የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርስቲ ግቢ ጉባኤ
Open in Telegram
የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ መደበኛ ቻናል ነው፡፡ በዚህ ቻናል 👉 ትምህርታዊ ጽሑፎች ፤የግቢ ጉባኤው መልዕክት ፤የክፍላት ማስታወቂያዎች ይተላለፉበታል፡፡ ሀሳብ አስተያየት ጥያቄ ካለ @ethiopia_1616 ላይ ይፃፉልን፡፡ contact 0923584792 /0928381616
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
430
Subscribers
No data24 hours
+17 days
-330 days
Posts Archive
❝ሰላም ለኪ ኦ ሐና እማ ለፀሓየ ጽድቅ ወላዲቱ ወእምሕይወቱ ለዘገብረ ሰማየ ወምድረ — ሰማይና ምድርን የፈጠረ የፀሓየ ጽድቅ እናትን የፀነስሽ ሐና ሆይ ሰላም ላንቺ ይሁን❞እንኳን ከፍጥረት ሁሉ ለከበረች ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ ልደት አደረሰን። ለልደታ የሚኖሩን መርሀግብራት፦ 👉ፀሎት 👉ት/ት 👉ስነ ፅሁፍ 👉ጥያቄ እና መልስ ዉድድር 👉አጋፔ 👉ቅኔ 👉ዜና ተዋህዶ 👉የአንድነት ዝማሬ ⏰ ቅዳሜ ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ ግቢ cafe ዉስጥ መርሀግብራችንን የምናካሂድ ይሆናል። እየተቀሳቀስን እንገኝ!!!
ሰላም እንዴት አላችሁ!!
የ pedagogy ተማሪዎች ልዩ ተከታታይ ትምህርት ዛሬም ይቀጥላል፤ በሰዓቱ በመገኘት ትምህርታችሁን እንድትከታተሉ!!!
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ለሁሉም የግቢያችን ኦርቶዶክሳውያን ተማሪዎች፣ ለቀድሞ ምሩቃን እንዲሁም ለግቢ ጉባዔያችን ወዳጆች የተላለፈ መልዕክት:
✨✨✨ ታላቅ የምስራች ✨✨✨
▬▬▬▬▬▬◈◈◈▬▬▬▬▬▬
ደረሰ....ደረሰ....ደረሰ!!!
የግቢ ጉባኤያችን ፴፯ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ደረሰ
እንኳን አደረሳችሁ!!!
Maqaa Abbaa Kan Ilmaa Kan Hafuura Qulqulluu Waaqa Tokko Ameen!
"Mana Kiristiyaanaa haa beeknu barsiifata ishees haa eegnu"
Yaa’ii Hafuuraa guddaa hundeeffama Yaa’i Moraa keenya Moraa Kotobee waggaa 37ffaa sababeeffachuudhaan qophaa’e
Caamsaa Guyyaa 2
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ከአንደኛ ዓመት ጀምሮ እግራችንን አጥባ ተቀብላን፣ በቤተሰብ መዋቅር እናት አባት ወንድም እህት ሰጥታን ፣ ሰኞ፣እሮብ እና አርብ ጉባኤ ወንጌል እየሰበከች ኮርስ አስተምራን ፣ በንስሐ አባት ጉባኤ ወደ ንስሐ እየመራችን ፣ በ ኑ እንቅረብ ቀን ለቅዱስ ቁርባን እያበቃችን ፣ በአገልግሎት ክፍላት በቤተክርስቲያን አገልግሎት እንድንጸና ምክንያት ለሆነችን የእናት ግቢ ጉባኤያችን የምስረታ በዓል በልዩ ድምቀት ልናከበር ዝግጅታችንን ጨርሰናል።
የግቢ ጉባኤያችን የምስረታ በዓል ከእመቤታችን የልደት በዓል ጋር በግንቦት ልደታ ማግስት በእለተ እሁድ ሚያዚያ 2 በመ/ቅ/ኢ/ወሐና ቤ/ክርስትያን የምናከብር ይሆናል።
እኛም በባለፈው ዓመት እመቤቴ ብታደርሰኝ ብታደርሳቹ ብለን የተሳልነውን ስለታችንን ሳንዘነጋ በአንድነት ከ ጓደኞቻችን ጋር በመሆን በመካነ ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና ቤተክርስቲያን እንድንገናኝ በክርስቶስ ፍቅር ጥሪያችንን እናቀርባለን።
▬▬▬▬▬▬◈◈◈▬▬▬▬▬▬
የኮ/ት/ዩ/ግ/ጉ/ፅ/ቤት
📲 Join and Share 🤳
@kotebegibi
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
✨ ጉባኤ ኒቆዲሞስ ✨
✨ሰኞ ሚያዚያ 26✨
ተወዳጇ እና ተናፋቂዋ የአንድነት ጉባኤያችን ጉባኤ ኒቆዲሞስ።
📌 በዕለቱ የሚኖሩን መርሐግብራት
ꔰ ጸሎት
ꔰ ትምህርተ ወንጌል
ꔰ የመዝጊያ ጸሎት
ሰዓት፦ 11፡15(30)-1:30
ቦታ፦ መ/ቅ/ኢ/ወሐና ቤተክርስቲያን ፍቅረ ሰላም
አዳራሽ
👉በሰዓቱ ጀምረን በሰዓቱ እንድንፈፅም
በሰዓቱ እንገኝ🙏
✨ኮተቤ ግቢ ጉባኤ✨
ሰላም ጤና ይስጥልን!
ልዩ ለእኅቶች ብቻ የተዘጋጀ ጉባኤ!ቀን:- ሚያዚያ 27 የአርበኞች ቀን ማክሰኞ ሰዓት:- በጠዋት 2.30 -10.30 ድረስ ምሳ በማእከሉ ይሸፈናል በመርሐ ግብሩም ትምህርታዊ ሥልጠና በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ልምድ ልውውጥና ውይይት ከእኅቶች የሚነሱ ጥያቄና መልስ ቦታ:- ሰአሊተ ምሕረት ቤ/ክ ቅዱስ ገብርኤል አዳራሽ መርሐ-ግብሩ ታላቅ ስንቅ የምንሰንቅበት መርሐ-ግብር ስለሆነ ያልሰሙትን እኅቶች በመቀስቀስ እንሳተፍ ማኅበረ ቅዱሳን ሰአሊተ ምሕረት ግቢ ጉባኤያት ማስተባበሪያ
ሰላም ጤና ይስጥልኝ! ልዩ ለእኅቶች ብቻ የተዘጋጀ ጉባኤ!
ጉባኤ አንስት
ቀን:- ሚያዚያ 27 የአርበኞች ቀን ማክሰኞ
ሰዓት:- በጠዋት 2.30 -10.30 ድረስ
ምሳ በማእከሉ ይሸፈናል
✅በመርሐ ግብሩም
ትምህርታዊ ሥልጠና
በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ልምድ ልውውጥና ውይይት
ከእኅቶች የሚነሱ ጥያቄና መልስ
👉ቦታ:-
ሰአሊተ ምሕረት ቤ/ክ ( ከሲ ኤም ሲ ቅዱስ ሚካኤል በአዳራሽ ምክንያት ወደ ሰአሊተ ምሕረት ተቀይሯል) መርሐ-ግብሩ ታላቅ ስንቅ የምንሰንቅበት መርሐ-ግብር ስለሆነ ያልሰሙትን እኅቶች በመቀስቀስ እንሳተፍመቅረት ያስቆጫል!! ከማኅበረ ቅዱሳን ሰአሊተ ምሕረት ግቢ ጉባኤያት ማስተባበሪያ
ቅዱስ ጊዮርጊስ በትዕግሥቱ ገድሉን ፈጸመ
ሚያዝያ 23 የልዳው ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ስለክርስቶስ በመመስከሩ በሰይፍ አንገቱን ተሰይፎ የሰማዕትነትን አክሊል የተቀበለበት ጊዜ ነው።
ይህ ታላቅ ሰማዕት በነበረበት ዘመን ሁሉ ‹‹ እኔ የክርስቲያን ወገን ነኝ እምነቴም በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ነው ›› በማለቱ ብቻ ብዙ የጸና መከራ ደረሰበት።
በወፍጮ ፈጩት።
በመጥረቢያ ፈለጡት።
በበሬ አስረው ጎተቱት።
እጆቹን የኋሊት አሰሩት።
ወደ እስር ቤት ወረወሩት።
ምላሱን በቢላዋ ቆረጡት።
በመጋዝ ለሁለት ሰነጠቁት።
ሰውነቱን በጩቤ ፈተፈቱት።
አስጎንብሰው አሸዋ ጫኑበት።
እጆቹና እግሮቹ ታስሮ ተገረፈ።
ጥርሶቹን በጉጥ አስረው ነቃቀሉት።
የብረት ጫማ አጥልቀው አስኬዱት።
ከብረት ድስት ውስጥ ጨምረው ቀቀሉት።
የጋለ ሳህን ጭንቅላቱ ላይ አስቀመጡበት።
ከእንጨት ላይ አንጠልጥለው በእሳት አጋዩት።
ቅጥራን አፍልተው በጭንቅላቱ ላይ ደፉበት።
ከብረት አልጋ ላይ አስተኝተው እሳት አነደዱበት።
ችቦ እና እሳት አንድደው በግራና በቀኝ አቃጠሉት።
በአፍንጫው ውስጥ በሚስማር መተው ቸነከሩት።
በመጨረሻም ከዚህ ሁሉ መከራ በኋላ ለሰባት ዓመታት ብዙ ተጋድሎዎችን ከፈጸመ በኋላ ንጉሡ የቅዱስ ጊዮርጊስ ራስ በሰይፍ እንዲቈረጥ አዝዞ ወደ መሰየፊያው ቦታ ይዘውት ሲሆዱ እሳት ከሰማይ ወርዶ 70ውን ነገሥታት ያቃጥላቸው ዘንድ መከራውም ከክርስቲያኖች ጸጥ ይል ዘንድ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጸለየ ወዲያውኑም እሳት ከሰማይ ወርዶ 70 ነገሥታትን ፈጃቸው።
ከዚያም ፊቱን ወደ ምሥራቅ መልሶ ራሱን ዘንበል አድርጎ ሚያዝያ 23 በሰይፍ ቆርጠውት የሰማዕትነትን አክሊል ተቀዳጅቷል።
ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ብዙ ቃል ኪዳንን ከሰጠው በኋላ በክብር ወደ ሰማይ ወጣ።
ኮ/ት/ዩ/ግ/ጉ
