሳ አለቃ ስማቼው ቢሻው
26.1) ምክትል:- መቶ አለቃ ለዓለም ጌታሁን
27) ወታደራዊ መረጃ------
27.1) ምክትል- -------
28) ጤና መምሪያ:- ዶክተር እንዳላማው ጤናው
28.1) ምክትል-- ዶክተር ደመቀ አያሌው | 536 |
| 6 | No text... | 368 |
| 7 | የጎጃም አርበኞች ታሪካዊ አንድነት ሊታወጅ ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተዋል።
በጉጉት የሚጠበቀው ታሪካዊ እርምጃ እውን ሊሆን ተቃርቧል። ጠላትም ሊደነግጥ ይገደዳል 😎
ከተበታተነ የትግል እንቅስቃሴ ወደ ተደራጀ፣ መዋቅራዊ እና ተቋማዊ እድገት እንሸጋገራለን!
ድል ለድል አድራጊው ፋኖ 💪💪 | 466 |
| 8 | https://youtu.be/lM0Vaj33K1c?si=bPmmXL0S6ZXQnylt | 346 |
| 9 | ሰበር መረጃ !
ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ የአመራር ምደባ አድርጓል። የቀድሞወቹ ሁለት እዝ አመራሮች በጋራ በአካል በመገናኘት ባካሄዱት ጉባኤ የተዋሃደው የጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ አመራር በሚከተለው መልኩ የኃላፊነት ምደባ ተደርጓል።
የሰብሳቢውን ቦታ አርበኛ ዮሐንስ ንጉሱ እና አርበኛ ባዬ ቀናው ለ3 ወራት ያክል በጥምር የሚመሩት ይሆናል፡፡
1ኛ/ ከሁለቱ አርበኞች በተጨማሪ የተመደቡ የስራ አስፈፃሚ አባላት:-
ተቀ/ምክ/ሰብሳቢ…………………አርበኛ ሰለሞን አጣናው
ም/ሰብሳቢ ለፖለቲካ ጉዳዮች………አርበኛ ኪሩቤል ጎቤ
ወታደራዊ አዛዥ…………………….አርበኛ ደረጀ በላይ
ምክ/ወታደራዊ አዛዥ………………አርበኛ አሻምበል አምሳሉ ማዘንጊያ
ምክ/ወታራዊ አዛዥ ለአስተዳደር ጉዳዮች....አርበኛ ሸጋ ጌታቸው
ወታራዊ አማካሪ…………………………ኮ/ል አበራ አዛናው
ፖለቲካ መምሪያ…………………..……አርበኛ አንተነህ ድረስ
ዘመቻ መምሪያ……………………….አርበኛ ተሾመ አበባው
ጽ/ቤት ኃላፊ……………………….አርበኛ በየነ አለማው
አደረጃጀት ጉዳይ …..……………..አርበኛ አበበ መልኬ
ፋይናንስና ግዥ መምሪያ……….አርበኛ ሐብታሙ ሙላው
ሎጅስቲክ መምሪያ…………….………አርበኛ በላዬ ዘለቀ
ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ………….…አርበኛ ጋሻው ግዛት
ሕዝብ አስተዳደር መምሪያ………….አርበኛ ንጉሴ አዱኛ
ልዩ ዘመቻ መምሪያ..……………….አርበኛ አስፋው ሰርፀ
ወታደራዊ ስልጠና መምሪያ…….……አርበኛ ጌታሰው በሬ
ወታደራዊ እቅድና ስትራቴጂ መምሪያ…..አርበኛ ተመስገን አብርሃም
ምክ/ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ……..……አርበኛ ስጦታው ዳኛው/ባሻ
ሜካናይዝድ ጦር መምሪያ………..አርበኛ ሲሳይ አሸብር
ቴክኖሎጅና ምህንድስና መምሪያ……አርበኛ ያለው አዱኛ
ጥናትና ስትራቴጂ መምሪያ………..አርበኛ ዘመነ እረኛው
ትምህርትና ስልጠና መምሪያ……….አርበኛ ዘላለም በላይነው
ሕግና ስነ-ምግባር ጉዳይ መምሪያ……አርበኛ ማሩ ቢተው
ማሕበራዊ ጉዳዮች መምሪያ………..አርበኛ ብዙአየሁ ወንድምነው
ሴቶችና ወጣቶች መምሪያ………..አርበኝት አስምሪው መሳፍንት ተስፉ
ሰው ሃብት አስተዳር መምሪያ….……አርበኛ አዳነ ፀጋ
ሃብት አፈላላጊ መምሪያ….…………..አርበኛ ማሩ በሪሁን
ኢንዶክትሪኔሸን መምሪያ…..………አርበኛ ተመስገን ውባንተ
የውስጥ ኦዲት መምሪያ……………..አርበኛ ግዛቸው አሌ
ጤና መምሪያ……………………………አርበኛ አታለለ ሰጠኝ
እቅድ ዝግጅትና ግምገማ መምሪያ ……አርበኛ ታደሰ ወርቁ
ቁጥጥርና ኦዲት ኮሚቴ ሰብሳቢ…………አርበኛ ባንቲደር እውነቱ
ሕግና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ሰብሳቢ…………አርበኛ ወልደአረጋይ ሸርብ
ወታራዊ ፍርድ ቤት ሰብሳቢ……………..አርበኛ ታርቆ ከበደ
2ኛ) ምክትል የስራ አስፈጻሚ መምሪያዎች
ምክ/ፖለቲካ መምሪያ………………..…አርበኛ ዳኛው አጣናው
ምክ/ጽ/ቤት………………………..አርበኛ መ/አ ገዳም ካሳ
ምክ/አደረጃጀት ጉዳይ…………………...አርበኛ ብርሃኑ ነጋ
ምክ/ፋይናንስና ግዥ መምሪያ…………..አርበኛ ስጦታው መልኬ
ምክ/ሎጅስቲክ መምሪያ…………………አርበኛ ደፋሩ አቤ
ምክ/ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ…………አርበኛ ማንደፍሮ ተሰማ
ምክ/ ሕዝብ አስተዳደር መምሪያ……….አርበኛ ዋሴ ታደሰ
ምክ/ልዩ ዘመቻ መምሪያ..………………...አርበኛ ሙሉዬ ደሴ
ምክ/ወታደራዊ ስልጠና መምሪያ…………ሻምበል መሳፍንት ተስፉ
ምክ/ወታደራዊ እቅድና ስትራቴጂ………...አርበኛ እያቸው ብርሃኑ
ምክ/ሜካናይዝድ ጦር መምሪያ…….…….አርበኛ ንጋት አየለ
ምክ/ቴክኖሎጅና ምህንድስና መምሪያ…….አርበኛ አለሜ ባዬ
ምክ/ጥናትና ስትራቴጂ መምሪያ………...አርበኛ ፋሲል ሙሏለም
ምክ/ትምህርትና ስልጠና መምሪያ………..አርበኛ አብዩ ማሩ
ምክ/ሕግና ስነ-ምግባር መምሪያ………..…አርበኛ ደመቀ አለሙ
ምክ/ማሕበራዊ ጉዳዮች መምሪያ…………..አርበኛ ደምሰው ድረስ
ምክ/ሴቶችና ወጣቶች መምሪያ……………….አርበኝት ገነት ፀጋው
ምክ/ሰው ሃብት አስተዳደር መምሪያ………አርበኛ ወዳጅ አስፋው
ምክ/ሃብት አፈላላጊ መምሪያ ….…………..አርበኛ አስማማው ዋለልኝ
ምክ/ኢንዶክትሪኔሸን መምሪያ ….…………አርበኛ አዲሱ መሰለ
ምክ/የውስጥ ኦዲት መምሪያ………………..አርበኛ መ/አ ቢራራ
ምክ/ወታደራዊ መረጃና መገናኛ መምሪያ……አርበኛ ሚናስ አለማየሁ
ምክ/ጤና መምሪያ…………………………..አርበኛ ምዕራፍ ሙጨ
ምክ/እቅድ ዝግጅና ግምገማ መምሪያ……….አርበኛ መ/አ ኃይለየሱስ ታደሰ
3ኛ) ሌሎች የስራ ክፍል ኃላፊዎች፡-
የሕዝብ ሰላምና ደህንነት ከፍል…………አርበኛ መለሰ ተሾመ
ምርኮኛ አስተዳደር ከፍል …………….አርበኛ አለማየሁ ሰማ
ወታደራዊ ቃል አቀባይ………………..አርበኛ ቢኒያም አለምነህ
ቀጠናዊ ትብብር……………………...አርበኛ ዘመኑ ታደሰ
ሰማዕታት ቤተሰብ ድጋፍ ክፍል………..አርበኛ አማኑኤል ተፈራ
ስንቅ አቅርቦት ክፍል…………………..አርበኛ ክንዱ ግርማ
ሒሳብ ሹም…………………………….አርበኛ አያናው አዱኛ
መሰረተ-ልማትና ኢኮኖሚ ክፍል……..አርበኛ አበበ አመኑ
ኦርዲናንስ……………………………..አርበኛ ዳንኤል አስረስ
ፐርሶኔል …………………………….አርበኛ ዮናስ አያልቅበት
ግዥ ክፍል ………………………….አርበኝት ትዕግስት ተረፈ
ገንዘብ ያዥ……………….…………..አርበኛ መላክ ተስፋ
ሕዝብ አገልግሎት ………………….አርበኛ አለባቸው ጌጡ
ኪነ-ጥበብና መዝናኛ ክፍል…………..አርበኛ አስተውል አምሳሉ
ታሪክና ማሕደር ክፍል ……………..አርበኛ አንዷለም አሰፋ
አባት አርበኞች ማደራጃ ክፍል………አርበኛ ጌትነት ስመኝ
ማሕበራዊ ፍርድ ሸንጎ………………..አርበኛ ማናለ ገላጋይ
ፕሮጀክት ቀረፃና አስተዳደር …………አርበኛ ባንቲ ጌትነት | 440 |
| 10 | No text... | 412 |
| 11 | ''አዲስ አበባን የኦሮሚያ አካል እናደርጋታለን'' ምክከር ኮሚሽን
ኦህዴድ አዲስአበባን ስልታዊ በሆነ መንገድ ለመጠቅለል አልሞ እየሰራ ነው።
በኦሮሞ ብልጽግና/ኦህዴድ በኩል አዲስ አበባን በደረጃ እና በስልታዊ መንገድ ወደ ኦሮሚያ ክልል ለማካተት የታለመ የተቀናጀ የፖለቲካ እንቅስቃሴ መጀመሩን ከምክክሩ የውውይት ሰነድ ሾልኮ የደረሰን መረጃ ያመላክታል።
ምክክር ኮሚሽኑ በኦህዴድ-ብልፅግና ቀጭን ትዕዛዝ አዲስ አበባን የኦሮሚያ አካል ማድረግ የሚል አደገኛ አማራጭ በውይይት ሰነድ ውስጥ በማካተት በሂደት ህጋዊ እና ቅቡል ለማድረግ በፖለቲካ ድራማ እያጀበ መሆኑም ተረጋግጧል።
ኦሮሞ በአዲስአበባ ጉዳይ የተለየ ባለቤትነት ያለው ይመስል፣ እንደ አዋላጅ ነርስ ፅንስ ሲመለምል የሚውለው የመስፍን አርአያና እና የአብይ አህመድ ምክክር ኮሚሽን አዲስ አበባን ''የኦሮሚያ አካል'' ማድረግ የሚል የማጭበርበሪያ አማራጭ ለምክክር ባቀረበው ሰነድ ውስጥ አካቶ አቅርቧል።
በመብት እና በባለቤትነት ደረጃ፣ በአዲስአበባ ጉዳይ ከኦሮሞ በተሻለ አማራ የባለቤትነት ጥያቄ የማቅረብ ምክንያታዊ መብት አለው። በከተማዋ የሚኖሩ ሌሎች የኢትዮጵያ ህዝቦችም እንዲሁ፤ ነገር ግን የአብይ አህመድ የከሸፈ ምክክር ኮሚሽን አዲስአበባን ራስ ገዝ፣ የፌደራል አካል፣ ራሷን የቻለች ክልል የሚሉ የይስሙላ ማጀቢያዎችን ደርድሮ ''የኦሮሚያ አካል'' እናድርጋት የሚል አደገኛ ፅንፍ በማካተት ለመጠቅለል እየሞከረ ይገኛል።
በአጠቃላይ አሁን ያለው የብልፅግና የምክክር ኮሚሽን ሂደት በፖለቲካዊ ተጽዕኖ ስር የወደቀና ገለልተኝነት የጎደለው ከመሆኑ ባሻገር አገራዊ መግባባት ሊፈጥር ቀርቶ የበለጠ የፖለቲካ ክፍፍልንና አለመረጋጋትን የሚወልድ ነው።
ምክክር እና ኮሚሽን የተባሉት ፖለቲካዊ ፅንሶችም እንደ ምክክሩ ተስፋ አይኖራቸውም፤ ደግነቱ በፍርድ ቤት ይቀይሩታል እንጂ 🤣🤣🤣
አይ ምክክሮች 🤔🤔 | 358 |
| 12 | No text... | 356 |
| 13 | 🎯 ፍትሐዊው ባለ ሚዛን!
(አዲሱ ደረበ)
የአማራ ሕዝብ ሁሌም ቢሆን ፍትሐዊ፣ ባለሚዛንና ሥርዓት አዋቂ ሕዝብ ነው። ለመንግሥት፣ ለሕግና ለመንግሥታዊ አሠራር ያለው ቀናኢነትና አክብሮት ለዘመናት የጸና ቢሆንም፣ ይህ በጎ እሴቱ ግን ግፍና ጭቆና በእርሱና በወገኖቹ ላይ ሲጫኑ እጁን አጣጥፎ እንዲቀመጥ አድርጎት አያውቅም። ዛሬማ ይልቁን በአማራዊ ማንነቱ ላይ የህልውና አደጋና የዘር ማጥፋት ጥቃት ተደቅኖበት እንዴት ዝም ይላል? ወትሮም ቢሆን ኢ-ፍትሐዊነትንና ጥቃትን እምቢ ለማለትና ለመፋለም ቦዝኖ የሚያውቅ ሕዝብ አይደለም!
እውነቱ አሁን እንደሚታየው ነው፤ እንኳን አሁን መላው አማራ በየአቅጣጫው አለሁ ብሎ በአንድነት ተሰልፎ ይቅርና፣ ወትሮም ቢሆን በየትኛውም አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በአጥቢያው ተደራጅቶ ግፈኞችንና ወራሪዎችን ለመታገል አንዲት ሰከንድ የማያመነታ ብርቱና ኩሩ ሕዝብ ነው። የታሪክ መዝገብ ለዚህ ሕያው ምስክር ነው፤ የፋሽስት ጣሊያንን እብሪትና ወረራ፤ ዘመናዊ የጦር መሣሪያና የመርዝ ጋዝ ሳይበግረው ዱር ቤቴ ብሎ ተፋልሟቸዋል። በቀደሙት ስርአቶች ሁሉ የመሬት ግብር ጭቆና በበረታበት ወቅትም፣ የማይከሰሱና የማይጠየቁ የሚመስሉትን መሳፍንቶች አልገብርም ብሎ በመሬት ግብር እምቢተኝነት አንቀጥቅጧቸዋል።
በአህጉር ደረጃ ገናና ስምና ግዙፍ የጦር ግንባር የነበረውን የደርግን መራር ግፍና ቀይ ሽብር የመታገልና የመቋቋም ታሪካዊ ውርስ ያለው ነው፤ ለዚህም የጀግኖች ምድር አቸፈር፣ በለሳና ሰቆጣ ሕያው ምስክሮች ናቸው። እንዲሁም የወያኔ ኢሕአዴግን ዘረኛ አገዛዝ ከዘረኝነት፣ ከጠባብነትና ከመድሎ እንዲወጣ ያለ ምንም ፍርሃትና ተሸማቃቂነት በአደባባይ የተጋፈጠውና የታገለው ይኸው ሕዝብ ነው።
ዛሬማ መደራጀት፣ መቀራረብና በጋራ የአማራነት ጉዳይ ላይ በጋራ መሰለፍን ዘመኑም፣ የታሪክ አጋጣሚውም ፈቅዶለታል! ትናንት የፋሽስት ጣሊያን የመርዝ ጋዝ ያልበተነውና ያላበረከከው ሕዝብ፣ ዛሬ በፋሽስቱ አብይ አሕመድ ድሮን በፍጹም አይንበረከክም። የደርግን አሰቃቂ ቀይ ሽብር በጽናት የተሻገረው አቅሙ፣ በዛሬው ገዢ ቡድን የዘር ማጥ*ፋት ዘመቻ አይፈታም። የወያኔ የትጥቅ ማስፈታት አዋጅና በሐውልት ማቆም አንገት አስደፊነት ተግባር ያልተሰበረው ወኔ፣ በዛሬው የብአዴንና የአገዛዙ ሱሪ የማስፈታት ዘመቻ ከቶ ድል አይደረግም።
ጥቅሙን፣ ጉዳቱንና ክብሩን አሳምሮ የሚያውቅ፣ ፍትሐዊ ባለሚዛን የሆነው የአማራ ሕዝብ—ትናንት ጅራፍ እያጮኸ ያልተሰማውን አጠቃላይ ብሶቱን፣ ዛሬ በእውነተኛው የፋኖ ክንድና በጥይት አረር እየታገለ፣ መብቱንና ሕልውናውን እያስከበረ ይገኛል። ከትናንት እስከ ዛሬ ባልተለወጠው የገዢዎች ክፋት፣ ሴራና የወገናችን መራር አኗኗር ውስጥ አንድ ቋሚና የማይናወጥ ትልቅ እሴት አለ፤ እርሱም የአማራ ሕዝብ እምቢ ባይነትና የማይበገር ወኔ ነው!
ድል ለአማራ የህልውና ትግል! 🎯 | 476 |
| 14 | በ''ፅምዶ'' ትርክት እና በብልፅግና ሴራ መካከል ያለው የአፋብን ድርጅታዊ ቁመና !!
✍️✍️ ያሬድ ሙሉነህ
የአንድ ህዝባዊ የህልውና ትግል ጥንካሬ የሚለካው የራስን ትክክለኛ የፖለቲካ አጀንዳ ለይቶ በማወቅ እና ከውጭ የሚመጡ፣ የትግሉን መስመር የሚያሳስቱ ባዕድ ትርክቶችን በፅኑ በመከላከል ላይ ነው።
በአሁኑ ወቅት የአማራን ፋኖ ትግል አቅጣጫ ለማስቀየርና በደጋፊው ዘንድ ግራ መጋባትን ለመፍጠር ሆን ተብለው የሚረጩ ብልፅግናዊ አጀንዳዎች ይታያሉ። ከነዚህም መካከል የ''ፅምዶ''ን ትርክት ከአማራ ፋኖ ጋር ለማገናኘት የሚደረገው ሙከራ አንዱና ዋነኛው ነው።
''ፅምዶ'' የአማራ ህዝብ የፖለቲካ ጥያቄም ሆነ የፋኖ የትግል ግብ አይደለም። ይህ አጀንዳ የራሱ የሆነ ጂኦፖለቲካዊ መነሻ ያለው የትግራይ እና የኤርትራ አጀንዳ ብቻ መሆኑ መታወቅ ይኖርበታል።
የአማራ ህዝብ በአሁኑ ወቅት እየታገለው ያለው ለህልውናው፣ ለታሪካዊ ርስቶቹ መከበር፣ ለሰብአዊ መብቱ መከበር እና በሀገሪቱ ፖለቲካ ውስጥ የሚገባውን ስፍራ ለማግኘት እንጂ የሌሎች ቀጣናዊና ውስጣዊ ኃይሎችን የትርክት ፍጆታ ለማስፈጸም አይደለም።
''ፅምዶን'' ፖለቲካዊ ግብ አድርገው የሚቆጥሩ በትግል ውስጥ የተደበቁ ውስን ግለሰቦች ቢኖሩም ይህንን የአማራ ያልሆነን አጀንዳ አገዛዙ ላይ ጫና መፍጠር በሚል ስሌት ብቻ በግድ እየጎተቱ ከአማራ ፋኖ ጋር ለማጣበቅና የአፋብን ይፋዊ አቋም አስመስሎ ለማቅረብ የሚደረገው ጥረት ግን ትክክል አይደለም። ፅምዶ .. ከቃሉ መጠሪያ ጀምሮ የአማራ የሆነ ነገር የለውም።
ይልቁንም ይህንን አጀንዳ ከሚገባው በላይ መለጠጥ የገዥውን የብልፅግና ቡድን አጀንዳ የማስፈፀም ድጋፍ ተደርጎ ይቆጠራል።
የፅምዶን አጀንዳ ወደ ፋኖ መንደር ለመግፋት መሞከር የትግሉን ማዕከላዊ መስመር ማሳሳትና ለብልፅግና የፕሮፓጋንዳ ግብአት ማቅረብ ነው።
ብልፅግና ይህንን አጀንዳ በስፋት የሚያራግብበት ሁለት ዋነኛ ምክንያቶች አሉት።
1. ፋኖ ዋና ጠላቱንና የትግል አቅጣጫውን ለይቶ እንዳይጓዝ፣ ትኩረቱን ወደ ሌላ የውጭ አጀንዳ እንዲያዞር ማድረግ።
2. ገዥው ቡድን በአማራ ህዝብ ላይ እየፈጸመ ያለውን ግፍና ጭፍጨፋ ሸፍኖ፣ ፋኖን ከሌሎች የውጭ ሀይሎች አጀንዳ ጋር የተሰለፈ አስመስሎ ለመወንጀል የሚፈልገውን የሀሰት ትርክት በማመቻቸት የህዝብ ድጋፍ የማግኘት ነው።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) በድርጅታዊ አሰራሩ፣ በመዋቅራዊ ጥንካሬው እና በስትራቴጂካዊ አቅጣጫው የጠላትንም ሆነ የተስፈኛ ካድሬዎችን አጀንዳ የሚያከሽፍ ቁመና ላይ ይገኛል።
አፋብን የሚመራበት ግልጽ የፖለቲካ ፕሮግራም እና የትግል መመሪያ የአማራን ህዝብ ዘላቂ ጥቅም ብቻ ማዕከል ያደረገ ነው። ከማንኛውም የባዕድ ርዕዮተ-ዓለምና አጀንዳም የጸዳ መሆኑንም በተደጋጋሚ ጊዜ የድርጅቱ የግንኙነት ድምፅ በሆኑ አመራሮች ተገልጿል።
አፋብን የአማራን ህዝብ መሰረታዊ ጥቅሞች፣ ታሪካዊ ርስቶች እና የህልውና ዋስትናዎችን አሳልፎ የማይሰጥ እና በመርህ ላይ የተመሰረተ ትግል እያካሄደ ያለ ጠንካራ ድርጅት መሆኑንም በሚያሳልፋቸው ውስጣዊ ውሳኔዎች እያስመሰከረ ይገኛል።
በአጠቃላይ ''ፅምዶ''የአማራ ፋኖ አጀንዳ አይደለም፤ ሊሆንም አይችልም። ይህንን የትግራይና የኤርትራን አጀንዳ ከፋኖ ጋር ለማገናኘት የሚቋምጡ አካላት የብልፅግናን ዕድሜ ለማራዘም የሚሰሩ አካላት ናቸው። ( ይህ ድምዳሜ ግለሰባዊና ቡድናዊ የሆኑ ስሁት እንቅስቃሴዎችን በመመልከት ከስጋት የመነጨ ምክንያታዊ ትችት የሚያቀርቡት ወንድሞችን አያካትትም)።
ይህ ማለት ግን ፋኖ ከሌሎች ሀይሎች ጋር የሚፈጥረው አጋርነትና ትብብር አይኖርም ማለት አይደለም።
የትጥቅ ትግል በባህሪው ስልታዊ፣ ፖለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ ትብብሮችን የሚጠይቅ በመሆኑ አገዛዙን ለማስወገድ፤ ፋኖ ከአጋር አካላት ጋር አብሮ ለመስራት ሁልጊዜም ዝግጁ እንዲሆን ይጠበቃል።
ሆኖም ግን፣ ማናቸውም አይነት አጋርነት ወይም ትብብሮች በዘፈቀደና በፌስቡከኛ ጩኸት ሳይሆን መርሆዎች ላይ ተመስርተው መከናወን ይኖርባቸዋል።
ትብብሮች የሚፈጠሩት በግለሰቦች ፍላጎት፣ በስሜት ወይም በሶሻል ሚዲያ ጫና ሳይሆን፣ በድርጅታዊ አሰራር፣ በግልጽ ውይይትና በማዕከላዊ አመራሩ ውሳኔ ብቻ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ ማናቸውም ታክቲካልም ሆነ ስትራቴጂካዊ አጋርነት የአማራን ህዝብ ህልውና፣ ታሪካዊ ርስቶችና ስትራቴጂካዊ ጥቅሞች አሳልፎ በማይሰጥና ሳይሸራረፉ በሚያስክብር መልኩ መቃኘት ይኖርበታል።
ፋኖ የራሱን ማዕከላዊ መስመርና የትግል አጀንዳ በፅናት ጠብቆ፣ ከማንኛውም በጎ ፈቃድ ካለው አካል ጋር መርህን መሠረት ያደረገ አጋርነት የመፍጠር ድርጅታዊ ብስለት፣ብቃት እና መብት አለው። ስለዚህ ''ፅምዶ'' የሚለው የብልፅግናው የግርግር አጀንዳ በቀጥታ የአማራ ፋኖን የሚመለከት አጀንዳ አይደለም። ነገር ግን የዚህ አጀንዳ ባለቤቶች የአማራን ህዝብ ጥቅም ሳይነኩ ብልፅግናን የመገርሰስ ፖለቲካዊ መብት አላቸው። (በተለይ የህወሀት እንቅስቃሴ በትኩረት መጤን እንዳለበት በተደጋጋሚ ተቃውሞች የሚቀርቡት ከላይ የቀረቡትን ስጋቶች መነሻ በማድረግ ነው።)
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን)ም የአገዛዙን የፈጠራ የፕሮፖጋንዳ መሰናክሎች በድርጅታዊ ብስለቱ እና በአላማ ፅናቱ እያለፈ፣ የትግሉን ማዕከላዊ መስመር ጠብቆ የአማራን ህዝብ ጥቅሞች በዘላቂ መንገድ የማስከበር ታሪካዊ ግዳጁን በብቃት እንደሚወጣ ሙሉ እምነት አለን።
በውስጠ ድርጅታዊ ትግል እየተመራን ወደ ዘላቂ ድል እንገሰግሳለን!
ድል ለአማራ ፋኖ !
አማራ ያሸንፋል 💪💪 | 475 |
| 15 | https://youtu.be/XrH0GBd5vII?si=IXRxgvy_gMSllwVg | 365 |
| 16 | በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መንዝ አውራጃ በብልፅግና ጦር ላይ ድንገተኛ ጥቃት መፈጸሙን ወንዱ አስቻለው ደሴ ክፍለ ጦር አስታወቀ!!
ሐምሌ 12/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር ወንዱ አስቻለው ደሴ ክፍለ ጦር በብልፅግና ጥምር ጦር ላይ በቀን 11/11/2018 ዓ.ም መብረቃዊ እርምጃ ወሰደ። ኮሩ ከግንባር ባደረሰን መረጃ መሠረት የወንዱ አስቻለው ደሴ ክፍለ ጦር 3ኛ ሻለቃ ቃኘዎች ከሞላሌ ወደ መሀል ሜዳ በመንቀሳቀስ ላይ በነበረው የብልፅግና ኮማንዶ ጦር ላይ «አግዎ» በተባለ ስፍራ ሲሆን፣ በተጠና ወታደራዊ ስልት በተመራው ድንገተኛ ወታደራዊ እርምጃ በጠላት ኃይል ላይ ከፍተኛ የሙትና ቁስለኛ ጉዳት ማድረስ መቻሉን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ገልጿል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት"!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ !! | 541 |
| 17 | በሸዋ ጠቅላይ ግዛት 5 የጉድኝት ክላስተሮችን ያሳተፈ ታሪካዊ መድረክ ተካሄደ!
በቀን 11/11/2018 ዓ.ም በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ በተሬ ክላስተር በተደረገው ታሪካዊ መድረክ ላይ፤ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት የአሳምነው ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች፣ የአባት አርበኞች መምሪያ አመራሮች፣ በቀጠናው የሚገኙ የፖለቲካ መምሪያ አስተባባሪዎች እንዲሁም የኮር እና ከ5ቱም ክላስተሮች የተውጣጡ አመራሮች በተገኙበት የትግሉን እድገት የሚመጥን የ6 ወር የሥራ ሪፖርትና ውይይት ተደርጓል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሥር የሚገኙትን አምስት (5) የጉድኝት ክላስተሮች፣ እነሱም፦
1.የተሬ ክላስተር
2.መዘዞ ክላስተር
3.የባሽ ክላስተር
4.የኤፍራታና ግድም ክላስተር
5.የአሎሎ ክላስተር
የእነዚህን ክላስተሮች አስተዳደሮች ወደ አንድ መድረክ በማምጣት የ6 ወር የሥራ ሪፖርት እንዲያቀርቡ ተደርጓል። በዚህ ውይይት ላይ በክላስተሮቹ የተሰሩ ስራዎች ቀርበው፤ በሕዝብ አስተዳደር፣ በፍትህ፣ በሰላምና ደህንነት እንዲሁም በአባት አርበኛ ታጋዮች መጠርነፍና ማደራጀት ዙሪያ ውጤታማ ስራዎች እንደተከናወኑ ተገልጿል። በተጨማሪም በየክላስተሮቹ የነበሩ የአሰራር እቅፋቶችና የሕዝብ ጥያቄዎች ቀርበው ጥልቅ ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በሁሉም ወገን ከሕዝብና ከመሪዎቹ ለተነሱት ጥያቄዎች የአባት አርበኞች መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ማሞ ማስረሻ እና የዕዙ ከፍተኛ አመራር አርበኛ ዮናስ ባባው ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በመድረኩ የሙሐመድ ቢሆነኝ ኮር ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ፋኖ ምናሉ ከበደ በመገኘት በወታደራዊ ጉዳዮች ላይ ለተነሱ የሕዝብ ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ ሰጥቷል።
በመጨረሻም፣ የፖለቲካ መምሪያ የቀጠናው አስተባባሪዎች መድረኩን በመምራትና በማስተባበር፣ ለቀጣይ የትግል እንቅስቃሴ አቅጣጫ በመስጠት እንዲሁም ለአምስቱ ክላስተሮች መልካም አፈፃፀምና የትግል ንቅናቄን በበሰለ መልኩ በመምራታቸው የዕውቅና ምስክር ወረቀት እና የአርበኞች ምስል በሽልማት መልክ ተበርክቶላቸው መድረኩ በስኬት ተጠናቋል።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ | 401 |
| 18 | No text... | 396 |
| 19 | No text... | 372 |
| 20 | ከሶስት ዓመታት በላይ በዘለቀው የአማራ ክልል ጦርነት አገዛዙ ያሰለፋቸውና በህዝብ ላይ የጦር ወንጀል እየፈፀሙ የሚገኙ ጀነራሎች!
1) ሰሜን ምዕራብ ዕዝ - ዋና አዛዥ ሌ/ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ
2) ምስራቅ ዕዝ - ዋና አዛዥ ሌ/ጄኔራል መሐመድ ተሰማ
3) 10ኛ ዕዝ (ሰሜን ዕዝ) - ዋና አዛዥ ሜ/ጄ ግዛው ኡማ
4) 13ኛ ዕዝ - ዋና አዛዥ ሜ/ጄ ተስፋዬ አያሌው
5) 11ኛ ዕዝ - ዋና አዛዥ ሌ/ጄኔራል አድማሱ ዓለሙ
6) ሰሜን ምስራቅ ዕዝ - ዋና አዛዥ ሌ/ጄኔራል አሰፋ ቸኮል
7) 9ኛ ሜካናይዝድ ዕዝ በከፊል - ዋና አዛዥ ሜ/ጄኔራል ከፍያለው አምዴ
8. የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ - ዋና አዋዥ ሌ/ጄኔራል ሹማ አብደታ
9) 6ኛ ዕዝ - ዋና አዛዥ ሜ/ጄኔራል ብርሃኑ ጥላሁን
10) ደቡብ ዕዝ (በከፊል) - ዋና አዛዥ ሌ/ጄነራል ሰለሞን ኢተፋ
11) በመከላከያ መረጃ - ዋና ኃላፊ ጄኔራል ጌታቸው ጉዲና
ኢታማዦር ሹሙና ምክትላቸው ሳይረሱ! | 305 |
